ch
Feedback
Isaiah 48 Apologetics

Isaiah 48 Apologetics

前往频道在 Telegram

✟ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ✟ "14 The grace of the Lord Jesus Christ, and the love of God, and the communion of the Holy Ghost, be with you all. Amen." (2Corinthians 13:14) 📌 ሌላኛው ቻናላችን:- @ovadiah

显示更多
6 596
订阅者
-124 小时
+307
+12330
帖子存档
🚩 ከርዕሳችን ጋር ተያያዥነት ያላቸው የቀደሙ ጽሑፎች 1) መንፈስ ቅዱስ:- ከአብ ጋር አንድ መለኮት የሆነው አምላካችን! (በብሉይ ኪዳን) https://t.me/TheTriune/908 2) መንፈስ ቅዱስ አካል/Person እንደ ሆነ ብሉይ ኪዳን አያስተምርምን? https://t.me/TheTriune/586

🚩 ጌታ ቢረዳን በምርጫችሁ መሰረት "ነገረ ሥላሴ በብሉይ ኪዳን" በሚለው እንሄድበታለን

🚩 ቀድሞ 100 የሞላውን እንሄድበታለን

🚩 በየትኛው ርዕስ እንማር?
Anonymous voting

🚩 በየትኛው ርዕስ እንማር?
Anonymous voting

🚩 ይታይ

🚩 ድጋሚ ሲዋሽ ተያዘ በዮሐንስ 1:1 ዙሪያ ለዋሸው ኡስታዝ የተሰጠ ምላሽ https://vt.tiktok.com/ZSXhQ17JK/

🚩 እግዚአብሔር (አብ) የእግዚአብሔር (ወልድ) አባት ነው! ለኦንሊ ጂሰሱ ቄስ የሀሰት ትምህርት የተሰጠ ምላሽ https://vt.tiktok.com/ZSC4YU6FU/

♦️ በዚህ ቦታ ላይ እግዚአብሔር አምላክ "..አወጣጡ ከቀድሞ ጀምሮ ከዘላለም የሆነ.." ብሏል። #አወጣጡ ማለት ምን ማለት ነው? በዚህ ስፍራ ላይ አምላካችን እግዚአብሔር የእስራኤል ገዢ ሆኖ ወደ ፊት የሚነሳው መሲህ አወጣጡ ከቀድሞ ጀምሮ ከዘላለም የሆነ እንደሆነ ተናግሯል። በዚህ ቦታ ላይ "አወጣጡ" የሚለው የዕብራይስጥ ቃል "מוֹצָאֹתָיו/ሞጻቲዮ" የሚለው የዕብራይስጥ ቃል ሲሆን እንደ አገባቡና እንደ አውዱ የተለያየ ትርጉም ሊኖረው ይችላል። ከዚህ ቃል ትርጉሞች አንዱ ውልደት ወይም begetting ነው! በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ይህ ቃል ውልደትን ለማመልከት ጥቅም ላይ ውሏል። ለምሳሌ፦ "ለጌዴዎንም ብዙ ሚስቶች ነበሩትና #ከወገቡ_የወጡ ሰባ ልጆች ነበሩት" (መሳ 8:30) በዚህ ቦታ ላይ ጌዴዎን ብዙ ሚስቶች ስለነበሩት ከወገቡ የወጡ ሰባ ልጆች እንደነበሩት እናነባለን። "..ከወገቡ የወጡት.." ሲል ከእርሱ የተወለዱት ማለት ነው። #የወጡት የሚለው ቃል ውልደትን የሚያመለክት ቃል ነው። እዚህ ክፍል ላይ "..የወጡት.." ተብሎ የተተረጎመው የዕብራይስጥ ቃል "יֹצְאֵי/ያጻይ" የሚለው ቃል ሲሆን (H3318) ሚክ 5:2 ላይ ራሱ ቃል ነው። ስለዚህ ከዚህ በመነሳት ይህ ቃል ውልደትን ሊያመለክት እንደሚችል መረዳት እንችላለን። የKJV ኢንግሊዘኛው ትርጉም "begotten" ብሎ ያስቀመጠው ለዚህ ነው። ይህ #ወጣ ወይም "יֹצְאֵי/ያጻይ" የሚለው ቃል ውልደትን ወይም begetting ሊያሳይ እንደሚችል ያረጋግጣል፦ "And Gideon had threescore and ten sons of his body #begotten for he had many wives" (Judges 8:30) ሌላ ምሳሌ፦ "እግዚአብሔርም ጽኑዓን ኃያላኑንና መሳፍንቱን አለቆቹንም ከአሦር ንጉሥ ሰፈር እንዲያጠፋ መልአኩን ሰደደ። የአሦርም ንጉሥ አፍሮ ወደ አገሩ ተመለሰ። ወደ አምላኩም ቤት በገባ ጊዜ #ከወገቡ_የወጡት ልጆቹ በዚያ በሰይፍ ገደሉት" (2ዜና 32:21) በዚህ ቦታ ላይ ኢየሩሳሌምን መያዝ አቅቶት ወደ ሀገሩ የተመለሰው የአሦር ንጉሥ ሰናክሬም ወደ ሀገሩ አፍፎ ከተመለሰ በኋላ ከወገቡ የወጡት ልጆች እንደገደሉት እናነባለን። "..ከወገቡ የወጡት.." ሲል ከእርሱ የተወለዱት ማለት ነው። #የወጡት የሚለው ቃል ውልደትን የሚያሳይ ቃል ነው። እዚህ ክፍል ላይ "..የወጡት.." ተብሎ የተተረጎመው የዕብራይስጥ ቃል "מִיצִיאֵי/ማይጽያይ" የሚለው ቃል ሲሆን (H3329) ሚክ 5:2 ላይ ያለው ራሱ ቃል ነው። ስለዚህ ከዚህ በመነሳት ይህ ቃል ውልደትን ሊያመለክት እንደሚችል መረዳት እንችላለን። ሌላ ምሳሌ፦ "ከያዕቆብ ጋር ወደ ግብፅ የገቡት ሰዎች ሁሉ #ከጉልበቱ_የወጡት፥ ከልጆቹ ሚስቶች ሌላ፥ ሁላቸው ስድሳ ስድስት ናቸው" (ዘፍ 46:26) በዚህ ስፍራ ላይ መጽሐፍ ቅዱስ ወደ ዮሴፍ መልሶ አባቱን ያዕቆብን ካገኘው በኋላ ወደ ግብፅ ምድር የተመለሱትን የያዕቆብን ልጆች ስም ዝርዝር ይዘረዝራል። ከዚያም የስም ዝርዝራቸውን ከዘረዘረ በኋላ "..ከጉልበቱ የወጡት.." ይላቸዋል። ከጉልበቱ የወጡት ማለት ከእርሱ የተወለዱት ማለት ነው። #የወጡት የሚለው ቃል ውልደትን የሚያመለክት ቃል ነው። እዚህ ክፍል ላይ "..የወጡት.." ተብሎ የተተረጎመው የዕብራይስጥ ቃል "יֹצְאֵי/ያጻይ" የሚለው ቃል ሲሆን (H3318) ሚክ 5:2 ላይ ራሱ ቃል ነው። ስለዚህ ከዚህ በመነሳት ይህ ቃል ውልደትን ሊያመለክት እንደሚችል መረዳት እንችላለን። ሌላ ምሳሌ፦ "ከያዕቆብ #ጕልበት_የወጡት ሰዎች ሁሉ ሰባ ነፍሶች ነበሩ፤ ዮሴፍም አስቀድሞ በግብፅ ነበረ" (ዘጸ 1:5) በዚህ ቦታ ላይም ወደ ግብፅ ምድር የወረዱት አስራ አንዱ የያዕቆብ ልጆችና ከእነርሱ በፊት በግብፅ የነበረው የዮሴፍ ስም ዝርዝር ተዘርዝሮ እንመለከታለን። ስማቸውን ሲዘረዝር "..ጉልበት የወጡት.." ይላቸዋል። ከጉልበቱ የወጡት ማለት ከእርሱ የተወለዱት ማለት ነው። #የወጡት የሚለው ቃል ውልደትን የሚያመለክት ቃል ነው። እዚህ ክፍል ላይ "..የወጡት.." ተብሎ የተተረጎመው የዕብራይስጥ ቃል "יֹצְאֵי/ያጻይ" የሚለው ቃል ሲሆን (H3318) ሚክ 5:2 ላይ ራሱ ቃል ነው። ስለዚህ ከዚህ በመነሳት ይህ ቃል ውልደትን ሊያመለክት እንደሚችል መረዳት እንችላለን። ሌላ ምሳሌ፦ "ዳዊትም አቢሳንና ባሪያዎቹን ሁሉ። እነሆ #ከወገቤ_የወጣው ልጄ ነፍሴን ይሻል፤ ይልቁንስ ይህ የብንያም ልጅ እንዴት ነዋ? እግዚአብሔር አዝዞታልና ተዉት፥ ይርገመኝ" (2ሳሙ 16:11) በዚህ ስፍራ ላይ ንጉሥ ዳዊት የሳኦል ዘመድ የሆነ ሳሚ የሚባል ሰው ይረግመው ዘንድ በጀመረ ጊዜ የተናገረውን ነገር እናያለን። ከወገቤ የወጣው ልጄ (አቤሴሎም) ነፍሴን ይሻል ይልቁንስ ይህ የብንያም ልጅ እንዴት ነዋ?! ይላል። "..ከወገቤ የወጣው ልጄ.." ሲል ከእኔ የተወለደው ልጄ ማለት ነው። #የወጣው የሚለው ቃል ውልደትን የሚያሳይ ቃል ነው። እዚህ ክፍል ላይ "..የወጣው.." ተብሎ የተተረጎመው የዕብራይስጥ ቃል "יֹצְאֵי/ያጻይ" የሚለው ቃል ሲሆን (H3318) ሚክ 5:2 ላይ ራሱ ቃል ነው። ስለዚህ ከዚህ በመነሳት ይህ ቃል ውልደትን ሊያመለክት እንደሚችል መረዳት እንችላለን። ✍️ ስለዚህ በሚክ 5:2 ላይ ይህንኑ ቃል በመጠቀም #አወጣጡ ከቀድሞ ጀምሮ ከዘላለም የሆነ ሲል #ውልደቱ ከቀድሞ ጀምሮ ከዘላለም የሆነ ማለት ነው። ልዩነቱ ከላይ ባየናቸው ምሳሌዎች የሰው ውልደት በጊዜ የተገደበ፥ ስጋዊ፥ የባህርይ አንድነት የሌለው ውልደት ነው። ከቀድሞ ጀምሮ ከዘላለም የሆነው ይህ ወልደ ከአብ የተወለደበት ዘላለማዊ ውልደት ግን እንደ ፍጡራን ሰዎች ያለ ውልደት አይደለም። ምክንያቱም ዘላለማዊ ነው፥ ከዘላለም ጀምሮ የነበረው ደግሞ መለኮት ነው (መዝ 74:12 ዘጽ 3:14) መለኮት ደግሞ መንፈስ ነው (ዮሐ 4:23-24 1ቆሮ 15:45) ደግሞም አንድ ባህርይ ነው (ፊል 2:6 ዘጽ 23:21) ስለዚህ ወልድ ከአብ የተወለደበት ውልደቱ በጊዜ ያልተገደበ ዘላለማዊ፥ ቁስ ያልሆነ መንፈሳዊ ደግሞም የባህርይ አንድነቱን ያማከለ ውልደት ነው። ♦️ ወልድ በዘላለማዊው ውልደት (The Eternal Begetting) ከአብ ከመወለዱ የተነሳ ነው ዓለም ሳይፈጠር በፊት ሆነ በስጋ ከመምጣቱ በፊት የእግዚአብሔር ልጅ የሆነው፦ "ሁሉን ወራሽ ባደረገው ደግሞም #ዓለማትን_በፈጠረበት_በልጁ በዚህ ዘመን መጨረሻ ለእኛ ተናገረን" (ዕብ 1:2) በዚህ ቦታ ላይ ሐዋርያው ጳውሎስ ዓለማትን በፈጠረበት በልጁ በማለት ዓለማት በልጁ ከመፈጠራቸው ባሻገር ዓለማት ሲፈጠሩ እንኳ ልጁ ልጅ እንደነበር ገልጿል። ልጁ እንዴት አለማት ሲፈጠሩም የአብ ልጅ ሆነ ካልን በዘላለማዊው ውልደት ከአብ በመወለዱ ነው። "ከሥጋ የተነሣ ስለ ደከመ ለሕግ ያልተቻለውን #እግዚአብሔር_የገዛ_ልጁን #በኃጢአተኛ_ሥጋ_ምሳሌ በኃጢአትም ምክንያት #ልኮ አድርጎአልና እንደ መንፈስ ፈቃድ እንጂ እንደ ሥጋ ፈቃድ በባንመላለስ በእኛ የሕግ ትእዛዝ ይፈጸም ዘንድ ኃጢአትን በሥጋ ኰነነ" (ሮሜ 8:3-4) በዚህ ቦታ ላይ ሐዋርያው ጳውሎስ እግዚአብሔር የገዛ ልጁን በኃጢአተኛ ስጋ ምሳሌ እንደ ላከ ሲናገር እንመለከታለን። አብ ልጁን በስጋ ከላከው ልጁ በስጋ ከመላኩ በፊትም ልጅ ነበር ማለት ነው። በስጋ ከመላኩ በፊትም ልጅ ባይሆን ኖሮ "..ልጁን በኃጢአተኛ ስጋ ምሳሌ ላከው.." አይልም ነበር። ልጁ በስጋ ከመላኩ በፊትም ልጅ የነበረው በዘላለማዊው ውልደት ከአብ በመወለዱ ነው። ▶️ ይቀጥላል

🚩 የወልድ ዘላለማዊ ውልደት በብሉይ ኪዳን (ክፍል 1) 🚩 The Eternal Begetting of The Son in The Old Testament (Part 1) በመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮና በታሪካዊው ክርስትና ውስጥ የወልድ ዘላለማዊ አስተምህሮ ወይም The Eternal Begetting of The Son የሚባል አስተምህሮ አለ። እርሱም ምንድነው ወልድ በዘላለማዊ ውልደት ከአብ ተወልዷል የሚለው አስተምህሮ ነው። ወልድ ዘላለማዊ እንጂ ጊዜያዊ ባልሆነ፥ መንፈሳዊ እንጂ ቁሳዊ ባልሆነ፥ ያን አንዱን መለኮታዊ ባህርይ ባለያየ ውልደት ከአብ ተወልዷል። ወልድ የአብ ዘላለማዊ ልጅ የሆነው ከዚህ ዘላለማዊ ወልደት የተነሳ ነው። ቀጥለን እንደምንመለከተው ይህ አስተምህሮ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሲሆን ከመጀመሪያው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በነበሩ ክርስቲያኖች ዘንድ የታመነ ነው። ለምሳሌ ከአብያተክርስቲያናት መከፋፈል በፊት በነበረችው በአንዲቷ ቤተክርስቲያን በተካሄደው የኒቂያ ጉባዔ የእምነት መግለጫ ወይም The Nicene Creed ላይ "..begotten of the Father before all ages.." ወይም "..ከዘመናት ሁሉ በፊት ከአብ የተወለደ.." ይላል። ቀጠል አድርጎም "..begotten not created.." ወይም "..የተወለደ እንጂ ያልተፈጠረ.." ይላል። እነዚህ ሀረጎች በሙሉ ወልድ ከአብ የተወለደበትን ዘላለማዊ ውልደቱን የሚያመለክቱ ናቸው። ስለዚህ ይህ ትምህርት በአንዲቱ ቤተክርስቲያን ይታመን የነበረው ጥንታዊው የክርስትና ትምህርት መሆኑን ያሳያል። ከጉባዔውም ባሻገር ከአብያተክርስቲያናት መከፋፈል በፊት የነበሩ የቤተክርስቲያን አባቶች እና አብያተክርስቲያናቱ ከተከፋፈሉ በኋላ የመጡት የሁሉም አብያተክርስቲያናት አባቶች ያስተማሩት ትምህርት ነው። ይህን በስፋት መመልከት የሚቻል ሲሆን ለናሙና ያህል ከክፍፍሉ በፊት የነበሩ ሶስት የቤተክርስቲያን አባቶች በዚህ ጉዳይ ምን እንዳሉ እንመልከት፦ 1) St. Athanasius (296 AD - 373 AD) "..We understand in like manner that The Son is #begotten not from without but #from_The_Father.." (Discourse against the Arians, Discourse 2:33) 1) ቅዱስ አትናቴዎስ (296 AD - 373 AD) "..እኛም በዚሁ መንገድ ወልድ ከውጪ [ከአንዱ መለኮታዊ ባህርይ ውጪ] ሳይሆን #ከአብ_እንደተወለደ እንረዳለን.." (ጸረ አርዮሳውያን ስብከት; ስብከት 2:33) ከ451 የቤተክርስቲያን መከፋፈል በፊት በነበረችው አንዲቱ ቤተክርስቲያን ውስጥ የነበረው እውቁ የቤተክርስቲያን አባት ቅዱስ አትናቴዎስ ወልድ ከአብ መወለዱን የአርዮሳውያንን የስህተት ትምህርት በመቃወም በጻፈው ስብከቱ ላይ እንዲህ ገልጿል። ይህ ወልድ በዘላለማዊ ውልደት ከአብ ተወልዷል የሚለው ትምህርት በጥንታዊው ክርስትና ይታመን እንደነበር ያሳያል። 2) St. Cyril of Jerusalem (315 AD - 386 AD) "..God is a spirit, his generation is spiritual: for bodies beget bodies, and for the generation of bodies time needs must intervene, but time intervenes not in #the_generation_of_The_Son_from_The_Father. And in our case what is begotten is begotten imperfect. but #The_Son_of_God_was_begotten_perfect; For what he is now, that is He also from the beginning, #begotten_without_a_beginning" (Catechetical Lecture 11:7) 2) ቅዱስ ቄርሎስ ዘኢየሩሳሌም (315 AD - 386 AD) "..እግዚአብሔር መንፈስ ነው ስለዚህ ወላዲነቱ መንፈሳዊ ነው። ሰውነት የሚወልደው ሰውነትን ነው። ለሰውነት ውልደት ደግሞ የጊዜ ጣልቃ ገብነት የግድ አለ። #ወልድ_ከአብ_በተወለደበት_ውልደት ግን የጊዜ ጣልቃ ገብነት የለም። ለእኛ [ለሰዎች] ሲሆን ተወላዲው የሚወለደው ፍጹም ሆኖ አይደለም። #የእግዚአብሔር_ልጅ_ግን_የተወለደው_ፍጹም_ሆኖ_ነው። አሁን የሆነውን ነገር ከመጀመሪያውም ነበር፥ #የተወለደውም_ያለ_ጅማሬ_ነው" (ለአዲስ ክርስቲያኖች የተሰጠ ትምህርት 11:7) ከአራተኛው ክፍለ ዘመን የአብያተክርስቲያናት መከፋፈል በፊት የነበረው ሌላኛው የቤተክርስቲያን አባት ቅዱስ ቄርሎስ ዘኢየሩሳሌም ወልድ ጅማሬ በሌለው፥ መንፈሳዊ በሆነ፥ ፍጹም (perfect) ውልደት ከአብ እንደተወለደ ገና ላልተጠመቁ ግን ወደ ክርስትና ለመጡ ሰዎች ባስተማረው ትምህርት ላይ ገልጾ እንመለከታለን። ይህ ወልድ በዘላለማዊ ውልደት ከአብ ተወልዷል የሚለው ትምህርት በጥንታዊው ክርስትና ይታመን እንደነበር ያሳያል። 3) Novatian (200 AD - 258 AD) "..Therefore, Christ is both Lord and God, who was not otherwise seen by Abraham, except that as God the Word, #He_was_begotten_of_God_the_Father before Abraham himself" (On The Trinity, 18) 3) ኖቬሽን (200 AD - 258 AD) "..ስለዚህ ክርስቶስ ጌታም አምላክም ነው፥ ለአብርሃምም እግዚአብሔር ቃልን ሆኖ እንጂ አልታየውም። ከአብርሃም በፊትም #ከእግዚአብሔር_አብ_ተወልዶ_ነበር" (በእንተ ሥላሴ፥ 18) ይህም የቤተክርስቲያን አባት ከ451 የአብያተክርስቲያናት መከፋፈል በፊት የነበረ የቤተክርስቲያን አባት ሲሆን ወልድ አብርሃም ከፈጠሩ በፊት እንኳን ከአብ እንደተወለደ ስለ ሥላሴ ባብራራበት መጽሐፉ ከላይ በምንመለከተው መልኩ አስተምሯል። ይህ ወልድ በዘላለማዊ ውልደት ከአብ ተወልዷል የሚለው ትምህርት በጥንታዊው ክርስትና ይታመን እንደነበር ያሳያል። ✍️ መጽሐፍ ቅዱስ ይህን ትምህርት የሚያስተምረው የቱ ጋር ነው? አንዲቷ ቤተክርስቲያን ያካሄደችው ጉባኤ እና ከ451 የአብያተክርስቲያናት መከፋፈል (Schism) በፊት የነበሩ አባቶች በሙሉ መግባባት (consensus) ያስተማሩት ይህ ትምህርት በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አለ ወይ ስንል መልሱ አዎ ይሆናል። የእግዚአብሔርን ልጅ ዘላለማዊ ውልደት የሚናገረውን የመጀመሪያውን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል እንመልከት፦ "አንቺም ቤተ ልሔም ኤፍራታ ሆይ፥ አንቺ በይሁዳ አእላፋት መካከል ትሆኚ ዘንድ ታናሽ ነሽ፤ ከአንቺ ግን #አወጣጡ #ከቀድሞ ጀምሮ #ከዘላለም_የሆነ፥ በእስራኤልም ላይ ገዥ የሚሆን ይወጣልኛል" (ሚክ 5:2) በዚህ ስፍራ ላይ እግዚአብሔር አምላክ ወደ ፊት በእስራኤል ላይ ገዢ የሚሆን መሲህ እንደሚወጣለት ሲናገር እንመለከታለን። ነገር ግን ይህ ወደ ፊት የሚመጣው መሲህ አወጣጡ ከጥንት ከዘላለም ጀምሮ የሆነ እንደሆነ አምላካችን እግዚአብሔር በዚህ ቦታ ላይ ገልጿል። "ቀድሞ" እና "ዘላለም" የሚሉት የዕብራይስጥ ቃላት "קדם/ቄዴም" እና "עולם/ኦላም" የሚሉት ቃላት ሲሆኑ ዘላለማዊነትን ያመለክታሉ (ዘዳ 33:27 መዝ 93:2) አንድ ላይ ተጫፍረው ሲመጡ ደግሞ ዓለም ከመፈጠሩ በፊት የነበረውን ዘላለማዊ እውነታ ያመለክታሉ (ምሳ 8:23) ስለዚህ ይህ የሚመጣው መሲህ ዘላለማዊ ነው።

🚩 ጀምሯል ኑ..!

🚩 እግዚአብሔር ቢፈቅድ እና ብንኖር ዛሬ ማለትም እሁድ 10 ሰዓት ላይ ከአንድ ሙስሊም ወገናችን ጋር ውይይት ይኖረናል ርዕስ:- ክርስቶስ ተሰቅሏል ወይስ አልተሰቀለም?

🚩 ጥሩ የቴሌግራም ቻናል ልጠቁማችሁ 👇 https://t.me/YD_APOLOGETICS

♦️ ይህን እውነት በዚያው በኤፌሶን መጽሐፍ ውስጥ እንመለከተዋለን። በኤፌሶን መጽሐፍ ውስጥ አንድ አካል ወይም one body ብሎ የአማኞችን ሲያመለክት ሁሌም የአማኞችን ጉባኤ ወይም ቤተክርስቲያንን ነው፦ "ይህም፥ አሕዛብ አብረው እንዲወርሱ፥ #በአንድ_አካልም (body) አብረው እንዲሆኑ፥ በወንጌልም መስበክ በክርስቶስ ኢየሱስ በሆነ የተስፋ ቃል አብረው እንዲካፈሉ፥ ለቅዱሳን ሐዋርያትና ለነቢያት በመንፈስ አሁን እንደ ተገለጠ በሌሎቹ ትውልዶች ዘንድ ለሰው ልጆች አልታወቀም" (ኤፌ 3:5-6) በዚህ ቦታ ላይ ሐዋርያው ጳውሎስ አሕዛብ አብረው እንዲወርሱ በአንድ አካልም አብረው እንዲሆኑ በወንጌልም መስበክ በክርስቶስ ኢየሱስ በሆነ የተስፋ ቃል አብረው እንዲካፈሉ ይላል። ይህ ማለት አሕዛብ የክርስቶስ ኢየሱስ ወንጌል ተሰብኮላቸው በጌታ ኢየሱስ ካመኑት አይሁድ ጋር በአንድ አካል ሆነው የተስፋን ቃል እንዲካፈሉ ማለት ነው። ይህ ማለት አሕዛብ ክርስቲያን ሆነው በአካሉ ወይም በቤተክርስቲያን እንዲጨመሩ ማለት ነው። ይህ በኤፌሶን መጽሐፍ ውስጥ ሐዋርያው ጳውሎስ አካል ቤተክርስቲያን ማለቱ እንደሆነ ያሳያል። "ሁላችን የእግዚአብሔርን ልጅ በማመንና በማወቅ ወደሚገኝ አንድነት፥ ሙሉ ሰውም ወደ መሆን፥ የክርስቶስም ሙላቱ ወደሚሆን ወደ ሙላቱ ልክ እስክንደርስ ድረስ፥ ቅዱሳን አገልግሎትን ለመሥራትና #ለክርስቶስ_አካል (body) ሕንጻ ፍጹማን ይሆኑ ዘንድ" (ኤፌ 4:12-13) ኤፌ 4:4 ላይ አንድ አካል ካለ በኋላ ወረድ ብሎ እዛው ከቁ.12-13 ላይ የጸጋ ስጦታዎች የተሰጡት የክርስቶስን አካል ወይም ቤተክርስቲያንን ፍጹም ለማድረግ እንደሆነ ሐዋርያው ጳውሎስ ይናገራል። ሁላችንም የእግዚአብሔርን ልጅ በማመንና በማወቅ ወደሚገኝ አንድነት፥ ሙሉ ሰውም ወደ መሆን፥ የክርስቶስም ሙላት ወደሆነ ወደ ሙላቱ እስክንደርስ ድረስ እና ቅዱሳን አገልግሎትን ለመሥራትና ለክርስቶስ አካል ሕንጻ ፍጹማን ይሆኑ ዘንድ በቁ.7 እና በቁ.11 ላይ የተገለጹት የጸጋ ስጦታዎች ተሰጥተዋል። በኤፌ 4:4 አውድ አካል ወይም body ሲል ቤተክርስቲያንን እንደሚያመለክት ያረጋግጣል። ✍️ ስለዚህ በኤፌ 4:4 ላይ በመጠራታችሁ አንድ አካል ሲል ሰዎች ክርስቲያን ሆነው ሊጨመሩባት የሚገባት የክርስቶስ ቤተክርስቲያን ናት። በዚህ ክፍል ላይ አንድ ተስፋ የተባለው የዘላለም ሕይወት ተስፋ ሲሆን (ቲቶ 3:7 ቲቶ 1:2) አንድ አካል የተባለችው ደግሞ የክርስቶስ አካል የሆነችው ቤተክርስቲያን ናት (1ቆሮ 12:12 ኤፌ 3:5-6) አንድ መንፈስ የተባለው መንፈስ ቅዱስ ሲሆን (1ቆሮ 12:13 1ቆሮ 12:11) አንድ ጌታ የተባለው ደግሞ የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው (1ቆሮ 8:6 ሮሜ 10:9-12) አንድ ሃይማኖት የተባለው ለቅዱሳን አንድ ጊዜ የተሰጠው የክርስትና ሃይማኖት ሲሆን (ይሁዳ 1:3 ሐዋ 6:7) አንድ ጥምቀት የተባለው ሰዎች ከክርስቶስ ጋር ለመተባበር የሚጠመቁት የውኃ ጥምቀት ነው (ገላ 3:27 ቆላ 2:12) ከሁሉ በላይ የሆነው በሁሉም የሚሰራው አንድ አምላክ የሁሉም አባት የተባለው ደግሞ የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ አባት እግዚአብሔር አብ ነው (1ቆሮ 12:6 ኤፌ 3:14-15) ✍️ ይህ "አንድ አካል" ሲል መለኮት አንድ ማንነት ብቻ ነው እያለ እንዳልሆነ በግልጽ የሚያሳይ ነው። ምክንያቱም "አንድ አካል" ሲል መለኮት አንድ ማንነት ብቻ ነው እያለ ከሆነ.. አንድ አምላክ፥ አንድ ጌታ፥ አንድ መንፈስ ብሎ አብን ወልድን እና መንፈስ ቅዱስን ባልዘረዘረ ነበር። በግልጽ የማንነት ልዩነትን ባማከለ ሁኔታ ስለ አብ ስለ ወልድ ስለ መንፈስ ቅዱስ መናገሩ "አንድ አካል" ሲል ስለ ቤተክርስቲያን እየተናገረ እንጂ መለኮት አንድ ማንነት ብቻ ነው እያለ እንዳልሆነ ያረጋግጣል። ጥያቄዎች 1) በኤፌ 4:4 ላይ አንድ አካል የተባለው ማን ነው? 2) በPerson እና በBody መካከል ያለው ልዩነት ምንድነው? 3) አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ሶስት አካል ናቸው ሲባል ሶስት Persons ማለት ሆኖ ሳለ ስለ Body የሚናገርን ክፍል መጥቀስ ስህተት አይሆንምን? 4) በአፌ 4:4 ላይ " #በመጠራታችሁ" ይላል። እነ ማን ናቸው የተጠሩት? 5) በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ "መጠራት" የሚለው ሀሳብ ምንን ለማመልከት ጥቅም ላይ ውሏል? 6) "አንድ አካል" የሚለው ሀረግ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ምንን ለማመልከት ጥቅም ላይ ውሏል? 7) አንድ አካል ማለት መለኮት አንድ ማንነት ነው ማለት ከሆነ..አንድ አምላክ የተባለው ማነው? አንድ ጌታ የተባለው ማን ነው? አንድ መንፈስ የተባለው ማን ነው? ▶️ መደምደሚያ በኤፌ 4:4 ላይ ሐዋርያው ጳውሎስ "አንድ አካል" ሲል መለኮት አንድ ማንነት ወይም Person ብቻ ነው እያለ እንዳልሆነ በበቂ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ ለመመልከት ሞክረናል። በመጀመሪያ ደረጃ ክፍሉ ስለ body እንጂ ስለ Person አይናገርም። ስለዚህ ከመለኮት የአካል/Person ሶስትነትና የባህርይ/Substance አንድነት አይናገርም። ሲቀጥል ክፍሉ ሲጀምር " #በመጠራታችሁ" ብሎ በመጀመሩ እየተናገረ ያለው ከኢ-አማኒነት ወደ ክርስትና ስለመጡት ሰዎች እንደሆነ በመጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃዎች አይተናል። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ደግሞ የክርስቲያኖች ሕብረት ወይም ቤተክርስቲያን "አንድ አካል" ወይም "One Body" ተብላ እንደምትጠራ በብዙ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃዎች አይተናል። ከዚያም በተጨማሪ በክፍሉ በግልጽ አንድ አምላክ (አብ) አንድ ጌታ ወልድ (ወልድ) አንድ መንፈስ (መንፈስ ቅዱስ) በግልጽ አካላዊ ልዩነትን (Hypostatic Distinction) በማከለ ሁኔታ በመግለጹ "አንድ አካል" ሲል መለኮት አንድ ማንነት ብቻ ነው እያለ እንዳልሆነም ለመመልከት ሞክረናል። የክፍሉ ትክክለኛ አረዳድ ይህ ነው። ወደዚህ እውነት ያልመጣችሁ ወገኖች ወደ ትክክለኛውን የወንጌል ጥሪ ተቀብላችሁ እውነተኛይቱ የክርስቶስ አካል ውስጥ ትጨመሩ ዘንድ የዘወትር ጸሎታችን ነው ጌታ ይርዳን!

🚩 አንድ አካል ቤተክርስቲያን ናት ራሳቸውን "የሐዋርያት ቤተክርስቲያን" ብለው የሚጠሩት ወይም በተለምዶ "Only Jesus" የሚባሉት ወገኖች መለኮት አንድ ማንነት ወይም Person ነው ለማለት እጅግ በተሳሳተ መንገድ ከሚጠቅሷቸው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች አንዱ ኤፌሶን 4:4 ነው። እነዚህ ወገኖች ይህን ክፍል በመጥቀስ "እግዚአብሔር አንድ አካል ብቻ ነው" ለማለት ይሞክራሉ። ክፍሉ ግን እውን መለኮት አንድ ማንነት/person ብቻ መሆኑን ያሳያልን? እግዚአብሔር ቢፈቅድ ዛሬ ላይ ይህን ክፍል ለመመልከት የምንሞክር ይሆናል። ክፍሉ እንዲህ ይላል፦ "በመጠራታችሁ በአንድ ተስፋ እንደ ተጠራችሁ #አንድ_አካልና አንድ መንፈስ አለ" (ኤፌ 4:4) በዚህ ቦታ ላይ ሐዋርያው ጳውሎስ ክርስቲያኖች እንዴት ሕብረት ማድረግ እንዳለባቸው ይናገራል። በቁ.2-3 ላይ በትሕትና ሁሉና በየዋህነት በትዕግሥትም እርስ በእርሳችሁ በፍቅር ታገሱ፥ በሰላም ማሰሪያ የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ ካለ በኋላ በቁ.4 ላይ በመጠራታችሁ በአንድ ተስፋ እንደተጠራችሁ አንድ አካልና አንድ መንፈስ አለ ይላል። እነዚህ ወገኖች ይህን ክፍል በተሳሳተ ሁኔታ ለመረዳታቸው የመጀመሪያው ማሳያ ኤፌ 4:4 "አንድ አካል" ሲል "One Body" እያለ እንጂ "One Person" እያለ አይደለም። ኤፌ 4:4 ላይ "አካል" ተብሎ የተተረጎመው የግሪክ ቃል "σῶμα/ሶማ" የሚለው የግሪክ ቃል ሲሆን በኢንግሊዘኛው "body" ተብሎ ተተርጉሟል፦ "4 There is #one_body, and one Spirit, even as ye are called in one hope of your calling;" (Ephesians 4:4) ክርስቲያኖች አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ሶስት አካላት ናቸው ስንል ሶስት Persons ናቸው እያልን እንጂ ሶስት bodies ናቸው እያልን አይደለም። ስለዚህ እነዚህ ወገኖች የአማርኛው ቃል በመመሳሰሉ ምክንያት ብቻ ከርዕሰ ጉዳዩ ጋር የማይገናኝን ጥቅስ በመጥቀስ የተሳሳተ እምነት ላይ እንዳሉ ክርስትናንም በተሳሳተ መንገድ እየተቃወሙ እንደሆነ ከዚህ በቀላሉ መረዳት ይቻላል። ✍️ ታዲያ ኤፌ 4:4 በትክክል ምን እያለ ነው? በአፌ 4:4 ላይ "አንድ አካል" ሲል እያመለከተ ያለው በክርስቶስ ኢየሱስ አምነው የጌታ አካል የሆኑትን የአማኞች ስብስብ ወይንም ቤተክርስቲያንን ነው። ይህንን የምናውቅበት ብዙ መንገድ አለ። ጥቅሱ ሲጀምር የሚጀምረው " #በመጠራታችሁ.." ብሎ ነው። የተጠሩት እነ ማን ናቸው? ከዓለም ወደ በክርስቶስ ኢየሱስ በማመን ወደ ዘላለምን ሕይወት የተጠሩት አማኞች ናቸው። ይህ ኤፌ 4:4 ላይ "አንድ አካል" ሲል እያመለከተ ያለው እነዚህን የተጠሩትን አማኞች እንደሆነ ያሳያል፦ "ማንም ተገርዞ ሳለ #ተጠርቶ እንደ ሆነ፥ ወደ አለመገረዝ አይመለስ፤ ማንም ሳይገረዝ #ተጠርቶ እንደ ሆነ አይገረዝ" (1ቆሮ 7:18) በዚህ ቦታ ላይ ሐዋርያው ጳውሎስ ግርዛትን አስመልክቶ ክርስቲያኖችን ሲመክር እንመለከታለን። ማንም ተገርዞ ሳለ ተጠርቶ እንደሆነ ወደ አለመገረዝ አይመለስ ይላል። ይህ ማለት አንድ ሰው ክርስቲያን ከመሆኑ በፊት ተገርዞ ከነበር ክርስቲያን ከሆነ በኋላ ወደ አለመገረዝ መመለስ የለበትም ማለት ነው። ከዚያም ይቀጥልና ማንም ሳይገረዝ ተጠርቶ እንደሆነ አይገረዝ ይላል። ይህ ማለት አንድ ሰው ክርስቲያን ከመሆኑ በፊት ያልተገረዘ ከነበር ክርስቲያን ከሆነ በኋላ መገረዝ የለበትም ማለት ነው። ስለዚህ "መጠራት" ሲል ክርስቲያን መሆን ማለቱ እንደሆነ ከዚህ እንረዳለን። "ወንድሞች ሆይ፥ እናንተ ለአርነት #ተጠርታችኋልና፤ ብቻ አርነታችሁ ለሥጋ ምክንያትን አይስጥ፥ ነገር ግን በፍቅር እርስ በርሳችሁ እንደ ባሪያዎች ሁኑ" (ገላ 5:13) በዚህ ቦታ ላይ ሐዋርያው ጳውሎስ የገላትያን ክርስቲያኖች ለአርነት እንደተጠሩ ሲነግራቸው እንመለከታለን። ይህ ማለት ክርስቲያኖች ከመሆናቸው በፊት ከነበሩበት የሕግ ሸክም አሁን ጌታ ኢየሱስን አምነው ክርስቲያኖች በመሆናቸው ምክንያት ከዚያ ሸክም አርነት ወጥተዋል ማለት ነው። በቁ.11 ላይ እስካሁን ስለ መገረዝ ወይም ሕግን ስለመፈጸም እንደማይሰብክ ያስተማረው ለዚያ ነው። ስለዚህ ለአርነት ተጠርታችኋል ሲል ክርስትያን የሆናችሁት ለአርነት ነው ማለቱ ነው። ይህ "መጠራት" የሚለውን ሀሳብ ክርስቲያን መሆንን ለማመልከት እንደሚጠቀመው ከዚህ እንረዳለን። "በእግዚአብሔር ለተወደዳችሁና ቅዱሳን ልትሆኑ #ለተጠራችሁ በሮሜ ላላችሁት ሁሉ፥ ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን" (ሮሜ 1:7) በዚህ ቦታ ላይ ሐዋርያው ጳውሎስ በእግዚአብሔር ለተወደዳችሁና ቅዱሳን ልትሆኑ ለተጠራችሁ በሮሜ ላላችሁት ሁሉ ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን ይላል። ሐዋርያት ጳውሎስ ይህን ሰላምታ እያቀረበ ያለው በሮሜ ላሉት ክርስቲያኖች ሲሆን ቅዱሳን ልትሆኑ የተጠራችሁ ይላቸዋል። ይህ ማለት የተጠሩት ወይም ክርስቲያኖች የሆኑት ቅዱሳን ለመሆን ነው። ክርስቲያኖች በመሆናቸውም ሐዋርያው ጳውሎስ እነርሱን ክርስቲያኖች አድርጎ በመቁጠር መልእክት ጽፎላቸዋል። ስለዚህ "መጠራት" የሚለውን ሀሳብ ክርስቲያን መሆንን ለማመልከት እንደሚጠቀመው ከዚህ እንረዳለን። ▶️ ስለዚህ በአፌ 4:4 ላይ " #በመጠራታችሁ.." ካለ በኋላ "አንድ አካል" ሲል ይህን ከኢ-አማኒነት ወደ ክርስቲያንነት የተሻገሩትን የአማኞች ወይም የክርስቲያኖችን ሕብረት እያመለከተ እንደሆነ ከዚህ እንረዳለን። በዚያው አውድ ላይ "መጠራት" የሚለውን ሀሳብ ለክርስቲያኖች ጥቅም ላይ ያዋለው ለዚያ ነው፦ "እንግዲህ በጌታ እስር የሆንሁ እኔ #በተጠራችሁበት_መጠራታችሁ እንደሚገባ ትመላለሱ ዘንድ እለምናችኋለሁ" (ኤፌ 4:1) "አንድ አካል" ባለበት በዚያው በኤፌ 4:4 አውድ ላይ "እንግዲህ በጌታ እስር የሆንሁ እኔ በተጠራችሁበት መጠራታችሁ እንደሚገባ ትመላለሱ ዘንድ እለምናችኋለሁ" ይላል። በተጠራችሁበት መጠራታችሁ ሲል ባገኛችሁት የክርስትና ሕይወት እንደሚገባ ትመላለሱ ዘንድ እለምናችኋለሁ ማለት ነው። ሰዎቹ ከአለማመን ወደ ክርስትና ስለ መጡ ክርስቲያን ሊመላለስ በሚገባው ሕይወት እንዲመላለሱ እየመከራቸው ነው። ይህ "መጠራት" የሚለውን ሀሳብ በዚያው በኤፌ 4:4 ከኢ-አማኒነት ወደ ክርስትና የመጡትን ሰዎች ለማመልከት እንደሚጠቀመው ያሳያል። ✍️ ይህ የክርስቲያኖች ጉባኤ ምን ይባላል? በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ክርስቲያን እንዲሆኑ የተጠሩት የክርስቲያኖች ወይም የአማኞች ሕብረት "አካል" ወይም "body" ተብሎ ተብሏል። ክርስቶስ የቤተክርስቲያን ራስ ነው (ቆላ 1:18) አማኞች ደግሞ የእርሱ አካል ናቸው። ስለዚህ ኤፌ 4:4 ላይ በመጠራታችሁ አንድ አካል ሲል ክርስቲያኖችን ሕብረት እንደሚገልጽ ከዚህ እንረዳለን፦ "እንዲሁ ብዙዎች ስንሆን በክርስቶስ #አንድ_አካል (body) ነን፥ እርስ በርሳችንም እያንዳንዳችን የሌላው ብልቶች ነን" (ሮሜ 12:5) "እናንተም #የክርስቶስ_አካል (body) ናችሁ እያንዳንዳችሁም ብልቶች ናችሁ" (1ቆሮ 12:27) " #በአንድ_አካልም (body) የተጠራችሁለት ደግሞ የክርስቶስ ሰላም በልባችሁ ይግዛ። የምታመሰግኑም ሁኑ" (ቆላ 3:15) "አይሁድ ብንሆን የግሪክ ሰዎችም ብንሆን ባሪያዎችም ብንሆን ጨዋዎችም ብንሆን እኛ ሁላችን በአንድ መንፈስ #አንድ_አካል (body) እንድንሆን ተጠምቀናልና። ሁላችንም አንዱን መንፈስ ጠጥተናል" (1ቆሮ 12:13)

✍️ ስለዚህ በዮሐንስ 5:31-32 ላይ ለጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ የሚመሰክረው ሌላ ምስክር እግዚአብሔር አብ እንጂ ስራ ሊሆን አይችልም። ምክንያቱም ይህ ሌላ ምስክር "እርሱ" ወይም "He" ተብሎ ተጠርቷልና። በተጨማሪም በመላው የመጽሐፍ ቅዱስ አውድና በአቅራቢያው ባለው አውድ "እርሱ" ወይም "He" ተብሎ ለኢየሱስ የሚመሰክረው ምስክር አብ እንደሆነ መጽሐፍ ቅዱስ ያስተምራል። በሚያስገርም ሁኔታ ቅድም ባየነውና በዚያው በዮሐ 5:31-32 አቅራቢያ ባለው አውድ ማለትም በቁ.37 ላይ ለጌታ ኢየሱስ የሚመሰክረው አብ "እርሱ" ወይም "He" ተብሏል፦ "የላከኝ #አብም 👉 #እርሱ 👈 ስለ እኔ #መስክሮአል። ድምፁን ከቶ አልሰማችሁም፥ መልኩንም አላያችሁም" (ዮሐ 5:37) "37 And #the_Father 👉 #himself 👈 which hath sent me, hath borne #witness of me. Ye have neither heard his voice at any time, nor seen his shape." (John 5:37) ይህ በማያሻማ ሁኔታ በዮሐ 5:31-32 ላይ ያለው ለጌታ ኢየሱስ የሚመሰክርለት ሌላ ምስክር አብ እንደሆነ ያረጋግጣል። ምክንያቱም በአንድ አውድ ባሉት በሁለቱም ቦታዎች ላይ "እርሱ" ወይም "He" ተብሏልና። ከመስካሪነቱ ባሻገር። ይህ በማያሻማ ሁኔታ ሌላ ምስክር የተባለው አብ እንደሆነ ያረጋግጣል። ♦️ አብ ደግሞ ከኢየሱስ የተለየ ሌላ ምስክር ከሆነ ኢየሱስና አብ አንድ ማንነት ሊሆኑ አይችሉም። ሌላነቱ ወይም the otherness የሚያመለክተው የማንነት ልዩነትን ነው። ጌታ ኢየሱስ " #ለራሴ ብመሰክር ምስክርነቴ እውነት አይደለም" ሲል ራሴ የሚለው የራሱን ማንነት ነው። ከዚያ "ስለ እኔ የሚመሰክረው #ሌላ ነው" ሲል #ሌላ የሚለው ያን #ራሱን ያልሆነውን ሌላን ማንነት ነው። ኢየሱስ አብ ከሆነ አንደኛ ለራሴ አልመሰክርም ብሎ ለራሱ መሰከረ ማለት ይሆናል ሲቀጥል ሌላ ምስክር ማለቱም ትርጉም አይኖረውም። ስለዚህ ይህ ክፍል ኢየሱስ አብ እንዳልሆነ ያረጋግጣል። ጥያቄዎች 1) በዮሐ 5:31-32 ላይ "እርሱ" ወይም "He" የተባለው ማን ነው? 2) በመላው መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሥራ "እርሱ" ወይም "He" የተባለበት ቦታ አለ? 3) ከላይ ለማየት እንሞከርነው አብ "እርሱ" ወይም "He" ተብሏል። ይህ በዮሐ 5:31-32 ላይ ያለው "እርሱ" ወይም "He" የተባለው ሌላ ምስክር መሆኑን አያሳይም? 4) በዮሐ 5:31-32 አውድ ላይ ባለው ዮሐ 5:37 ላይ ለኢየሱስ የመሰከረው አብ መሆኑ፥ በዮሐ 5:31-32 ላይ ያለው ሌላ ምስክር አብ መሆኑን አያሳይምን? 5) በዮሐ 5:37 ላይ አብ "እርሱ" ወይም "He" መባሉ በዮሐ 5:31-32 ላይ ያለው "እርሱ" ወይም "He" የተባለው ሌላ ምስክር መሆኑን አያሳይም? 6) በዩሐ 5:31-32 ላይ ኢየሱስ ለራሴ ብመሰክር ምስክርነቴ እውነት አይደለም ብሏል። ራሴ ሲል የራሱን ማንነት እያመለከተ አይደለምን? 7) በዩሐ 5:31-32 ላይ ኢየሱስ ለራሴ ብመሰክር ምስክርነቴ እውነት አይደለም ብሏል። ኢየሱስ አብ ከሆነ ለራሱ መሰከረ ማለት አይሆንምን? ታዲያ ምስክርነቱ እንዴት እውነት ይሆናል? 8) በዮሐ 5:31-32 ላይ ኢየሱስ ስለ እርሱ የሚመሰክረው ሌላ ምስክር እንደሆነ ገልጿል። ሌላ ማለት ምን ማለት ነው? 9) በዮሐ 5:31-32 ላይ ኢየሱስ ስለ እርሱ የሚመሰክረው ሌላ ምስክር እንደሆነ ገልጿል። አብ ከኢየሱስ ሌላ ማንነት ካልሆነ #ሌላ መባሉ ትርጉሙ ምንድነው? ▶️ መደምደሚያ በዮሐንስ 5:31-32 ላይ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እርሱና አባቱ እግዚአብሔር አብ የተለያዩ ማንነት መሆናቸውን ገልጿል። እርሱ ስለ ራሱ ከመሰከረ ምስክርነቱ እውነት እንደማይሆንና ለእርሱ የሚመሰክረው ሌላ ምስክር እንደሆነ ገልጿል። በዚያ ቦታ ላይ ሌላ ምስክር የተባለው ሥራ ሳይሆን አባቱ እግዚአብሔር አብ ነው። በሌሎች የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች አባቱ እግዚአብሔር እንደመሰከረለት ተገልጿል፥ በአውዱም የመሰከረለት አብ እንደሆነ ተገልጿል። በተጨማሪም "እርሱ" ወይም "He" በሚለው ማንነትን ወይም Person አመልካች ቃል በመጠቀም የሚመሰክርለት አባቱ እንደሆነ ገልጿል። ስለዚህ እግዚአብሔር አብ ለልጁ ለኢየሱስ የሚመሰክረው ሌላ ምስክር እንጂ ኢየሱስ እንዳልሆነ ከዚህ ክፍል እንረዳለን። አለዚያ "..ለራሴ ብመሰክር ምስክርነቴ እውነት አይሆንም.." ደግሞም "..ሌላ ምስክር.." የሚሉት ቃል ትርጉም አይኖራቸውምና። ይህን እውነት ተረድታችሁ ወደ እውነተኛው አምላክ ወደ እግዚአብሔርና ወደ ልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ ያልመጣችሁ ወገኖች ወደ እርሱ ትመጡ ዘንድ የዘወትር ጸሎታችን ነው። ጌታ ይርዳን!

🚩 ሌላ ምስክር የተባለው አብ ነው በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ እና አባቱ እግዚአብሔር አብ የተለያዩ ማንነቶች መሆናቸውን ከሚያሳዩት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች አንዱ ዮሐንስ 5:31-32 ነው። በዚያ ክፍል ላይ እግዚአብሔር አብ ከጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ የተለየ ሌላ ምስክር ተብሏል። እናንብበው፦ "31 እኔ ስለ እኔ ስለ ራሴ ብመሰክር #ምስክሬ እውነት አይደለም 32 #ስለ_እኔ_የሚመሰክር #ሌላ ነው፥ #እርሱም ስለ እኔ የሚመሰክረው ምስክር እውነት እንደ ሆነ አውቃለሁ" (ዮሐ 5:31-32) በዚህ ቦታ ላይ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ እራሱ ቢመስክር ምስክርነቱ እውነት እንዳልሆነ፥ ስለ እርሱ የሚመሰክረው ሌላ ምስክር እንደሆነ እና እርሱም ወይም ሌላኛው ምስክር ስለ እርሱ የሚመሰክረ ምስክርነት እውነት መሆኑን ሲናገር እንመለከታለን። ስለዚህ በዚህ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል መሰረት ከኢየሱስ የተለየ ሌላ ምስክር ለኢየሱስ ይመሰክርለታል ማለት ነው። እንደ መጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮ ለኢየሱስ የሚመሰክርለት ይህ ሌላኛው ምስክር እግዚአብሔር አብ ነው። እግዚአብሔር አብ በደመና ጌታ ኢየሱስ ልጁ መሆኑን መስክሮለታል (ማቴ 3:17) አባት ሆይ ስምህን አክብረው ሲለው "አከበርሁት ደግሞም አክብሬዋለሁ" የሚል ድምፅ በማሰማት በዙሪያው የነበሩ ሰዎች አብ የኢየሱስ አባት፥ ኢየሱስ ደግሞ የአብ ልጅ መሆኑን እንዲያውቁ መስክሮለታል (ዮሐ 12:28-30) በድጋሚም ልጁ መሆኑን ከደመና ድምፅ በማሰማት መስክሮለታል (ማር 9:7) ስለዚህ በዚህ ክፍል ላይ ጌታ "ሌላ ምስክር" ብሎ የሚጠራው አብን ነው ማለት ነው። ይህንንም እውነት በዚያው በዮሐ 5:31-32 አውድ ላይ እንመለከተዋለን። በዚያ ክፍል ላይ ለክርስቶስ ኢየሱስ የሚመሰክርለት ምስክር አብ እንደሆነ ጌታ ገልጿል፦ "የላከኝ #አብም እርሱ #ስለ_እኔ #መስክሮአል። ድምፁን ከቶ አልሰማችሁም፥ መልኩንም አላያችሁም" (ዮሐ 5:37) በቁ.31-32 ላይ ስለ እኔ የሚመሰክር ሌላ ምስክር አለ ካለ በኋላ ወረድ ብሎ፥ ጌታ ኢየሱስ በቁ.37 ላይ እርሱን የላከው አብ ስለ እርሱ እንደመሰከረ በመናገር በቁ.31-32 ላይ ሌላ ምስክር ያለው አብን እንደሆነ ገልጿል። ስለዚህ በትክክለኛው አውዳዊ አፈታት (contextual interpretation) በቁ.31-32 ላይ ሌላ ምስክር የተባለው በቁ.37 ላይ ለልጁ ለኢየሱስ የመሰከረው እግዚአብሔር አብ ነው። ✍️ ይህ ቀጥተኛና ግልጽ የሆነው የመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮ ሆኖ ሳለ የOnly Jesus አማኞች በዮሐ 5:31-32 ላይ ሌላ ምስክር የተባለው አብ ሳይሆን ክርስቶስ የሰራው ስራ ነው ይላሉ። ይህ እጅግ በጣም ስህተት የሆነ ኢ-መጽሐፍ ቅዱሳዊ አረዳድ ነው። ምክንያቱም በዮሐ 5:31-32 ላይ የተነገረለት ሌላ ምስክር "እርሱ" ወይም "He" ተብሏል፦ "31 እኔ ስለ እኔ ስለ ራሴ ብመሰክር ምስክሬ እውነት አይደለም 32 ስለ እኔ የሚመሰክር #ሌላ ነው፥ 👉 #እርሱም 👈 ስለ እኔ የሚመሰክረው ምስክር እውነት እንደ ሆነ አውቃለሁ" (ዮሐ 5:31-32) "31 If I bear witness of myself, my witness is not true. 32 There is #another that beareth witness of me; and I know that the witness which 👉 #he 👈 witnesseth of me is true" (John 5:31-32) ይህ "እርሱ" ወይም "He" የሚለው ቃል ማንነትን ወይም Person የሚያመለክት ቃል ሲሆን በመላው መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አንድም ጊዜ ለስራ ጥቅም ላይ ውሎ አያውቅም። ስራ "እርሱ" ወይም "He" ተብሎ የተጠራበት አንድም የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል የለም። ምክንያቱም ስራ ተግባር እንጂ ማንነት አይደለም። ስለዚህ ልክ እንደ ማንነት "እርሱ" ወይም "He" ተብሎ ሊጠራ አይችልም። ስለዚህ በዮሐ 5:31-32 ላይ "እርሱ" ወይም "He" የተባለው ሌላ ምስክር ስራ ሊሆን አይችልም። ▶️ በተቃራኒው ግን እግዚአብሔር አብ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በተደጋጋሚ "እርሱ" ወይም "He" ተብሎ ተጠርቷል። ይህ በዮሐ 5:31-32 ላይ የተነገረለት ሌላ ምስክር መሆኑን በሚገባ ያረጋግጣል። ለምሳሌ፦ "እኔ ከራሴ አልተናገርሁምና፤ ነገር ግን #የላከኝ_አብ 👉 #እርሱ 👈 የምለውን የምናገረውንም ትእዛዝ ሰጠኝ" (ዮሐ 12:49) "49 For I have not spoken of myself; but #the_Father which sent me, 👉 #he 👈 gave me a commandment, what I should say, and what I should speak" (John 12:49) በዚህ ቦታ ላይ እግዚአብሔር አብ "እርሱ" ወይም "He" ተብሎ ሲጠራ እንመለከታለን። ጌታ ኢየሱስ የሚናገረው ከራሱ እንዳልሆነና የላከው አብ የሚለውን የሚናገረውንም ትዕዛዝ እንደሰጠው ሲገልጽ አብን "እርሱ" ወይም "He" ብሎ ጠርቶታል። ይህ አብ "እርሱ" ወይም "He" ተብሎ እንደሚጠራ ያሳያል። "ኢየሱስም አላቸው። እግዚአብሔርስ አባታችሁ ከሆነ በወደዳችሁኝ ነበር፤ እኔ #ከእግዚአብሔር ወጥቼ መጥቻለሁና፤ 👉 #እርሱ 👈 ላከኝ እንጂ ከራሴ አልመጣሁምና" (ዮሐ 8:42) "42 Jesus said unto them, If God were your Father, ye would love me: for I proceeded forth and came from #God; neither came I of myself, but 👉 #he 👈 sent me" (John 8:42) በዚህ ቦታ ላይም እግዚአብሔር አብ "እርሱ" ወይም "He" ተብሎ ሲጠራ እንመለከታለን። ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ከእግዚአብሔር ዘንድ ወጥቶ መምጣቱንና እርሱ እንደላከው እንጂ ከራሱ እንዳልመጣ ሲናገር እግዚአብሔርን ወይም አብን "እርሱ" ወይም "He" ብሎ ጠርቶታል። ይህ አብ "እርሱ" ወይም "He" ተብሎ እንደሚጠራ ያሳያል። "እኔም አላውቀውም ነበር፥ ዳሩ ግን በውኃ አጠምቅ ዘንድ #የላከኝ 👉 #እርሱ 👈 መንፈስ ሲወርድበትና ሲኖርበት የምታየው፥ በመንፈስ ቅዱስ የሚያጠምቅ እርሱ ነው አለኝ" (ዮሐ 1:33) "33 And I knew him not: but 👉 #he 👈 that #sent me to baptize with water, the same said unto me, Upon whom thou shalt see the Spirit descending, and remaining on him, the same is he which baptizeth with the Holy Ghost" (John 1:33) በዚህ ስፍራ ላይም እግዚአብሔር አብ "እርሱ" ወይም "He" ተብሎ ሲጠራ እንመለከታለን። መጥምቁ ዮሐንስ እግዚአብሔር እንደላከው ሲናገር የላከኝ "እርሱ" ወይም "He" በማለት የላከው እግዚአብሔር አብን "እርሱ" ወይም "He" ብሎ ይጠራዋል። ይህ እግዚአብሔር አብ "እርሱ" ወይም "He" ተብል እንደሚጠራ ያሳያል።

🚩 አርሲ ውስጥ እየፈሰሰ ያለው የኦርቶዶክሳውያን ደም ወደ እግዚአብሔር ይጮሃል! እግዚአብሔር የነፍሰ ገዳይነትን መንፈስ ይገስጽልን!

🚩 የምንበላው የአብን ሥጋ ነው? ለኦንሊ ጂሰሱ ቄስ የአጋንንት ትምህርት የተሰጠ ምላሽ https://vt.tiktok.com/ZSxcouYVQ/