1 474
订阅者
无数据24 小时
-37 天
-2130 天
帖子存档
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በመደመር መንግሥት ዕይታ ፣ የዘርፎች እመርታ የ3ኛ ዙር የከተማዋ ሰልጣኞች የልማት ስራዎች ጉብኝት::
በአዲስ አስተሳሰብ ፣ በአዲስ የስራ ባህል እየተመራች የምትገኘው አዲስ አበባ በአዲስ የለውጥ ምዕራፍ ውስጥ ትገኛለች።
ለረጅም ዘመናት በጥልቅ ጉስቁልና ውስጥ የኖረችው ከተማችን በመፍጠር እና በመፍጠን በተሰሩ አበረታች ስራዎች ለነዋሪዎቿ ምቹ ለጎብኚዎቿ ተመራጭ መሆን ጀምራለች ።
"በመደመር መንግስት እይታ የዘርፎች እመርታ " በሚል ርዕስ ሲሰለጥኑ የቆዩ የሶስተኛ ዙር የአዲስ አበባ ሰልጣኝ አመራሮች በከተማችን የተሰሩ ፕሮጀክቶችን መጎብኘት ጀምረዋል።
ነዋሪዎች ባሉበት ሆነዉ አገልግሎት ማግኛት የሚችሉበት የተቀናጀ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ዲጂታል ስርአት
Jiraattoonni bakkuma jiran ta'anii tajaajila argachuu kan ittiin danda'an sirna dijitaalawaa galmeessa siivilii fi tajaajila jiraattummaa qindaa'aa.
በዛሬው እለት ህዳር 26 ቀን 2018 ዓ.ም በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 09 ከቀኑ 9:45 ሰአት ላይ ሀዲድ ገበያ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ በንግድ መኖሪያ ቤቶች ላይ ተከስቶ የነበረዉ የእሳት አደጋ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር ውሏል ።
የእሳት አደጋው የተከሰበት ቦታ ለአደጋ መቆጣጠር ስራ ምቹ ያልሆነ ፣ ቤቶቹ የተገነቡበት ግብዓቶች ፈጣን ተቀጣጣይ ከሆኑ ከቆርቆሮና ከእንጨት የተገነቡ በመሆኑ እሳቱ ተስፋፍቶ የከፋ ጉዳት ሳያደርስ በፍጥነት መቆጣጠር መቻሉን የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።
የእሳት አደጋው መንስኤ በፖሊስ እየተጣራ ሲሆን በሰው ላይ ምንም አይነት ጉዳት አልደረሰም ።
ኮሚሽኑ አሁን ያለንበት ወቅት ሞቃታማና ነፋሻማ የአየር ንብረት ለእሳት መከሰትና መባባስ አስተዋጽኦ የሚያደርግ በመሆኑ ህብረተሰቡ እሳትና የኤሌክትሪክ ኃይል ምንጮችን ሲጠቀም ከወትሮው የተለየ ጥንቃቄ እንዲያደርግ አሳስቧል ።
ለእሳትና ለሌሎች ድንገተኛ አደጋዎች እንዲሁም ለአንቡላንስ አገልግሎቶች በ939 ፈጥነዉ ያሳዉቁ!
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
በመጪው ሰኞ በይፋ አገልግሎት መስጠት የሚጀምረው አዲሱ የተቀናጀ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ዲጂታል ስርአት ባለጉዳዮች የምባይል ስልካቸውንና የተለያዩ የቴክኖሎጂ አማራጮችን በመጠቀም በአካል ሳይገኙ ባሉበት ሆነው አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል ከመሆኑ በተጨማሪ ፈጣን፣ቀልጣፋና ከብልሹ አሰራር የጸዳ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ነው።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
በአዲስ አበባ በአገልግሎት አሰጣጥም እንደ ሌሎችም የልማት ስራዎቻችን ሁሉ እምርታ ለማምጣት በትኩረት እየሰራን እንገኛለን !
ከትናት በስቲያ የገቢዎች የደረሰኝ ቁጥጥር በባለሙያዎች ዩኒፎርም ላይ የተገጠመ ድምፅና ምስል የሚወስድ የካሜራ ቴክኖሎጂ መጠቀም መጀመራችን ይታወቃል።
ዛሬም የሲቪል ምዝገባና የነዋሪዎች አገልግሎት አሰጣጥን ይበልጥ የሚያዘምን አዲስ የተቀናጀ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ዲጂታል ስርአትን አስጀምረናል።
አዲሱ ሲስተም ባለጉዳዮች የምባይል ስልካቸውን፣ የተለያዩ የቴክኖሎጂ አማራጮችን በመጠቀም በአካል ሳይገኙ ባሉበት ሆነው አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችል፣ የግዴታ ፎርም መሙላትን የሚያስቀር፣ በኢምግሬሽን፣ በጤና፣ በፍርድ ቤት፣ በብሄራዊ መታወቂያ እና በሎሎችም በተቋማት መካከል ቅንጅት እና መናበብን የሚፈጥር ፣ የመታወቂያ አሰጣጥ ላይ ያለ ባለፋይሉ ባለቤት ይሁንታ ለማንም በእርሱ የቤት ቁጥር መታወቂያ እንዳይሰጥ መቆጣጠር የሚያስችል እና ሌሎችም በርካታ ዝርዝር አገልግሎቶችን አጣምሯል።
ስራ ላይ የዋለው የ Civil Registration and Vital Statistics with ID ሲስተም ከዚህ ቀደም በወረቀት ይሰጡ የነበሩ የተለያዩ እንግልቶችን የሚያስቀር፣ ብልሹ አሰራርን በመከላከልና ግልጽነትን በማምጣት ረገድ የጀመርነውን ሰፊ ስራ ይበልጥ ውጤታማ የሚያደርግ ነው ።
ይህንን ወሳኝ ቴክኖሎጂ በአጭር ጊዜ ላበለፀገው ለኢትዮዽያ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲቲዩት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ወርቁ ጋቸናን እና የኢንስቲቲዩቱን ባለሙያዎች፣ እንዲሁም የሲቪል ምዝገባና የነዋሪዎች ኤጀንሲ ሀላፊዎችና ሰራተኞችን በራሴና በከተማችን ነዋሪዎች ስም ከልብ አመሰግናለሁ ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ !
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
የቀድሞ የፓንአፍሪካ አቀንቃኝ መሪዎች ቤተሰቦች የዓድዋ ድል መታሰቢያን እየጎበኙ ነው
የቀድሞ የፓንአፍሪካ አቀንቃኝ መሪዎች ልጆች እና ቤተሰብ አባላት የዓድዋ ድል መታሰቢያን እየጎበኙ ይገኛሉ።
የዓድዋ ድል መታሰቢያን እየጎበኙ ከሚገኙ የቀድሞ የፓንአፍሪካ አቀንቃኝ መሪዎች ቤተሰብ አባላት መካከል የኩዋሚ ንክሩማ፣ የጁሊየስ ኔሬሬ፣ የኮለኔል ሙዓመር ጋዳፊ ቤተሰብ አባላት ይገኙበታል።
በአፍሪካ ለመጀመሪያ ጊዜ በአዲስ አበባ በተካሄደው የአፍሪካ ሚድያ አዋርድ ተሳታፊ የነበሩት ልዑካኑ በአዲስ አበባ የተገነቡ እና በመገንባት ላይ ያሉ የልማት ሥራዎችን እየጎበኙ ነው።
አዲስ አበባ በዘርፈ ብዙ አበርክቶዋ የአፍሪካ ሚዲያ ሽልማትን እንድታስተናግድ ተመርጣ ኃላፊነቷን በብቃት እየተወጣች ትገኛለች።
በፈጣን የለውጥ ጎዳና ላይ ያለችው የአፍሪካ መዲናዋ አዲስ አበባ በታሪክ የመጀመሪያ የሆነው የፓን-አፍሪካ የሚዲያ ሽልማትን ከትላንት ጀምሮ እያስተናገደች ሲሆን፣ ሥነ-ሥርዓቱ ዛሬ ምሽት ፍጻሜውን እንደሚያገኝ ይጠበቃል።
አዲስ አበባ የ2025 የአፍሪካ ሚዲያ ሽልማትን (AMA) ለማስተናገድ የተመረጠችው በነበራትና አሁንም ይበልጥ አጠናክራ ባስቀጠለችዉ ፈርጀ _ብዙ አበርክቶዋ ሲሆን ከተማዋ የአህጉሪቱ ዲፕሎማሲያዊ ዋና ከተማ ከመሆኗም በላይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ባሳየችው ከፍተኛ ለውጥ ምክንያት ነው ተብሏል።
በተጨማሪም ኢትዮጵያ የአፍሪካ ነጻነት ተምሳሌት እና የፓን-አፍሪካኒዝም ማጠንጠኛ በመሆኗ፣ በአፍሪካ የነጻነት አባቶች ልጆች እና በአፍሪካ ሕብረት ብሮድካስቲንግ ትብብር የተዘጋጀውን የመጀመሪያ መርሐ-ግብር ለማስተናገድ ትክክለኛዋ ምርጫ መሆናም ታዉቋል።
አዲስ አበባ ባለፉት ሁለት ዓመታት በሠራችው ሥራ ከዓለም አቀፍ ከተሞች ጋር የሚወዳደር ለውጥ እያመጣች በመሆኗ በዚህ ምክንያትም በርካታ ዓለም አቀፍ ኮንፈረንሶችን እንዲሁም የአፍሪካ ሕብረት ጉባኤዎችን ጨምሮ የተለያዩ አፍሪካን የተመለከቱ መድረኮች፤ የመላው አፍሪካ ጋዜጠኞች፣ የሚዲያ ሥራ አስፈፃሚዎች እና የፖለቲካ መሪዎች በደንብ የሚያውቋት መሰብሰቢያቸው ጭምር መሆን በመቻሏ ለዛሬዉ ታሪካዊ መድረክ ለማስተናገድ በቅታለች።
በሌላ በኩልም ከመላው አህጉሪቱ እና ከተለያዩ የዓለም አካባቢዎች የሚመጡ ሰዎችን በምቾት የሚያተናግደው የኢትዮጵያ አየር መንገድ መገኛ አዲስ አበባ መሆኗ የሽልማቱ እጩዎች እና የሚዲያ ባለሙያዎች እንዲመርጧት ያስቻላት መሆኑም ታዉቋል።
ሽልማቱ ትክክለኛ የአፍሪካ ፍላጎት መገለጫ እንዲሆን የታሰበ ሲሆን፣ አዘጋጆቹ ይህን መስፈርት የምታሟላ እና የፓን አፍሪካ መነሻ የሆነችው አዲስ አበባ እንደሆነች በመተማመን ዝግጅቱ በአዲስ አባባ እንዲካሄድ ያደረጉ እዉነታዎች ናቸዉ ተብሏል።
በውድድሩ ከ40 ሀገራት የተውጣጡ ከ800 በላይ የሚዲያ ባለሙያዎች በተለያዩ ዘርፎች የተሳተፉ ሲሆን፣ ታዋቂ ፖለቲከኞች፣ የአፍሪካ ነፃት አባቶች ልጆች እና የዋና ዋና መገናኛ ብዙኃን ሥራ አስፈፃሚዎች የዝግጅቱ ታዳሚዎች ናቸው።
የአፍሪካ ሕብረት ብሮድካስቲንግ፣ የፓትሪስ ሉሙምባ ፋውንዴሽን፣ የክዋሜ ንክሩማህ ፋውንዴሽን፣ የምዋሊሙ ኒዬሬሬ ፋውንዴሽን፣ የኬኔት ካውንዳ ሌጋሲ ፋውንዴሽን፣ የሲሱሉ ፋውንዴሽን ለማኅበራዊ ፍትህ እና የፒኤልኦ ሉሙምባ ፋውንዴሽን ከዝግጅቱ ዋና አጋሮች መካከል እንደሆኑም ተረጋግጧል።
ከ800 ተወዳዳሪዎች መካከል ሃያ አንዱ እጩዎች በተለያዩ ምድቦች ዛሬ ምሽት አሸናፊውን ይፋ ለሚያደርገው ፍጻሜ የደረሱ ሲሆን የአፍሪካ ሚዲያ ሽልማት በጋዜጠኝነት፣ በብሮድካስቲንግ፣ በዲጂታል ሚዲያ እና በትርክት ግንባታ የአፍሪካ ስኬቶችን ያሳዩ የሚዲያ ተወካዮች በአንድነት የሚሳተፉበት እና የሚሸለሙበት ተብሏል።
የሽልማት ዝግጅቱ አፍሪካውያን ስለማንነታቸው እና የአፍሪካ ሕዝቦችን ደማቅ ማንነት በራሳቸው እንዲተርኩ የሚያስችላቸውን ዕድል እንደሚከፍትላቸው የሁነቱ አጋር የሆነው አር.ቲ መዘገቡ ታዉቋል።
ደረቅ ቆሻሻን መልሶ በመጠቀምና ዑደት በማድረግ ሀብት እንዴት መፍጠር እንደሚቻል የሚያሳይ አውደርእይ ተከፈተ።
"ደረቅ ቆሻሻ በአግባቡ ከተያዘ ሀብት ነው" በሚል መሪ-ቃል የየካ ክፍለ ከተማ ጽዳት አስተዳደር ጽ/ቤት በስሩ ያሉ ወረዳዎችን፣ ት/ቤቶችን እና የፈጠራ ባለሙያዎችን ያሳተፈ የመልሶ መጠቀምና ዑደት ማድረግ ኢግዚቪሽንና ፎቶ አውደ-ርዕይ ለዕይታ አቅርቧል።
የኤግዚብሽኑ ዋና አላማ ደረቅ ቆሻሻ በአግባቡ ከተያዘ ሀብት መሆኑን ማሳያና ለበርካታ ወጣቶችና ሴቶች በስራ እድል ተጠቃሚ በማድረግ የኢኮኖሚ ገቢን ለመፍጠር የሚያስችል መሆኑ በመድረኩ ተገልፅዋል።
ኤግዚሽኑን በክብር እንግድነት ተገኝተው መርቀው የከፈቱት የአዲስ አበባ ከተማ ፅዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ገዛኸኝ ዴሲሳ እንደተናገሩት ይህ ኤግዚቢሽን ቆሻሻን በአግባቡ ከተጠቀምን የጤና ጠንቅ ሳይሆን ትልቅ ሀብት መሆኑን ትልቅ ማሳያ እንደሆነ ጠቁመው ይህም ከወዳደቀ ቆሻሻ የእለት ከእለት መጠቀሚያ ሊሆኑ የሚችሉ የቤት እቃዎች መስራትና ጥቅም ላይ ማዋል እንደሚቻል ማረጋገጫ ነው ሲሉ ገልፀዋል።
አቶ ገዛኸኝ አክለውም ባሳለፍነው ዓመት ደረቅ ቆሻሻን ወደ ሃብትነት ከመቀየር አኳያ 106 ሺህ ቶን ደረቅ ቆሻሻን ወደ መልሶ መጠቀምና ኡደት በማድረግ በዘርፉ የተሰማሩ አካላት ከ1.6 ቢሊዮን ብር ገቢ ማገኝታቸውን አስታውሰው በተመሳሳይም በያዝነው በጀት የሩብ አመት ከደረቅ ቆሻሻ ከ515 ሚሊዮን ብር በላይ መገኘት መቻሉን ጠቁመዋል።
ከተማችን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በርካታ የስራ እንቅሳቀሴ ውስጥ መሆኗን የገለፁት አቶ ገዛኸኝ ከእነዚህም የስራ እንቅስቃሴዎች መካከል አንዱ ከተማዋን ፅዱ : ውብና ለኑሮ ተስማሚ የማድረግ ስራ ነው ብለዋል።
የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ፍፁም ኃይሌ በበኩላቸው የካ ክፍለ ከተማን የብልፅግና ከፍታ ማሳያ ተምሳሌትነት የማድረግ ራዕይ እውን የሚሆነው ቆሻሻን ወደ ሀብትነት በመቀየር እና አካባቢውን ለነዋሪዎች ምቹ ማድረግ ሲቻል በመሆኑ ይህንን ለማሳካት በጋራ መስራት ይገባል ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
የካ ክፍለ ከተማን የብልፅግና ከፍታ ማሳያ ተምሳሌት የማድረግ ራዕይ ስኬታማ እንዲሆን የደረቅ ቆሻሻ መልሶ መጠቀም ስራን ማሳደግ እንደሚገባ አቶ ፍፁም ኃይሌ አሳስበዋል።
ቆሻሻን መልሶ መጠቀም ጥሬ ዕቃዎችን ከማውጣት ጋር ተያይዞ የሚመጣውን የተፈጥሮ ሀብት ብክነትና የኢነርጂ ፍጆታ በእጅጉ ይቀንሳል፤ ይህም ለዘላቂ ልማት ትልቅ አስተዋጽኦ የሚያደርግ መሆኑን የክፍለ ከተማው የፅዳት አስተዳደር ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ከፍያለው ተሾመ ገልፀዋል።
በዓውደ ርዕዩ ላይ እንደ ፕላስቲክ ፣ ብረታ ብረት፣ ወረቀት እና ጨርቃጨርቅ ያሉ ተጥለው የሚባክኑ ቆሻሻዎች በፈጠራና በእደ ጥበብ ስራዎች አማካኝነት ወደ ተለያዩ የመገልገያ ቁሳቁስነት ተሰርተው ለእይታ ቀርበዋል።
የቆሻሻ መልሶ መጠቀም ሂደት ብዙ ሰዎችን የሚጠይቅ በመሆኑ በስራ ዕድል ፈጠራ ዙሪያ ትልቅ ሚና የሚጫወት መሆኑ በመድረኩ ተገልፆል።
በመርሀ ግብሩ ላይ አመራሮችን ጨምሮ ተማሪዎች፣ የፈጠራ ባለሙያዎች እና ነዋሪዎች ተሳትፈዋል
ህዳር 25/ 2018 አ.ም
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
https://linktr.ee/aacitymanager
ዛሬ 26 ሺህ ቤቶችን ለአገራችን የመጀመሪያ በሆነ የግንባታ ቴክሎጂ በላፍቶ ሳይት ስራ አስጀምረናል።
በዚህ ዓመት ከያዝናቸው ዋነኛ እቅዶች መካከል ቀዳሚው ለከተማችን ነዋሪዎች የቤት አቅርቦትን ተደራሽ ማድረግ ነው።
በመሆኑም በዚህ ዓመት ከ100 ሺህ በላይ ቤቶችን ለመገንባት አቅደን በርካታ ተግባራትን እያከናወንን ሲሆን፣ እቅዳችንን በጥራትና በፍጥነትን እውን ለማድረግ ለአገራችን የመጀመሪያ የሆነውን Cold-Formed Steel (CFS) የግንባታ ቴክኖሎጂን መጠቀም አንድ አማራጭ አድርገን ዛሬ ስራ አስጀምረናል።
ይህ ቴክኖሎጂ በሌላው ዓለም የተለመደ ሲሆን፣ ቤቶችንም ሆነ ህንፃዎችን በፋብሪካ ውስጥ የሚገጣጠሙ ብረቶችን በመጠቀም ወለልን፣ ግድግዳና ጣሪያን ጨምሮ ሁሉንም ክፍል በፍጥነትና በጥራት ማምረት የሚያስችል አሰራር ነው።
የዚህን የቴክኖሎጂ ፋብሪካ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለከተማ የተከልን ሲሆን፣ በፈጠራና ፍጥነት መርህ ግንባታን ከሳይት ወደ ፋብሪካ በመቀየር የግንባታ ፍጥነትን በማሳደግ፣ ወጪን በመቀነስና ጥራትን በማሻሻል አንጻር ተመራጭ ነው።
አስተዳደራችን እንደወትሮው የነዋሪውን ጥያቄ ለመመለስ እና ተጠቃሚነቱን ለማረጋገጥ በጠንካራ የፕሮጀክት ማኔጅመንት፣ ዲስፕሊን እና በ24/7 የስራ መርሃ ግብር ፕሮጀክቱ በጥራትና በፍጥነት ተጠናቅቆ ለታለመለት አላማ እንዲውል ያደርጋል።
ይህን ከከተማችን አልፎ ለአገር ጠቃሚ የሆነ ቴክኖሎጂን ወደ አገር ይዘዉ የመጡትን የሌጋሲ ሆም ድርጅት ባለቤት ኢንጂነር ያሬድ አፈወርቅን በራሴና በከተማ አስተዳደሩ ስም አመሰግናለሁ ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
