Eneho Books እነሆ መጻሕፍት
前往频道在 Telegram
እነሆ መጻሕፍት | ዘወትር በልዮ ቅናሽ 0912735000 / 0905222224 ➍ኪሎ ምኒሊክ ት/ቤት ፊት ለፊት ሮሚና ዝቅ ብሎ
显示更多8 642
订阅者
无数据24 小时
+107 天
-3330 天
帖子存档
+4
4 ኪሎ መጻሕፍት መንገድ ዳር ከሚሸጡ ሰዎች መካከል አንዱ ነው ዓባይነህ አሁን 4ኪሎ ጆሊ ባር ሥር የተወሰኑ መጻሕፍት ይዞ ይሸጣል ከያዛቸው መጻሕፍት ውስጥ
የታሪክ ማስታወሻ
ሕይወቴና የኢትዮጵያ እርምጃ ቅጽ 1 እና 2
የተቆለፈበትና
ሌላ ሰው
አንድ አንድ ቅጂ አለው የምትፈልጉ በዚህ ስልክ ደውሉለት 0913581579
*ነገ ቅዳሜ ቀጠሮ ይዘናል!*
•••••••••••••••••••••••••
"የማምሻ ወጎች" እና "ኑሮ እና ፖለቲካ"ን መግዛት የምትፈልጉ፣ ገዝታችኹ ማስፈረም የምትሹ ወይም ጥቂት ቁጭ ብለን የንቃን ሸጋ ቡና እየጠጣን እንጨዋወት የምትሉ እንሆ ለኹለተኛ ጊዜ፣ ነገ ቅዳሜ ሁምናሳ ገርቢቻ ረቢ እና በኀይለ እግዚአብሔር ገብረ እግዚአብሔር ይጠብቋችኋል።
አድራሻ:- አራት ኪሎ ከሰብለ ሬስቶራንት ጀርባ፣ ወደ ዐዲሱ ታክሲ ተራ በሚወስደው መንገድ፣ የቀድሞ ማኅበራዊ ዋስትና የነበረበት ሕንጻ ሥር።
ሰዓት:- ከ4:00 - 10:00 ሰዓት።
ጎበዝ! ...መጽሐፍ ማስመረቅ ባንችል እንኳን እንዲኽ እንገናኝ እንጂ!
*እንገናኝ**
አዲስ ዲጂታል መጽሔት ነው በሊንኩ ገብታችሁ ማንበብ ትችላላችሁ።
ፕሌቶ ሰለግለሰቦች፣ ስለሀገርና ዓለም ፍትሕ ኹነኛው መፍትሔ እነዚህ አካላት በየተፈጠሩለት መስክ መሠማራት አለባቸው ይለናል፡፡ ፊሎዞፈሩ/ፈላስፋው ሲመራ፣ ኦግዚላሪው/ ወታደሩ ዳርድንበር ሲያስጠብና ፈላስፋውን ሲያግዘው፤ ፕሮዲውሰሩ ሲያመርት ፍትሕ ልክክ ብላ መሬት ትረግጣለች፤ ያኔ ችግርና ለሰው ልጅ የሚሻክር ነገር ይጠፋና ሠላም፣ ፍቅር፣ ሕብረት፣ አንድነት፣ ጥጋብ ፣ ቅንጦት. . . ኹሉ ሙሉ ሀገር ይገነባል ይለናል፡፡
በአንድ አጋጣሚ ስህተትና በጉልበት ፕሮዲውሰሮች መሪ ሲሆኑ ሀገር ምን ያህል ኢ-ፍትሓዊና ለዜጎቿ ሲኦል እንደምትሆን የኢትዮጵያን አሁናዊ እውነታ በዚህ ጽሑፍ መነጽር ዐይቶ መታዘብ ጥሩ ማሣያ የሚሆን ይመስለኛል፡፡
ተበድሮም ሆነ እርዳታ ተለግሦት ያገኜውን ፈንድ ተጨማሪ ሀብት ወደሚያፈራ፣ ወደተሻለ ምርት ወደሚያሳድግና የአገርን ምጣኔ ሀብት ወደሚያሻሽል ኢንቨስትመንት የማያስገባ አመራር በአንፃሩ ደግሞ በየትኛውም መንገድ ያገኜውን ፈንድ በምጣኔ ሀብቱ ፈጣንና ተጨባጭ ለውጥ በማያመጡ የውበትና የቅንጦት ተግባራት/መናፈሻ፣ ሕንፃ፣ ቀለማቀለም፣ የባለሥልጣን መንሸራሸሪያ መኪኖች፣ የመንገድ መብራትና ዛፍ ለመሣሰሉት ከዛም ለሚከፋ ለርስ በርስ ጦርነት የጦር መሣሪያ ግዢ የሚያባክን መንግስት ከላይ ካየናቸው በየትኞቹ ግለሰቦች እየተመራ እንደሆነ ማወቅ ቀላል ነው። መፍትሔውም እንዲሁ፡፡
“ፍትህ ወፍልስፍና” በታገል አምሳል ተዘጋጅቷል፤ ሙሉውን በእንገናኝ ቅጽ ፩ መጽሔታችን ላይ ያገኙታል፡፡
ለማንበብ የቴሌግራም ሊንኩን ይጠቀሙ!
👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/engenagndigitalm/64
"ንጹሕ ሃሳብ፤ ነጻ አስተሳሰብ!!!"
+9
*ሐዋሳ ታነባለች ለ6ተኛ ግዜ በሐዋሳ ተጀምሯል።*
ከ ጥቅምት 24 እስከ ጥቅምት 30 2018ዓ.ም በየሦስት ወር የሚዘጋጀው የመጻሕፍት ዓውደ ርእይ ተጀምሯል እነዚህን ከ አዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ ፕሬስ የሚያሳትማቸው ተወዳጅ መጻሕፍት እና የተለያዩ አዳዲስ መጻሕፍት Eneho books - እነሆ መጻሕፍት በልዩ ቅናሽ ሲዳማ ባሕል አዳራሽ ይዞላችሁ ቀርቧል ብቅ እያላችሁ የምትፈልጉትን መጽሐፍ ሸምቱ።
ዝግጅቱን በየሦስት ወሩ ሰማይ መልቲ ሚድያ እና ኢዮብ መጻሕፍት በቅንጅት ያዘጋጁታል።
የዛሬ ሳምንት ሰኞ ጥቅምት 24
ጸሐፊ፦ Wasihun Belay
ርእስ፦አልንበረከክም
ጉዳዩ፦ የመጻሕፍት ምርቃት
ቦታው፦ ብሔራዊ ቴአትር
ሰዓት፦ ከምሽቱ 11:30
**ምናልባት በዚህ በኩል ቢገኝ እባካችሁ???**
"ብዙ የጥናትና ምርምር ሥራዎቼን የያዘ ላፕቶፔን ተሰረቅኹ‼ ውድ ኢትዮጵያዊያን ተባበሩኝ!"
እኅታችን መሠረት ተጫኔ ትባላለች። በዐዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፓለቲካ ሳይንስ የፒኤችዲ ተማሪ ናት። ለዓመታት የደከመችባቸው ለኅትመት የተዘጋጁ የጥናት ሥራዎችን፣ የምርምር ጽሑፎችን፣ የመስክ የጥናት መረጃዎችን እንዲኹም በርካታ ሰነዶችን የያዘ ላፕቶፕ (DELL) ኮምፒዩተሯን ኀሙስ መስከረም 8 ቀን 2018 ዓ.ም ከፒኤችዲ ተማሪዎች ማንበቢያ ክፍል (PhD Students' Reading Room) ውስጥ ተሰርቃለች።
ስርቆቱ የተፈጸመው ከተቀመጠችበት ቦታ ተነስታ የማንበቢያው ክፍል በር ላይ ለሚጠብቃት ሰው መልእክት ለማድረስ በተንቀሳቀሰችበት ቅጽበት ነው።
እኅታችን ድርጊቱ እንደተፈጸመ በዩንቨርስቲው ውስጥ ለሚመለከተው ክፍል አመልክታ የነበረ ቢኾንም የሰረቀውን ግለሰብ የሚያሳይ፣ በደኅንነት ካሜራ ከተቀረጸ ቪዲዮ ውጪ ምንም መረጃ አላገኘችም።
ቪዲዮው፣ ሌባው ወደ ማንበቢያ ክፍል ሲገባ፣ ከዚያም ላፕቶፑን በሌላ ቦርሳ ይዞ ከሬጅስትራር የፒኤችዲ ተማሪዎች ማንበቢያ ክፍል ይዞ ሲወጣ ያሳያል። (4:16 - 4:22 ማለትም በስድስት ደቂቃ ውስጥ)
"በዚኽ ቪዲዮ ላይ ያለኸው ግለሰብ ከፒኤችዲ ቤተ መጻሕፍት (ከዋናው ሬጅስትራር) የወሰድከውን ላፕቶፕ እባክኽ መልስልኝ!" እያለችኽ ነው እኅታችን።
"እጅግ በጣም የደከምኹበት፣ ብዙ መስዋዕት የከፈልኹበት፣ ጊዜ እና ጉልበቴን ለረዥም ጊዜያት ያፈሰስኹበት፣ በገንዘብ የማይለካ ሰነዶችን የያዘ ላፕቶፕ ነውና ለደኅንነትኽ በማያሰጋ መልኩ ከዚኽ በታች በማስቀምጥልኽ ስልክ ወይም በቴሌግራም በማዋራት እባክኽ መልስልኝ!" ብላ እየተማጸነች ነው።
እኅታችን አያይዛም፣ "ንብረቴ የማይመለስ ከኾነ ግን በደኅንነት ካሜራ የተቀረጸ ቪዲዮ ስላለ በቀጣይ በሕግ የማስጠይቅኽና በማኅበራዊ ትስስር ገጾች ላይ ምስልኽን የምንለጥፍ ይኾናል!" ብላኻለች።
እባካችኹ ሌሎቻችኹም ይኽን መረጃ #Share በማድረግ ተባበሩኝ ብላችኋለች።
ባለ ንብረት፣ መሠረት ተጫኔ
ስልክ:- +251 91 172 4665
*ዛሬ እና ነገ ብቻ*
ሐዋሳ ሲዳማ ባሕል አዳራሽ ፊት ለፊት ብቅ ብትሉ እነዚህን የመሳሰሉና ሌሎች መጻሕፍት ያገኛሉ።
መሸ ደሞ አምባ ልውጣ!
አምባ ወጥቼ እኩለ-ሌት፥ ስለት ገብቼ በስሟ
ከርሞ ሰይጣን በሷ አስቶኝ፥ ልገላገል ከሕመሟ
ጠበሏ አፋፍ በጨረቃ፥ ደጋግሜ፥ ማሕሌት ቆሜ
ሆዴ ቃትቶ ባር ባር ብሎ፥ እርቃኔን ከሷ ታድሜ
ደጀ ሰላሟን በአራት እግር፥ ተንበርክኬ ተሳልሜ
በሥጋዬ እሚነደውን፥ በጸሎት ላቤ አጣጥሜ
እፎይ ብዬ አመስግኜ፥ ውዳሴዋን ደጋግሜ ገና ከደጅዋ እልፍ ሳልል፤ ደሞ ይምጣ የቁም ሕልሜ?
ሌት በጥምቀቷ የነጣው፤ ነጋ፥ ደፈረሰ ደሜ።
ለሷ እንጂ ለኔ አልያዘልኝ፤ አዬ የስለት አታምጣ!
በውጣ ውረድ በጠበል፥ ባሣር ወዜ ቢገረጣ
ልክፍቷ እንደሁ አልለቀቀኝ፥ መሸ ደሞ አምባ ልውጣ!
፲፱፻፶፩ - ቢሾፍቱ
እነዚህ ሦስት መጻሕፍት ከገበያ ከክፉ ረጅም ግዜ አስቆጥረዋል ሐዋሳ ሲዳማ ባሕል አድልራች ፊት ለፊት በተዘጋጀው ዓውደ ርእይ ላይ ያገኟቸዋል ያሎት ቀን ዛሬና ነገ ብቻ ነው። ብቅ ብለው የቅናሹ ተጠቃሚ ሁኑ።
ሐዋሳ በተዘጋጀው የመጻሕፍት ዓውደ ርእይ ላይ ሲዳማ ባሕል አዳራሽ ፊት ለፊት ያገኙታል።
ርእስ፦የትዝታዬ ማኅደር
ግለታሪክ
ጸሐፊ፦ ጌታቸው በለጠ
”አብዬ" እያልን የምንጠራቸው የግዕዝ መምህራችን አቶ ዓለማየሁ ሞገስ የዩኒቨርስቲው ጎምቱ መምህር ነበሩ፡፡ የግዕዝን ቋንቋ ብቻ ሳይሆን ምሥጢሩንም ጭምር የተካኑ ምሁርነበሩ::
ትምህርታቸውን የሚጀምሩት በቀልድና በተረብ እንደሆነ ስለምናውቅ የማስታወሻ አብዬ ተራ ደብተራችንን ገልጸን ለመጻፍ የምንዘጋጀው የክፍለ ጊዜው አጋማሽ ግድም ነው: ዓለማየሁ የእያንዳንዳችንን የዕውቀት ልክ በአግባቡ ይመዝኑ ስለነበር ስማችንን በተራ እየጠሩ አንዳንዶቻችንን በግዕዝ ትምህርት እንድንገፋ ሲመክሩን፣ አንዳንዶቻችንን ደግሞ የግዕዝ ትምህርት እጣ ክፍላችሁ ስላይደለ አትድከሙ በማለት እቅጩን ይነግሩን ነበር።
“በትንሽ በትልቁ ቆሽቆሽ” የሚለው ስድባቸው ልዩ መታወቂያቸው ነበር። የአብዬ ዓለማየሁ “ቆሸቆሽ” የሚል ቀልድ አዘል ስድብ ያልደረሰው ተማሪ ስለመኖሩ ግን እጠራጠራለሁ::
አንድ ዕለት ክፍል ውስጥ አስተምረው ሊወጡ ሲሉ ከተማሪዎች መካከል ዓለማየሁ አበበን፣ እኔን እና ብቃለ ስዩምን (ዶ/ር በአፀደ ሥጋ የተለየን) ጠርተው በትምህርታችን ንቁ መሆናችንን ከገለፁልን በኋላ “ቢቻለኝማ ጎጃም በረሃ ወስጄያችሁ አንዲት ነገርባቀምሳችሁ ዕውቀት ፍንትው ብላ ትበራላችሁ ነበር" ያሉትን አልዘነጋም:: የእዚህአነጋገራቸው ምሥጢር የገባኝ ውሎ አድሮ ነው::
የኢትዮጵያ ደራሲያን ማኅበር 11ኛ ዙር የክረምት የሥነ ጽሑፍ ሥልጠና ምዝገባ እየተካሄደ ነው ለተጨማሪ መረጃ ከስር ባለው ስልክ ቁጥር በመደወል ማግኝት ይችላሉ።
*የድጋሚ ኅትመት ትሩፋት*
**አልቦ ዘመድ /ቄሳርና አብዮት**
ከብርሃኑ ድንቄ
የጨረቃ ውበት የሚደነቀው እኮ በመሬት ላይ ሆነን ዓይኖቻችን ወደ ሰማይ አቅንተን ብሩራዊ (silvery) ብርሃኗን በሩቁ ስንመለከት እንጂ እርሷን እየረገጥን በመንሸርሸር አይደለም። George Croly የተባለው ፖ8ት Diana በሚል ርእስ የጻፈውን አንብበዋል?
አላነበብኩም ምን አለ?,
- -በጣም ድንቅ ነው- ልጥቀስልዎት:-..
How like a queen comes forth the lonely moon From slow opening curtains of the clouds Walking in beauty to her midnight throne.
- የዚህን የገጣሚዎች ሥራ እንደቁም ነገር ታነባለህ?» ሲሉ ሽማግሌው በንቀት አኳኋን ራሳቸውን ስለነቀነቁበት ፀሐዩ ተገረመ፣ አዘነም። ሳይንቲስት፣ ቤት፣ ድራማቲስት፣ ኖቬሊስት የተባለው የFaustus ደራሲ (Goethe) ይኸን ቢሰማ ኖሮ ምን ባለ! ሲል አሰበ። ከሽማግሌው ጋራ ንግግሩን መቀጠል በፍጹም አልቻለም። እርሱ በመጀመሪያ የሽማግሌውን ሽበት ሲመለከት በረዢሙ እድሜያቸው ውስጥ ያጠራቀሙትን ትምህርተ ጥበብ (wisdom) ያካፍሉኛል ብሎ ተስፋ ነበረው። ግን ይህን አነጋገራቸውን በሰማ ጊዜ አስተሳሰቡ ሁላ ተዘበራረቀበት። ምናልባት ፀሐዩን ያረጋጋው ነገር ቢኖር በሚከተለው የተገለጠው አንድ ጥንታዊ የኢትዮጵያ ቅኔ መሆን አለበት።
ዋዜማ
ለመልአክ ኢናከብሮ፣ ለእመ አስረደ ከንፈ በመጠነ ነዊህ ቆሙ፣
ለፆፍ ወለትንንያ እስመ ክንፍ ቦሙ፡፡
ወበሲበቱ ለሰብእ ኢናክብሮ ቀዲሙ፣
ፅዓዳ ሲበት እስመ ሀለዎሙ፣ ለዕፀው ወለአዕባን ኵሎሙ።
ፀሐዩ ይህን ቅኔ ለራሱ እያነበበ «ወይ የአገሬ ባለቅኔ! ያልተናገረው ትምህርተ ጥበብ የለም እኮ! ግን ማን ቢሰማው?» አለ በትካዜ ራሱን እየነቀነቀ።
የቅኔው መልእከት ባጭሩ፦
ክንፍ አለኝ፣መልአክ ነኝ፣ ብለህ አትፎክር
ትንኝም ክንፍ አላት ባየር ለመብረር።
