ch
Feedback
Addis Ababa City Manager Office

Addis Ababa City Manager Office

前往频道在 Telegram
1 474
订阅者
无数据24 小时
-37 天
-2130 天
帖子存档
አዲስ አበባን እንደ ስሟ ውብ አበባ የማድረግ ስራ የነዋሪዎቿን ኑሮ መለወጥንም ማዕከል ያደረገ ነው። Hojiin Finfinnee akkuma maqaashee abaaboo miidhagduu taasisuun jireenyaa jiraattotaa jijjiiruu giddugaleessa kan godhateedha.

እንኳን ደስ አለን! በእግር ኳስ ስፖርት የጀመርነው ፕሮጀክት ፍሬ በማፍራት ላይ ነው። ዛሬ በመዲናችን አዲስ አበባ ሲካሄድ በነበረው የምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ አገራት ከ17 ዓመት በታች ውድድር፣ ብሔራዊ ቡድናችን የኬንያ አቻውን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት በመርታት ከ 22 ዓመታት በኋላ ለአፍሪካ ዋንጫ ማለፍ ችሏል። ይህ ድል የእግር ኳስ ስፖርት ወዳድ ለሆነው ህዝባችን የዘመናት ቁጭት በቅርቡ መልስ እንደሚያገኝ ያሳየ ነው። ቀይ ቀበሮዎቹ ያስመዘገቡት ውጤት ለዘርፉ የሰጠነው ትኩረት ውጤት እያፈራ መሆኑን ማሳያ ነው። በራሴና በከተማ አስተዳደሩ ስም መላው የቡድኑ አባላትን፣ የኢትዮዽያን ሕዝብ እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እወዳለሁ። ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ! Baga Gammadne! Piroojektiin ispoortii kubbaa miilaatiin eegallee firii buusuu eegaleera. Har'a madiinaa teenya Finfinneetti gaggeeffamaa kan ture dorgommii biyyoota Afrikaa bahaa fi giddugaleessaa umrii 17 gadiitiin, gareen biyyaalessaa biyya keenyaa qixasaa Keeniyaa galchii 3 fi On moo'achuun waggoota 22 booda waancaa Afrikaatiif darbuu danda'eera. Injifannoon kuni uummata keenya ispoortii kubbaa miilaa jaalatuuf gaabbii barootaaf dhiheenyatti deebii akka argatu kan mul'isuudha. Jeedalootni Diddiimoon milkaa'inni galmeessan xiyyeeffannoon damichaaf laanne milkaa'ina galmeessaa jiraachuu mul'istuudha. Maqaa koo fi bulchiinsa magaalichaan miseensota garichaa hunda fi uummattoota Itoophiyaan baga gammaddan jechuun barbaada. Waaqni Itoophiyaa fi Uummata Ishee Haa Eebbisu!

ከአዲስ አበባ የግብር አሰባሰብና የገቢዎች አገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ለሚኖር ማንኛዉም አይነት ቅሬታ መፍታት የሚያስችል አዲስ አሰራር በከንቲባ ፅ/ቤት ስር ተዋቅሯል ። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የገቢዎች ቢሮ ስር የተዘረጋዉ የቅሬታ አፈታት ስርዓት እንደተጠበቀ ሆኖ ባዛ ያልረካ ግብር ከፋይ ከንቲባ ፅ/ቤት ማንኛዉንም አይነት ከገቢ አሰባሰብ ፣ ከሰራተኞች ስነምግባር እና አገልግሎት አሰጣጥ ጋር የሚነሱ የግብር ከፋዮች ቅሬታዎችን ለመፍታት ዘወትር ሐሙስ ኃላፊዎች በተገኙበት የሚደመጥ እና ተጣርቶ ምላሽ የሚሰጥበትን አሰራር ዘርግቷል ። ሁልጊዜም የአገልግሎት አሰጣጡን ለማሻሻል የሚተጋዉ እና ህዝብን አዳምጦ ምላሽ መስጠትን የትኩረት ማእከሉ ያደረገዉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በከንቲባ ፅ/ቤት በሚስጥር ጥቆማ የሚሰጥበትን ነፃ የጥሪ ማእከል 9977 ፣ የሚስጥር ሳጥንን ጨምሮ በተጨባጭ ቅሬታዉን በአካል ለበላይ አመራር ማቅረብ የሚችልበትን አሰራር የፊታችን ሐሙስ ጀምሮ ወደ ተግባር ይገባል ። በመሆኑም ከመጪዉ ሐሙስ ህዳር 25/2018 ጀምሮ ጠዋት ከ 2 ሰአት እስከ 7 ሰአት ድረስ ከገቢዎች ጋር ብቻ የተያያዘን ቅሬታ አመራሩ ተቀብሎ የሚስተናግድ መሆኑን በመረዳት በከንቲባ ፅ/ቤት ተጨባጭ ቅሬታ ያላችሁ ማቅረብ የምትችሉ መሆኑን የከተማዉ አስተዳደር ያሳዉቃል ። አስተዳደራችን ለቀልጣፋ እና ፍትኃዊ አገልግሎት ይተጋል !

በመደመር መንግስት ዕይታ፣ የዘርፎች ዕምርታ | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች የሰጡት ስልጠና:- ክፍል ሁለት https://www.facebook.com/share/14QqEUPwuXW/?mibextid=wwXIfr

ኤጀንሲው በ12ኛው የኢትዮጵያ የጥራት ሽልማት ውድድር " ከፍተኛ የአድናቆት ደረጃ" ተሸላሚ ሆነ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ተወዳዳሪ አገልግሎት ሰጪ ተቋም መሆን እንዲችል በ12ኛው የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ውድድር ላይ የተሳተፈ ሲሆን በዚሁ መሰረት በታላቁ ቤተ-መንግስት በተዘጋጀው የእውቅና መድረክ የከፍተኛ የአድናቆት ደረጃ / Award of Special Honorbale Certificate / ተሸላሚ ሆኗል። ተቋሙ ለህዝብ የሚሰጠውን አገልግሎት ለማሻሻል ከተለመደው አሰራር በመውጣት ተወዳዳሪ ሊያደርገው የሚችሉ አለም አቀፍ መስፈርትን መሰረት ያደረገ አዲስ ሲስተም እያስለማ የሚገኝና እና ወደ ተግባር ለማስገባት በሂደት ላይ የሚገኝ ሲሆን የተቋሙን አገልግሎት አሰጣጥ ጥራት በማምጣት የተገልጋዩን እርካታ ለመጨመር ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ ተነግሯል። ኤጀንሲው በ12ኛው ሃገር አቀፍ የጥራት ሽልማት ውድድር ላይ አመልክተው ከተወዳደሩ እና የደረጃውን እውቅና ካገኙ ጥቂት ድርጅቶች ብቸኛ የመንግስት አገልግሎት ሰጪ ተቋም በመሆን የደረጃዉን እዉቅና ያገኘ ሲሆን በዉድድሩ በማመልከት፣ መመዘኛዎችን በመሙላት እንዲሁም የተሰሩ ስራዎች የመስክ ምልከታ ሂደትን ጭምር አልፏል። ተቋሙ በህዝብ የተመሰከረለት ጥራት ያለው አገልግሎት የሚሰጥ ተቋም ሆኖ ማየት እስኪቻል የሃገር አቀፍ የጥራት ሽልማት ውድድር ተሳታፊ ሆኖ እንደሚቀጥል በዕለቱ ሽልማቱን ተገኝተው የወሰዱት የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮሴፍ ንጉሴ የተናገሩ ሲሆን ውድድሩን የመንግስት ተቋማት በስፋት እንዲሳተፉና የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራት ደረጃቸዉን እንዲፈትሹ፤ እንዲያሻሽሉ እንዲሁም ዓለም አቀፍ የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደትን እንዲያቁ የሚያስችል የዉድድር ዓይነት መሆኑን ገልፀዋል። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

ዛሬ በከተማችን በተለያየ ደረጃ የሚገኙ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ጎብኝተናል። ባለፉት የለውጥ ዓመታት በጥቃቅንና አነስተኛ አደራጅተን በዘርፉ የስራ እድል የፈጠርንላቸው እና በግላቸውም በተፈጠረው ምቹ ሁኔታ ስራ የጀመሩ አምራቾች አሁን ላይ ወደ ኢንዱስትሪ ደረጃ አድገው በአጭር ጊዜ ፍሬያማ እየሆኑ መምጣታቸውን በማየታችን ደስ ብሎናል። በጎበኘናቸው ኢንዱስትሪዎች የተፈጠሩ የስራ ዕድሎች፣ የምርት ሂደት በተለይም በተኪ ምርት እና ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን በማምረት ረገድ እያከናወኑት ያለው ስራ አበረታች ነው። የከተማ አስተዳደራችን ለነባሮቹም ሆነ ለአዳዲሶቹ ኢንዱስትሪዎች ውጤታማነት እያደረገ ያለውን የመስሪያ ቦታ የማቅረብ እና ሁለንተናዊ ድጋፍ በቀጣይም አጠናክሮ ይቀጥላል ። ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ ! Har'a magaalaa keenyatti sadarkaalee garaagaraa irratti kan argaman Industiriilee oomishaa daaw'anneerra. Waggoota jijjiiramaa dabran waldaalee xixiqqaan gurmeessinee damichaan carraa hojii kanneen uumneefi dhuunfaanis haala mijataa uumameen oomishtoonni hojii eegalan amma gara sadarkaa industiriitti guddatanii yeroo gabaabaa keessatti bu'aqabeessa ta'aa dhufuusaanii arguu keenyatti gammadanee jirra. Idustiriiwwan daawwannetti carraaleen hojii uumaman, haalli oomishaa keessattuu oomisha bakka bu'aa fi oomishaalee gabaa alaaf dhihaatan gama oomishuutiin hojiin hojjetaa jiran jajjabeessoodha. Bulchiinsi magaalaa keenyaa milkaa'ina indaastiriiwwan haaraa fi buuleyyiifis taasiaa kan jiru bakka hojii dhiheessuu fi deeggarsa hundagaleessa taasisuu fuuldurattis cimsee itti fufa. Waaqni Itoophiyaa fi Uummataa Ishee Haa Eebbisu!

በመደመር መንግስት ዕይታ፣ የዘርፎች ዕምርታ | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች የሰጡት ስልጠና:- ክፍል ሁለት https://www.facebook.com/share/14QqEUPwuXW/?mibextid=wwXIfr

20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን የሁሉም ኢትዮጵያውያን መሰባሰቢያና የጋራ ድምቀት በሆነችው በመዲናችን አዲስ አበባ ፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ክቡር አቶ አገኘሁ ተሻገር፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ክብርት ወይዘሮ ሎሚ በዶ፣ የሁሉም ክልሎች ምክር ቤት አፈ ጉባኤዎች እና ሌሎችም ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት በከተማችን የኢትዮጵያዊያንን ህብረ-ብሔራዊ አንድነት በሚያጎላ መልኩ በደማቅ ሥነ-ሥርዓት፣ ውብና ታሪካዊ ሆኖ በተገነባው አራዳ ፓርክ በአዲስ አበባ ደረጃ አክብረናል። የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀንን በመዲናችን “ዴሞክራሲያዊ መግባባት ለህብረ ብሔራዊ አንድነት" በሚል መሪ ቃል ስናከብር፣ የሁለንተናዊ ብልፅግና ጉዟችንን መሰረት መገንባትን ይበልጥ የምናረጋግጥበት እና በብዝሃነት ደምቀን አንድነታችንን በሚያጠናክር መልኩ ነው። ኢትዮጵያችን ታይታ የማትጠገብ፤ ምድረ ቀደምት፤ የብዙ ባህልና ቅርስ ሀብቶች እንዲሁም የጀግንነት ታሪክ ባለቤት በመሆኗ ከትውልድ ወደ ትውልድ ታፍራና ተከብራ እንድትኖር እጅ ለእጅ ተያይዘን መትጋታችንን አጠናክረን እንቀጥላለን። ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ! ከንቲባ አዳነች አቤቤ

የኤጀንሲው የሰራተኞች የቁጠባና ብድር ማህበር በይፋ ተመሰረተ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ከማዕከል እስከ ወረዳ የሚገኙ ሰራተኞች በጋራ በመሆኑ ያቋቋሙት የሰራተኞች የገንዘብ የቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር የምስረታ ጉባኤው አካሂዷል፡፡ በማህበሩ የምስረታ ጉባኤ ላይ በቢሮ ኃላፊ ማዕረግ ምክትል ዋ/ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ይመኙሻል ታደሰ ባስተላለፉት መልዕክት ኤጀንሲው በከተማችን የተሻለ አገልግሎት የሚሰጥ፣አዳዲስ ሀሳቦችን እና አሰራሮችን የሚያመነጭ ተቋም መሆኑን በመጥቀስ የተመሰረተው የሰራተኞች የገንዘብ የቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ከሀሳብ ወደ ተግባር የመጣ ድርጅት ነው ሲሉ ገልፀዋል፡፡የተጀመረውን የቁጠባ እና ብድር ማህበር ወደ ኢንቨስትመንት በመለወጥ እና በማሳደግ የሰራተኛውን ህይወት ለመለወጥ የተደረገ ፈር ቀዳጅ ስራ መሆኑንም አክለዋል፡፡ የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮሴፍ ንጉሴ በበኩላቸው ሰራተኛው ራሱን በኢኮኖሚ እንድገነባ ለማድረግ የኤጀንሲው አንዱ የሪፎርም አካል ተደርጎ ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ ካለን ቆጥበን በጋራ በመተሳሰብ የተሻለ ነገን ለመፍጠር እንሰራለን ሲሉ ተናግረዋል፡፡ በቢሮ ኃላፊ ማዕረግ ምክትል ዋና ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ይመኙሻል ታደሰ፣የህብረት ስራ ኤጀንሲ የተለያዩ ኃላፊዎች፣የኤጀንሲው የቀድሞ ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮናስ አለማየሁ እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የተገኙበት እና በምረታው ከ1ሺ745 ሰራተኞች በመስራችነት በተካፈሉበት የኤጀንሲው ሰራተኞች የገንዘብ የቁጠባና ብድር ማህበር በጉባኤው የማህበሩን የተለያዩ የሥራ አስፈፃሚ አካላት በመምረጥ በሙሉ ድምፅ አፅድቋል፡፡ ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

የኤጀንሲው የሰራተኞች የቁጠባና ብድር ማህበር በይፋ ተመሰረተ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ከማዕከል እስከ ወረዳ የሚገኙ ሰራተኞች በጋራ በመሆኑ ያቋቋሙት የሰራተኞች የገንዘብ የቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር የምስረታ ጉባኤው አካሂዷል፡፡ በማህበሩ የምስረታ ጉባኤ ላይ በቢሮ ኃላፊ ማዕረግ ምክትል ዋ/ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ይመኙሻል ታደሰ ባስተላለፉት መልዕክት ኤጀንሲው በከተማችን የተሻለ አገልግሎት የሚሰጥ፣አዳዲስ ሀሳቦችን እና አሰራሮችን የሚያመነጭ ተቋም መሆኑን በመጥቀስ የተመሰረተው የሰራተኞች የገንዘብ የቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ከሀሳብ ወደ ተግባር የመጣ ድርጅት ነው ሲሉ ገልፀዋል፡፡የተጀመረውን የቁጠባ እና ብድር ማህበር ወደ ኢንቨስትመንት በመለወጥ እና በማሳደግ የሰራተኛውን ህይወት ለመለወጥ የተደረገ ፈር ቀዳጅ ስራ መሆኑንም አክለዋል፡፡ የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮሴፍ ንጉሴ በበኩላቸው ሰራተኛው ራሱን በኢኮኖሚ እንድገነባ ለማድረግ የኤጀንሲው አንዱ የሪፎርም አካል ተደርጎ ሲሰራ መቆየቱን በመጥቀስ ካለን ቆጥበን በጋራ በመተሳሰብ የተሻለ ነገን ለመፍጠር እንሰራለን ሲሉ ተናግረዋል፡፡ በቢሮ ኃላፊ ማዕረግ ምክትል ዋና ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ይመኙሻል ታደሰ፣የህብረት ስራ ኤጀንሲ የተለያዩ ኃላፊዎች፣የኤጀንሲው የቀድሞ ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮናስ አለማየሁ እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የተገኙበት እና በምረታው ከ1ሺ745 ሰራተኞች በመስራችነት በተካፈሉበት የኤጀንሲው ሰራተኞች የገንዘብ የቁጠባና ብድር ማህበር በጉባኤው የማህበሩን የተለያዩ የሥራ አስፈፃሚ አካላት በመምረጥ በሙሉ ድምፅ አፅድቋል፡፡ ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager

ንጹህ መንደር፣ንጹህ ብሎክ፣ንጹህ አካባቢና ንጹህ ከተማ በጋራ እንፍጠር ። በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 02 አስተዳደር ነዋሪውን ያሳተፈ የአንድ ማዕከል የጽዳት ንቅናቄ በሳራ አንፖል ቀጠና ተካሄደ።ለነዋሪዎች ፅዱና ምቹ አካባቢ ለመፍጠር የሁሉም ነዋሪ ተሳትፎ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተገልጿል ። በፅዳት ንቅናቄው ላይ የአዲስ አበባ ከተማ ጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ምክትል ዳሬክተር አቶ ሙላት ተገኝ ከዚህ በፊት በፅዳት ዙሪያ በተሰራው ግንዛቤ ፈጠራ ስራ ህብረተሰቡ ጋር የተሻለ አመለካከት መፈጠሩን ገልፀው አሁንም ፅዳት ከራስ አካባቢ በመጀመር አካባቢያችን ማፅዳት ላይ ትኩረት መደረግ እንዳለበት ተናግረዋል። እንዲሁም በያዝነው ህዳር ወር ቆሻሻ የሚሰበስብና የማይበሰብስ ተብሎ ተለይቶ መሰብሰብ እንዳለበትም ሰፊ የሆነ የግንዛቤ ማጎልበቻ ንቅናቄ ስራው እየተካሄደ መሆኑን ገልጸው ይህንኑ ወደ ተግባር በመተርጎም ቆሻሻን ወደ ሃብት የመቀየሩን ተግባር ማጠናከር ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ጽዳት አስተዳደር ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ ባህሩ አሚን በበኩላቸው የክፍለ ከተማው ነዋሪዎች በጽዳት ንቅናቄ ላይ የሚያደርጉትን ተሳትፎ ከማጠናከር በተጨማሪ መኖሪያቸውንና አካባቢያቸውን ሁልጊዜም በንጽህና በመጠበቅ ጽዳትን ባህል ማድረግ እንደሚገባም ጥሪ አቅርበዋል። በጽዳት ንቅናቄው የወረዳው ጠቅላላ አመራር፣የአካባቢው ነዋሪዎች፣የጽዳት ሰራተኞች፣የባጃጅ ማህበራት ደንብ ማስከበርና ልማታዊ ሴፍቲኔት ተጠቃሚዎች ተሳትፈዋል። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች https://linktr.ee/aacitymanager