ch
Feedback
የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)

前往频道在 Telegram

ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።

显示更多
2 635
订阅者
无数据24 小时
+157
+5530
帖子存档
ጥቅምት 8 በዚህ ቀን ታላቁ አባት አባ አጋቶን መታሰቢያው ነው፡፡ ይህ ቅዱስ ታላቅ ጻድቅ ገዳማዊና የእግዚአብሔር ሰው ሲሆን አንደበቱን ከክፋት ይከለክል ዘንድ ለ30 ዓመታት ድንጋይ ጐርሶ ኖሯል። ይህንን ቅዱስ አባት  ሊቃውንት ሲገልጹት "ክምረ ክምር ጽድቁ እስከ አስተርአየ" ይሉታል። ትእግስቱ ደግነቱ አርምሞው ትሩፋቱ ከመነገር በላይ ነው። በነበረበት በ4ኛው መቶ ክ/ዘመንም እንደ ኮከብ ያበራ ታላቅ አባት ነው። ታላቁ ገዳማዊ አባት አባ አጋቶን የታላቁ መቃርዮስ የመንፈስ ልጅ ነው። ገዳመ አስቄጥስ እልፍ አእላፍ ቅዱሳንን ስታፈራ ይህ አባት ቅድሚያውን ይይዛል። ምንም በብዛት የሚታወቀው በአርምሞው (በዝምታው) ቢሆንም ባለ ብዙ ትሩፋት አባት ነው። የሚገርመው የቀደሙ አባቶቻችን የፈለገውን ያህል መናኝ ቢሆኑም የሰው ጥገኛ መሆንን አይፈልጉም። "ሊሠራ የማይወድ አይብላ" የሚለውን መለኮታዊ ትዕዛዝ መሠረት አድርገው ከተጋድሎ በተረፈቻቸው ሰዓት ሥራ ይሠራሉ። አንዳንዶቹ እንደሚመስላቸው ምናኔ ሥራ መፍታት አይደለምና ሰሌን ዕንቅብ ሠፌድ የመሳሰለውን ይሠፋሉ።  አባ አጋቶንም በአንደበቱ ድንጋይ ጐርሶ በእግሮቹ ቀጥ ብሎ ቆሞ እንቅቦችን ይሠፋ ነበር። ቅዱሱ የሰፋውን ወደ ገበያ ይዞ  ይወጣል በጠየቁትም ዋጋ ሽጦት አንዲት ቂጣ ይገዛል። የተረፈውን ገንዘብ ግን እዚያው ለነዳያን አካፍሎት ይመጣል እንጂ ወደ ገዳሙ አይመልሰውም። አንድ ቀን እንደልማዱ የሠፋቸውን እንቅቦች ተሸክሞ ወደ ገበያ ሲሔድ መንገድ ላይ አንድ የኔ ቢጤ ወድቆ ያገኛል። እንደ ደረሰም ስመ እግዚአብሔር ጠርቶ ይለምነዋል። አባ አጋቶን ከእንቅቦቹ ውጪ ምንም ነገር አልነበረውምና "እንቅቡን እንካ" አለው። ነዳዩ ግን ወይ የሚበላ ካልሆነም ገንዘብ እንደሚፈልግ ይነግረዋል። ወዲያው ደግሞ "የምትሠጠኝ ነገር ከሌለህ ለምን ወደ ገበያ ተሸክመህ አትወስደኝም?" አለው። የነዳዩ አካል እጅግ የቆሳሰለ በመሆኑ እንኩዋን ሊሸከሙት ሊያዩትም የሚከብድ ነበር። ጻድቁ ግን ደስ እያለው ያለማመንታት አንስቶ ተሸከመው። ከረጅም መንገድ በኋላ ከገበያ በመድረሳቸው አውርዶ ከጐኑ አስቀመጠው። ያ ነዳይ አላፊ አግዳሚውን ሁሉ ቢለምንም የሚዘከረው አጣ። አባ አጋቶን አንዷን እንቅብ ሲሸጥ "ስጠኝ?" ይለዋል። ጻድቁም ይሠጠዋል። እንዲህ "ስጠኝ" እያለ የእንቅቦቹን ዋጋ ያ ነዳይ ወሰደበት። አባ አጋቶን ግን ምንም ቂጣ ባይገዛም በሆነው ነገር አልተከፋምና ሊሔድ ሲነሳ ነዳዩ "ወደ ቦታየ ተሸክመህ መልሰኝ" አለው። አባቶቻችን ትእግስታቸው ጥግ የለውምና ጐንበስ ብሎ በፍቅር አንስቶት አዘሎት ሔደ። ካነሳበት ቦታ ላይ ሲደርሱ ይወርድለት ዘንድ ጻድቁ ቆመ። ነዳዩ ግን አልወርድም አለ። ትንሽ ቆይቶ ግን ለቀቀው ሊያየው ዞር ቢል መሬት ላይ የለም። ቀና ሲል ግን ያየውን ነገር ማመን አልቻለምና ደንግጦ በግንባሩ ተደፋ። ነዳይ መስሎ እንዲያ ሲፈትነው የነበረው ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ነበርና ክንፎቹን ዘርግቶ በብርሃን ተከቦ በግርማ ታየው ከወደቀበትም አነሳው። "ወዳጄ አጋቶን ፍሬህ ትእግስትህ ደግነትህ ግሩም ነውና ዘወትር ካንተ ጋር ነኝ" ብሎት ተሰወረው፤ ጻድቁም በደስታ ወደ በዓቱ ሔደ። አባ አጋቶን ተረፈ ዘመኑን በአርምሞ ኑሮ ዐርፏል። የአባታችን በረከት በሁላችንም ላይ ጸንቶ ይኑር። አሜን። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12

በብዙ የማሚያተርፉበት መርሐግብር በሰባቱ ምስጢራት ዙርያ ሲደረግ የነበረው የረቡዕ ውይይት ስለተጠናቀቀ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ነገ ረቡዕ 12:00 በአዲስ ርዕስ ይጀመራል። ኑ እንመካከር እንወያይ
በብዙ የማሚያተርፉበት መርሐግብር በሰባቱ ምስጢራት ዙርያ ሲደረግ የነበረው የረቡዕ ውይይት ስለተጠናቀቀ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ነገ ረቡዕ 12:00 በአዲስ ርዕስ ይጀመራል። ኑ እንመካከር እንወያይ ለየእለቱ እንቅስቃሴያችን ስንቅን እንያዝ።

ጥቅምት_5 አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ (ገብረ ሕይወት) የዕረፍታቸው መታሰቢያ አቡነ_ገብረ_መንፈስ_ቅዱስ (ገብረ ሕይወት) ጻድቁ የተወለዱት ግብፅ (ንሒሳ አካባቢ) ሲሆን አባታቸው ስምዖን እናታቸው አቅሌስያ ይባላሉ። አባታችን ገብረ ሕይወት የጻድቃን አለቃ የቅዱሳን የበላይ ተጋድሎአቸውና ድንቅ ተአምራቸው እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ቅዱስ ሰው ናቸው። የጻድቁን ክብር መናገር የሚችል ምን አንደበት ይኖራል? እንደ ምንስ ባለ ብራና ይጻፋል? ዜናቸውንስ ለመስማት የታደለ እንደ ምን ዓይነት ሰው ይሆን? አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስ ለ562 ዓመታት በዚህች ዓለም ሲኖሩ እህል ያልቀመሱ /ምግባቸው ምስጋና ነውና/ ልብስ ያልለበሱ /ጠጉር አካላቸውን ይሸፍን ነበርና/ ሐዋርያዊ ሆነው ከግብፅ እስከ ኢትዮዽያ ብዙ ነፍሳትን ያዳኑ አባት፤ ሃገራችንን አስምረው አስራት እንድትሆናቸውም ተቀብለው ምድረ ከብድ አካባቢ አርፈዋል። ጻድቁ ገብረ መንፈስ ቅዱስም ገብረ ሕይወትም ይባላሉ። በ562 ዓመታት ሕይወታቸው እንደ ሐዋርያት ከምድረ ግብፅ እስከ ኢትዮዽያ ወንጌልን ሰብከዋል። በዚህም በሚሊዮን (አእላፍ) ለሚቆጠሩ ነፍሳት የድኅነት ምክንያት ሆነዋል። ጻድቁ እንደ ሰማዕታትም ከከሃዲ ሰዎች ብዙ መከራን ተቀብለዋል። እንደ ባሕታውያን ለብዙ መቶ ዓመታት ሰው ሳያዩ ቆይተዋል። ለየት የሚለው ግን የጽድቅ ሕይወታቸው ነው፤ ከእልፍ አዕላፍ አጋንንት ጋር ተዋግተው ድል ማድረግ ችለዋልና። የንሒሳው ኮከብ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ለኢትዮጵያ ልዩ ፍቅር አላቸው። ስለ ሃገሪቱና ሕዝቧ ፍቅር ሲሉ ለ100 ዓመታት በደብረ ዝቋላ መከራን ተቀብለዋል። ምሕረትን ሲለምኑ ሥጋቸው አልቆ በአጥንታቸው ቁመው ነበርና ሃገራችን አሥራት ሆና ተሰጠቻቸው። ስለዚህም ነው በሃገሪቱ ውስጥ ከ2,000 በላይ የጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳማትና አድባራት ዛሬም ድረስ ያሉት። በ8ኛው ክ.ዘ አካባቢ የተወለዱት አባታችን ያረፉት በ14ኛው መቶ ክ.ዘ አካባቢ ነው። ፍጥረታትን ሁሉ አዘው መጋቢት 5 ቀን ሲያርፉ ግሩማን መላእክት ገንዘው አካላቸውን ሠውረዋል። ሥላሴን የተሸከመ አካላቸው በጐልጐታ ተቀብሯል የሚሉም አሉ። "ሰላም ለመቃብሪከ ዘኢተከሥተ ለባዕድ: ከመ መቃብሩ ለሙሴ ወልደ ዮካብድ: ዜና መቃብሪከሰ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ጸማድ: ቦ ዘይቤ በኢየሩሳሌም አጸድ: ወቦ ዘይቤ ኀለወ በከብድ።" እንዲል። ጻድቁ አባታችን አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ እረፍቱ መጋቢት 5 ቀን ነው ይህ ደግሞ በታላቁ ዓብይ ጾም ወቅት ነው ፍትሃ ነገስት አንቀጽ 15 ላይ በዓብይ ጾም በዓል ማክበር ይከለክላል የሀዘን ወቅት ነውና ከበሮ አይመታም እልልታና ጭብጨባ የለም ፍጹም ሀዘን እንጂ የመጋቢት 27 ስቅለት ጥቅምት 27 ቀን እንደሚከበረው ሁሉ ወደ ጥቅምት 5 ቀን ተዛውሮ እንዲከበር ተደረገ፡፡ የጻድቁ ገብረ መንፈስቅዱስ በረከት በሁላችንም ላይ ይደር።  ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ የአሜሪካ የሕክምና ቆይታቸውን አጠናቀው ወደ አገራቸውና ወደ መንበረ ክብራቸው በሰላም ተመለሱ። *** ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃ
+7
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ  የአሜሪካ የሕክምና ቆይታቸውን አጠናቀው ወደ አገራቸውና ወደ መንበረ ክብራቸው በሰላም ተመለሱ። *** ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በሰሜን አሜሪካ ሲያደርጉት የቆዩትን ሕክምና አጠናቀው ዛሬ ማለዳ ወደ አገራቸውና ወደ መንበረ ክብራቸው በሰላም ተመለሱ። ቅዱስ ፓትርያርኩ ዛሬ ማለዳ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት  ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የኒውዮርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት መምሪያ ኃላፊዎች፣ ክቡር መልአከ ሕይወት አባ ኃይለ ገብርኤል ነጋሽ የቅዱስ ፓትርያርኩ ልዩ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ፣ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ደማቅ አቀባበል አድርገውላቸዋል። በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳምም ለቤተ ክርስቲያንና ለቅዱስነታቸው ክብር የሚመጥን የእንኳን ደህና መጡ መርሐ ግብር ተከናውኗል። ቅዱስ ፓትርያርኩ ወደ አሜሪካ ያቀኑት ከአንድ ዓመት በፊት ተይዞላቸው በነበረ የሕክምና ቀጠሮ ምክንያት ነው። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12

የሐዘን መግለጫ የሰንበት ት/ቤታችን አባል የሆነው የወንድማችን ሐብቶም ገብሩ ባለቤት ከዚህ ዓለም ድካም ያረፈች በመሆኑ የቀብር ሥነ_ሥርዓቱ ነገ 01/02/2016ዓ.ም ከቀኑ 8:00 - 9:00 ድረስ በደብረ ገሊላ ቅዱስ አማኑኤል ቤተክርስቲያን የሚፈፀም ስለሆነ የምንችል በሰዓቱ ተገኝተን የሐዘኑ ተካፋይ በመሆን እንድናጽናናቸው ይሁን ቅዱስ እግዚአብሔር የእህታችንን ነፍስ ይማርልን ለወንድማችንም መፅናናቱን ያድልልን፡፡

በሰንበት ት/ቤታችን ወጣት ክፍል በክረምቱ ወቅት እንዲሁም በመደበኛ መርሐ ግብር መንፈሳዊ ትምህርቶችን ሲማሩ የነበሩ 125 ተማሪዎች መስከረም 27/2016 ዓ.ም በድምቀት አስመርቃለች። ቅዱስ እግዚአ
+2
በሰንበት ት/ቤታችን ወጣት  ክፍል በክረምቱ ወቅት እንዲሁም በመደበኛ መርሐ ግብር መንፈሳዊ ትምህርቶችን ሲማሩ የነበሩ 125  ተማሪዎች መስከረም 27/2016 ዓ.ም በድምቀት አስመርቃለች።  ቅዱስ እግዚአብሔር አምላካችን በምግባር በሃይማኖት ያጽናልን። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12

ለብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ጥቅምት 1 ቀን 2016 ዓ.ም በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ገዳም አቀባበል ይደረግላቸዋል ። *** መስከረም 29 ቀን 2016 ዓ.ም """"""""""""""""""""""""""""" አዲስአበባ -ኢትዮጵያ ****** ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ነሐሴ 27ቀን 2015ዓ.ም ለሕክምና ወደ አሜሪካ ማቅናታቸው ይታወሳል። በዚህም መሰረት በአገረ አሜሪካን ሲያደርጉት የሰነበቱትን ሕክምና አጠናቀው ጥቅምት 1 ቀን 2016 ዓ.ም ወደ አገራቸውና ወደ መንበረ ክብራቸው የሚመለሱ በመሆኑ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት ሰባት አባላት ያሉት ኮሚቴ ተቋቁሞ ለአቀባበሉ ስኬታማነት አስፈላጊውን ሥራ ሁሉ በማከናወን ላይ ይገኛል። ስለሆነም ቅዱስነታቸው ሕክምናቸውን ጨርሰው በሰላም ወደ ሀገራቸውና ወደ መንበረ ክብራቸው መመለሳቸውን በማስመልከት ጥቅምት 1ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 1:00 ሰዓት ላይ በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ዶ/ር የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የኒዩዎርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የጠቅላይ ቤተክህነት የየመምሪያው ኃላፊዎች፣ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሥራ ኃላፊዎች፣ የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች፣ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን፣ወጣት የሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች፣ ምዕመናን በተገኙበት የአቀባበል መርሐ ግብሩ የሚካሔድ ስለሆነ በሰዓቱ በመገኘት ከቅዱስነታቸው በረከት እንድትቀበሉ መንፈሳዊ ጥሪአችንን እያስተላለፍን ይህ የአቀባበል መርሐ ግብር የቤተክርስቲያናችንንና የቅዱስ ፓትርያርኩን ክብር በሚመጥን መልኩ በደመቀ ሁኔታ መከናወን ይቻል ዘንድ የአዲስ አበባ አድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች፣ወጣት የሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎችና ማኅበራት ሰዓቱን በማክበር ተገኝታችሁ ለቅዱስነታቸው ያላችሁን አባታዊ ክብር እንድትገልጹና አባታዊ ቡራኬ እንድትቀበሉ የቅዱስ ፓትርያርኩ አቀባበል ኮሚቴ ጥሪውን በማክበር ያስተላልፏል። ምንጭ:- የ/ኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12

ናሁ አስተርአየ ጽጌ እንደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ  ከመስከረም ፳፮ እስከ ኅዳር ፮ ያለው ወቅት ወርኃ ጽጌ (የጽጌ/የአበባ ወር) ይባላል፡፡ በወርኃ ጽጌ አበባዎች ያብባሉ ፍሬም ያፈራሉ በዚህም ወቅት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን፣ ይጠብቃት ዘንድ ከታዘዘው አረጋዊው ዮሴፍ ጋር ስትኖር መልኳ አንዳንድ ጊዜ እንደ ጽጌረዳ አበባ ቀይ ሁና፣ በሌላ ጊዜ ደግሞ እንደ ሮማን አበባ ነጭ ሁና ስትታየው፣  ቀይ የነበረው መልኳ ተለውጦ እንደ ሮማን አበባ ጸዓዳ ነጭ፣ ነጭ የነበረው እንደ ጽጌረዳ አበባ ቀይ ሆኖ  ሲለወጥ በመደንገጥ እርሷ መሆኗን ለማረጋገጥ ‹‹ማርያም›› ብሎ እየጠራ ያረጋግጥ ነበር፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስለዚህ ምሥጢር ሲያስረዳ ‹‹መልኳ እንደ ጽጌረዳና እንደ ሮማን አበባ ይለዋወጥበት ስለነበር በአንድ ዓይነት መልክ አላወቃትም›› ብሏል፡፡ በዚህም ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እመቤታችንን በአበባ፣ ጌታችንን ደግሞ በፍሬ እየመሰሉ ለማመስገንና ለማወደስ በሚያስችል ምሥጢር የስደቱ ጊዜ በወርኃ ጽጌ እንዲዘከር አድርገዋል፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለዘለዓለሙ የማይደርቀውን የሕይወት ፍሬ ኢየሱስ ክርስቶስን ያስገኘችልን ንጽሕት እና  የማትጠወልግ አበባ ናት፡፡ ጌታችን ኢየሱስም ከተወለደ ሁለት ዓመት ሲሞላው በዘመኑ የነበረው  ንጉስ ሔሮድስ ሕፃኑ ክርስቶስን ሊገድለው ስለፈለገ መልአኩ ‹‹ተነሳና እናቱንና ብላቴናውን ይዘህ ወደ ግብፅ ሽሽ›› ብሎ  ለዮሴፍ ነገረው፡፡ እመቤታችንም ከዮሴፍ ጋር ልጇን ይዛ ወደ ግብፅ ተሰደደች፡፡ ከጨካኙ ንጉሥ ሔሮድስ ሽሽትም እመቤታችን ልጇን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ይዛ  ወደ ግብፅና ኢትዮጵያ ተሰደዱ። በግብፅ በረሃ ሲጓዙም እመቤታችን ወደ ትዕማን ቤት ሄዳ ነበር፡፡ የቤቱ እመቤት ባየቻት ጊዜ ‹‹ከየት መጣሽ? ብላ ጠየቀቻት፤ እመቤታችንም ‹‹ከይሁዳ ምድር የተሰደድኩ ስደተኛ ነኝ›› ብላ መለሰችላት፡፡ ‹‹አንቺ ሴት ደረቅ ነሽ መሰለኝ፤ በድርቅናሽ ቤትሽን ትተሽ ትዞርያለሽ፤ እንዳንቺ ያለች ቆንጆ ሴት ከአዳራሽ ወደ ዕልፍኝ ይላል እንጂ ሀገሩን ትቶ ሀገር ለሀገር አይንከራተትም›› ብላም ተተናኮለቻት፡፡ አረጋዊው ዮሴፍም ‹‹ለለማኝ ቢኖር ይሰጡታል፤ ባይኖር ደግሞ ካለበት ያድርስህ ይባላል እንጂ እንዲህ እንደ ፍላፃ ልብ የሚወጋ ነገር ይናገሩታልን ›› ብሎ በተናገራት ጊዜ ያቺ ኮቲባ የተባለችው የእመቤቲቱ ገረድ ‹‹ይህ  ሽማግሌ ደፍሮ እመቤቴን እንዲህ ይመልስላታል?›› ብላ ዮሴፍን በጥፊ ቃጥታ ሕፃኑን ደግሞ ነጥቃ ጣለችው፡፡ በዚያን ጊዜም ሕፃኑ ኢየሱስም አለቀሰ፤ እመቤታችን እርሱን ተከትላ ምርር ብላ አለቀሰች፤ ልታነሳውም በምትሞክርበት ጊዜ ዮሴፍ ‹‹ተይው፤ አምላክነቱ ይገለጽ›› ብሎ ከለከላት፡፡ ወዲያውኑ ትዕማንን ከገረድዋ ኮቲባ ጋር መሬት ተከፍቶ ዋጣቸው፡፡ ከዚህም በኋላ  ስድስት ወር ያህል እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከልጇና ከዮሴፍ እንዲሁም ከሰሎሜ ጋር በዚያ ቤት ከተቀመጡ በኋላ እመቤታችን ልጇን እንዳይገሉባት በማሰብ ዱር ለዱር ተንከራተተች ፡፡ በበረሃ ሲጓዙ ሁለት ወንበዴዎች አገኟቸው፡፡ የለበሱትን አልባሳት ገፈውም ወሰዱባቸው፤ ወንበዴዎቹም በመቀጠል ምን ማድረግ እንዳለባቸው ቊመው ሲማከሩ እመቤታችን ልጇን የሚገድሉባት መስሏት አለቀሰች፡፡ ሆኖም ግን ጥጦስ የተባለው አንዱ ወንበዴ ካደረበት ፍቅርና ርኅራኄ የተነሣ ‹‹እነዚህ ሰዎች አሳዘኑኝ! ወደዚህ ቦታ የመጡት ያለ ምክንያት አይሆንምና እንተውላቸው›› ብሎ ልብሳቸውን መለሰላቸው፤ በጉዟቸውም አገዛቸው ፡፡ ከዚህም በኋላ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሕፃኑ ልጇን ይዛ ወደ ኢትዮጵያ ተጓዘች፤ ኢትዮጵያውያንም  በፍቅር ሳስተው ተቀብለው አሳረፏቸው፤ እንዲያውም አንዳንዶቹም ቤታቸውን በመልቀቅ አስተናገዷቸዋል፡፡ ብዙዎችም ‹‹ደም ግባቱ ከሰው ልጆች ሁሉ ያምራል›› ተብሎ የተነገረለትን የጌታችንን መልክ በማየት ብቻ ለማመን በቅተዋል፡፡ አንዳንድ ሰይጣን ያደረባቸው ሰዎች ቢያጋጥሟቸውም በበረሃ ውስጥ የሚኖሩ ሽፍታዎችም ለጌታችን ያሳዩት ርኅራኄና ፍቅር የተለየ ነበር፡፡ እመቤታችን በኢትዮጵያውያን ደግነትና ፍቅር በመደሰቷ ጌታችን ኢትዮጵያን በእመቤታችን ምልጃ አስጠበቃት፤ የዐሥራት ሀገርም አድርጎ ሰጣት፡፡ ለፍቅሩ ሳስተው ለተቀበሏቸው ኢትዮጵያውያንና ግብፃውያንም የግብፅንና የኢትዮጵያን ገዳማት ባረከላቸው፡፡ እመቤታችንም ከልጇ ጋር በግብፅ ለሦስት ዓመት ከስድስት ወር በስደት ኖራለች፤ ንጉሥ ኄሮድስም ከሞተ በኋላ የእግዚአብሔር መልአክ በሕልሙ ‹‹የሕፃኑን ነፍስ የሚሹት ሞተዋልና ተነሣ፤ ሕፃኑንና እናቱንም ይዘህ ወደ እስራኤል ሀገር ተመለስ›› አለው፡፡ አረጋዊው ዮሴፍም እመቤታችንንና ልጇ ኢየሱስን ይዞ ወደ እስራኤል ተመለሰ፡፡  እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጋር በበረሃ መሰደዷን እያሰብንና ከዓይኗ በፈሰሰው ዕንባ ብዛት ቸርነትና ምሕረትን እንድታሳስብልን የአምላካችን እግዚአብሔር ፍቃድ በመሆኑ ይህንን በማሰብ ወርኃ ጽጌን በጾምና በጸሎት እንማልዳለን፡፡ ጾሙ የፈቃድ ቢሆንም የእመቤታችንን ስደት እያሰብን እንጾማለን፡፡ ከጾሙ በረከት ያሳትፈን። ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/finotebirhan12 የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12