ch
Feedback
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

前往频道在 Telegram

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።

显示更多
2 639
订阅者
-224 小时
+87
+5630
帖子存档
የከበረ እንጦንዮስም ይህን በሰማ ጊዜ እጅግ አዘነ ቁሞም እንዲህ ብሎ ፀለየ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ እለምንሀለሁ በአፍርጊያ ውስጥ ወዳለ ወደ በርኪኖን አገር እንድሄድ ፈቃድህ ከሆነ ምልክትን ግለጥልኝ ነገር ግን ያንተ ፈቃድ ይሁን ይህንንም ባለ ጊዜ ብርህት ደመና መጣች በዚያችም ሰአት ተሸክማ ወደ አፍርንጊያ አገር አደረሰችው ንጉሱም ደስ አለው ህዝቡና ሰራዊቱም ሁሉ በሽተኞችንም አቀረቡለትና ሁሉንም ፈወሳቸው የፅድቅና የህይወትንም መንገድ እያስተማራቸው ከእነርሱ ዘንድ ስድስት ወር ኖረ። በእሁድም እለት ያቺ ብርህት ደመና ተሸክማ ወደ ገዳሙ ታደርሰውና ከልጆቹ ጋር ተገናኝቶ ያረጋጋቸዋል በማግስቱም ዳግመኛ ተሸክማ ወደ አፍርንጊያ አገር ትመልሰዋለች። ከዚህም በኃላ በእግዚአብሄር ፈቃድ በደመና ተጭኖ ወደ ገዳሙ አንደኛውን ተመለሰ። በአንዲት እለትም ስንፍና መጣበት እንዲህ የሚለውም ቃል መጣ ታይ ዘንድ ወደ ውጪ ውጣ በወጣ ጊዜም መልአኩን አየው በላዩም የምንኩስና ልብስ አለ መታጠቂያ ቅናት የመስቀል ምልክት ያለው ቀሚስ በወገቡም አስኬማ በራስ ቁር አምሳልም በራሱ ላይ ቆብ አለ እርሱም ተቀምጦ ሰሌን ይታታል ከዚያም ተነስቶ ይፀልያል ዳግመኛም ተቀምጦ ሰሌኑን ይታታል በየሰአቱም እንዲህ የሚል ቃል ወደርሱ መጣ እንጦንዮስ ሆይ እንደዚህ ስራ አንተም ከሰንፍና ከሰይጣናት ጦርነት ታርፋለህ ያንን ያየውንም ተቀብሎ እንዲሁ አስመስሎ የሚሰራ ሆነ ከዚያችም እለት ወዲህ ስንፍናና የሰይጣናት ወጊያ አልመጣበትም። የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብዙ ጊዜ ተገልፆ አረጋግቶታል አፅንቶታልም። አሁንም እንዲህ አለው የመረጥሁህ እንጦንዮስ ሆይ በእውነት እነግርሀለሁ እኔን ስለመውደድህ በዚች በረሀ ውስጥ ብቻህን በመጋደልህና በማገልገልህ ስለ ድካምህ ስምህን ክፍ ከፍ አደርጋለሁ ስልጣንህንም በአለም ዳርቻ ሁሉ ከፍ አደርገዋለሁ። ገዳማትንና አድባራትንም መነኩሳትን የተመሉ ሆነው ቅኖች የዋሀን ፃደቃን እንደሚኖሩባቸው አደርጋቸዋለሁ ይልቁንም ያንተ ገዳማት እነርሱ እስከ ፍፃሜ ይኖራሉ። መታሰቢያህንም የሚያደርገውን ሁሉ ለድሆች ምፅዋትን ለቤተክርስቲያን መባ በስምህ የሚሰጠውን ሁሉ እኔ ኃጢአቱን ሁሉ እደመስሳለሁ ከቶ ስቃይን አያያትም በውስጡ ስጋህ የሚቀበርበትንም ገዳም እጅግ ከፍ ከፍ አደርገዋለሁ በውስጡም እንደ መላእክት የሆኑ ደጋጎች መነኮሳት እንዲኖሩበት አደርጋለሁ ከእነርሱም እስከ አለም ፍፃሜ አለቃ የሚሆን አይታጣም የምድር ነገስታት መሳፍንትና ሹማምንት ለገዳምህና ፍለጋህን ለሚከተሉ ልጆችህም እጅ መንሻ ተሸክመው እንዲመጡ አደርጋለሁ ጌታችንም ይህንን ከተናገረው በኃላ ከእርሱ ዘንድ ወደ ሰማያት በታላቅ ክብር አረገ አባ እንጦኒም ፈፅሞ ደስ አለው። ከዚህም በኃላ ስለ ቤተክርስቲያን መፍረስ እንዲህ ብሎ ትንቢት ተናገረ መናፍቃን በላይዋ ይሰለጥናሉ ከዚህም በኃላ ወደ ቀድሞው ስርዓቷ ትመለሳለች ዳግመኛም ስለ መነኮሳት እነርሱ እጅግ እንደሚበዙ ገዳሞቻቸውንና አድባራቶችን በመተው ወርደው ከአለማውያን መካከል በከተማዎችና በቦታዎች ውስጥ እንደሚኖሩ ስለ አለም ፍፃሜም ትንቢት ተናገረ። ይህም አባ እንጦንዮስ አባ መቃርስን አስኬማንና የምንኩስና ልብስን ያለበሰው ያረጋጋውና ያፅናናው ከእርሱ የሚሆነውንም ያስረዳው ነው ደቀ መዝሙሩና ልጁ ስለሆነ። ከዚህም በኃላ የገዳማውያን አለቃ ወደሆነ ወደ አባ ቡላ ሄደ እርሱም ለስጋው ያሰበና በሀዋርያዊ አትናቴዎስ ልብስ የገነዘው ነው።እረፍቱም እንደቀረበ በአወቀ ጊዜ በትሩን ለልጁ ለአባ መቃርስ ምንጣፉን ለአባ አትናቴዎስ የፍየል ሌጦ ዐጽፉን ለልጁ ለኤጲስቆጶስ ለአባ ስራብዮን እንዲሰጡ ልጆቹን አዘዛቸው። ከዚህም በኃላ ከምድር ላይ ጋደም አለ ነፍሱንም በእግዚአብሄር እጅ ሰጠ ወደርሱም ሁሉም የመላእክት ማኅበር መጥተው በክብር በምስጋና ፍፁም ተድላ ደስታ ወዳለበት ዘላለማዊ እረፍት ተቀብለው አሳረጉት። ስጋውን ግን ልጆቹ እንዳዘዛቸው ሰወሩት እርሱ የቅዱሳን ሰማእታትን ስጋቸውን የሚገልጡትን ይገስፃቸው ነበርና ስለ እነርሱ ስጋ ብዙ ገንዘብ እስከመቀበል ደረሰው አለማዊ ጥሪት ያደርጉታልና። ይህም የከበረና የተመሰገነ አባት እንጢንዮስ እስከ መልካም ሽምግልና ደረሰ እጅግም አረጀ ግን ወደ ወደደውም ክርስቶስ እስከ ሄደ ድረስ መልኩ አልተለወጠም ብርታቱ ፅናቱም መላው እድሜው መቶ ሀያ አመት ነው። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳን መላእክት ጸሎትና ምልጃ ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።https://t.me/finotebirhan12

የዚህም ቅዱስ ወላጆቹ ንፁሀን ክርስቲያን ናቸው እርሱም ከታናሽነቱ ጀምሮ ተንኮል ሽንገላ በልቡ ውስጥ የለውም ከወላጆቹም ጋር ወደ ቤተክርስቲያን ሂዶ በቆረበ ጊዜ ከህፃናት ጋር በመጫወት ከቶ አይሳሳቅም ነበር። ጥቂት በአደገም ጊዜ ራሱን ዝቅ አድርጎ ለወላጆቹ ይታዘዝ ነበር ሰባት አመትም በሆነው ጊዜ የቤተ ክርስቲያን መፃህፍትን ተማረ ያን ጊዜም የእስክንድርያ አገር ሊቀ ጳጳሳት አባ ቲዎናስ የተሾመበት ዘመን ነበር የእንጦንዮስንም ወሬውን ሰምቶ መልእክተኞችን ልኮ ወደርሱ አስመጣው ባረከውና ስለርሱ እንዲህ ብሎ ትንቢት ተናገረ ይህ ህፃን በእግዚአብሄር ፊት ታላቅ ይሆናል ዜናውም በአለሙ ሁሉ ይወጣል እጁንም በላዩ ጭኖ ዲቁና ሾመው። ከዚህም በኃላ ወላጆቹ በሞቱ ጊዜ ታናሽ ብላቴና እኅት ትተውለት ነበር።ከሰባት ወርም በኃላ እንደ ልማዱ ወደ ቤተ ክርስቲያን በሄደ ጊዜ የመንፈስ ቅዱስ ፍቅር በልቡ አደረበትና በኀሳቡ በአለም የሚሰራውን ሁሉ አባቶቻችን ሀዋርያት ሁሉን የአለምን ስራ ትተው ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን እንዴት ተከተሉት በሀዋርያት ስራ መፅሀፍም እንደተፃፈ ጥሪታቸውን እየሸጡ የሽያጩንም ዋጋ በሀዋርያት እግር ስር ያኖሩትን አሰበ እግዚአብሄር በሰማያት ያዘጋጀላቸው ዋጋቸው ምን ያህል ይሆን አለ ይህም ኀሳብ በልቡ ውስጥ የሚመጣ የሚወርድ ሆነ። ከዚህም በኃላ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሄደ የክብር ባለቤት ጌታችን በከበረ ወንጌል ለባለፀጋው የተናገረውን ሰማ እንዲህ ሲል ፍፁም ትሆን ዘንድ ከወደድክ ሂድ ጥሪትህን ሁሉ ሸጠህ ለድኆች ስጥ በሰማይም ላንተ ድልብ አድርገው መጥተህም ተከተለኝ። ከእግዚአብሄርም ዘንድ ይህን ልዩ ኀሳብ አግኝቶ ይህ ቃል ስለርሱ እንደተነገረ አሰበ በዚያንም ጊዜ ከቤተ ክርስቲያን ወጣ ለአባቱም ያማረ ሰፊ ምድር ነበረው ለአገሩም ሰዎች ሰጣቸው ለርሱ የተውለትንም ጥሪታቸውን ሁሉ ሸጦ ለድኆችና ለችግረኞች ሰጣቸው እኅቱንም ወስዶ ከደናግል ገዳም አስገባት። በዚያንም ወራት የምንኩስና ስርአት አልተገለፀም ነበር እግዚአብሄርንም ለማገልገል የሚሻ ከመንደር ጥቂት ወጣ ብሎ ብቻውን በመቀመጥ በፆም በፀሎት ተወስኖ ይጋደላል የከበረ እንጦንዮስም እንዲሁ አደረገ ሰይጣናትም በስንፍናና በዝሙት ጦር የሚዋጉት ሆኑ በህልሙም የሴት ገፅ በማሳየት አብራውም እንደምትተኛ ያደርጓታል። ከዚህም በኃላ በባህር ዳርቻ ወዳለች የመቃብር ቤት ሂዶ በዚያ የሚኖር ሆነ በላዩ በአደረ በእግዚአበሄርም ረድኤት በተጋድሎ በረታ ምግቡንም ከዘመዶቹ ወገን ያመጡላት ነበር ሰይጣናትም ሲጋደል አይተው ቀኑበት ታላቅ ዱብደባንም ደብድበው ጥለውት ሄዱ ዘመዶቹም ሲመጡ እንደ ሞተ ሆኖ ወድቆ አገኙት ተሸክመውም ወደ ቤተ ክርስቲያን ወሰዱት ጌታችንም አዳነው በነቃም ጊዜ ወደ ቦታው ተመልሶ ይጋደል ዘንድ ተጋድኖውን ጀመረ። በዚያንም ጊዜ ሰይጣናትን ወደርሱ ሲመጡ አያቸው በአራዊት አምሳል በአንበሶችና በተኩላዎች የተመሰሉ አሉ በእባቦችና በጊንጦችም የተመሰሉ አሉ ያስፈሩትም ዘንድ አንዱም አንዱ በላዩ ተነሳሱ እንጦንዮስም በእኔ ላይ ለእናንተ ስልጣን ካላችሁ ከእናንተ አንድ ያሸንፈኝ ነበር ብሎ ዘበተባቸው ወዲያውኑ እንደ ጢስ ተበተኑ በሰይጣናት ላይ ድልን እግዚአብሄር ሰጥቶታልና ሰይጣናትም ከሚያመጡበት መከራና ስቃይ አረፈ። ምግቡንም በአመቱ ሁለት ጊዜ ያበስላል በፀሀይም ያደርቀዋል ወደበአቱም ማንም እንዲገባ አያሰናብትም የሚሻውም ሁሉ በውጭ ይቆምና ድምፁን ይሰማል እንጂ ሀያ አመትም እንዲህ ታላቅ ተጋድሎን እየተጋደለ በገደል ተጠምዶ ኖረ። ከዚህም በኃላ ፍፁም የሆነ እግዚአብሄርን መፍራትንና አምልኮቱን ለሰዎች ወጥቶ ያስተምር ዘንድ እግዚአብሄር አዘዘው ስለዚህም ወደ ፍዩም አገር ወጥቶ ብዙዎች ደቀ መዛሙርትን ሰብሰቦ አስተማራቸው በእግዚአብሄርም ህግ አፀናቸው ደቀ መዛሙርቶቹ በውስጣቸው የሚኖሩባቸው ብዙዎች ገዳማት ተሰሩለት። ስለ ሀይማኖትም ስደት በሆነበት ወራት በሰማእትነት መሞት ወዶ ወደ እስክንድርያ ሀገር ሄዶ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ታመነ ከቶ አልያዙትም በክርስቶስም ስም የታሰሩ እስረኞችን በመጎብኘት ቢአረጋጋቸውና ቢአፅናናቸውም አልያዙትም መኮንኑም እንደማይፈራ ባየው ጊዜ ከፍርድ አደባባይ ውስጥ እንዳይታይ አዘዘው እርሱ ግን ሁልጊዜ መታየቱን አለተወም እንዲአሰቃየውና በሰማእትነትም እንዲሞት የሚያስቆጣውን ነገር ይናገረው ነበር መኮንኑም በእርሱ ላይ ምንም ክፉ ነገር አላደረገም አምላካዊት ኃይል ከልክላዋለችና። ሊቀ ጳጳሳት ጴጥሮስ ለሰማእታት ፍፃሜ ሆኖ የመከራው ወራት ከአለፈ በኃላ እንጦኒ ወደ ገዳሙ ተመለሰ ይህም በአምላክ ፍቃድ ሆነ የሚለብሰውም ማቅ ነበር በዘመኑ ሁሉ ገላውን በውኃ አልታጠበም ብዙዎች በሽተኞችም ወደርሱ ይመጣሉ በላያቸውም ሲፀልይ ይድናሉ። ብዙዎች ህዝቦችም ትምህርቱን ሊሰሙ ወደርሱ ሲመጡ በአያቸው ጊዜ ብቻውንም ይኖር ዘንድ እንዳልተውት አይቶ ከእርሱ ስለሚደረገው ነገር ልቡ እንዳይታበይ ፈራ እነርሱ ወደሚያውቁት ቦታ ወደላይኛው ግብፅ ይሄድ ዘንድ ወዶ ወደ ባህሩም ወደብ ደርሶ መርከብ እየጠበቀ ተቀመጠ ከሰማይም ወደርሱ ቃል መጣ እንዲህም አለው እንጦንዮስ ሆይ ወዴት ትሄዳለህ ከዚህስ ምን ትሻለህ አለው እርሱም ብዙዎች ወደእኔ ስለሚምጡ እንደምፈልገው ለብቻ መኖር አልተቻለኝም ስለዚህም ወደ ላይኛው ግብፅ እሄድ ዘንድ ወደድኩ አለ ያም ቃል መልሶ እንዲህ አለው ወደ ላይኛው ግብፅ ብትሄድ ድካምህ ደግሞ እጥፍ ይሆናል ብቻህን መኖር ከወደድክ ግን የሶስት ቀን ጎዳና ያህል ወደ ውስጠኛው በረሀ ተጓዝ። በዚያንም ጊዜ በዚያች ጉዳና ሊጓዙ የሚሹ የዓረብ ሰዋችን አያቸው ወደ እርሳቸውም ሒዶ አብረሮአቸው ይሔድ ዘንድ ለመናቸው እነርሱም በደስታ ተቀበሉት ወደ አንድ እጅግ ረጅም ወደ ሆነ ተራራ እስከሚደርስ የሦስት ቀን ጉዳና ተጓዘ በዚያም የጠራና የቀዘቀዘ ውኃ አለ ዳግምም የሰሌን የተምር ዕንጨቶች መቃቃዎችም በብዛት አሉበት እንጦኒዮስም ያንን ቦታ ወደደው ዓረቦችም ምግቡን የሚያመጡለት ሆኑ ብዙዎች የከፋ አራዊትም ነበሩ በጸሎቱም እግዚአብሔር አስወገዳቸው ወደዚያም ቦታ ከቶ አልተመለሱም። አንዳንድ ጊዜም ወደ ባሕሩ ዳርቻ በመውጣት ደቀ መዛሙርቶቹን ጉብኝቶና አረጋግቶ በበረሀ ወስጥወደአለው ቦተው ይመለሳል ። ከዚህም በኋላ በጸድቁ ንጉሥ ቁስጠንጢስዘንድ ዜናው በተሰማ ጊዜ በጸሎቱያስበው ዘንድ ንጉሡ አየለ መነዉ ደብዳበ ጻፈለት የከበረ እንጦንዮስ ግን ወደ ንጉሥ ደብዳቤ ዘወር አላለም ለወገኖቹ እንዲህ አላቸውእንጂ የንጉሠ ነገሥት ክርስቶስ ደብዳቤ እንሆበላያችን ይነበባል ወንድሞችም እንዲህ ብለው ለመኑት ይህ ንጉሥ የክርስቲያንን ወገኖች የሚወድ ጻድቅ ሰው ነው ደብዳቤ ጽፈህ ልታጽናናው ይገባል ከዚህም በኃላ እያፅናናውና እየባረከው ፃፈለት። ዳግመኛም በአፍርንጊያ ንጉስ ዘንድ ዜናው በተሰማ ጊዜ ወደ ከበረ እንጦንዮስ እንዲህ ብሎ ፃፈ ወደ እኛ መጥተህ በእኛ ላይ በአገራችንና በሰራዊታችን ላይ በረከትን ታሳድር ዘንድ ስለ ጌታችን ክርስቶስ መከራዎች እኔ ወዳንተ ፈፅሜ እማልዳለሁ።

🔴#ስንክሳር ጥር_22 አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ጥር ሃያ ሁለት በዚች ቀን የሊቀ መላእክት #ቅዱስ_ዑራኤል በዓለ ሲመቱ ነው፣ የከበረና የገነነ የመነኰሳት ሁሉ አባት አባት #ቅዱስ_እንጦንስ አረፈ፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_ዑራኤል_ሊቀ_መላዕክት ጥር ሃያ ሁለት በዚህች ቀን ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ የሆነው ሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል በዓለ ሲመቱ ነው፡፡ ኢዮር፣ ራማ እና ኤረር የተባሉ ሦስት የመላእክት ከተሞች አሉ፡፡ እግዚአብሔር ቅዱሳን መላእክት ከፈጠራቸው በኋላ በነገድ 100 በአለቃ 10 አድርጎ በሦስቱ ሰማያት አስፍሯቸዋል፡፡ ኢዮርን በ4፣ ራማን በ3፣ ኤረርንም በ3 ከፍሎ ነው በዐሥሩ ከተማ ያሰፈራቸው፡፡ በዚህም መሠረት ኢዮርን ላይና ታች አድርጎ በ4 ከተማ ከፍሏታል፡፡ በእርሷ ያሉትን መላእክትን በ40 ነገድ 4 አለቃ አድርጎ ከፈላቸው፡፡ የመጀመሪያው ነገድ ‹‹አጋእዝት›› ይባላሉ፡፡ አለቃቸው ሣጥናኤል ነበር፤ እርሱም የመላእክትን ሁሉ ጸሎት ወደ እግዚአብሔር ያሳርግ ነበር፡፡ ከክብሩ ሲዋረድ ቅዱስ ሚካኤል በምትኩ ተሹሞበታል፡፡ ሁለተኛው ነገድ ‹‹ኪሩቤል›› ይባላሉ፡፡ እነርሱም መንበረ ሥላሴን ይሸከማሉ፡፡ የቀሳውስት አምሳል ናቸው፡፡ አለቆቻቸው ገጸ ሰብና ገጸ አንበስ ናቸው፡፡ በሦስተኛው ከተማ በኢዮር ያሉት ሱራፌል ይባላሉ፡፡ የዲያቆናት አምሳል ናቸው፡፡ በትንቢተ ኢሳያስ በምዕራፍ 6 ላይ የተገለጹትና ኢሳያስን ከለምጹ እንዲፈወስ ያደረጉት ናቸው፡፡ አለቆቻቸው ገጸ ላህምና ገጸ ንስር ናቸው፡፡ (በነገራችን ላይ ‹‹ከሩቤል›› ወይም ‹‹ሱራፌል›› የሚባሉ የግለሰብ መጠሪያ ስሞች ስህተት ናቸው፡፡ አንደኛ እነዚህ ስሞች የብዙ መላእክት መጠሪያን የሚወክሉ ናቸው፡፡ ለአንዱ ሲሆን ‹‹ኪሩብ፣ ሱራፊ›› ይባላል፡፡ ‹ኪሩቤል› ወይም ‹ሱራፌል› ማለት ግን የብዙ ቁጥራቸው መጠሪያ ነው፡፡ ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ የቅዱሳን መላእክትን ስም እንዳለ በቁሙ ወስዶ ለግል መጠሪያ ስም ማዋል ተገቢ አይደለም፡፡ ‹‹ወለተ ሚካኤል፣ ክንፈ ገብርኤል….›› እየተባሉ ይሰየማሉ እንጂ ቀጥታ ‹ሚካኤል›፣ ‹ገብርኤል› እያሉ ሰዎችን መሰየም ስህተት ነው፡፡ 4ኛው ከተማ በኢዮር ያሉት ኃይላት ይባላሉ፡፡ የእሳት ሰይፍ ይዘው በሥሉስ ቅዱስ ፊት የሚቆሙ ናቸው፡፡ በመንፈሳዊ ሕይወት የዛሉና የደከሙ ክርስቲያኖችን የሚያበረታቱ ናቸው፡፡ አለቃቸውም ቅዱስ ሚካኤል ነው፡፡) ዳግመኛም እግዚአብሔር በራማ ያሉትን መላእክት በ30 ነገድ በ3 አለቃ አድርጎ ከፈላቸው፡፡ የመጀመሪያዎቹ ‹‹አርባብ›› ይባላሉ፡፡ የሥላሴ እልፍኝ አስከልካዮች ናቸው፡፡ የእግዚአብሔርን መንበር በክንፎቻቸው ይሸፍናሉ፡፡ አለቃቸው ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡ ሁለተኞቹ በራማ ከተማ ያሉት ‹‹መናብርት›› ይባላሉ፡፡ ለእግዚአብሔርን እጅግ ቅርብ የሆኑ ናቸው፡፡ የመብረቅ ጋሻቸውን የእሳት ጦራቸውን ይዘው የሥላሴ ጋሻ ጃግሬዎች ሆነው በተጠንቀቅ ይቆማሉ፡፡ የሰውን ችግር ለእግዚአብሔር ያቀርባሉ፡፡ መዝ. 88፡6፡፡ አለቃቸው ቅዱስ ሩፋኤል ነው፡፡ ሦስተኞቹ በራማ ከተማ ያሉት ‹‹ሥልጣናት›› ይባላሉ፡፡ መላውን ፍጥረት ለመጠበቅ ሥልጣን የተሰጣቸውና የምጽአት ዕለት አዋጅ ነጋሪዎች ናቸው፡፡ ዳን. 12፡1፡፡ አለቃቸው ቅዱስ ሱርያል ነው፡፡ ዳግመኛም እግዚአብሔር በኤረር ያሉትን መላእክት በ30 ነገድ በ3 አለቃ አድርጎ ከፈላቸው፡፡ የመጀመሪያዎቹ ‹‹መኳንንት›› ይባላሉ፡፡ የስላሴ የእሳት ባለ ቀስት ናቸው፡፡ የሰው ልጅ ልዩ ጠባቂዎች ናቸው፤ በተለይ በአደጋ ጊዜ ሎጥን እንዳዳኑት ፈጥነው ይደርሳሉ፡፡ በዕለተ ምጽዓት የሰውን ሁሉ ዐፅም ሰብስበው ለትንሣኤ ዘጉባኤ ያበቃሉ፡፡ አለቃቸው ቅዱስ ሰዳካኤል ነው፡፡ ሁለተኛዎቹ ‹‹ሊቃናት›› ይላሉ፡፡ የሥላሴ የእሳት ፈረሶች ናቸው፡፡ በእሳት ፈረስ ይመላለሳሉ፡፡ እነዚህም 24ቱ ካህናተ ሰማይ ሲሆኑ አለቃቸው ቅዱስ ሰላታኤል ነው፡፡ በኤረር ከተማ የሰፈሩት ሦስተኛዎቹ ‹‹መላእክት›› ይባላሉ፡፡ ፍጥረትን ሁሉ የሚጠብቁ ናቸው፡፡ አለቃቸው ቅዱስ አናንኤል ነው፡፡ በእነዚህ የማይጠበቅ ፍጥረት የለም፡፡ ከአዝርእት ጀምሮ ሁሉን ይጠብቃሉ፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ በራእዩ ‹‹በእግዚአብሔር ፊት የሚቆሙ 7 መላእክትን አየሁ›› (ራዕ. 8፡2) እንዳለ ሊቃነ መላእክት በቁጥር 7 ናቸው፡፡ እነርሱም፡- ቅዱስ ሚካኤል፣ ቅዱስ ገብርኤል፣ ቅዱስ ሩፋኤል፣ ቅዱስ ራጉኤል፣ ቅዱስ ዑራኤል፣ ቅዱስ ፋኑኤል እና ቅዱስ አፍኒን ናቸው፡፡ ‹‹ዑራኤል›› የሚለው ስም ‹ዑር› እና ‹ኤል› ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ስም ነው፡፡ ‹‹ዑራኤል›› ማለት ትርጉሙ ‹‹የብርሃን ጌታ፣ የአምላክ ብርሃን›› ማለት ነው፡፡ ቅዱስ ዑራኤል ከ7ቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ ሲሆን ከፍጥረተ ዓለም ጀምሮ በመብረቅና በነጎድጓድ ላይ የተሾመ መልአክ ነው፡፡ በመሆኑም መጽሐፈ ሄኖክ እንደሚገልጸው መባርቅት ለጥጋብና ለበረከት እንዲበርቁ ነጎድጓድም ለሰላም እንዲሆን ያሰማራል፡፡ ምሥጢረ ሰማይንና ሰማያዊውን ዕውቀት ሁሉ ለሄኖክ የገለጸለት መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡ የፀሐይን፣ የጨረቃን፣ የከዋክብትንና የሰማይ ሠራዊትን ብርሃንን የሚመራው ይኸው ገናና መልአክ ነው፡፡ መጽሐፈ ሄኖክ 28፡13፡፡ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ለዓለም ቤዛ ሆኖ በተሰቀለ ጊዜ ክቡር ደሙን በብርሃን ጽዋ ተቀብሎ በብርሃነ መነሳንስ በዓለም ላይ የረጨው ይኸው ገናና መልአክ ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡ ለነቢዩ ዕዝራ ሱቱኤል ጽዋ ጥበብን አጠጥቶ ሰማያዊውን ምሥጢር የገለጠለት መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡ ዕውቀት ተሠውሮበት ለነበረው ለኢትዮጵያዊው ሊቅ ለአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫም በእመቤታችን ትእዛዝ ጽዋ ጥበብን አጠጥቶ ሰማያዊውን ምሥጢር የገለጠለት ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡ ‹‹ዑራኤል የተባለ መልአክ ሊረዳኝ መጣ፡፡›› መጽሐፈ ዕዝራ 2፡1፡፡ አምላካችን እግዚአብሔር የሕይወትና የይቅርታ ዝናም በምድራችን ላይ ያዘንብ ዘንድ እንዲሁም የእርሻችንን አዝመራ በዝናም አብቅሎ በፀሐይ አብስሎ ለምግብነት እንዲበቃ ከፈጣሪ ዘንድ ምሕረትን የሚለምን መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡ ሊቁ አባ ጊዮርጊስም በመልአኩ አማላጂነት እጅግ ብዙ ድርሰቶችን የደረሱት መልአኩ ጽዋ ሕይወትን ካጠጣቸው በኋላ ነው፡፡ በመጀመሪያም አባ ጊዮርጊስ የተወለዱት በቅዱስ ዑራኤል አብሳሪነት ነው፡፡ በቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ የተመሠረቱ አብዛኞቹ ቅዱሳት ገዳማት በቅዱስ ዑራኤል መሪነት ነው፡፡ ድርሳኑ ላይ የማይጠቅሳቸው የሀገራችን የከበሩ ቅዱሳት ገዳማትና ቅዱሳን ነገሥታት የሉም፡፡ የብርሃን እናቱ ድንግል ወላዲተ አምላክን ከልጇ ከአምላካችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ስትሰደድ መንገድ እየመራ ወደ ግብጽ እና ወደ አገራችንን ኢትዮጵያ ያመጣቸው ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡ እመቤታችንን ከተወደደ ልጇ ጋር በደመና ጭኖ መላ ኢትዮጵያን ካስጎበኛት በኋላ ቅድስት አገራችንን ለእመቤታችን የዓሥራት አገር እንድትሆን ያደረገው መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል ነው፡፡ መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል በዓመት 3 ዓበይት በዓላት አሉት፡፡ ጥር 22 በዓለ ሲመቱ ነው፡፡ መጋቢት 27 የጌታችንን ክቡር የሆነ ወርቀ ደሙን ለዓለም የረጨበት ነው፡፡ ሐምሌ 22 ቀን ቅዳሴ ቤቱ የሚከበርበትና ለነቢዩ ዕዝራ ሱቱኤል የዕውቀትን ጽዋ ያጠጣበት ዕለት ነው፡፡ ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #አባ_እንጦንስ_ርዕሰ_መነኮሳት በዚችህ ቀን በግብፅ አገር ከአቅማን ከተማ የከበረና የገነነ የመነኰሳት ሁሉ አባት በገዳም ለሚኖር እንደ ኮከብ የሚያበራላቸው አባት እንጦንዮስ አረፈ።

ቅዱስ ጎርጎርዮስም እንደ ልማዱ ሊቀድስ ወደ መሰዊያው በወጣ ጊዜ የከበረች ድንግል እመቤታችን ማርያም ተገለፀችለትና ዛሬ ወደኔ ትመጣለህ አለችው የቁርባኑንም ቅዳሴ ሲጨርስ ህዝቡ በቀናች ሀይማኖት ፀንተው እንዲኖሩ ይመክራቸውና ያስተምራቸው ዘንድ ወንድሙን ባስልዮስን ለመነው እርሱም እንደሚያንቀላፋ ሆነ በቀሰቀሱትም ጊዜ ሞቶ አገኙት ቅዱስ ባስልዮስም ሳጥን እንዲሰሩለት አዘዛቸው። ፀሎታትንም በመፀለይ መዝሙራትንም በመዘመር በማመስገንም እንደሚገባ ገንዞ በመቃብር ውስጥ አኖሩት። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_ኤርምያስ_ነቢይ በዚህች ቀን የካህኑ ኬልቅዩ ልጅ ታላቁ ነቢይ ኤርምያስ መታሰቢያው ነው። ይህም እውነተኛ ነቢይ የአሞጽ ልጅ የይሁዳ ንጉሥ ኢዮስያስ በነገሠ በዐሥራ ሦስት ዓመቱ ማስተማር ጀመረ። ከዚያም በይሁዳ ንጉሥ በኢዮስያስ ልጅ በኢዮአቄም ዘመን ዐሠራ አንዱ የሴዴቅያስ ዘመነ መንግሥቱ እስከሚፈጸም በአምስተኛው ወር ኢየሩሳሌም እስከ ተማረከችበት ጊዜ ያስተምር ነበር። ስለ ራሱ እንዲህ ሲል ራሱ ተናገረ የእግዚአብሔር ቃል ወደኔ መጣ እግዚአብሔርም እንዲህ አለኝ "በእናትህ ማሕፀን ሳልፈጥርህ ወደድኩህ ከእናትህም ማሕፀን ሳትወጣ መረጥኩህ ለአሕዛብም መምህር አደረግሁህ አለኝ።" ይህም ነቢይ የእግዚአብሔርን አምልኮና ሕጉን በመተዋቸው እንዲህ ሲል የእስራኤልን ልጆች ገሠጻቸው። ተጠበቁ ንስሐም ግቡ የእግዚአብሔር ቁጣው በላያችሁ እንዳይመጣ። ሁለተኛም እንዲህ ብሎ አስረዳቸው ወደ ፈጣሪያችሁ እግዚአብሔር ካልተመለሳችሁ ያለዚያ የከላውዴዎንን ንጉሥ ናቡከደነጾርን በላያችሁ እርሱ ያሥነሣዋል ይማርካችኋልም እንደቃሉም ሆነ። ሁለተኛም ሕዝቡ ተማርከው ሰባ ዘመን እንደሚኖሩ ትንቢት ተናገረ። ደግሞ የክብር ባለቤት ኢየሱስ ክርስቶስ ለኩነተ ሥጋ እንደሚመጣና መከራ እንደሚቀበል የአስቆሮቱ ይሁዳ እንደሚሸጠውና ሠላሳ ብር እንደሚወስድ ተናገረ። ስለ ብዙ ሥራዎችም ተናገረ አይሁድ ግን ሊገድሉት ወደው ገርፈው አሥረው በጒድጓድ ውሰጥ ጣሉት እግዚአብሔርም አዳነው። እርሱ ግን ስለእነርሱ ይለምንና ይማልድ ነበር እግዚአብሔርም ስለ እርሳቸው ወደእኔ አትማልድ እነርሱ ከክፋታቸው አይመለሱምና አለው። ናቡከደነጾርም የኢየሩሳሌምን ሕዝብ በማረከ ጊዜ ከእሳቸው ጋራ አልማረከውም። ነገር ግን ከምርኮ የቀሩት ወደ ግብጽ አገር ወሰዱት የግብጽን ሰዎች ሲያጠፉአቸው የነበሩ በግብጽ ወንዞች የሚኖሩ አራዊትን በእርሱ ጸሎት እግዚአብሔር አጠፋቸው። ከዚያም ወደ ባቢሎን አገር ወሰዱት በዚያም የእስራኤል ልጆች ከምርኮ እስኪመለሱ ትንቢት እየተናገረ ሕዝቡን ሲአስተምር ኖረ። የትንቢቱ ወራትም በተፈጸመ ጊዜ አይሁድ በደንጊያዎች ወገሩት ነፍሱንም በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ። የህይወት የድኅነት አለኝታ የሆነች እርሷን እናቱን ለሰጠን እግዚአብሔር ምስጋና ይሁን በፀሎቷም ከክፉ ነገር ይጠብቀን አሜን።https://t.me/finotebirhan12

ስጋዋንም ያሳዪት ዘንድ ወደ መቃብርዋ በአደረሱት ጊዜ በመቃብር ውስጥ ስጋዋን አላገኙም ደንግጠውም አደነቁ ያን ጊዜ ከመላእክት ጋር ወደ ሰማይ ስታርግ እመቤታችንን እንዳገኛት ቶማስ ነገራቸው። ሀዋርያትም ይህን በሰሙ ጊዜ የእመቤታችንን እርገቷን ስለ አላዩ እጅግ አዘኑ ስጋዋን በምድር ውስጥ ይተው ዘንድ እንዳልወደደ መንፈስ ቅዱስ አስገነዘባቸው። ከዚህም በኃላ አንድ ጊዜ ደግሞ እርሷን ያሳያቸው ዘንድ እንዳለው ጌታችን ቃል ኪዳን በማድረግ ተስፋ ስጣቸው እነርሱም እስከ ነሀሴ አስራ ስድስት በረስፋ ኖሩ። የእመቤታችንም የእድሜዋ ዘመን ስልሳ አራት አመት ነው በአባትና እናቷ ቤት ሶስት አመት ከሰባት ወር በቤተ መቅደስም አስራ ሁለት አመት በዮሴፍም ቤት ሰላሳ አራት አመት ከሶስት ወር ከጌታ እርገት በኃላ በወንጌላዊ ዮሀንስ ቤት አስራ አራት አመት ነው። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅድስት_ኢላርያ በዚህችም እለት የሮሜ አገር ንጉስ የዘይኑን ልጅ የከበረች ኢላርያ አረፈች። የዚችም ቅድስት አባቷ እግዚአብሔርን የሚውድ ሀይማኖቱ የቀና ነው ይቺን ቅድስት ኢላርያንና ሁለተኛዋን እኃቷን ወለደ ከእንርሱም በቀር ወንድ ልጅ የለውም። ይቺም ቅድስት ኢላርያ የምንኮስና ልብስን የመላእክትንም አስኬማ ትለብስ ዘንድ የምትመኝ ሆነች ከቤተመንግስትም ወጥታ ልብሷን ለውጣ የወንድ ልብስ ለብሳ ወደ ግብፅ ሀገር ሄድች። ከዚያም ወደ አስቄጠስ ገዳም ደረሰች በዚያም ስሙ አበሰ ባውሚን የሚባለውን ፍፁም ሽማግሌ ፃድቅ ሰውን አግኝታ ሀሳቧን ሁሉ ነገረችው እርሷ ሴት እንደ ሆነችም አስረዳችው እርሱም ምስጢሯን ሰውሮ ለብቻዋ በዋሻ ውስጥ አስገባት ይጎበኛትና ልትሰራው የሚገባትን ያስተምራት ነበር። እንዲህም ሆና አስራ ሁለት አመት ኖረች ፅህም ስለሌላትም ለአረጋውያን መነኰሳት ጃንደረባ ትመስላቸው ነበር።በወንድ ስም አጠራርም አባ ኢላርዮን ብለው ይጠሩዋታል። ከአባቷ ዘንድ በቀረችው በሁለተኛዋ ግን ርኩስ ሰይጣን አደረባትና ያሰቃያት ጀመር ያድኗትም ዘንድ ለባለ መድሀኒቶች አባቷ ብዙ ገንዘብ ሰጠ ግን አልተቻላቸውም። ከዚህም በኃላ የከበሩ አረጋውያን መነኮሳት ወዳሉበት አስቄጥስ ገዳም ይልካት ዘንድ መኳንንቶቹ መከሩት የቅድስናቸው ወሬ በሮም ሀገሮች ሁሉ ተሰምቷልና በዚያንም ጊዜ ወደ ቅዱሳኑ ከብዙ ሰራዊት ጋር ላካት ለቅዱሳኑም መልእክትን ፃፈላቸው እንዲህ ሲል የተከበራችሁ አባቶቼ ሆይ የደረሰብኝን ኃዘን አስረዳችኃለሁ እግዚአብሔር ሁለት ሴቶቸ ልጆችን ሰጥቶኝ ነበር። አንዲቱ ከአለም ሸሸች ወደየት ቦታ እንደምትኖር አላውቅም በሁለተኛዪቱም በላይዋ ርኩስ መንፈስ ተጫነበት እኔ መፅናኛ ትሆነኛለች ብዬ እየሰብኩ ነበር አሁንም በፀሎታቸሁ እግዚአብሔር ያድናት ዘንድ በላይዋ እንድትፀልዩ አኔ ቅድስናችሁን እለምናሉ። ቅዱሳን መነኮሳትም የንጉሱን ደብዳቤ በአነበቡ ጊዜ በላይዋ ሊፀልዩ ጀመሩ በላይዋ ያደረ ሰይጣንም ከኢላርዮን በቀር ከማደሪያዬ የሚያሰጠኝ የለም ብሎ ጮኸ። አርጋውያኑም ጃንደረባ የሚሏትን ኢላርያን ጠርተው እግዚአብሄር እስከ አዳናት ድረስ የንጉሱን ልጅ ወስደህ በላይዋ ፀልይ አሏት ቅድስት ኢለርያም እኔ በደለኛ ሰው ነኝ ይህን ጭንቅ የሆነ ስራን መስራት አልችልም አለቻቸው። በአሰገደድዋትም ጊዜ ወደ በአትዋ ወሰዳ በላይዋ ፀለየች ሰይጣነም ትቷት ሸሸ እህቷ እንደሆነች ታውቃለች ስለዚህ አቅፋ ትስማት ነበር ስለ ናፍቆቷና ስለ ፍቅርዋ ወደ ውጭ ወጥታ ታለቅሳለች። ከዚህም በኃላ ወደ ከበሩ አረጋውያን አደረሰቻችና እነሆ በፀሎታችሁ እግዚአብሔር አድኗታል ወደ አባቷ መልሷት አለቻቸው። እነርሱም እጅግ ደስ ብሏቸው ወደ አባቷ መለሱዋት ለእግዚአብሔርም ምስጋና አቀረቡ። ወደ ሮሜ አገርም ወደ አባቷ በደረሰች ጊዜ አባትና እናቷ ስለ መዳንዋ በእርሷ እጅግ ደስ አላቸው የቤተ መንግስትም ሰዎችም ሁሉ እግዚአብሔርን አመሰገኑት። አባቷም በገዳም ከቅዱሳን አባቶች ጋር አኗኗርሽ እንዴት ነበር ብሎ ጠየቃት እርሷም እንዲህ ብላ ነገረችው ያ ያዳነኝ አባ ኢላርዮን የሚባል አባት አብዝቶ ይወደኛል አቅፎም ይስመኛል ንጉሱም ይህን ሰምቶ በልቡ ታወከ ለመነኩሴ ሴቶችን መሳም ይገባዋልን አለ። በዚያንም ጊዜ በእኔ ላይ ይፀልይ ዘንድ አገሬንም ይባርክ ዘንድ ልጄን ያዳናትን አባ ኢላርዮንን ወደኔ ላኩት የሚል ደብዳቤ ፅፎ ወደ ቅዲሳን አረጋውያን ላከ። አረጋውያንም ቅድስት ኢላርያን ጠርተው ወደ ንጉስ እንድትሄድ አዘዙዋት እርሷም ይተዋት ዘንድ አረጋውያን አባቶችን አልቅሳ ለመነቻቸው። እንርሱም እንዲህ አሉዋት ይህ ንጉስ ክርስቲያኖችን የሚወድ ፃድቅ ነው ቅዱሳት መፃህፍትም እንደሚያዙን ትእዛዙን መተላለፍ አይቻለንም ይህንንም ብለው አስገድደው ላኩዋት። ወደ ንጉሱም በደረሰች ጊዜ ንጉሱና የቤተ መንግስት ሰዎች ሁሉም በክብር ተቀብለው ተሳለሟት ከዚህም በኃላ ንጉሱና ንግስቲቱ ለብቻቸው ሆነው ወደ ውስጠኛው አዳራሽ አስገለሉዋትና ንጉሱ እነዲህ ብሎ ጠየቃት አንተ ልጄን እንደምትስማት በሰማሁ ጊዜ በሀሳቤ ታውኬ አለሁ መነኩሴ ሴትን መሳም አይገባውምና ይህን ነገር ትገልጥልኝ ዘንድ እሻለሁ። የከበረች ኢላርያም በነገርኳችሁ ጊዜ ወደ አስቄጥስ ገዳም መሄድን ላትከለክሉኝ የከበረ ወንጌልን አምጥታችሁ ማሉልኝ አለቻቸው እነርሱም እንዳለችው ማሉላት። በዚያንም ጊዜ ልጃቸው ኢላርያ እንደሆነች ነገረቻቸው። አወጣጧም እንዴት እንደሆነ ልብሶቿንም ለውጣ የወንድ ልብስ እንደለበሰች አስረዳቻቸው በአካሏም ውስጥ ያለ ምልክትን አሳየቻቸው። በዚያንም ጊዜ ታላቅ ጩኸትን ጮኹ አቅፈው እየሳሟት አለቀሱ ከእኛ ዘንድ እንድትሄጂ ከቶ አንተውሽም አሏት እርሷም በከበረ ወንጌል የማላችሁትን መሀላ አስቡ አለቻቸው። እነርሱም ከእርሱ ጋር አርባ ቀን ያህል እንድትኖር ለመኑዋትና አርባ ቀን አብራቸው ኖረች ከዚህም በኃላ ወደ ቦታዋ ሄደች። ከዚያችም እለት ወዲህ በአስቄጥስ ገዳም ለሚኖሩ ቅዱሳን የከበሩ አረጋውያን መነኮሳት ለፍላጊታቸው ይሆን ዘንድ የግብፅን ምድር ሁሉ ግብር እንዲሰጧቸው ንጉስ ዘይኑን አዘዘ በዚያንም ወራት በአባ መቃርስ ገዳም አራት መቶ የመነኮሳትን ቤቶች ሰሩ በአባ ዮሀንስም ገዳም ሰባት መቶ በአባ ሙሴ ገዳም ሶስት መቶ ቤቶችን ሰሩ። ከዚህም በኃላ ቅድስት ኢላርያ አምስት አመት ከኖረች በኃላ አረፈች ከእረፍቷም አስቀድሞ እርሷ ሴት እንደሆነች ያወቀ የለም። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ቅዱስ_ጎርጎርዮስ_ዘኑሲስ በዚህችም እለት የኑሲስ ኤጲስቆጶስ የባስልዮስ ወንድም የከበረ ጎርጎርዮስ የእፍቱ መታሰቢያ ነው እነሆ የአባቱንና የወንድሙን መታሰቢያቸውን በዚህ ወር ጥር ስድስት ቀን ፅፈናል። ይህም ቅዱስ ጎርጎርዮስ እጅግ የተማረ አዋቂ ነበረ በደሴቶችም ላይ ኤጲስቆጶስነት ተሾመ እነሆ በዚህ ወር በአስራ አምስት ቀን የሆነውን ከገድሉ ጥቂት እንፅፋለን።ስለርሱም እንዲህ ተባለ እርሱ መስዋእቱን ለማክበር በሚቀድስ ጊዜ በመሰዊያው ላይ ሲወርድ መንፈስ ቅዱስን የሚያየው ሆነ ከዚህም በኃላ ኪሩብን አየው በደረቱም ውስጥ አቀፈው በመሰዊያውም ላይ ሳለ ወደ ዝምታና ተደሞ አደረሰው ሰዎችም ሁሉ ስጋዊ እንቅልፍ የሚያንቀላፋ ይመስላቸው ነበር። በኤጲስቆጶስነት ሹመት ሰላሳ ሶስት ዘመናት በተፈፀመለት ጊዜ ወንድሙ ቅዱስ ባስልዮስ ሊጠይቀው መጣ እርሱ ከተጋድሎ ብዛት የተነሳ በፅኑ ደዌ የሚታመም ሆኖ ነበርና በቅዱስ ባስልዮስ መምጣት ደስ አለው።

🔴#ስንክሳር ጥር_21 አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ጥር ሀያ አንድ በዚች ቀን ለእመቤታችን ለከበረች #ድንግል_ማርያም የእረፍቷ መታሰቢያ ነው፣ የከበረች #ቅድስት_ኢላርያ አረፈች፣ የባስልዮስ ወንድም የከበረ #ቅዱስ_ጎርጎርዮስ የእረፍቱ መታሰቢያ ነው፣ የካህኑ ኬልቅዩ ልጅ ታላቁ #ነቢይ_ኤርምያስ መታሰቢያው ነው። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #በዓለ_አስተርዕዮ_ማርያም ጥር ሀያ አንድ በዚች ቀን አምላክን ለወለድች ለእመቤታችን ለከበረች ድንግል ማርያም የእረፍቷ በአል መታሰቢያ ነው።ያን ጊዜ እመቤታችን በልጅዋ በጌታችን በፈጣሪያችንና በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በከበረ መቃበሩ ቦታ ትፀልይ ነበረ ከዚህም አለም እንደምትለይ መንፈስ ቅዱስ ነገራት ከዚህም በኃላ ከደብረ ዘይት ደናግል መጡ ጌታችን ነግሮዋቸዋልና እርሷም ነገረቻቸው። በዚያንም ጊዜ እመቤታችን እንዲህ ብላ ፀለየች፦ "ልጄ ወዳጄ ጌታዬና ፈጣሩዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ልመናዬን ተቀብለህ ደቀ መዝሙርህን ዮሀንስን በዚች ሰአት አምጣው።እንዲሁም ህያዋን እንደሆኑ ሀዋርያትን ሁሉንም ነፍሳቸውንም የለየሀቸውን አምጣቸው አንተ የህያዋንና የሙታን አምላክ ነህና ላንተም ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን። በዚያንም ጊዜ በመንፈስ ቅዱስ ትእዛዝ ከኤፌሶን አገር ዮሀንስን ደመና ተሸክማ ወደ እመቤታችን ማርያም አደረሰችው ሰገደላትና በፊቷ ቁሞ እንዲህ አላት ሰላምታ ይገባሻል ጌታችንን ፈጣሪያችንንና መድኃኒታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን የወለድሺው ፀጋን የተመላሽ ደስ ይበልሽ አንቺ ከዚህ አለም ተለይተሽ በክብር በምስጋና ወደ ዘላለም ህይወት ትሄጂአለሽና። ይህም ስሙ ክብር ምስጉን የሆነ ጌታችንና ፈጣሪያችን ድንቆች ተአምራቶችን በአንቺ ላይ ከገለጠ በኃላ ነው። እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ይህን በሰማች ጊዜ እጅግ ደስ አላትእግዚአብሄርንም እንዲህ ብላ አመሰገነችው ፈጣሪዬ ጌታዬ ላንተ ምስጋና ይሁን አንተ የለመንኩህን ሰጥተኸኛልና አሁንም ነፍሴን ተቀብለው ወደ ሰማይ ወደ አንተ ሊአሳርጓት ከሚመጡ መላእከቶችህ ጋር በመምጣትህ የምለምንህን ሁሉ ስጠኝ። በዚያንም ጊዜ ከሰማይ እንዲህ የሚል ቃል መጣ እነሆ አሁን መላእክት ይደርሳሉ ሀዋርያትም ሁሉ ከምድር ዳርቻ በደመና ተጭነው ለሰማይና ለምድር ጌታ ለኢየሱስ ክርስቶስ እናቱ ወደ ሆነች ወደ ቅድስት ድንግል ይደርሳሉ። ወዲያውኑ ሁሉም ሀዋርያት የሞቱትም ከመቃብራቸው ተነስተው ወደ እመቤታችን ደርሰው ሰገዱላት አምላከችን ከአንቺ የተወለደ ፀጋን የተመላሽ ሆን ደስ ይበልሽ እርሱ ከዚህ አለም ለይቶ ቃል ኪዳን እንደሰጠሽ በክብር በምስጋና ከርሱ ጋር ያሳርግሻልና አሏት። በዚያንም ጊዜ እመቤታችን በአልጋዋ ላይ ተቀመጠች ሀዋርያትንም እንዲህ አለቻቸው ፈጣሪዬ ፈጣሪያቸው ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሚመጣ እናንተንም እንዳየኃችሁ እንደማየው አሁን አውቅሁ ከዚህ ከስጋዬም ወጥቼ ወደዘላለም ህይወት እሄዳለሁ ነገር ግን ትነግሩኝ ዘንድ እሻለሁ ከዚህም አለም እንደምለይ ከወዴት አወቃችሁ ። ጴጥሮስና ሐዋርያት ሁሉም ወዳንቺ እንመጣ ዘንድ መንፈስ ቅዱስ አዘዘን በደመና ላይም በተጫን ጊዜ ወዳንቺ እንደ አይን ጥቅሻ ፈጥነን ደረስን አሏት። እመቤታችንም ማርያምም ይህን ነገር ከሀዋርያት በሰማች ጊዜ ድምጿን ከፍ አድርጋ እንዲህ አለች ጌታዬና ፈጣሪዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ክቡር ምስጉን የሆነ ስምህን ፈፅሜ አመሰግናለሁ።የእኔን የአገልጋይህን መከራ ተመልክተህ ድንቅ ኃይልህን አድርገህልኛልና ከእንግዲህ ወዲያ ትውልድ ሁሉ ያከብሩኛል ያመሰግኑኛል። ፀሎቷንና ምስጋናዋን ስትጨርስ ሀዋርያትን እንዲህ አለቻቸው እጣን አምጥታችሁ በማጠን የጌታዬን ኢየሱስ ክርስቶስን ስሙን ጥሩት እነርሱም እንዳዘዘቻቸው አደረጉ ።በዚያንም ጊዜ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እልፍ አእላፍት መላእክት አጅበው እያመሰገኑት መጣና አረጋጋት ያዘጋጀላትንም ተድላ ደስታ ነገራት በዚያንም ብዙዎች ድንቆች ተአምራቶች ተደረገ እውሮች አይተዋልና፣አንካሶች ቀንተው ሄደዋልና ደንቆሮዎች ሰምተዋልና ለምፃሞች ነፁ አጋንንትም ከሰዎች ወጥተው ሄዱ ዲዳዎች ተናገሩ በሽታና ደዌ ያለበት ሁሉ ዳነ እመቤታችን ድንግል ማርያም ወዳለቸወበት ቤት በቀረብ ጊዜ ከደዌያቸው ይፈወሳሉና። ከዚህም በኃላ እመቤታችን ተወዳጅ ልጅዋን እንዲህ አለችው በአየር ውስጥ ተበትነው ከሚኖሩ ከሚያስደነግጡ ግሩማን መላእክት የተነሳ ከእሳት ባህርም እፈራለሁ ጌታችንም ከእናንተ ለማንም በአለሁ ላይ ስልጣን የለውም አላት። ከስጋዋም የምትለይበት ጊዜ ሲደርስ ሀወሰርያትና ደናግል ትባርካቸው ዘንድ እያለቀሱ ለመኑዋት እጃዋን በላያቸው ዘርግታ ባረከቻቸው በዚያንም ጊዜ ጌታችን ንፅህት ነፍሷን ከስጋዋ ለይቶ በመለኮታዊ እጆቹ ይዞ በብርሀን ልብስ አጎናፅፎ ወደ ከፍተኛ መኖሪያ ከእርሱ ጋር አሳረጋት ስጋዋን ግን እንደሚገባ ገንዘው ወደ ጌቴሴማኒ ተሸክመው እንዲወስዷት ሀዋርያትን አዘዛቸው። ነፍሷ ከስጋዋ ከመውጣቷ በፊት በሰው አንደበት ይህ ነው ተብሎ የማይነገር ብርሀንን እያየች ነበር የክብር ባለቤት ጌታችን ክርስቶስም እንግዲህ ስጋሽን ተድላ ወዳለበት ገነት አፈልሳለሁ ዳግመኛም ስጋሽን ከነፍስሽ ጋር አዋህጄ አስነስቼ መላእክት በውስጡ በፊትሽ ሆነው በሚያመሰግኑበት ተመሳሳይ በሌለው ተድላ ደስታ በአለበት ማደሪያ አኖርሻለሁ አላት። እመቤታችንም እንዲህ አለች አቤቱ በረቀቀ ጥበብህ ይህን ሁሉ የሰራህ አመሰግንሀለሁ ሁለተኛም ልመናዬን ትሰማ ዘንድ እለምንሀለሁ በስሜ ወደ አንተ የሚለምነውን ሁሉ ልመናውን ተቀበለው በመከራም ውስጥ ሆኖ ስሜን ጠርቶ ወዳንተ የሚለምነውን ከመከራው ሁሉ አድነው በሰማይም በምድርም በስራው ላይ ሁሉ አንተ ከሀሊ ነህና መታሰቢያዬን በውስጧ የሚያደርጉትን ቦታ ሁሉ ባርክ በእኔ ስም የሚያቀርቡትን የሁሉንም መስዋእታቸውን ተቀበል። ጌታችንም እንዲህ ብሎ መለሰላት የለመንሽኝን ሁሉ አደርግልሻለሁ ደስ ይበልሽ ከእኔ ከአባቴ ከመንፈስ ቅዱስ ዘንድ ፀጋ ክብር ባለሟልነት ተሰጥቶሻልና ስምሽንም ጠርቶ የሚለምን ሁሉ በዚህም አለም በሚመጣውም አለም አይጠፋም። እመቤታችንም ከአረፈች በኃላ ጌታችን እንዳዘዘ ወደ ጌቴሴማኒ ሊወስዷት ሀዋርያት ገንዘው ተሸከሟት። አይሁድም በሰሙ ጊዜ ስጋዋን ሊአቃጥሉ ወጡ ከእነርሱም አንዱ ከምድር ላይ ይጥላት ዘንድ የእመቤታችንን አልጋዋን ያዘ ያን ጊዜ ከእግዚአብሄር የታዘዘ መልአክ እጆቹን በእሳት ሰይፍ ቀጣውና እጆቹ በአልጋዋ ላይ ተንጠለጠሉ። ያን ጊዜ በጌታችን አምኖ ወደ እመቤታችን እያለቀሰ እንዲህ ብሎ ለመነ የእውነተኛ አምላክ የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ እናት አንቺ በእውነት ድንግል የሆንሽ በእኔ ላይ ይቅርታ ታደርጊ ዘንድ እለምንሻለሁ በሀዋርያትም ልመና እጆቹ ተመልሰው እንደቀድሞው ደኅነኞች ሆኑ። በቀበሩዋትም ጊዜ ከዚያ ሶስት ቀን ኖሩ እረፍቷም የሆነው እሁድ ቀን በጥር ወር በሀያ አንድ በዚች ቀን ነበረ ጌታችንም ብርሀናውያን መላእክትን ላከ እነርሱም ስጋዋን ከመቃብር ወስደው በገነት ውስጥ በእፀ ህይወት ስር አኖሩዋት። ሀዋርያ ቶማስ ግን ያን ጊዜ አልነበረም በደመና ላይ ተጭኖ እርሱ ሲመጣ መላእክት ሲአሳርጓት እመቤታችንን አገኛት መላእክትም ለአምላክ እናት ለእመቤታችን ድንግል ማርያም ና እጅ ንሳ አሉት እርሱም ሰገደላትና ተሳለማት ከእርሷም ተባረከ ከዚህም በኃላ ወደ ሀዋርያት ደረሰ ። እነርሱም እመቤታችንን ማርያምን እንደ አረፈችና እንደ ቀበርዋትም ነገሩት ቶማስም ስጋዋን እስከማይ አላምንም አላቸው።

አባቱም በመጣ ገዜ ያንን የወርቅ ወንጌል አሳየችው እርሱም ለልጁ ያሠራለት ወንጌል እንደሆነ አወቀ።አባቱና እናቱም ወደ እርሱ ሔደው ስለ ልጃቸው ጠየቁት እርሱም ከዚህ ጨርቅና ከዚህ ትንሽ ማደሪያዬ ውስጥ በቀር በሌላ እንዳትቀብሩኝ ማሉልኝ አላቸው። በአማላቸውም ጊዜ እርሱ ልጃቸው እንደሆነ ነገራቸው ያን ጊዜም ጮኹ መሪር ልቅሶንም አለቀሱ የሮሜ ከተማ ሽማግሌዎችና ሕዝቡ ሁሉ ተሰበሰቡ ሰባቱ ቀንም ሲፈጸም ቅዱስ ዮሐንስ አረፈ። እናቱም መሐላዋን ረስታ አስቀድማ ለሠርጉ ያዘጋጀቻቸውን ያማሩ ልብሶች አውጥታ ገነዘችው።በዚያችም ጊዜ ታመመች አባቱ ግን መሐላውን አስታውሶ እነዚያን ያማሩ ልብሶች አስወገደ በጨርቆቹም ገነዙት በዚያ በትንሹ ማድሪያም ውስጥ ቀበሩት ከሥጋውም በሽተኞች የሚፈወሱበት ታላቅ ድኅነት ተገኘ። ከዚህም በኃላ በስሙ ያማረች ቤተ ክርስቲያን ሠርተው ሥጋውን በውስጧ አኖሩ። ከእርሱም ታላላቅ ድንቆችና ተአምራቶች ተገለጡ። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ሰማዕቱ_ቅዱስ_መርምህናም ዳግመኛም በዚህች ዕለት የታላቁ ሰማዕት የቅዱስ መርምሕናም ቤተ ክርስቲያኑ የከበረችበትና ተአምራቱ የተገለጠበት ዕለት ነው፡፡  ቅድስት ሣራና ወንድሟ መርምህናም አባታቸው የአቶር ንጉሥ ሲሆን እርሱም የተቀረጹ ጣዖታን ያመልክ ነበር፡፡ እናታቸው ግን አማኝ ክርስቲያን ነበረች፡፡ ቅዱስ መርምህናም አባቱን ለምኖና አስፈቅዶ ወደ ዱር ሄዶ አራዊትን ለማደን በወጣ ጊዜ እናቱ የሰማይና የምድር አምላክ እግዚአብሔር በላዩ በረከትን ያሳድርበት ዘንድ ከጸለየችለት በኋላ ሸኘችው፡፡ መርምህናም ከ40 ፈረሰኛ አገልጋዮቹ ጋር ወጥቶ ሄደ፡፡ ወደ አንድ ተራራም ወጥቶ በዚያ አደረ፡፡ በሌሊትም የታዘዘ መልአክ ጠራውና ‹‹መርምህናም ሆይ ተነሥተህ ወደዚህ ተራራ ጫፍ ላይ ውጣ፣ ስሙ ማቴዎስ የሚባል ቅዱስ ሰው ታገኛለህ፡፡ እርሱም የሕይወትን ነገር ይነግርሃል›› አለው፡፡ ቅዱስ መርምህናም ሲነጋ ወደ ተራራው ጫፍ ላይ ወጣና የበግ ጠጉር ለብሶ አባ ማቴዎስን ባገኘው ጊዜ እጅግ ፈራ፡፡ አባ ማቴዎስም ‹‹አይዞህ አትራ እኔም የእግዚአብሔር ፍጥረት ነኝና አትፍራ›› ብለው አበረቱት፡፡ መርምህናም የእግዚአብሔርን ስም ሲጠሩ ሲሰማ ‹‹አባቴ ከአማልክቶች በቀር አምላክ አለን?›› ብሎ ጠየቃቸው፡፡ በዚህም ጊዜ አባታችን የሃይማኖትን ነገር ሁሉንም አስተማሩት፡፡ መርምህናምም ‹‹ከራስ ጠጉሯ እስከ እግር ጥፍሯ ድረስ በለምጽ የተመታች እኅት አለችኝና እርሷን የአምላክህን ስም ጠርተህ ካዳንክልኝ በእውነት በአምላክህ አምናለሁ›› አላቸው፡፡ ሁለቱም ተያይዘው ከተራራው ወርደው ወደ ንጉሡ ቤት ሄደው መርምህናም ለእናቱ ያጋጠመውን ነገር ነገራትና በለምጽ የተመታችውን እኅቱን ሣራን በሥውር ወደ አባ ማቴዎስ ዘንድ ወሰዳት፡፡ አባታችንም መሬቱን ባርከው ውኃ አፍልቀው አጠመቋትና ከለምጹዋ ፈወሷት፡፡ አርባው ጭፍራዎችም አምነው ተጠመቁ፡፡ አባታችንም ሰማዕትነትን እንደሚቀበሉ ትንቢት ነግረዋቸው ባርከው መርቀው አሰናበቷቸው፡፡ መርምህናምም ወደ አባቱ ቤት በተለመሰ ጊዜ ጣዖቱ ቤት መግባትን እምቢ አለ፡፡ ከዚህም በኋላ አርባውን ጭፍራዎችና እኅቱን ሣራን ይዞ ወደ አንዲት ተራራ ላይ ወጥቶ ተቀመጠ፡፡ የአቶሩን ንጉሥ የሆነው አባቱ ‹‹ና መንግሥቴን ውረስ›› ብሎ ለቅዱስ መርምህናም ላከበት፡፡ ነገር ግን ቅዱስ መርምህናም ‹‹የጌታዬን ፈጽሞ የማይጠፋውን መንግሥት እሻለሁ›› ብሎ ለንጉሥ አባቱ ላከበት፡፡ ንጉሡም በቅድሚያ 40ውን አገልጋዮቹን ጭፍራዎች እንዲገድሏቸው አዘዘና ራስ ራሶቻቸውን እየቆረጡ ከጉድጓድ ውስጥ ጨመሯቸው፡፡ መርምህናምም ሲጸልይ ከሰማይ ‹‹መርምህናም ሆይ! ጸሎትህን ሰምቻለሁ…›› የሚል ድምፅ መጣለት፡፡ ወዲያውም በንጉሡ ወላጅ አባታቸው ትእዛዝ ቅዱስ መርምህናምና እኅቱ ቅድስት ሣራ አንገታቸውን ተሰየፉና የሰማዕትነት አክሊልን ተቀዳጁ፡፡ ሥጋቸውንም በጉድጓድ ጨምረው ሊያቃጥሏቸው ሲሉ ሥጋቸውን እግዚአብሔር ሰወረባቸው፡፡ ወዲያውም ታላቅ ንውጽውጽታ ሆነ፣ ፀሐይም ጨለመች፡፡ የሰየፏቸውም ፈርተው ሸሹ፡፡ ከዚህም በኋላ ሰይጣን በአባታቸው በአቶሩ ንጉሥ ላይ አድሮበት አሳበደው፡፡ እንደ እሪያም መጮህ ጀመረ፡፡ ክርስቲያን የሆነችው የቅዱስ መርምህናምና የቅደስት ሣራ እናታቸው ወደ አባ ማቴዎስ ሄዳ ንጉሡ በልጆቹ ላይ ያደረገውንና በእርሱም ላይ የተፈጸመበትን ነገር ነገረቻቸው፡፡ አባ ማቴዎስም ንጉሡን ዘይት ቀብተው ጸልየው ፈወሱት፡፡ በውስጡ አድሮበት የነበረውንም ሰይጣን በእሪያ መልክ ከንጉሡ ውስጥ አስወጡት፡፡ ንጉሡም ወደ ልቡ ሲመለስ በአባ ማቴዎስ ትምህርት በጌታችን አመነ፡፡ በሚገዛቸው አገሮች ሁሉ ያሉትን ሰዎች ይዞ ከነቤተሰቡ ተጠመቀ፡፡ ንጉሡም በእመቤታችን ስም ቤተ ክርስቲያን አሠራ፡፡ ንግሥቲቱ ሚስቱም የሰማዕታቱን ልጆቿን ሥጋ በሳጥን አድርጋ በውስጧ አኖረች፡፡ ከሥጋቸውም ብዙ ተአምራት ተገለጡ፡፡ አባታቸው የአቶሩ ንጉሥም ለችግረኞችና ለጦም አዳሪዎች እየመጸወተ በተጋድሎ ኖረ፡፡ የቅዱስ መርምህናምና የእኅቱ የቅድስት ሣራ እረፍታቸው ታኅሣሥ 14 ቀን ነው፡፡ ዳግመኛም በዚህች ዕለት የቅዱስ መርምህናም አባት ንጉሡ አቶርና የመርምህናም ማኅበርተኞች የሆኑ ቁጥራቸው 170 ሺህ የሆኑ ሰማዕታት የዕረፍታቸው መታሰቢያ ነው፡፡ ይህም የአቶሩ ንጉሥ ሰማክሬም ከሞተ በኋላ መንግሥቱን መጠበቅና ማዘዝ የማይችል ታናሽ ብላቴና ልጅ በአባቱ ፋንታ ነገሠ፡፡ እናቱም ስለ እርሱ ሹሞቹን ታዛቸው ነበር፡፡ ከለዳዊ ንጉሥም ይህን ሲሰማ የአቶርን መንግሥት ለመውሰድ መጣ፡፡ የንጉሡም ወታደሮችና የቅዱስ መርምህናምን መቃብር ይጠብቁ የነበሩ ሁሉ ለመዋጋት መጡ፡፡ የከለዳውያንም ንጉሥ አሸንፎ ከተማይቱን ወረራትና ብላቴናውን ንጉሥ ከእናቱ ጋር ገደላቸው፡፡ የአቶርም ሰዎች ተገዙለትና በላያቸው ነግሦ መንግሥትን ያዘ፡፡ ከጥቂት ቀኖችም በኋላ የአቶርን ሰዎች ሰብስቦ ስለ ሃይማኖታቸው ጠየቃቸው፡፡ ሕዝቡም በቅዱስ መርምህናም አምላክ አምነው በአባ ማቴዎስ ጥምቀት ክርስቲያን መሆናቸውን በነገሩት ጊዜ ለጣዖት እንዲሰግዱ አዘዛቸው፡፡ እሺ ብለው ለጣዖት የሰገዱ አሉ፡፡ የቅዱስ መርምህናምና የአባቱ አግልጋዮች ግን ንጉሡን ‹‹በሰውነታችን ላይ የፈለከውን አድርግ እንጂ ሃይማኖታችንን አንክድም›› አሉት፡፡ ነገሡም ቁጥራቸው 170 ሺህ የሆኑ ክርስቲያኖችን በሰይፍ ፈጃቸውና የሰማዕትነት አክሊልን ተቀዳጁ፡፡ እነርሱም የቅዱስ መርምህናም ማኅበርተኞች ተባሉ፡፡ ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።https://t.me/finotebirhan12

የከበረ አክሎግም ይህን አልሻም ነገር ግን እንድታሠቃየኝና እንድትገድለኝ ሥጋዬንም ወደ ሀገሬ እንድትልክ ማልልኝ አለው እርሱም ማለለት። በዚያንም ጊዜ የከበረ አክሎግ ወደ እግዚአብሔር እንዲህ ብሎ ለመነ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ልመናዬን ትሰማኝ ዘንድ ዛሬ ይህን የሞተውን ሕፃን ታስነሣው ዘንድ የከበረ ስምህም ይመሰገን ዘንድ እለምንሃለሁ ምስጋና ክብር ያንተ ነውና ለዘላለሙ አሜን። ይህንንም ሲል በመስቀል ምልክት በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም በሕፃኑ ላይ አማተበ ወዲያውኑ ሕፃኑ ተነሣ አሕዛብም ይህን ድንቅ ተአምር አይተው ሁሉም በአንድ ቃል በቅዱስ አክሎግ አምላክ እናምናለን ብለው ጮኹ። መኰንኑም ተቆጣ ከከተማም እንዲአወጧቸውና ሰፊ ጒድጓድ ቆፍረው እሳትንም አንድደው በውስጡ እንዲጨምሩዋቸው አዘዘ እንዲሁም አደረጉባቸውና ምስክርነታቸውን ፈጸሙ ቊጥራቸውም ስምንት መቶ ዘጠኝ ሆነ በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ከዚህም በኋላ አባ አክሎግን ጽኑዕ ሥቃይን አሠቃይተው ወደ ሀገሩ ወስደው በዚያ በሰይፍ ራሱን ይቆርጡ ዘንድ አርያኖስ አዘዘ አባ አክሎግም ይህን በሰማ ጊዜ እጅግ ደስ አለው እንዲህ እያለ ቁሞ ጸለየ "ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ እኔ ባሪያህ እለምንሃለሁ ቸርነትህን በሀገሬ ላይ በውስጧም በሚኖሩ ሰዎች ሁሉ ላይ ታደርግ ዘንድ የእጃቸውንም ሥራ ባርክ ሴቶቻቸውን፣ ልጆቻቸውን፣ እንስሶቻቸውን፣ እርሻዎቻቸውንም ባርክ ከመከራም ሁሉ አድናቸው ለሥጋዬም ጸጋህን ስጠው የታመመ ሁሉ ሥጋዬ ወዳለበት መጥቶ የከበረ ስምህን ጠርቶ ወዳንተ በሚጸልይ ጊዜ ከደዌው ይዳን። የተጋድሎዬን መጽሐፍ የሚጽፈውን ሁሉ መታሰቢያዬንም ለሚያደርግ ለቊርባንም ሥንዴን የሚሰጥ ወይም ዕጣንን ወይም ዘይትን ወይም ወይንን ለሚሰጥ ለሁሉም በመንግሥተ ሰማያት ዋጋቸውን ስጣቸው ስሞቻቸውንም በሕይወት መጽሐፍ ጻፍላቸው ሥጋዬንም በንጹሕ ልብስ የሚገንዘውን ነፍሱን የብርሃን ልብስን ሸፍናት ለአንተም ምስጋና ክብር ይሁን ለዘላለሙ አሜን። አባ አክሎግም ይህን በአለ ጊዜ እነሆ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገለጸለትና እንዲህ አለው። ወዳጄ የምወድህ የአባቴና የመንፈስ ቅዱስ ወዳጅ ሰላም ላንተ ይሁን ዋጋህን ልሰጥህ በመንግሥቴም ውስጥ ላሳርፍህ መጣሁ ሦስት አክሊላትንም አዘጋጀሁልህ አንዱ ስለ ድንግልናህ ሁለተኛው ስለ ሥቃይህ ሦስተኛው የዚህን ዓለም ክብር ንቀህ ስለተውህ ነው። በዚች ቀን ከእኔ የምትሻውን ሁሉ አደርግልሃለሁ ስለ ስሜ ስለአሠቃዩህ የማያልቅ ተድላን እሰጥሃለሁ የመላእክት ሠራዊትም እንዲአገለግሉህ አደርጋለሁ ዘላለማዊ ሕይወት ባለው በማዕዴ ውስጥም ከሁሉ ቅዱሳን ጋር ደስ ይልሃል። የመረጥኩህ አክሎግ ሆይ አንተን እነግርሃለሁ ሥጋህ ባለበት የሚማልደውን ሁሉ ርዳታ የሚሻውንም በችግር ውስጥም ወይም በደዌ ውስጥ በኀዘንም ላይ ሁሉንም እኔ አድናቸዋለሁ ልጁንም በስምህ የሚሰይመውን ሁሉ እኔ እባርከዋለሁ በበጎ አስተዳደግም አሳድገዋለሁ ከክፉ ነገር ሁሉ እጠብቀዋለሁ በስምህም መባ የሚአገባና ለችግረኞችም እስከ ቀዝቃዛ ውኃ ምጽዋት የሚሰጠውን እኔ ለሁሉም ኃጢአቱን ይቅር ብዬ የዘላለም ሕይወትን አወርሰዋለሁ ተክል ተክሎ ዘር ዘርቶ በስምህ የሚለምነኝም እባርክለታለሁ ፍሬውንም አበዛለታለሁ። ከአባ አክሎግ ጋር መነጋገርን ጌታችን ሲፈጽም ባረከው ሥጋውንም ጤነኛ አደረገውና ሳመው አባ አክሎግም እየተመለከተ በታላቅ ክብር ወደ ሰማይ ወጣ። ከዚህም በኋላ የከበረ አባ አክሎግ ወደ ወታደሮች መለስ ብሎ የታዘዛችሁትን ፈጽሙ አላቸው ወታደሮችም ፊቱ እንደ ፀሐይ እጅግ ሲያበራ በአዩት ጊዜ ከፊቱ ብርሃን ግርማ ገናናነት የተነሣ ወደርሱ መቅረብ ፈሩ ከእርሳቸውም ርኅራኄ የጎደለው ልቡ የደነደነ አንድ ሰው እጁን ዘርግቶ አንገቱን በሰይፍ መታውና በዚች ቀን ተጋድሎውን ፈጸመ መላእክትም ነፍሱን ተቀበሏት በፊቷም እየዘመሩ ወደሰማይ አሳረጓት። ወታደሮችም የአባ አክሎግን ሥጋ ከባሕሩ ዳር ትተው በመርከብ ተሳፍረው ወደ ሀገራቸው ተመለሱ ከዚያም ጐልማሶች ነበሩ ስለ ከበረ አባ አክሎግ በሰማዕትነት መሞት ወደ ሀገር ውስጥ ገብተው ለሕዝቡ ነገሩዋቸው።ሕዝቡም በሰሙ ጊዜ ተሰብስበው ከካህናቱ ጋር ሔዱ አንሥተውም በክብር ገነዙት ተሸክመውም ወደ ሀገር ውስጥ አድርሰው በአማረ ቦታ አኖሩት ከእርሱም ታላላቅ የሆኑ ድንቆች ተአምራቶች ተገለጡ። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #አቡነ_ዮሐንስ_ወንጌሉ_ዘወርቅ በዚህች እለት የከበረ አባ ዮሐንስ ወንጌሉ ዘወርቅ ሥጋው ወደ ሮሜ አገር የፈለሰበት እና ቤተ ክርስቲያኑ የከበረችበት ነው፡፡ ይህም ቅዱስ ከሮሜ አገር ነበር አባቱም አጥራብዮስ የሚባል ባለጠጋ ነው።የእናቱም ስም ብዱራ ይባላል። እንዲማርም ለመምህር ሰጡት ቅዱሳት መጻሕፍትንም ተማረ። ከዚህም በኃላ ገበታው የወርቅ የሆነ ወንጌልን ያሠራለት ዘንድ አባቱን ለመነው አባቱም እንደፈለገው አሠራለት ሁል ጊዜም ያነበው ነበር።በሚያነብ ጊዜም አባቱና እናቱ ደስ ይላቸው ነበር። በዚያም ወራት ወደ ኢየሩሳሌም የሚጓዝ መነኩሴ ወደ እነርሱ መጣ በእነርሱም ዘንድ አደረ ከቅዱስ ዮሐንስም ጋራ ተነጋግሮ የምንኩስናን ሥራ አመሰገነለት ይህን ዓለም እስከ ናቀና እንደ እርሱ መነኰስ ይሆን ዘንድ እስከ ወደደ ድረስ ልቡን ማረከው። ያን ጊዜም ያ መነኰስ ወደ ኢየሩሳሌም ተጓዘ ሁለተኛም ተመልሶ እንደ ልማዱ በእነርሱ ዘንድ አደረ።ቅዱስ ዮሐንስም መነኰሴው ወደ ገዳሙ ይወስደው ዘንድ ፈለገ መነኰሴውም አባትህን እፈራዋለሁ ልወስድህ አይቻለኝም አለው።ቅዱስ ዮሐንስም ከእርሱ ጋራ እንዲወስደውና ነፍሱን እንዲያድን አማለው። ከዚህም በኃላ በስውር ወሰደው በመርከብም ተጭነው ያ መነኮስ ወደሚኖርበት ገደም ደረሱ የገዳሙም አበ ምኔት የወጣቱን ዮሐንስን መልኩን አይቶ አደነቀ።ቅዱስ ዮሐንስም የምንኩስናን ልብስ ያለበሰው ዘንድ አበ ምኔቱን ለመነው አበ ምኔቱም ልጄ ሆይ የምንኵስና ሕግ እጅግ ጭንቅ ናት እኮ አለው።አብዝቶም በለመነውና ግድ ባለው ጊዜ ራሱን ላጭቶ አመነኰሰው። ከዚህም በኃላ ከጾም ከትጋትና ከኀዘን የተነሣ ሥጋው ደርቆ አጥንቶቹ እስከ ሚታዩ ድረስ በብዙ ተጋድሎ ተጸመደ።አበ ምኔቱም ልጄ ሆይ ለሰውነትህ እዘን ድካምህንም ቀንስ መነኰሳቱም ሁሉ እንደሚሠሩት ሥራ እያለ ያጽናናውና ይመክረው ነበር። በዚህ ተጋድለም ሰባት ዓመት በሆነው ጊዜ ከእነርሱ በረከትን ትቀበል ዘንድ ከመሞትህ በፊት ወደ አባትህና እናትህ ሒድ የሚል ራእይ አየ።ይህንንም ራእይ በሦስት ሌሊቶች ውስጥ አየ ለአበምኔቱም እንዴት እንዳየ ነገረው አበምኔቱም ይህ ራእይ ከእግዚአብሔር ዘንድ ስለ ሆነ ልትሔድ ይገባሃል አለው።ከገዳሙም በወጣ ጊዜ አንድ ምስኪን ሰው ጨርቅ ለብሶ አገኘ።የእርሱንም ልብስ ሰጥቶት ጨርቁን ወሰደ። ወደ አባቱ ቤትም በደረሰ ጊዜ በትንሽ ጎጆ ውስጥ በአባቱ ደጅ በጾም በጸሎትና በስግደት እየተጋደለ ባሮች ከአባቱ ማዕድ የሚጥሉለትን ፍርፋሪ እየተመገበ ሰባት ዓመት ኖረ።እናቱም በአንጻሩ ስታልፍ የሚከረፋ ሽታው ያስጨንቃት ነበር።ዕረፍቱም በቀረበ ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ ከሰባት ቀን በኃላ ከዚህ ዓለም ትወጣለህ ብሎ ነገረው። ያን ጊዜም ወደ እናቱ ልኮ ልምናውን ልትሰማ ወደ እርሱ መጣች ልጅዋም እንደሆነ ፈጥኖ አልነገራትም ነገር ግን በዚያች በታናሽ ማደሪያ ውስጥ በላዩ ባለ ጨርቅ እንድትቀብረው የለበሰውንም ጨርቅ እንዳትለውጥ አማላት።ከዚህም በኃላ ያንን የወርቅ ወንጌል ሰጣት።እንዲህም አላት ይህን መጽሐፍ አንብቡ እኔንም አስቡኝ።

🔴#ስንክሳር ጥር20 አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ጥር ሃያ በዚህች ዕለት ከሰባ ሁለቱ አርድእት አንዱ የከበረ #ሐዋርያ_አብሮኮሮስ አረፈ፣ የከበረ #ቀሲስ_አክሎግ በሰማዕትነት ሞተ፣ #አባ_ዮሐንስ_ወንጌሉ_ዘወርቅ ሥጋው ወደ ሮሜ አገር የፈለሰበት እና ቤተ ክርስቲያኑ የከበረችበት ነው፣ የታላቁ ሰማዕት #የቅዱስ_መርምሕናም ቤተ ክርስቲያኑ የከበረችበትና ተአምራቱ የተገለጠበት ዕለት ነው፡፡  ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #ሐዋርያ_ቅዱስ_አብሮኮሮስ ጥር ሃያ በዚህች ዕለት ወንጌልን ይሰብኩ ዘንድ በሽተኞችንም ይፈውሱ ዘንድ ጌታችን መርጦ ከላካቸው ከሰብዓ ሁለቱ አርድእት አንዱ የከበረ ሐዋርያ አብሮኮሮስ አረፈ። ይህም ቅዱስ በጽርሐ ጽዮን ከሐዋርያት ጋር ሁኖ ሳለ የአጽናኝ መንፈስ ቅዱስን ጸጋ ተሞላ። እርሱንም ሐዋርያት መርጠውት ከሰባቱ ዲያቆናት ጋር የተቆጠረ ሆነ እነርሱ መንፈስ ቅዱስ ያደረባቸው ዕውቀትም ያላቸው እንደሆኑ የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ ስለርሳቸው ምስክር ሆነ። ከዚህም በኋላ ለወንጌላዊ ቅዱስ ዮሐንስ ደቀ መዝሙሩ ሆነ ከእርሱም ጋር ወደ ብዙ አገሮች ሔደ በቢታንያ አገር በኒቆምድያ ከተማ ላይ በአንብሮተ እድ ኤጲስቆጶስነት ሾመው። እርሱም የክብር ባለቤት የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ሃይማኖት አስተማረ ከዮናናውያንም ብዙዎችን መልሶ ወደ ቀናች ሃይማኖት አስገባቸው በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠመቃቸው የወንጌልንም ትእዛዞች እንዲጠብቁ አስተማራቸው ቤተ ክርስቲያንንም ሠርቶ ቀሳውስትን ዲያቆናትን ሾመላቸው። ከዚህም በኋላ ያቺን አገር ወደሚከቧት አገሮች ወጣ በውስጣቸውም የከበረ ወንጌልን ሰበከ ብዙዎችንም ከስሕተት መለሳቸው አይሁድንም የክርስትና ጥምቀትን አጠመቃቸው ነገር ግን ብዙ መከራና ስደት ደርሶበታል ስለ ክርስቶስ ስም ተጋድሎውንም ሲፈጽም ጌታችንንም አገልግሎ በመልካም ሽምግልና አረፈ። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #አክሎግ_ሰማዕት በዚህችም ቀን በግብጽ አገር እልፈንት ከሚባል ከተማ የከበረ ቀሲስ አክሎግ በሰማዕትነት ሞተ። የዚህም ቅዱስ የአባቱ ስም ዲዮስቆርስ የናቱ ስም አፎምያ ነው እነርሱም ከከበሩ ወገኖች ውስጥ ናቸው በወርቅ በብር በላሞችና በበጎች በፈረሶችና በግመሎች እጅግ የበለጸጉ ናቸው ነገር ግን ልጅ የላቸውም ስለዚህም ያዝኑ ነበር። ልጅንም ይሰጣቸው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ሲለምኑ ኖሩ ልመናቸውንም ተቀብሎ ይህን የተባረከ ልጅ ሰጣቸው ስሙንም አክሎግ ብለው ጠሩት ይህ በእግዚአብሔር ዘንድ ጣዕም ያለው ይሆናል ማለት ነው። ስምንት ዓመትም በሆነው ጊዜ የእግዚአብሔርን ሕግ ይማር ዘንድ ለመምህር ሰጡት የቤተ ክርስቲያንንም ትምህርት ሁሉ ተማረ ሁል ጊዜም ወደ ቤተ ክርስቲያን በመሔድ ምስጋናዎችንና ጸሎቶችን ይሰማል ይህንንም የሚያደርግ ወደ መምህር ከመሔዱ አስቀድም ነው። በአንዲትም ዕለት ከመምህሩ ዘንድ ወጣ ወደ ቤቱም ሊሔድ በፈረስ ተቀምጦ ሁለት አገልጋዮችም ተከትለውት ሲጓዙ ብዙ ወንዶችና ሴቶች ተሰብስበው ሲጮሁ አያቸው የሆነውንም ሊያይ ወደ ርሳቸው ቀረበ። እባብ የነከሰውና ለሞትም የቀረበ አንድ ሕፃን በመካከላቸው ወድቆ አገኘ። የከበረ አክሎግም ይቺ ምልክት በስሜ የሚያምኑትን ትከተላቸዋለች በስሜም አጋንትን ያስወጣሉ አዳዲስ ቋንቋን ይናገራሉ የምድር አራዊቶችን በእጃቸው ይይዛሉ የሚጐዳቸውም ነገር የለም ያለውን የከበረ የወንጌልን ቃል አሰበ። በዚያንም ጊዜ የሕፃኑን እጅ ይዞ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ብሎ በላዩ በመስቀል ምልክት አማተበና ሕፃን ሆይ ከዚህ ክፉ እባብ መርዝ ትድን ዘንድ እናገርሃለሁ ጌታችን ንጹሕና እውነት በሆነ ቃሉ እባቡን ጊንጡን የጠላትን ኃይል ሁሉ ትረግጡ ዘንድ እነሆ ሥልጣን ሰጠኋችሁ ምንም የሚጎዳችሁ ነገር የለም ብሏልና አለ ወዲያውኑ ያ ልጅ ዳነ ከክፉ ነገርም ምንም ምን እንዳልደረሰበት ሆነ። ሕዝቡም ይህን ተአምር በአዩ ጊዜ እጅግ አደነቁ በቅዱሳኑ አድሮ ድንቅ ሥራ የሚሠራ እግዚአብሔርንም አመሰገኑት የዚችም ተአምር ወሬዋ በሀገሩ ሁሉ ተሰማ። ከመምህሩም ዘንድ ዐሥራ ሁለት ዓመት በሆነው ጊዜ አራቱን ወንጌሎች፣ የሐዋርያትን ሥራ፣ ዐስራ አራቱን የጳውሎስን መልእክቶች፣ ሰባቱን የሐዋርያት መልእክታት፣ የዮሐንስንም ራእይ፣ መቶ ሃምሳውን የዳዊት መዝሙራት፣ የነቢያትንና የሰሎሞንን መኅልይ ጠንቅቆ አጠና። ሁል ጊዜ በቀንና በሌሊት ያነባል በእሑድ ሌሊትም በቤተ ክርስቲያን ውስጥ እያገለገለ ያድራል ሁል ጊዜም አዘውትሮ ይጾማል ይጸልያል። ወላጆቹም ከአረፉ በኋላ ሰዎች መልካም ተጋድሎውን በአዩ ጊዜ ስለ እነርሱ ይጸልይ ዘንድ ቅስና እንዲሾምላቸው ኤጲስቆጶሱን ለመኑት እርሱ በዘመኑ ሁሉ በየሁለት ቀን በየሦስት ቀን በየሱባዔው ይጾማልና በልብሱም ውስጥ ማቅ ይለብሳልና። ቅስና ይሾም ዘንድ የእግዚአብሔር ጸጋ ጠራችውና ኤጲስቆጶሱም ወስዶ ሳይወድ በግድ ቅስና ሾመው በተሾመ ጊዜም ለአባ አክሎግ የክህነት ሹመት ይገባዋል ይገባዋል ይገባዋል እያለ ሲጮህ ሕዝቡ ቃልን ሰሙ ኤጲስቆጶሱና ሕዝቡም እጅግ አደነቁ እግዚአብሔርንም አመሰገኑት። ከእነዚያ ወራቶችም በኋላ በሀገሩ ሁሉ በክርስቲያን ወገኖች ላይ ከከሀዲዉ ዲዮቅልጥያኖስ ዘንድ ታልቅ መከራና ስደት ሆነ አብያተ ክርስቲያናትንም አፈረሰ ብዙዎችም በሰማዕትነት ሞቱ። ምስክርም ይሆን ዘንድ አባ አክሎግን እግዚአብሔር ጠራው እርሱም ቆመ ወደሰማይም ቀና በማለት እንዲህ ብሎ ጸለየ ዓለሙን ሁሉ የያዝክ ጌታዬ ፈጣሪዬ መድኃኒቴ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ በሀገርህ በሁለመናዋ ላሉ ሕዝብ ቸርነትህን ይቅርታህንና ሰላምህን አድርግ። ትባርካቸውም ዘንድ ከሰይጣናትም ስሕተት ታድናቸው ዘንድ ለእኔም ስለ ከበረው ስምህ ተጋድሎዬን እስከምፈጽም ያጸናኝ ዘንድ ቸር መልአክህን እንድትልክልኝ እለምንሃለሁ ኃይል ክብር ገንዘብህ የሆነ ለዘላለሙ አሜን። ከዚህም በኋላ በዙሪያው ወዳሉ ሰዎች ተመልሶ የሚሻ ይምጣ ከእኔ ጋር ይሒድ አለ የእርሱ ሰዎችና የሀገሩ ሰዎች ሦስት መቶ አርባ ተከተሉት በከፍታ ቦታ ላይም ቁመው እኛ በግልጥ ክርስቲያን ነን ብለው ጮኹ። የንጉሡም የሠራዊት አለቃ ሰምቶ አዘነ አባ አክሎግንም አሥሮ ለመኰንኑ ለአርያኖስ ሰጠው እርሱም ለአማልክት ስገድ አለው አባ አክሎግም ለክብር ባለቤት ለጌታዬና ለፈጣሪዬ ለኢየሱስ ክርስቶስ እሰግዳለሁ እንጂ እኔ ለረከሱ አማልክት አልሰግድም አለ። ቢዚያንም ጊዜ መኰንኑ አርያኖስ ተቆጣ አባ አክሎግንም ጽኑ ሥቃይን አሠቃይቶ ከእሳት ማንደጃ ውስጥ ጨመረው ከእግዚአብሔርም የታዘዘ መልአክ ወርዶ እሳቱን እንደ ጠል ቀዝቃዛ አደረገው አባ አክሎግም በእቶኑ መካከል ቁሞ ጸለየ። ከዚህም በኋላ መኰንኑ አርያኖስ ሦስት መቶ አርባውን ሰዎች እናንተ ኑ ለአማልክት ስገዱ አላቸው እነርሱም እንዲህ ብለው መለሱለት። እኛስ ከእግዚአብሔር በቀር ለረከሱ አማልክት አንሰግድም አሉት ራሶቻቸውንም በሰይፍ እንዲቆርጧቸው አዘዘና ቆረጧቸው የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበሉ። በዚያንም ጊዜ የመኰንኑ የአርያኖስ ልጁ ሞተበትና እጅግ አዘነ የከበረ አባ አክሎግም በአንተ ላይ በጎ ሥራ ብሠራ ፈጣሪዬ እግዚአብሔርን ብለምነው ልጅህን ቢያስነሣልህ ምን ትሰጠኛለህ አለው አርያኖስም የመቶ አለቃ አድርጌ ሹሜ በታላቅ ክብር ወደ ሀገርህ እልክሃሁ አለው።

ጻድቁ በወጣትነታቸው ወደ ጣና ባሕር ሄደው መሐምላ፣ ምፅሌና፣ አይፋር በተባሉና በሌሎችም አገሮች ወንጌልን ካስተማሩ በኋላ ወደ ትግራይ ሄደው በዚያ ገዳማቸውን መሠረቱና በዚያው ዐረፉ፡፡ ከጌታችን ጋር አብረው ማኅበር የጠጡ 3 ሺህ ቅዱሳን አክሱም አካባቢ ባለው በአቡነ ያፍቀረነ እግዚእ ገዳም ይከብራሉ፡፡ ገዳምነቱ የአቡነ ያፍቀረነ እግዚእ ይሁን እንጂ ዛሬ ላይ ግን በገዳማቸው የጻድቁ በዓል መከበር እየቀረ የእነዚህ 3 ሺህ ቅዱሳን ማኅበርተኞች በዓል ነው በድምቀት የሚከበረው፡፡ በገዳሙ ውስጥ የአቡነ ያፍቀረነ እግዚእ ቤተመቅደስ ለብቻ የ3ሺዎቹ ጻድቃን ማኅበርተኞች ቤተመቅደስም ለብቻ ይገኛሉ፡፡ ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን።https://t.me/finotebirhan12

🔴#ስንክሳር ጥር_19 አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ጥር ዐሥራ ዘጠኝ በዚህች ዕለት የከበሩ #የአባ_ዝሑራ #የአባ_ባሱራ የእናታቸውም #የኔራ ሥጋቸው የተገኘበት ነው፣ የታላቁ አባት #የአቡነ_አፍቅረነ_እግዚእ እረፍታቸው ነው። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #አባ_ባሱራ_እና_አባ_ዝሑራ ጥር ዐሥራ ዘጠኝ በዚህች ዕለት የከበሩ የአባ ዝሑራ የአባ ባሱራ የእናታቸውም የኔራ ሥጋቸው ተገኘ። እሊህ የከበሩ ተጋዳዮችም ጣዖት በሚመለክበት ዘመን ሳብሳ ከሚባል አገር በሰማዕትነት ሞቱ ሥጋዎቻቸውም በሳብሳ አገር በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚኖሩ ሆኑ ከንጹሐን ሰማዕታትም ዘመን ከዘጠኝ መቶ አርባ ሰባት ዓመት በኋላ የአፍርንጊ ሠራዊት ግብጽን ከበቧት የድምያጥንም ከተማ ወስደው በዚያ ነገሡ ከርሷ ጋርም በዙሪያዋ ያሉ ታላላቅ ከተሞችን ያዙ። የኮሞል ንጉሥም ይህም የግብጽ ንጉሥ ነው አፍርንጊያውያንንም ይወጋቸው ዘንድ ከግብጽ ሀገር ሁሉ ብዙ ሠራዊትን ሰበሰበ ሠራዊቱም ሲጓዙ ብዙዎች አብያተ ክርስቲያናትን አፈረሱ ከፈረሱትም ውስጥ አንዲቷ የእሊህ ቅዱሳን ሰማዕታት ሥጋቸው በውስጧ ያለባት ናት። ከሠራዊቱም አንዱ የቅዱሳን ሰማዕታት ሥጋ ያለበትን ሣጥን ወሰደ በውስጡ የሚደሰትበትን የዚህን ዓለም ገንዘብ እንደሚያገኝ አስቦ በከፈተው ጊዜ ከዕንቊ የከበረ የቅዱስንን ሥጋቸውን አገኘ ክብራቸውን ግን አላወቀም ከቤተ ክርስቲያኑ ግድግዳ ላይ ሥጋቸውን በትኖ ሣጥኑን ወስዶ ሸጠው። ምሕረቱ የበዛ የሚታገሥ ልዑል እግዚአብሔርም ወደ አፍርንጊ ሠራዊት እስከሚደርስ በእርሱ ላይ ታገሠ ጦርነትም በገጠሙ ጊዜ ከሁሉ አስቀድሞ እርሱ ተገደለ ባልንጀሮቹም ምስክር እንደሆኑ ወደ ሀገራቸው በተመለሱ ጊዜ የእግዚአብሔርን ክብር ፈጽመው ሰበኩ እንዲህም አሉ እርሱ አስቀድሞ በሰይፍ ተመታ ራሱንም ተቆረጠ ጐኖቹንም ሠነጣጥቀውት በክፉ አሟሟት ሞተ። የቅዱሳኑን ሥጋቸውን ያ ሰው በበተናቸው ጊዜ የአንድ ቄስ ሚስት የሆነች አንዲት ምእመን ሴት ቁማ ትመለከት ነበር ከዚህም በኋላ በጭልታ ወደርሳቸው ገብታ ደስ እያላት ወስዳ በመጐናጸፊያዋ ጠቀለለቻቸው እስላሞችንም ከመፍራቷ የተነሣ በቤተ ክርስቲያን ማዕዘን ውስጥ አኖረቻቸው በመጐናጸፊያዋም እንደ ተጠቀለሉ በጡብ ሸፈነቻቸው በዚያም ጡብ ተሸፍነው በዚያች ማዕዘን ውስጥ ሃያ ዓመት ያህል ኖሩ ከቀን ብዛትም የተነሣ ያቺ ሴት ወሬያቸውን ረሳች። እግዚአብሔርም ለወገኖቹ ጥቅም ይገልጣቸው ዘንድ በወደደ ጊዜ በዚያች ሴት ፊት ሌሎች ሰዎች አስታወሷቸው እርሷም በዚያን ጊዜ አስታወሰቻቸው ለካህናቱና ለምእመናኑ ነግራ ቦታቸውን አሳየቻቸው። ካህናቱም ገብተው ሥጋቸውን አነሡ ያማረች ሣጥንንም ሠርተው በውስጧ በክብር አኖሩዋቸው እንደ ዛሬዪቱም ዕለት በዓልን አደረጉላቸው ሁል ጊዜ በዚች ዕለት በዓል ያደርጉላቸው ዘንድ ስማቸውን በበዓላት ግጻዌ መጽሐፍ እንዲጽፉ የአገሩ ኤጲስቆጶስ አባ ገብርኤል አዝዟልና። ከዐፅሞቻቸውም ድንቆች ተአምራቶች ተገለጡ ከተአምራቶችም አንዲት የታወረች ልጅ ያለቻት ሴት ነበረች ተስፋ ከቆረጠችም በኋላ ከቅዱሳኑ ዐፅም በተማፀነች ጊዜ ዐይኖቿ ተገልጠውላት አየች እሊህንም ሰማዕታት በዚህ ክብር ያከበራቸውን የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አመሰገነችው። ✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞ #አቡነ_አፍቀረነ_እግዚእ_ዘጉጉቤን በዚህች ቀን አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ካመነኮሷቸው ከሰባቱ ከዋክብት አንዱ የሆኑት ታላቅ አባት አቡነ አፍቅረነ እግዚእ እረፍታቸው ነው። የመላእክትን ሕይወት በምድር የኖሩ እጅግ የከበሩ ታላላቅ የሀገራችንን ቅዱሳን ማለትም አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባን፣ አቡነ ያሳይ ዘማንዳባን፣ አቡነ ሳሙኤል ዘቆየፃን፣ አቡነ ሳሙኤል ዘጣሬጣን፣ አቡነ ታዴዎስ ዘባልታርዋን፣ አቡነ ያፍቅረነ እግዚእ ዘጉጉቤን እና አቡነ ዮሐንስ ዘጉራንቄን አስተምረውና አመንኩሰው ለጽድቅ ያበቋቸው አባት አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ናቸው፡፡ እነዚህንም ሰባቱን ቅዱሳን በአንድ ጊዜ ሲያመነኩሷቸው በዚያው ቅጽበት መንፈስ ቅዱስ ወርዶ ገዳሙን በብርሃን አጥለቅልቆት ታይቷል፡፡ ከሰማይም የምስክርነት ድምፅ ተሰምቷል፡፡ በዚህም ምክንያት አንድ ላይ የመነኮሱት እነዚህ ሰባቱ ቅዱሳን ‹‹ሰባቱ ከዋክብት›› እየተባሉ ይጠራሉ፡፡ እነዚህም ሰባቱ ከዋክብት የጣናን ባሕር በእግራቸው ጠቅጥቀው ተሻግረው ብዙዎቹን ደሴቱ ላይ ያሉ አስደናቂ የጣና ገዳማትን የመሠረቱት ናቸው፡፡ ከእነርሱም ውስጥ ትልቅ ጠፍጣፋ ድንጋይን እንደጀልባ ተጠቅመው በእርሱ ላይ ሆነው ወደ ደሴት የገቡ አሉ፡፡ በእግራቸውም እየረገጡ ባሕሩን የተሻገሩ አሉ፡፡ በሌላም ቦታ በየብስ የተሰማሩትም ቢሆኑ መጻሕፍቶቻቸውን በአንበሳ ጭነው የተጓዙ አሉ፡፡ አቡነ መድኃኒነ እግዚእ በደብረ ሊባኖሱ ሐዲስ ሐዋርያ የኢትዮጵያ ብርሃኗ በሆኑት በአቡነ ተክለ ሃይማኖት እጅ ከመነኮሱ በኋላ እርሳቸውም በተራቸው ያስተማሯቸውና ያመነኮሷቸው መነኮሳት ቁጥራቸው በውል አይታወቅም፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖትም ለአቡነ መድኃኒነ እግዚእ ‹‹ስፍር ቁጥር የሌላቸው ከዋክብት ቅዱሳንን›› በመንፈስ ቅዱስ እንደሚወልዱ ትንቢት ተናግረውላቸው ነበር፡፡ የተንቤኑን አቡነ ዐቢየ እግዚእን፣ የዞዝ አምባውን አቡነ አብሳዲን ጨምሮ አባታችን መድኃኒነ እግዚእ ብርሃን ሆነው በጣም ብዙ ቅዱሳንን የለኮሱ ታላቅ ጻድቅ ናቸው፡፡ በዚህም ምክንያት ‹‹ወላዴ አእላፍ ቅዱሳን›› ይባላሉ፡፡ አቡነ ያፍቅረነ እግዚእ ዛሬ ግሸን ላይ በክብር ተቀምጦ ሀገራችንን ከመዓት እየጠበቀ ያለውን የጌታችንን ቅዱስ መስቀል ካመጡት የአቡነ መድኃኒነ እግዚእ ልጆች ውስጥ አንዱ ናቸው፡፡ ዐፄ ዳዊት በዘመናቸው ረኃብ ስለነተሳ የደብረ ቢዘኑን አቡነ ፊሊጶስን ከገዳማቸው አስጠርተው ‹‹ምን ባደርግ ይሻለኛል?›› ብለው አማከሯቸው፡፡ አቡነ ፊሊጶስም ‹‹የጌታችንን መስቀል ያስመጡ›› ብለው መከሯቸው፡፡ ንጉሡ ዐፄ ዳዊትም ከኢየሩሳሌም፣ ከቍስጥንጥንያና ከእስክንድርያ መንግሥታት ጋር ተጻጽፈው ዓሥሩን ታላላቅ ቅዱሳን መርጠው ይዘው ሄደው መስቀሉን መስከረም 10 ቀን አምጥተውታል። በጽድቅ ሥራቸውና ተአምራትን በማድረግ በወቅቱ ታዋቂ የነበሩትና ቅዱስ መስቀሉን ያመጡት ዐሥሩ ቅዱሳንም የደብረ ቢዘኑ አቡነ ፊሊጶስ፣ የጣና ደሴቱ አቡነ ኂሩተ አምላክ፣ የጣና ደሴቱ አቡነ እንድርያስ፣ አቡነ በትረ ማርያም፣ አቡነ ዮሐንስ፣ አቡነ ታዴዎስ፣ አቡነ ያፍቅረነ እግዚእ፣ አቡነ ዘካርያስ፣ አቡነ ያሳይና አቡነ ቶማስ ናቸው፡፡ አቡነ ሳሙኤል ዘደብረ ዋሊ፣ አቡነ ያሳይ እና ያፍቅረነ እግዚእ እነዚህ ሦስቱ ቅዱሳን ወደ ጣና አብረው ከመጡና አብረው የተወሰነ ጊዜ ከቆዩ በኋላ አቡነ ሳሙኤል ወደ ዋልድባ ሲሄዱ አቡነ ያሳይ ማንዳባን ገዳምን አቀኑ፡፡ አቡነ አፍቅረነ እግዚእ ደግሞ ጌታችን ባዘዛቸው መሠረት ጣና ውስጥ በስማቸው የተጠራውን ገዳም አቅንተዋል፡፡ አቡነ ያፍቀረነ እግዚእ  ‹‹አፍቅረነ እግዚእ›› እየተባሉም ይጠራሉ፡፡ ይኸውም ‹‹ጌታ አምላክ ወደደን›› ማለት ነው፡፡ ትውልዳቸው ትግራይ አክሱም ሲሆን አባታቸው ገብረ ኢየሱስ እናታቸው አፎምያ የተባሉ ደጋግ ክርስቲያኖች ናቸው፡፡ ልደታቸው ሐምሌ 19 ቀን ነው፡፡ አቡነ ያፍቀረነ እግዚእ በገዳማዊ ሕይወታቸው በእጅጉ ይታወቃሉ፡፡ በንጉሥ ዓምደ ጽዮን ዘመን የነበሩ ሲሆን ደራሲና ፈላስፋም ናቸው፡፡ ጻድቁ ደራ ፎገራ ውስጥ ባለ አራር ዓምድ አስደናቂ ገድል አላቸው፡፡ ከደራ ፎገራ ተነሥተው በጣና አድርገው ፈላሾችንና ቅማንቶችን በሚገባ በማስተማርና በማጥመቅ ብዙ ሐዋርያዊ አገልግሎት ፈጽመዋል፡፡

4. በዚህ ጸረ ቤተ ክርስቲያን እና ኢ-ቀኖናዊ ድርጊት በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ እየኖሩ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ወይም በቦታው በመገኘት የጥፋት ድርጊቱ ተባባሪ የሆኑ ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን በሥራ ላይ የሚገኙ ሠራተኞችን በተመለከተ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ተገቢውን ክትትልና አስተዳደራዊ ውሳኔ እንዲሰጥ፤ 5. ይህን ታሪክ ይቅር የማይለውን ሕገ ወጥ አድራጎት እና የቀኖና ጥሰት በሐሳብ፤ በገንዘብ እና በሌላ በማንኛውም ሁኔታ ድጋፍ ሲያደርጉ የቆዩ እና በማድረግ ላይ ያሉ ማናቸውም ተቋማት እና ግለሰቦች ከዚህ ሕገ ወጥ አድራጎታቸው እንዲቆጠቡ ቅዱስ ሲኖዶስ በጥብቅ እያሳሰበ ይህ ባይሆን በሕግ አግባብ ተገቢው እንዲፈጸም ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ 6. በየደረጃው የሚገኙ የቤተ ክርስቲያኒቱ የሥራ ኃላፊዎች፤ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፤ መነኮሳት፤ አገልጋይ ካህናት፤ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች፤ ልዩ ልዩ የቤተ ክርስቲያኒቱ መንፈሳዊ ማህበራት እና ምእመናን እና ምእመናት ይህን ሕገ ወጥ አድራጎት ከመከላከል እና የቤተ ክርስቲያናችሁን ደህንነት ከመጠበቅ በተጨማሪ ለዚህ ሕገ ወጥ አድራጎት ልዩ ልዩ ድጋፍ የሚያደረግ ተቋማት እና ግለሰቦችን አስፈላጊውን ክትትል እና ቁጥጥር በማድረግ የመከላከል ሥራችሁን እንድትወጡ ዘንድ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ 7. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስምን ከፊትም ሆነ ከኃላ በመጨመር እና በመቀነስ በከፊልም ሆነ በሙሉ መጠቀም፤ ዓርማዋን፤ አድራሻዋን፤የአምልኮ እና የሥርዓት መፈጸሚያ የሆኑ ንዋያ ቅዱሳትንና አልባሳት እንዲሁም መጻሕፍት መገልገል የማይችሉ መሆኑ ታውቆ ይህንን ጉዳይ በየደረጃው ያሉ መንግሥታዊ አካላት እና የቤተ ክርስቲያኒቱ የሥራ ኃላፊዎች ተከታትለው እንዲያስፈጽሙ ቅዱስ ሲኖዶስ የወሰነ ሲሆን በተጨማሪም ይህን ውሳኔ ተላልፈው በሚገኙ ማናቸውም ግለሰቦች እና ተቋማት ላይ ተገቢውን ሕግ አግባብ ተከትሎ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ዓለማት የሚያስፈጽም ዓለም አቀፍ እና ሀገር አቀፍ የሕግ ባለሙያዎች በመመደብ ተገቢውን ሁሉ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት በኩል እንዲፈጸም ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ 8. አሁን የተከሰተውን ችግር አስመልክቶ ዝርዝር ጥናት እና የመፍትሔ ሐሳብ የሚያቀርብ አንድ ዐቢይ ኮሚቴ በቋሚ ሲኖዶስ እንዲሰየም ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ 9. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ያሳለፈውን ውሳኔ ከክቡር የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር ጀምሮ በየደረጃው ላሉት የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮች እንዲከናወኑ እና ይህ ውሳኔ ከሸኚ ደብዳቤ ጋር እንዲደርሳቸው ተወስኗል፡፡ 10. ይህን የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ውሳኔ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ክፍለ ዓለማት ለሚገኙ የቤተ ክርስቲኒቱ አገልጋዮች እና ምእመናን የግንዛቤ ማስጨበጫ የንቅናቄ መድረኮች እንዲካሔዱ እና በሀገር አቀፍ ደረጃ በማእከል የአህጉረ ስብከት ሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ታላቅ የንቅናቄ እና የግንዛቤ መድረክ እንዲከናወን ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ 11. በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ የሚገኙ መንግስታዊም ሆነ መነግስታዊ ያልሆነ ተቋማት፤ አኃት አቢያተ ክርስቲያናት፤ የምሥራቅ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት፤ የሮም ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እና ሌሎች አብያተ ክርስቲያናት፤ የዓለም አቢያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት፤ የመላው አፍሪካ አብያት ክርስቲያናት ጉባዔ እና ሌሎች የአብያተ ክርስቲያናት እና የሃይማኖት ጉባኤዎች በሙሉ እነዚህ የተወገዙት ግለሰቦች የኢትዮጵያ ኦርቶደክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን የማይወክሉ እና ምንም አይነት የሥራ ግንኙነት የሌላቸው መሆኑ ታውቆ ማናቸውም ግንኙነት በቤተ ክርስቲያኑቱ ስም እንዳያደርጉ በጽሑፍ አንዲገለጽ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ 12. እነዚህ ግለሰቦች ከሚሰጡት የተሳሳተ መረጃ አንዱ እኩይ ተግባራቸው የኦሮሞ ሕዝብ ጥያቄ እንደሆነ ማስመሰል ሲሆን ይኽ ተግባር ሃይማኖቱን የሚወድ፣ አባቶቹን የሚያከብር እና አስተዋይ የሆነውን የኦሮሞ ሕዝብ የማይወክል፣ የራሳቸውን የሥልጣን ጥማት ለማርካት ያደረጉት ሕገወጥ የቀኖና ጥሰት መሆኑ እንዲታወቅ፤ በተጨማሪም ለሚያሠራጩት የሐሰት አሉባልታ ወደፊት ተገቢው መልስ እንዲሰጥበት ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤ እስከ አሁን ድረስ በተፈጠረው ችግር ምክንያት ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ጎን በመሆን አጋርነታችሁን ያሳያችሁ፣ ለቤተ ክርስቲያን አንድነት እና ሉዐላዊነት መከበር የበኩላችሁን በመወጣት መግለጫ የሰጣችሁ ሁሉ በልዑል እግዚአብሔር ስም እያመሰገንን ለወደፊቱም በጸሎታችሁ እና በመልካም አጋርነታችሁ ከጎናችን እንድትሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ጥር 18 ቀን 2015 ዓ/ም አዲስ አበባ ኢትዮጵያ ምንጭ :-የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን መገናኛ ብዙሃን

(ጢሞ.3፣10፣ ቲቶ፣ 1፣5-7 ፍትሕ መን አንቀጽ 4) - ይህንም ቅዱሳን ሐዋርያት ሲመተ ኤጲስ ቆጶሳትን በተመለከተ በ3ኛው ቀሌምንጦስ “ኤጲስ ቆጶስ የሀገሩ ሰዎች፣ የሀገሩ ጳጳስ፣ ፈቅደውለት ይሾም፤ ቢገኙ ሦስት፣ ባይገኙ ሁለት፣ ኤጲስ ቆጶሳት ሁነው ይሹሙት” ብለዋል፡፡ ይህም ቅዱስ ሲኖዶስ በሌለበት ሀገር፣ ፓትርያርክ በሌለ ጊዜ ምእመናን እንዳይበተኑ ተብሎ የሚደረግ ነው እንጅ በቅዱስ ፓትርያርኩ ሊቀመንበርነት በመንፈስ ቅዱስ የሚመራውን የቅዱስ ሲኖዶስን ሉዓላዊ ሥልጣን በመጋፋት የሚፈጸም ከሆነ ግን ይህን ቀኖና በሕገወጥ መንገድ ለተፈጸመ ድርጊት መጥቀሱ በቅዱስ ወንጌል ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዳስተማረን በመንፈስ ቅዱስ ላይ የስድብ ቃል እንደመናገር ተቆጥሮ የማይሠረይ ኃጢአት መሆኑ ሊሠመርበት ይገባል፡፡ (ማቴ.12፣30-32 ሉቃስ 12፣10፣ ማርቆስ 3፡28-29 1ኛ ጢሞ 1፣13) የእነዚህ ሰዎች ተግባር በሥራ ላይ ያለውን በመንፈስ ቅዱስ የሚመራ ሕጋዊ የኢትዮጵያ ቅዱስ ሲኖዶስ የመፈንቅል፣ የታላቋን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን መዋቅር የመናድ፣ ሕጋዊ ተቋምን የማፍረስ ወይም የመናድ ተግባር በመሆኑ በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዟል፣ - ሠለስቱ ምዕትም ሲመተ ኤጲስ ቆጶሳትን በተመለከተ በኒቅያ በጻፉት ቀኖና በዘጠነኛው አንቀጽ አንዱም አንዱ ኤጲስ ቆጶስነት ሊሾም ቢሻ፣ የሀገሩ ሰዎች ቢፈቅዱለት፣ የሀገሩ ጳጳስ ካልፈቀደለት ኤጲስ ቆጶስነት መሾም አይገባውም ይህን አፍርሶ ቢገኝ ሲኖዶስ ያወግዘዋል፤ ሹመቱም ይቀራል” ብለዋል፡፡ ይህም በዚህ ወቅት ከቀኖና ቤተ ክርስቲያን ውጭ የጥንታዊት፣ ሐዋርያዊት፣ ብሔራዊትና ዓለም አቀፋዊት ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲየን ሕጋዊ ቅዱስ ሲኖዶስ ሉዓላዊ ስልጣን በመጋፋት በድፍረት ተፈጸመ የተባለው ሹመት አስቀድሞ በአበው ቅዱሳን የተወገዘ ነው፤ - ከዚህም ጋር ሲመተ ኤጲስ ቆጶሳት በሚፈጸምበት ጊዜ፣ ያለ ቅዱስ ፓትርያርኩ ፈቃድ ማንም ወደ ቤተ መንግሥት እንዲሔድ ቀኖና ቤተ ክርስቲያን አይፈቅድም፡፡ ይህንንም የተላለፈ ቢኖር ከጳጳሳና ከኤጲስ ቆጶሳት ማንም ማን ሊቀጳጳሳቱ ሳይፈቅድለት ወደ ንጉሥ ቤት አይሒድ ወለኲሉ ዘዐለወ ዘንተ ሲኖዶስ ያወግዞ ይህን ትእዛዝ ያፈረሰውን ሲኖዶስ ያወግዘዋል” ተብሎ ስለተወሰነ ዛሬም ከቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ እና ከቅዱስ ፓትርያርኩ ውጭ የሚደረግ ማናቸውም እንቅስቃሴ ሕገወጥ በመሆኑ በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዘዋል፤ - በቀኖና ቤተ ክርስቲያን … ሰው ሁሉ ማዕርጉን ጠብቆ ይኑር እንጅ፣ አንዱ ወደ አንዱ ማዕርግ አይተላለፍ፤ ይህን የሠራነውን ሥርዐት ያፈረሰውን ሰው ሲኖዶስ ያወግዘዋል ተብሎ በተጻፈው መሰረት እነዚህ ሕገወጥ አካላት በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዘዋል፤ - በሕገ ቤተ ክርስቲያን አንቀጽ 16 ንዑስ ቁጥር 30 የአጲስ ቀጶሳት መሾም አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ፣ በቤተ ክርስቲያን ቀኖና መሠረት እንዲመረጡና እንዲሾሙ የመወሰን ሥልጣን የቅዱስ ሲኖዶስ መሆኑን የሚደነግገውን ክፍል በግልጽ የጣሰ በመሆኑ፤ - በሕገ ቤተ ክርስቲያን አንቀጽ 37 ንዑስ ቁ.1 የኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ የሚፈጸመው ኤጲስ ቆጶሳት እንዲሾሙ አስፈላጊ መሆኑ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ሲታመንበትና ሲወሰን ብቻ እንደሚፈጸምና መደንገጉ፤ - በሕገ ቤተ ክርስቲያን አንቀጽ 18 ንዑስ ቁጥር 5 የቤተ ክርስቲያንን ሃይማኖታዊ ሕግጋትንና ቀኖናን የሚያፋልስ ሊቀ ጳጳስ /ኤጲስ ቆጶስ/ ከአባልነት እንደሚሰረዝ በመደንገጉ፤ ቅዱስ ሲኖዶስ አውግዟቸዋል፡፡ በአጠቃላይ የተፈጸመው ሕገ ወጥ ተግባር በሕገ ሰብእም ሆነ በሕገ እግዚአብሔር ሚዛን የተወገዘ ከመሠረተ እምነት የተለየ፣ በአበው ቀኖና፣ በሕገ ቤተ ክርስቲያን እና በቤተ ክርስቲያን አስተዳደር በአጠቃላይ ተቀባይት የሌለው ነው፡፡ ስለዚህ 1ኛ. በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ንኡስ አንቀጽ 138 መሠረት ጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት በሶዶ ዳጩ ወረዳ ሐሮ ባለወልድ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ፩ኛ. አባ ሳዊሮስ 2ኛ. አባ ኤዎስጣቴዎስ 3ኛ. አባ ዜና ማርቆስ የቤተ ክርስቲያንን ቀኖና በመጣስ ባልተሰጣቸው ስልጣን 26 ኤጴስ ቆጰሳትን ሾመናል፤ ሲኖዶስ አቋቁመናል በማለት በማኅህበራዊ እና በብሮድካስት ሚዲያዎች በሰጡት መግለጫ የተረጋገጠ በመሆኑ በዚሁ ድርጊታቸው በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭው ዓለም የሚኖረውን ሕዝበ ክርስቲያንን በማታለል የክህደት እና የኑፋቄ ተግባር በመፈጸማቸው በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ አውግዞ፤ ከቤተ ክርስቲያን የተሰጣቸውን ከዲቁና ጀምሮ ያለው ሙሉ ሥልጣነ ክህነት በመሻር አውግዞ ለይቷቸዋል፡፡ በመሆኑም፡- ሀ. ሥልጣነ ክህነታቸውና የማዕረግ ስማቸው በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ውሳኔ የተነሣ ስለሆነ ከዛሬ ጥር 18 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በቀድሞ ዓለማዊ ስማቸው እንዲጠሩ፤ ለ. በቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ አገልግሎት ዙርያም በሕይወትም ሆነ በሞት ማናቸውንም መንፈሳዊ አገልግሎት እንዳያገኙ ቅዱስ ሲኖዶስ አውግዞ ከቤተ ክርስቲያን ለይቷቸዋል፡፡ ሐ. በነዚህ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ አውግዞ በለያቸው ግለሰቦች ይመሯቸው በነበሩ አህጉረ ስብከት መንፈሳዊ አገልግሎት በማከናወን ሀገረ ስብከቱን የሚመሩ ብፁዐን አባቶችን ፩. ለደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ፪. ለኬንያ፤ኡጋንዳ፤ታንዛኒያ እና ሩዋንዳ ሀገረ ስብከት ፫. ለኢሉ አባቦራ እና በኖ በደሌ ሀገረ ስብከት ፬. በሰሜን አሜሪካ ለሜኒሶታ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት ፭. ለጉጂ፤ምዕራብ ጉጂ እና ቦረና ሊበን ዞኖች ሀገረ ስብከት ፮. ለምስካዬ ኅዙናን መድኃኒዓለም ገዳም በአባትነት የሚመሩ አበው ሊቃነ ጳጳሳት እንዲመደቡ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ወስኗል፡፡  ይሁን እንጅ ከላይ በስም ተጠቅሰው የተወገዙት ግለሰቦች በሠሩት የቀኖና ጥሰት ተጸጽው ይቅርታን ቢጠይቁ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን የምህረት ደጆች ሁል ጊዜ ክፈት መሆናቸውና በቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረት የምንቀበላቸው መሆኑን ቅዱስ ሲኖዶስ ያሳውቃል፤ 2. የቅዱስ ሲኖዶሱንና የቤተ ክርስቲያኒቱን ልዕልና በመዳፈር እና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን በመጣስ በተነሳሱ ግለሰቦች አማካኝነት የኤጲስ ቆጶስነት ሺመት አግኝተናል፤ ተሸመናል እያሉ የሚገኙ 25 መነኰሳት በሕገ ወጥ መንገድ ቀኖና ቤተ ክርስቲያንንን ጥሰው የተገኙ በመሆኑ አስቀድሞ ከቤተ ክርስቲያን የተሰጣቸው ከዲቁና ጀምሮ ያለው ሙሉ ሥልጣነ ክህነት ተሽሮ ከዛሬ ጥር 18 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ተወግዘው ከቤተ ክርስቲያን ተለይተዋል፡፡ 3. ከነዚሁ ግለሰቦች መካከል አንዱ የሆኑት አባ ጸጋዘአብ አዱኛን ከቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ ምልዐተ ጉባኤ ስብሰባ በፊት የቀኖና ጥሰቱንና ሕገ ወጥ አድራጎቱን በመረዳትና በመጸጸት ድርጊቱን በመቃወም ለቤተ ክርስቲያኒቱ ባቀረቡት የይቅርታ አቤቱታ መሠረት ቅዱስ ሲኖዶሱ ይቅርታውን የተቀበላቸው ሲሆን እንደሳቸው ሁሉ ከላይ የተወገዙት 25 ግለሰቦች በሠሩት የቀኖና ጥሰት ተጸጽው ይቅርታን ቢጠይቁ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን የምህረት ደጆች ሁል ጊዜ ክፈት መሆናቸውና በቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረት የምንቀበላቸው መሆኑን እንገልጻለን

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በፍትሕ መንፈሳዊ እንዲሁም በሕገ ቤተክርስቲያን አንቀጽ 19 ንዑስ ቁጥር 3 አስቸኳይና ድንገተኛ ጉዳይ ሲያጋጥም ምልዓተ ጉባኤ እንደሚያደርግ በተደነገገው መሠረት ጥር 18 ቀን 2015 ዓ.ም. ባካሄደው አስቸኳይ ምልዓተ ጉባኤ በቤተ ክርስቲያኒቷ ላይ በተፈጠረው ወቅታዊ የሃይማኖት፣ የቀኖና እና የአስተዳደራዊ ጥሰቶችን አስመልክቶ ውሳኔዎች አሳልፏል፡፡ ጥንታዊት፣ ሐዋርያዊትና ዓለም አቀፋዊት የሆነች ቅድስት ቤተክርስቲያን ሕዝብና አሕዛብን፣ ሰውና መላእክትን፣ ፍጡራን እና ፈጣሪን ይልቁንም በሰውና በእግዚአብሔር መካከል ያለውን ልዩነት አጥፍቶ የሰው ልጅ ሁሉ በቋንቋ፣ በቀለምና በጐሣ ሳይከፋፈሉ በአንድነት ሀብተ ወልድና ስመ ክርስትና አግኝተው ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ ከማህፀነ ዮርዳኖስ የተወለዱ በማየ ገቦ የተጠመቁ የቤተ ክርስቲያን ልጆች እንዲሆኑ ልዩነት የሌለባትን ዘለዓለማዊት መንግሥተ እግዚአብሔር እንዲወርሱ በደመ ክርስቶስ የተመሠረተች ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በየዘመናቱ የተነሣባትን ፈተና ሁሉ አልፋ ከእኛ ዘመን ደርሳለች፤ ምንም እንኳ ከቅዱሳት መጻሕፍትም ሆነ ከኦርቶዶክስ ትምህርተ ሃይማኖት ፈጽሞ በተለየ ሁኔታ ቤተ ክርስቲያንን በጐሣና በቋንቋ የመለየት ሂደት በዓለም አቀፍ ደረጃ እንግዳ ክስተት ቢሆንም ቤተ ክርስቲየን ከሃይማኖታዊና መንፈሳዊ ጠባይዋ በተለየ፣ ታሪኳንና ሥርዓቷን በማይመጥን፣ ከሕግ መንፈሳዊ፣ ከሕግ ጠባይአዊ እና ከሕገ አእምሮ በወጣ መልኩ የደረሰባት ጥቃት፣ እና የመፈንቅለ ሲኖዶስን ተግባር ቅዱስ ሲኖዶስን እጅግ አሳዝኖታል፤ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በታሪኳ ውስጥ ለሀገር አንድነት፣ ለፍትሕ፣ ለጥበብ፣ ለሕዝብ ትስስር፣ ለማኅበራዊ ዕድገት፣ ለጤና፣ ለሥነ-ምግባር መሠረት እና ዐምድ፤ ምሰሶ እና ማገር ሆና በዓለም አቀፍ ደረጃ የተፈራች፣ የተከበረች እና የተወደደች፤ ዕሴቷ እና ዕምቅ የዕውቀት ሀብቷ በምሁራን የታወቀ፣ በትምህርተ ዓለም ሳይቀር የተቀረጸ፤ በእውነተኛ ሊቃውንት የተመሠከረ፣ ቅርሶቿ የተመዘገቡላት ስትሆን፤ በቅርቡ ራስዋ በሾመቻቸው በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር ከፍተኛውና ሐዋርያዊ ተልእኮ እንዲወጡ አደራ በተሰጣቸው ሊቃነ ጳጳሳት መሠረተ እምነትን፣ ሃይማኖታዊ ቀኖናን፣ የአስተዳደር ሥርዓት ሁሉ በጣሰ፣ መንገድ በማኅበረሰብ ዕድገትና አስተዳደር ውስጥ ከሕዝብ ጋር የቆመች፣ ከፖለቲካ የጸዳች መንፈሳዊና ሕዝባዊት ተቋምነቷን በመካድ ከፍተኛ የሆነ ሕገ ወጥ ድርጊት፣ ተቋምን የመናድና መዋቅሯን የማፍረስ ተግባር ተከናውኗል፡- በዚሁ መሠረት፡- ጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት በሶዶ ዳጡ ወረዳ ከወሊሶ ከተማ ወጣ ብሎ በሚገኘው አሮ ባለ ወልድ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተፈጸመውን እጅግ አሳዛኝ እና ኢ-ሲኖዶሳዊ የሆነ አስነዋሪ፤ ሕገ ወጥ የቀኖና ቤተ ክርስቲያን ጥሰት አስመልከቶ ቅዱስ ሲኖዶስ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት አስቸኳይ የምልዐተ ጉባዔ አድርጓል፤ ቅዱስ ሲኖዶስም በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር ያሉ መላው አህጉረ ስብከት፤ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት አስተዳደር ጉባዔ፣ የሊቃውንተ ጉባኤ፤ የሕግ አገልግሎት መምሪያ፤ በዓለም አቀፍና ሀገር አቀፍ ደረጃ ያሉ የወጣቶች እና የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት፣ መንፈሳውያን ማኅበራት፤ የምእመናን እና አገልጋዮች ኅብረት፣ ሁሉም ኦርቶዶክሳውያን በደብዳቤ፣ በሚዲያ እና በአካል ከሰጡት ምክረ ሐሳብ እና የአቋም መግለጫ በመነሣት፤ በሀገር ውስጥ እና በውጪው ዓለም የሚገኙ የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ወዳጆች፣ በተለይም የግብጽ እስክንድርያ ኮፕቲክ ኦርቶዶከስ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕጋዊ ፓትርያርክ ውጭ የሚደረግ ሢመትን እንደማይቀበሉና ዕውቅና እንደማይሰጡ በላኩት የአቋም መግለጫ፣ የኤርትራ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ፣ የሕንድ ማላንካራ ኦርቶዶከስ ቤተ ክርስቲያን፣ እና የሌሎች አኀት ኦርቶዶከስ አብያተ ክርስያናት፣ የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት፣ ዓለም አቀፍ መንፈሳዉያን ተቋማት፣ የልማት እና የበጎ አድርጎት አጋር ድርጅቶች፤ ድርጊቱን በማውገዝ የማይቀበሉት መሆኑን የአቋም መግለጫ በመላክ ባሳዩት አጋርነት፤ አስቀድሞ እንደተገለጸው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በደመ ክርስቶስ ከተመሠረተችበት ጊዜ ጀምሮ ያለፈተና የኖረችበት ጊዜ እንደሌለ ቅዱሳት መጻሕፍትና የታሪክ መዛግብት ሲመሰክሩ በዘመነ ሐዋርያት ቢጽ ሐሳውያን፣ በዘመነ ሊቃውንት የተለያዩ መናፍቃን፣… በየጊዜው እየተነሡ ሲፈታተኗት ኑረዋል፡፡ አሁንም በግልጽ እንደሚታየው ከውጭም ከውስጥም በተደራጁ ምንደኞች በመፈተን ላይ ትገኛለች፡፡ ለዚህም ጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም. በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት፣ በሶዶ ዳጩ ወረዳ፣ ሀሮ በዓለ ወልድ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በአባ ሳዊሮስ መሪነት እጅግ አሳዛኝ ኢ-ሲኖዶሳዊ የሆነ አስነዋሪ፣ ሕገ-ወጥ፣ የቀኖና ቤተ ክርስቲያን ጥሰት አንዱ ሲሆን፤ በአባ ሳዊሮስ መሪነት የተፈጸመው የቀኖና ቤተ ክርስቲያን ጥሰት ፳፮ መነኰሳትን ከቀኖና የወጣ ሢመት በመስጠትና ሊቃነ ጳጳሳት በሚመሯቸው አህጉረ ስብከት በሕገ ወጥ መንገድ በመመደብ ከቀኖና ቤተ ክርስቲያን ጥሰት አልፎ ሃይማኖትን የሚከፋፍል፤ የሀገር አንድነትን የሚሸረሽር እና የሚያፈርስ፣ ምእመናንን ከምእመናን፣ ካህናትን ከካህናት፣ ሊቃውንትን ከሊቃውንት ወጣትን ከወጣት … የሚያጋጭና ደም የሚያፋስስ ፀጥታን የሚያናጋ መሆኑን ቅዱስ ሲኖዶስ ተገንዝሟል፤ በመሆኑም፤ - ከላይ እንደተገለጸው ሐዋርያት በሦስተኛው ቀሌምንጦስ በሃያ አምስተኛው አንቀጽ “በአውራጃው ሁሉ ያሉ ኤጲስ ቆጶሳት አለቃቸው ማንም እንደሆነ ማወቅ ይገባቸዋል፡፡ አለቃ ያድርጉት፤ ያለ ፍቃዱ ጥቃቅኑንም ደጋጉንም ሥራ ምንም ምን አይሥሩ፤ እርሱም ዳግመኛ ኤጲስ ቆጶሳቱ ሳይፈቅዱ ደጋጉን ሥራ አይሥራ ጥቃቅኑን ቢሠራ እዳ የለበትም፡፡ ሁሉም እንደ አንድ ልብ መካሪ፣ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ፣ ሁነው በአንድነት ይኑሩ” ብለው ወስነዋል፡፡ እነዚህ ሕገ ወጥ አካላት ይህን የሐዋርያት ቀኖናን በመሻራቸው፡፡ - ሁለተኛም በአርባ አራተኛው አንቀጽ “ሊቀጳጳሳት (ፓትርያርክ) ኤጲስ ቆጶሳት በተሾሙባቸው አገሮች የሚሠሩትን ሥራ፣ የሚያዙትን ትእዛዝ ይመርምር፡፡ የማይገባ ሥራ ሠርተው፣ የማይገባ ትእዛዝ አዝዘው፣ ቢያኝ ለውጦ የተገለጸለትን ትእዛዝ ይዘዝ፡፡ እርሱ ለሁሉ የሹመት አባታቸው ነውና፤ እነሱም ልጆቹ ናቸውና…” ብለዋል፡፡ ይህን ኢ-ቀኖናዊ ሥርዐተ ሲመት የፈጸሙት ግለሰቦች በሕገወጥ መንገድ በአደባባይ የቅዱስ ሲኖዶስን ሉዓላዊ ሥልጣን እና የቅዱስ ፓትርያርኩን መብት በመጣሳቸው፡፡ - ሢመተ ክህነትን በተመለከተ “ወአልቦ ዘይነሥእ ክብረ ለርእሱ ዘእንበለ ዘጸውዖ እግዚአብሔር … እንደ አሮን በእግዚአብሔር ከተጠራ በቀር ማንም ለራሱ ክብርን የሚወስድ የለም” (ዕብ 5፤4) እንደሚለው የእግዚአበሔር ቃል ከዲቁና ጀምሮ እስከ ፓትርያርክ ሹመት ድረስ ያለው ሹመት በመጀመሪያ ከእግዚአብሔር መጠራቱን የሚጠይቅ ሲሆን እንኳንስ ለተሿሟዎች ለመራጮችና ለአስመራጮች በቀኖና ቤተ ክርስቲያን የተወሰነ፣ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መስፈርት ያለው፣ መሆኑ ለሁሉም ግልጽ ነው፡፡ ይህንም ቅዱስ ጳውሎስ በጻፈው መልእክቱ በሰፊው ገልጾታል፡፡

4. በዚህ ጸረ ቤተ ክርስቲያን እና ኢ-ቀኖናዊ ድርጊት በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ እየኖሩ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ወይም በቦታው በመገኘት የጥፋት ድርጊቱ ተባባሪ የሆኑ ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን በሥራ ላይ የሚገኙ ሠራተኞችን በተመለከተ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ተገቢውን ክትትልና አስተዳደራዊ ውሳኔ እንዲሰጥ፤ 5. ይህን ታሪክ ይቅር የማይለውን ሕገ ወጥ አድራጎት እና የቀኖና ጥሰት በሐሳብ፤ በገንዘብ እና በሌላ በማንኛውም ሁኔታ ድጋፍ ሲያደርጉ የቆዩ እና በማድረግ ላይ ያሉ ማናቸውም ተቋማት እና ግለሰቦች ከዚህ ሕገ ወጥ አድራጎታቸው እንዲቆጠቡ ቅዱስ ሲኖዶስ በጥብቅ እያሳሰበ ይህ ባይሆን በሕግ አግባብ ተገቢው እንዲፈጸም ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ 6. በየደረጃው የሚገኙ የቤተ ክርስቲያኒቱ የሥራ ኃላፊዎች፤ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፤ መነኮሳት፤ አገልጋይ ካህናት፤ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች፤ ልዩ ልዩ የቤተ ክርስቲያኒቱ መንፈሳዊ ማህበራት እና ምእመናን እና ምእመናት ይህን ሕገ ወጥ አድራጎት ከመከላከል እና የቤተ ክርስቲያናችሁን ደህንነት ከመጠበቅ በተጨማሪ ለዚህ ሕገ ወጥ አድራጎት ልዩ ልዩ ድጋፍ የሚያደረግ ተቋማት እና ግለሰቦችን አስፈላጊውን ክትትል እና ቁጥጥር በማድረግ የመከላከል ሥራችሁን እንድትወጡ ዘንድ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ 7. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስምን ከፊትም ሆነ ከኃላ በመጨመር እና በመቀነስ በከፊልም ሆነ በሙሉ መጠቀም፤ ዓርማዋን፤ አድራሻዋን፤የአምልኮ እና የሥርዓት መፈጸሚያ የሆኑ ንዋያ ቅዱሳትንና አልባሳት እንዲሁም መጻሕፍት መገልገል የማይችሉ መሆኑ ታውቆ ይህንን ጉዳይ በየደረጃው ያሉ መንግሥታዊ አካላት እና የቤተ ክርስቲያኒቱ የሥራ ኃላፊዎች ተከታትለው እንዲያስፈጽሙ ቅዱስ ሲኖዶስ የወሰነ ሲሆን በተጨማሪም ይህን ውሳኔ ተላልፈው በሚገኙ ማናቸውም ግለሰቦች እና ተቋማት ላይ ተገቢውን ሕግ አግባብ ተከትሎ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ዓለማት የሚያስፈጽም ዓለም አቀፍ እና ሀገር አቀፍ የሕግ ባለሙያዎች በመመደብ ተገቢውን ሁሉ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት በኩል እንዲፈጸም ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ 8. አሁን የተከሰተውን ችግር አስመልክቶ ዝርዝር ጥናት እና የመፍትሔ ሐሳብ የሚያቀርብ አንድ ዐቢይ ኮሚቴ በቋሚ ሲኖዶስ እንዲሰየም ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ 9. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ያሳለፈውን ውሳኔ ከክቡር የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር ጀምሮ በየደረጃው ላሉት የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮች እንዲከናወኑ እና ይህ ውሳኔ ከሸኚ ደብዳቤ ጋር እንዲደርሳቸው ተወስኗል፡፡ 10. ይህን የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ውሳኔ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ክፍለ ዓለማት ለሚገኙ የቤተ ክርስቲኒቱ አገልጋዮች እና ምእመናን የግንዛቤ ማስጨበጫ የንቅናቄ መድረኮች እንዲካሔዱ እና በሀገር አቀፍ ደረጃ በማእከል የአህጉረ ስብከት ሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ታላቅ የንቅናቄ እና የግንዛቤ መድረክ እንዲከናወን ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ 11. በሀገር ውስጥም ሆነ ከሀገር ውጭ የሚገኙ መንግስታዊም ሆነ መነግስታዊ ያልሆነ ተቋማት፤ አኃት አቢያተ ክርስቲያናት፤ የምሥራቅ ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት፤ የሮም ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን እና ሌሎች አብያተ ክርስቲያናት፤ የዓለም አቢያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት፤ የመላው አፍሪካ አብያት ክርስቲያናት ጉባዔ እና ሌሎች የአብያተ ክርስቲያናት እና የሃይማኖት ጉባኤዎች በሙሉ እነዚህ የተወገዙት ግለሰቦች የኢትዮጵያ ኦርቶደክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን የማይወክሉ እና ምንም አይነት የሥራ ግንኙነት የሌላቸው መሆኑ ታውቆ ማናቸውም ግንኙነት በቤተ ክርስቲያኑቱ ስም እንዳያደርጉ በጽሑፍ አንዲገለጽ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ 12. እነዚህ ግለሰቦች ከሚሰጡት የተሳሳተ መረጃ አንዱ እኩይ ተግባራቸው የኦሮሞ ሕዝብ ጥያቄ እንደሆነ ማስመሰል ሲሆን ይኽ ተግባር ሃይማኖቱን የሚወድ፣ አባቶቹን የሚያከብር እና አስተዋይ የሆነውን የኦሮሞ ሕዝብ የማይወክል፣ የራሳቸውን የሥልጣን ጥማት ለማርካት ያደረጉት ሕገወጥ የቀኖና ጥሰት መሆኑ እንዲታወቅ፤ በተጨማሪም ለሚያሠራጩት የሐሰት አሉባልታ ወደፊት ተገቢው መልስ እንዲሰጥበት ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤ እስከ አሁን ድረስ በተፈጠረው ችግር ምክንያት ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ጎን በመሆን አጋርነታችሁን ያሳያችሁ፣ ለቤተ ክርስቲያን አንድነት እና ሉዐላዊነት መከበር የበኩላችሁን በመወጣት መግለጫ የሰጣችሁ ሁሉ በልዑል እግዚአብሔር ስም እያመሰገንን ለወደፊቱም በጸሎታችሁ እና በመልካም አጋርነታችሁ ከጎናችን እንድትሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስ ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ጥር 18 ቀን 2015 ዓ/ም አዲስ አበባ ኢትዮጵያ ምንጭ :-የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን መገናኛ ብዙሃን

(ጢሞ.3፣10፣ ቲቶ፣ 1፣5-7 ፍትሕ መን አንቀጽ 4) - ይህንም ቅዱሳን ሐዋርያት ሲመተ ኤጲስ ቆጶሳትን በተመለከተ በ3ኛው ቀሌምንጦስ “ኤጲስ ቆጶስ የሀገሩ ሰዎች፣ የሀገሩ ጳጳስ፣ ፈቅደውለት ይሾም፤ ቢገኙ ሦስት፣ ባይገኙ ሁለት፣ ኤጲስ ቆጶሳት ሁነው ይሹሙት” ብለዋል፡፡ ይህም ቅዱስ ሲኖዶስ በሌለበት ሀገር፣ ፓትርያርክ በሌለ ጊዜ ምእመናን እንዳይበተኑ ተብሎ የሚደረግ ነው እንጅ በቅዱስ ፓትርያርኩ ሊቀመንበርነት በመንፈስ ቅዱስ የሚመራውን የቅዱስ ሲኖዶስን ሉዓላዊ ሥልጣን በመጋፋት የሚፈጸም ከሆነ ግን ይህን ቀኖና በሕገወጥ መንገድ ለተፈጸመ ድርጊት መጥቀሱ በቅዱስ ወንጌል ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዳስተማረን በመንፈስ ቅዱስ ላይ የስድብ ቃል እንደመናገር ተቆጥሮ የማይሠረይ ኃጢአት መሆኑ ሊሠመርበት ይገባል፡፡ (ማቴ.12፣30-32 ሉቃስ 12፣10፣ ማርቆስ 3፡28-29 1ኛ ጢሞ 1፣13) የእነዚህ ሰዎች ተግባር በሥራ ላይ ያለውን በመንፈስ ቅዱስ የሚመራ ሕጋዊ የኢትዮጵያ ቅዱስ ሲኖዶስ የመፈንቅል፣ የታላቋን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን መዋቅር የመናድ፣ ሕጋዊ ተቋምን የማፍረስ ወይም የመናድ ተግባር በመሆኑ በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዟል፣ - ሠለስቱ ምዕትም ሲመተ ኤጲስ ቆጶሳትን በተመለከተ በኒቅያ በጻፉት ቀኖና በዘጠነኛው አንቀጽ አንዱም አንዱ ኤጲስ ቆጶስነት ሊሾም ቢሻ፣ የሀገሩ ሰዎች ቢፈቅዱለት፣ የሀገሩ ጳጳስ ካልፈቀደለት ኤጲስ ቆጶስነት መሾም አይገባውም ይህን አፍርሶ ቢገኝ ሲኖዶስ ያወግዘዋል፤ ሹመቱም ይቀራል” ብለዋል፡፡ ይህም በዚህ ወቅት ከቀኖና ቤተ ክርስቲያን ውጭ የጥንታዊት፣ ሐዋርያዊት፣ ብሔራዊትና ዓለም አቀፋዊት ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲየን ሕጋዊ ቅዱስ ሲኖዶስ ሉዓላዊ ስልጣን በመጋፋት በድፍረት ተፈጸመ የተባለው ሹመት አስቀድሞ በአበው ቅዱሳን የተወገዘ ነው፤ - ከዚህም ጋር ሲመተ ኤጲስ ቆጶሳት በሚፈጸምበት ጊዜ፣ ያለ ቅዱስ ፓትርያርኩ ፈቃድ ማንም ወደ ቤተ መንግሥት እንዲሔድ ቀኖና ቤተ ክርስቲያን አይፈቅድም፡፡ ይህንንም የተላለፈ ቢኖር ከጳጳሳና ከኤጲስ ቆጶሳት ማንም ማን ሊቀጳጳሳቱ ሳይፈቅድለት ወደ ንጉሥ ቤት አይሒድ ወለኲሉ ዘዐለወ ዘንተ ሲኖዶስ ያወግዞ ይህን ትእዛዝ ያፈረሰውን ሲኖዶስ ያወግዘዋል” ተብሎ ስለተወሰነ ዛሬም ከቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ እና ከቅዱስ ፓትርያርኩ ውጭ የሚደረግ ማናቸውም እንቅስቃሴ ሕገወጥ በመሆኑ በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዘዋል፤ - በቀኖና ቤተ ክርስቲያን … ሰው ሁሉ ማዕርጉን ጠብቆ ይኑር እንጅ፣ አንዱ ወደ አንዱ ማዕርግ አይተላለፍ፤ ይህን የሠራነውን ሥርዐት ያፈረሰውን ሰው ሲኖዶስ ያወግዘዋል ተብሎ በተጻፈው መሰረት እነዚህ ሕገወጥ አካላት በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዘዋል፤ - በሕገ ቤተ ክርስቲያን አንቀጽ 16 ንዑስ ቁጥር 30 የአጲስ ቀጶሳት መሾም አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ፣ በቤተ ክርስቲያን ቀኖና መሠረት እንዲመረጡና እንዲሾሙ የመወሰን ሥልጣን የቅዱስ ሲኖዶስ መሆኑን የሚደነግገውን ክፍል በግልጽ የጣሰ በመሆኑ፤ - በሕገ ቤተ ክርስቲያን አንቀጽ 37 ንዑስ ቁ.1 የኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ የሚፈጸመው ኤጲስ ቆጶሳት እንዲሾሙ አስፈላጊ መሆኑ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ሲታመንበትና ሲወሰን ብቻ እንደሚፈጸምና መደንገጉ፤ - በሕገ ቤተ ክርስቲያን አንቀጽ 18 ንዑስ ቁጥር 5 የቤተ ክርስቲያንን ሃይማኖታዊ ሕግጋትንና ቀኖናን የሚያፋልስ ሊቀ ጳጳስ /ኤጲስ ቆጶስ/ ከአባልነት እንደሚሰረዝ በመደንገጉ፤ ቅዱስ ሲኖዶስ አውግዟቸዋል፡፡ በአጠቃላይ የተፈጸመው ሕገ ወጥ ተግባር በሕገ ሰብእም ሆነ በሕገ እግዚአብሔር ሚዛን የተወገዘ ከመሠረተ እምነት የተለየ፣ በአበው ቀኖና፣ በሕገ ቤተ ክርስቲያን እና በቤተ ክርስቲያን አስተዳደር በአጠቃላይ ተቀባይት የሌለው ነው፡፡ ስለዚህ 1ኛ. በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ንኡስ አንቀጽ 138 መሠረት ጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት በሶዶ ዳጩ ወረዳ ሐሮ ባለወልድ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ፩ኛ. አባ ሳዊሮስ 2ኛ. አባ ኤዎስጣቴዎስ 3ኛ. አባ ዜና ማርቆስ የቤተ ክርስቲያንን ቀኖና በመጣስ ባልተሰጣቸው ስልጣን 26 ኤጴስ ቆጰሳትን ሾመናል፤ ሲኖዶስ አቋቁመናል በማለት በማኅህበራዊ እና በብሮድካስት ሚዲያዎች በሰጡት መግለጫ የተረጋገጠ በመሆኑ በዚሁ ድርጊታቸው በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭው ዓለም የሚኖረውን ሕዝበ ክርስቲያንን በማታለል የክህደት እና የኑፋቄ ተግባር በመፈጸማቸው በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ አውግዞ፤ ከቤተ ክርስቲያን የተሰጣቸውን ከዲቁና ጀምሮ ያለው ሙሉ ሥልጣነ ክህነት በመሻር አውግዞ ለይቷቸዋል፡፡ በመሆኑም፡- ሀ. ሥልጣነ ክህነታቸውና የማዕረግ ስማቸው በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ውሳኔ የተነሣ ስለሆነ ከዛሬ ጥር 18 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በቀድሞ ዓለማዊ ስማቸው እንዲጠሩ፤ ለ. በቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ አገልግሎት ዙርያም በሕይወትም ሆነ በሞት ማናቸውንም መንፈሳዊ አገልግሎት እንዳያገኙ ቅዱስ ሲኖዶስ አውግዞ ከቤተ ክርስቲያን ለይቷቸዋል፡፡ ሐ. በነዚህ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ አውግዞ በለያቸው ግለሰቦች ይመሯቸው በነበሩ አህጉረ ስብከት መንፈሳዊ አገልግሎት በማከናወን ሀገረ ስብከቱን የሚመሩ ብፁዐን አባቶችን ፩. ለደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ፪. ለኬንያ፤ኡጋንዳ፤ታንዛኒያ እና ሩዋንዳ ሀገረ ስብከት ፫. ለኢሉ አባቦራ እና በኖ በደሌ ሀገረ ስብከት ፬. በሰሜን አሜሪካ ለሜኒሶታ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት ፭. ለጉጂ፤ምዕራብ ጉጂ እና ቦረና ሊበን ዞኖች ሀገረ ስብከት ፮. ለምስካዬ ኅዙናን መድኃኒዓለም ገዳም በአባትነት የሚመሩ አበው ሊቃነ ጳጳሳት እንዲመደቡ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ወስኗል፡፡  ይሁን እንጅ ከላይ በስም ተጠቅሰው የተወገዙት ግለሰቦች በሠሩት የቀኖና ጥሰት ተጸጽው ይቅርታን ቢጠይቁ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን የምህረት ደጆች ሁል ጊዜ ክፈት መሆናቸውና በቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረት የምንቀበላቸው መሆኑን ቅዱስ ሲኖዶስ ያሳውቃል፤ 2. የቅዱስ ሲኖዶሱንና የቤተ ክርስቲያኒቱን ልዕልና በመዳፈር እና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን በመጣስ በተነሳሱ ግለሰቦች አማካኝነት የኤጲስ ቆጶስነት ሺመት አግኝተናል፤ ተሸመናል እያሉ የሚገኙ 25 መነኰሳት በሕገ ወጥ መንገድ ቀኖና ቤተ ክርስቲያንንን ጥሰው የተገኙ በመሆኑ አስቀድሞ ከቤተ ክርስቲያን የተሰጣቸው ከዲቁና ጀምሮ ያለው ሙሉ ሥልጣነ ክህነት ተሽሮ ከዛሬ ጥር 18 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ተወግዘው ከቤተ ክርስቲያን ተለይተዋል፡፡ 3. ከነዚሁ ግለሰቦች መካከል አንዱ የሆኑት አባ ጸጋዘአብ አዱኛን ከቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ ምልዐተ ጉባኤ ስብሰባ በፊት የቀኖና ጥሰቱንና ሕገ ወጥ አድራጎቱን በመረዳትና በመጸጸት ድርጊቱን በመቃወም ለቤተ ክርስቲያኒቱ ባቀረቡት የይቅርታ አቤቱታ መሠረት ቅዱስ ሲኖዶሱ ይቅርታውን የተቀበላቸው ሲሆን እንደሳቸው ሁሉ ከላይ የተወገዙት 25 ግለሰቦች በሠሩት የቀኖና ጥሰት ተጸጽው ይቅርታን ቢጠይቁ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን የምህረት ደጆች ሁል ጊዜ ክፈት መሆናቸውና በቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረት የምንቀበላቸው መሆኑን እንገልጻለን

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በፍትሕ መንፈሳዊ እንዲሁም በሕገ ቤተክርስቲያን አንቀጽ 19 ንዑስ ቁጥር 3 አስቸኳይና ድንገተኛ ጉዳይ ሲያጋጥም ምልዓተ ጉባኤ እንደሚያደርግ በተደነገገው መሠረት ጥር 18 ቀን 2015 ዓ.ም. ባካሄደው አስቸኳይ ምልዓተ ጉባኤ በቤተ ክርስቲያኒቷ ላይ በተፈጠረው ወቅታዊ የሃይማኖት፣ የቀኖና እና የአስተዳደራዊ ጥሰቶችን አስመልክቶ ውሳኔዎች አሳልፏል፡፡ ጥንታዊት፣ ሐዋርያዊትና ዓለም አቀፋዊት የሆነች ቅድስት ቤተክርስቲያን ሕዝብና አሕዛብን፣ ሰውና መላእክትን፣ ፍጡራን እና ፈጣሪን ይልቁንም በሰውና በእግዚአብሔር መካከል ያለውን ልዩነት አጥፍቶ የሰው ልጅ ሁሉ በቋንቋ፣ በቀለምና በጐሣ ሳይከፋፈሉ በአንድነት ሀብተ ወልድና ስመ ክርስትና አግኝተው ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ ከማህፀነ ዮርዳኖስ የተወለዱ በማየ ገቦ የተጠመቁ የቤተ ክርስቲያን ልጆች እንዲሆኑ ልዩነት የሌለባትን ዘለዓለማዊት መንግሥተ እግዚአብሔር እንዲወርሱ በደመ ክርስቶስ የተመሠረተች ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በየዘመናቱ የተነሣባትን ፈተና ሁሉ አልፋ ከእኛ ዘመን ደርሳለች፤ ምንም እንኳ ከቅዱሳት መጻሕፍትም ሆነ ከኦርቶዶክስ ትምህርተ ሃይማኖት ፈጽሞ በተለየ ሁኔታ ቤተ ክርስቲያንን በጐሣና በቋንቋ የመለየት ሂደት በዓለም አቀፍ ደረጃ እንግዳ ክስተት ቢሆንም ቤተ ክርስቲየን ከሃይማኖታዊና መንፈሳዊ ጠባይዋ በተለየ፣ ታሪኳንና ሥርዓቷን በማይመጥን፣ ከሕግ መንፈሳዊ፣ ከሕግ ጠባይአዊ እና ከሕገ አእምሮ በወጣ መልኩ የደረሰባት ጥቃት፣ እና የመፈንቅለ ሲኖዶስን ተግባር ቅዱስ ሲኖዶስን እጅግ አሳዝኖታል፤ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በታሪኳ ውስጥ ለሀገር አንድነት፣ ለፍትሕ፣ ለጥበብ፣ ለሕዝብ ትስስር፣ ለማኅበራዊ ዕድገት፣ ለጤና፣ ለሥነ-ምግባር መሠረት እና ዐምድ፤ ምሰሶ እና ማገር ሆና በዓለም አቀፍ ደረጃ የተፈራች፣ የተከበረች እና የተወደደች፤ ዕሴቷ እና ዕምቅ የዕውቀት ሀብቷ በምሁራን የታወቀ፣ በትምህርተ ዓለም ሳይቀር የተቀረጸ፤ በእውነተኛ ሊቃውንት የተመሠከረ፣ ቅርሶቿ የተመዘገቡላት ስትሆን፤ በቅርቡ ራስዋ በሾመቻቸው በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር ከፍተኛውና ሐዋርያዊ ተልእኮ እንዲወጡ አደራ በተሰጣቸው ሊቃነ ጳጳሳት መሠረተ እምነትን፣ ሃይማኖታዊ ቀኖናን፣ የአስተዳደር ሥርዓት ሁሉ በጣሰ፣ መንገድ በማኅበረሰብ ዕድገትና አስተዳደር ውስጥ ከሕዝብ ጋር የቆመች፣ ከፖለቲካ የጸዳች መንፈሳዊና ሕዝባዊት ተቋምነቷን በመካድ ከፍተኛ የሆነ ሕገ ወጥ ድርጊት፣ ተቋምን የመናድና መዋቅሯን የማፍረስ ተግባር ተከናውኗል፡- በዚሁ መሠረት፡- ጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት በሶዶ ዳጡ ወረዳ ከወሊሶ ከተማ ወጣ ብሎ በሚገኘው አሮ ባለ ወልድ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተፈጸመውን እጅግ አሳዛኝ እና ኢ-ሲኖዶሳዊ የሆነ አስነዋሪ፤ ሕገ ወጥ የቀኖና ቤተ ክርስቲያን ጥሰት አስመልከቶ ቅዱስ ሲኖዶስ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት አስቸኳይ የምልዐተ ጉባዔ አድርጓል፤ ቅዱስ ሲኖዶስም በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር ያሉ መላው አህጉረ ስብከት፤ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት አስተዳደር ጉባዔ፣ የሊቃውንተ ጉባኤ፤ የሕግ አገልግሎት መምሪያ፤ በዓለም አቀፍና ሀገር አቀፍ ደረጃ ያሉ የወጣቶች እና የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት፣ መንፈሳውያን ማኅበራት፤ የምእመናን እና አገልጋዮች ኅብረት፣ ሁሉም ኦርቶዶክሳውያን በደብዳቤ፣ በሚዲያ እና በአካል ከሰጡት ምክረ ሐሳብ እና የአቋም መግለጫ በመነሣት፤ በሀገር ውስጥ እና በውጪው ዓለም የሚገኙ የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ወዳጆች፣ በተለይም የግብጽ እስክንድርያ ኮፕቲክ ኦርቶዶከስ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕጋዊ ፓትርያርክ ውጭ የሚደረግ ሢመትን እንደማይቀበሉና ዕውቅና እንደማይሰጡ በላኩት የአቋም መግለጫ፣ የኤርትራ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ፣ የሕንድ ማላንካራ ኦርቶዶከስ ቤተ ክርስቲያን፣ እና የሌሎች አኀት ኦርቶዶከስ አብያተ ክርስያናት፣ የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት፣ ዓለም አቀፍ መንፈሳዉያን ተቋማት፣ የልማት እና የበጎ አድርጎት አጋር ድርጅቶች፤ ድርጊቱን በማውገዝ የማይቀበሉት መሆኑን የአቋም መግለጫ በመላክ ባሳዩት አጋርነት፤ አስቀድሞ እንደተገለጸው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በደመ ክርስቶስ ከተመሠረተችበት ጊዜ ጀምሮ ያለፈተና የኖረችበት ጊዜ እንደሌለ ቅዱሳት መጻሕፍትና የታሪክ መዛግብት ሲመሰክሩ በዘመነ ሐዋርያት ቢጽ ሐሳውያን፣ በዘመነ ሊቃውንት የተለያዩ መናፍቃን፣… በየጊዜው እየተነሡ ሲፈታተኗት ኑረዋል፡፡ አሁንም በግልጽ እንደሚታየው ከውጭም ከውስጥም በተደራጁ ምንደኞች በመፈተን ላይ ትገኛለች፡፡ ለዚህም ጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም. በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት፣ በሶዶ ዳጩ ወረዳ፣ ሀሮ በዓለ ወልድ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በአባ ሳዊሮስ መሪነት እጅግ አሳዛኝ ኢ-ሲኖዶሳዊ የሆነ አስነዋሪ፣ ሕገ-ወጥ፣ የቀኖና ቤተ ክርስቲያን ጥሰት አንዱ ሲሆን፤ በአባ ሳዊሮስ መሪነት የተፈጸመው የቀኖና ቤተ ክርስቲያን ጥሰት ፳፮ መነኰሳትን ከቀኖና የወጣ ሢመት በመስጠትና ሊቃነ ጳጳሳት በሚመሯቸው አህጉረ ስብከት በሕገ ወጥ መንገድ በመመደብ ከቀኖና ቤተ ክርስቲያን ጥሰት አልፎ ሃይማኖትን የሚከፋፍል፤ የሀገር አንድነትን የሚሸረሽር እና የሚያፈርስ፣ ምእመናንን ከምእመናን፣ ካህናትን ከካህናት፣ ሊቃውንትን ከሊቃውንት ወጣትን ከወጣት … የሚያጋጭና ደም የሚያፋስስ ፀጥታን የሚያናጋ መሆኑን ቅዱስ ሲኖዶስ ተገንዝሟል፤ በመሆኑም፤ - ከላይ እንደተገለጸው ሐዋርያት በሦስተኛው ቀሌምንጦስ በሃያ አምስተኛው አንቀጽ “በአውራጃው ሁሉ ያሉ ኤጲስ ቆጶሳት አለቃቸው ማንም እንደሆነ ማወቅ ይገባቸዋል፡፡ አለቃ ያድርጉት፤ ያለ ፍቃዱ ጥቃቅኑንም ደጋጉንም ሥራ ምንም ምን አይሥሩ፤ እርሱም ዳግመኛ ኤጲስ ቆጶሳቱ ሳይፈቅዱ ደጋጉን ሥራ አይሥራ ጥቃቅኑን ቢሠራ እዳ የለበትም፡፡ ሁሉም እንደ አንድ ልብ መካሪ፣ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ፣ ሁነው በአንድነት ይኑሩ” ብለው ወስነዋል፡፡ እነዚህ ሕገ ወጥ አካላት ይህን የሐዋርያት ቀኖናን በመሻራቸው፡፡ - ሁለተኛም በአርባ አራተኛው አንቀጽ “ሊቀጳጳሳት (ፓትርያርክ) ኤጲስ ቆጶሳት በተሾሙባቸው አገሮች የሚሠሩትን ሥራ፣ የሚያዙትን ትእዛዝ ይመርምር፡፡ የማይገባ ሥራ ሠርተው፣ የማይገባ ትእዛዝ አዝዘው፣ ቢያኝ ለውጦ የተገለጸለትን ትእዛዝ ይዘዝ፡፡ እርሱ ለሁሉ የሹመት አባታቸው ነውና፤ እነሱም ልጆቹ ናቸውና…” ብለዋል፡፡ ይህን ኢ-ቀኖናዊ ሥርዐተ ሲመት የፈጸሙት ግለሰቦች በሕገወጥ መንገድ በአደባባይ የቅዱስ ሲኖዶስን ሉዓላዊ ሥልጣን እና የቅዱስ ፓትርያርኩን መብት በመጣሳቸው፡፡ - ሢመተ ክህነትን በተመለከተ “ወአልቦ ዘይነሥእ ክብረ ለርእሱ ዘእንበለ ዘጸውዖ እግዚአብሔር … እንደ አሮን በእግዚአብሔር ከተጠራ በቀር ማንም ለራሱ ክብርን የሚወስድ የለም” (ዕብ 5፤4) እንደሚለው የእግዚአበሔር ቃል ከዲቁና ጀምሮ እስከ ፓትርያርክ ሹመት ድረስ ያለው ሹመት በመጀመሪያ ከእግዚአብሔር መጠራቱን የሚጠይቅ ሲሆን እንኳንስ ለተሿሟዎች ለመራጮችና ለአስመራጮች በቀኖና ቤተ ክርስቲያን የተወሰነ፣ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መስፈርት ያለው፣ መሆኑ ለሁሉም ግልጽ ነው፡፡ ይህንም ቅዱስ ጳውሎስ በጻፈው መልእክቱ በሰፊው ገልጾታል፡፡

የዛሬው የቅዱስ ሲኖዶስ የጸሎት መርሐግብር በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ተከናውኗል። ከብጹዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ በፎቶ
+4
የዛሬው የቅዱስ ሲኖዶስ የጸሎት መርሐግብር በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ተከናውኗል። ከብጹዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ በፎቶ