ch
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

前往频道在 Telegram

📈 Telegram 频道 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU 的分析概览

频道 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 14 484 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 6 043,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 334

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 14 484 名订阅者。

根据 30 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 530,过去 24 小时变化为 23,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 39.14%。内容发布后 24 小时内通常能获得 10.20% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 666 次浏览,首日通常累积 1 477 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 33

📝 描述与内容策略

尚未提供频道描述。

凭借高频更新(最新数据采集于 01 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。

14 484
订阅者
+2324 小时
+1447
+53030
帖子存档
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አማላክ አሜን!! የጌታችን ጥምቀት እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳችሁ። ጥምቀት ማለት ቃላዊ ፍቺው መነከር ፣ መዘፈቅ ፣ ውኃ ውስጥ ገብቶ መውጣት ፣ ብቅ ጥልቅ ማለት ሲሆን በምሥጢራዊ ትርጉሙ ግን ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ ከማሕጸነ ዮርዳኖስ ከእግዚአብሔር በመወለድ የቅድስት ሥላሴን ልጅነት ማግኘት ማለት ነው። ጌታችን ለኒቆዲሞስ ባስተማረው ትምህርት "ሰው ዳግመኛ ከውኃ እና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርስም።" በማለት ጥምቀት ዳግመኛ የምንወለድበትና የጸጋ ልጅነት የምናገኝበት ርስቱን የምንወርስበት መሆኑን ነገረን። ዮሐ 3፡5 አንድም ጥምቀት ከክርስቶስ ጋር በሞቱ መተባበር ከእርሱ ጋር አብሮ መሞት መቀበርና መነሳት በአዲስ ሕይወት መመላለስ ማለት ነው። ለዚህም ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በሮሜ መልእክቱ በጥምቀት ከእርሱ ሞትና ትንሳኤ ጋር የምንተባበር መሆኑን ሲነግረን "እንግዲህ ክርስቶስ በአብ ክብር ከሙታን እንደ ተነሣ እንዲሁ እኛም በአዲስ ሕይወት እንድንመላለስ፥ ከሞቱ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ በጥምቀት ከእርሱ ጋር ተቀበርን። ሞቱንም በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ከተባበርን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ደግሞ ከእርሱ ጋር እንተባበራለን፤" ሮሜ 6:4-5 ወደ ጌታችን ጥምቀት ስንመጣ እርሱ እከብር አይል ክቡር እቀደስ አይል በባሕርይው ቅዱስ የሆነ አምላክ በጸጋ ያይደለ የባሕርይ የአብ አንድያ ልጁ ሲሆን ስለምን ተጠመቀ ብንል 1ኛ ለብዙ ዘመናት ተሰውሮ የነበረውን ነገረ ሥላሴ በገሐድ በግልጽ ያሳውቅ ያስረዳ ዘንድ ነው። ነገረ ሥላሴ በምሳሌ እና በምሥጢር ካልሆነ በቀር በብሉይ በገሐድ ተገልጦ አናየውም። የእግዚአብሔርን የአካል ሦስትነት በጎላ በተረዳ ያየነው በጌታችን ጥምቀት በባሕረ ዮርዳኖስ ነው። እግዚአብሔር አብ በደመና "እርሱን ስሙት" እያለ ሲመሰክር እግዚአብሔር ወልድ በተለየ አካሉ ሲጠመቅ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል ሲወርድ ታይተዋል። ማቴ 3:13-17 2ኛ የእኛን ጥምቀት ይባርክልን ዘንድ ነው። ክርስቶስ ከገሊላ ወደ ግብጽ በመሰደዱ የሰማእታት የክርቲያኖችን ስደት ባርኮ ቀድሶ ሲሰጥ ነው። ቁጭ ብሎ ከሊቃውንት እግር ሥር የተማረው የመማርን አገልግሎት ለኛ ለምዕመናን ይባርክልን ዘንድ ነው። የጾመውም ጾማችንን ባርኮ ቀድሶ ይሰጠን ዘንድ ነው። እንዲሁም የተጠመቀው የኛን የክርስቲያኖችን ጥምቀት ይባርክልን ዘንድ ነው። 3ኛ ለኛ አርአያ አብነት ይሆነን ዘንድ ነው። ጌታችን ወደ ዮሐንስ ሄዶ በባርያው እጅ በመጠመቁ ትሕትናን ከእርሱ እንማራለን። እርሱን አርአያ አብነት አድርገን እኛም ወደ ካህናት ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሄደን እንጠመቃለን። ይህንንም አብነት አድርገው ታቦታቱ ከመንበራቸው ወደ ባሕረ ጥምቀት በመውረድ ጎዳናውንም እየባረኩ ወደ መንበረ ክብራቸው ይመለሳሉ። አንድም መጠመቅ እንደሚገባን እንማር ዘንድ እርሱ ተጠምቆ አሳይቶናል። ጾሞ ጹሙ ፣ ይቅር ብሎ ይቅር በሉ ፣ ትእዛዛትንም ፈጽሞ ትእዛዛትን ፈጽሙ እንዳለን እንዲሁ ተጠምቆም እንጠመቅ ዘንድ አርአያ አብነት ሆነን። የበዓሉን ዓላማ ተረድተን የዲያቢሎስን ሥራ ድል የምንነሳበት ለክብረ ሰብዕ የምንቆምበትና ከበጎ ነገር ጋር ብቻ የምንተባበርበት ይሆን ዘንድ ምኞታችንን እየገለጽን ቸሩ አምላካችን ለሀገራችን ኢትዮጽያ ጽኑ ሰላምን አቤቱ የፍቅርና ቸርነት አምላክ ለእኛ ለልጆችህ ተወልደህ እንዳዳንከን ለሀገራችን እና ለሕዝቦቿ ሰላም እና አንድነትን አውርድልን። በዓሉን ስናከብር ላዘኑ መጽናናትን፣ ለታመሙ ምህረትን ለተቸገሩ በረከትን፣ ሰላም ላጡ ሰላምን ያድልልን። ይቆየን! ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/nssu.eotcss ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️ Website 👇 https://eotc-gssu.org/a/

መልአኩም እንዲህ አላቸው:- እነሆ ለሕዝብ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለው እና አትፍሩ ፤ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና። ሉቃስ 2:10_1
መልአኩም እንዲህ አላቸው:- እነሆ ለሕዝብ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለው እና አትፍሩ ፤ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና። ሉቃስ 2:10_11 አቤቱ የፍቅርና ቸርነት አምላክ ለእኛ ለልጆችህ ተወልደህ እንዳዳንከን ለሀገራችን እና ለሕዝቦቿ ሰላም እና አንድነትን አውርድልን። በዓሉን ስናከብር ላዘኑ መጽናናትን፣ ለታመሙ ምህረትን ለተቸገሩ በረከትን እየለመንን በተግባር ደግሞ በኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮ በጎ ልምዳችን መሠረት ለተቸገሩት ሁሉ በመድረስ እንዲሆን ቤተ ክርስቲያናችን ከእኛ ከልጆቿ ሁሌም ትሻለች። ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg ✍️ FaceBook 👇https://www.facebook.com/nssu.eotcss ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU

"በመወለዱ ብዙዎች ደስ ይላቸዋል።" ሉቃ 1፡14 እንኳን ለብጹዕ አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ። የእግዚአብሔርን ቃል መስማት ብርቅ በነበረበት በዘመነ ብሉይ ብዙዎችን ያስደሰተ አንድ ልደት ነበር። ይኸውም የመጥምቀ መለኮት የቅዱስ ዮሐንስ ልደት ነው። የመጥምቁ ወላጆች በእግዚአብሔር ዘንድ ጻድቃን እና ፍጹማን እንደነበሩ መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል። እነዚህ ደጋግ ቅዱሳን የመውለጃቸው ጊዜ ካለፈና ካረጁ ሙቀት ልምላሜም ከተለያቸው በኋላ ብዙዎችን ወደ አምላክ የሚመራ ከአምልኮተ በንስሐ ከአምላካቸው የሚያስታርቃቸው የጌታውን መንገድ የጠረገውን አምላኩን ለማጥመቅ የታደለውን ነቢይ ለመውለድ በቁ። በእነርሱ አንጻር ደግሞ የብጹዕ አባታችን የአቡነ ተክለሃይማኖት ወላጆች የሆኑት ካህኑ ጸጋ ዘአብ እና ቅድስት እግዚሐርያም በእግዚአብሔር ፊት ጻድቃን የነበሩ በጾም ፣ በጸሎት ፣ በስግደትና በምጽዋት የተወሰኑ የጽድቅ የትሩፋት ሥራን ይሠሩ የነበሩ እንደሆነ በገድለ ቅዱስ ተክለሃይማኖት ላይ ተጽፎ እናገኛለን። እነዚህም ቅዱሳን ልክ እንደ መጥምቁ ወላጆች ልጅን አጥተው ለረጅም ዘመን መካን ሆነው ይኖሩ ነበር። ያሉትን የማይረሳ የለመኑትን የማይነሳ አምላክ ለዓለም ሁሉ የወንጌልን ብርሃን የሚያበስር ሐዲስ ሐዋርያ በቅድስናና በክብሩ ከሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ጋር ሃያ አምስተኛ ሆኖ ያመሰገነውን ጻድቅ አቡነ ተክለሀይማኖትን በታህሳስ 24 ቀን ሰጣቸው። ጻድቁ የተወለዱት ኢቲሳ ደብረ ጽላልሽ ዞረሬ ቅዱስ ሚካኤል በተባለው ቦታ ነው። ስማቸውንም ፍስሐ ጽዮን ብለው ሰየሟቸው። በመጽሐፍ "ከሕፃናት እና ከሚጠቡ አፍ ምስጋናን ለራስህ አዘጋጀህ።" መዝ 8:2 ማቴ 21:16 እንደተባለ በተወለዱ በሦሥተኛ ቀናቸው "አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስቅዱስ። አንዱ አብ ቅዱስ ነው አንዱ ወልድ ቅዱስ ነው አንዱ መንፈስ ቅዱስ ቅዱስ ነው።" ብለው በእናታቸው እቅፍ ሳሉ አመስግነዋል። እናታቸውም "ልጄ ሆይ ምን ትላለህ ላንተ የሚገባው ጡት መጥባት ነው ይህ የአባትህ ሥራ ነው።" ብላ አደነቀች። ባሏ ጸጋ ዘአብም ሲመጣ ሕፃኑ ያደረገውን ነገረቸው። እርሱም "ልጄ ሆይ እግዚአብሔር ይባርክህ። እንዲህ እያልክ ስቀድስ አይህ ዘንድ እመኛለው።" ብሎ ባረኳቸው። ለአካለ መጠን ደርሰው አውሬ ለማደን ወደ ጫካ እንደወጡ አስቀድሞ ቅዱስ ጴጥሮስን ከአሳ አጥማጅነት የጠራ ጌታችን ለእርሳቸው ተገልጦ "ከእንግዲህ ወዲህ አውሬ ሳይሆን ሰውን በወንጌል መረብነት የምታጠምድ አረግሀለው ስምህም ተክለሃይማኖት ይሁን።" ብሎ አዲስ ስምን ሰጥቷቸውና ባርኳቸው በክብር ወደ ሰማይ አረገ። በነቢየ ልዑል ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት "ጻድቅ እንደዘንባባ ያፈራል። እንደ ዝግባም ያድጋል። በእግዚአብሔር ቤት ተተክለዋል። በአምላካችን አደባባይ ውስጥም ይበቅላሉ።" መዝ 91(92):12–13 ተብሎ እንደተነገረ ይህንንም ዓለም በወንጌል አብርተው ሕሙማንንም እየፈወሱ ሙታንንም እያስነሱ መራራውን ዓለም ጨው ሆነው አጣፍጠው ለኢትዮጵያና ለዓለም 29 ዓመታት ቆመው ጸልየው እንደ ዘንባባ አፍርተው ነሐሴ 24 ቀን ከአምላካችን ቃልኪዳን ተቀብለው በክብር አርፈዋል። የአባታችን ረድኤት በረከት በሀገራችን በኢትዮጵያና በህዝበ ክርስቲያኑ ላይ ለዘላለም ጸንቶ ይኑር። አሜን። ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg ✍️ FaceBook 👇https://www.facebook.com/nssu.eotcss ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU አገልግሎቱን ይከታተሉ!! ሰብስክራይብ ላይክ እና ሼር በማድረግ ለሌሎች እንዲደርስ ያድርጉ!

"የአራተኛውም መልክ የአምላክን ልጅ መልክ ይመስላል።" ዳን 3፡25 እንኳን አደረሳችሁ!!! ታኅሣሥ 19 በዚህች ቀን የከበረ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ሠለስቱ ደቂቅ አናንያ ፣ አዛርያ እና ሚሳኤልን ን
"የአራተኛውም መልክ የአምላክን ልጅ መልክ ይመስላል።" ዳን 3፡25 እንኳን አደረሳችሁ!!! ታኅሣሥ 19 በዚህች ቀን የከበረ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ሠለስቱ ደቂቅ አናንያ ፣ አዛርያ እና ሚሳኤልን ንጉሡናቡከደነጾር ላቆመው ምስል አንሰግድም እግዚአብሔር አምላካችንንም አንክድም በማለታቸው ከተጣሉበት የእቶን እሳት ያዳነበት ቀን ነው። ከመልአኩ ከቅዱስ ገብርኤል ረድኤት በረከት ይክፈለን!!! ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg ✍️ FaceBook 👇https://www.facebook.com/nssu.eotcss ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU አገልግሎቱን ይከታተሉ!! ሰብስክራይብ ላይክ እና ሼር በማድረግ ለሌሎች እንዲደርስ ያድርጉ!

ባዕታ ለማርያም አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አምነን ሐዋርያት በሠሯት በአንዲት ቤተ ክርስቲያን አምነን ቅዱሳን ስለ እመቤታችን ክብር ከነገሩን ጥቂት ነገርን ማለት እንጀምራለን። ማርያም ማለት የቃሉ ትርጓሜ ስጦታ ማለት ነው። መጀመሪያ ለእናት ለአባቷ ስጦታ ሆናለች። ለብዙ ዘመናት መካን ሆነው ልጅን ለመውለድ ሳይታደሉ ዕለት ዕለት ወደ ቤተ እግዚአብሔር እየሔዱ ልመናን ስዕለትን ከማቅረብ ያልሰለቹ ሐና እና ኢያቄም በእርጅናቸው ወራት ያገኟት ናትና እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ከአምላክ ያገኘንሽ ስጦታችን ነሽ ሲሉ ማርያም አሏት። ፍጻሜው በእርሷ እናትነት ላመንን ለክርስቲያኖች ሁሉ በዮሐንስ ወንጌላዊ በኩል እናታችሁ ትሁን ተብላ ከፈጣሪ ያገኘናት ስጦታችን ናት። ዮሐ 19፡26 ስለማይነገር ስጦታው እናመሰግነው ዘንድ የሚገባ ልዑል እግዚአብሔር እናታችን ብለን የምንመካባትን ማርያምን ሰጥቶናል። ስጦታ ማርያምን ልጅ ሆና የተቀበሉት ሐና እና ኢያቄም 3 ዓመት ከራሳቸው ጋር ካኖሯት በኋላ ሐና ባሏን ኢያቄምን "ወንድሜ ሆይ ልጃችንን ለቤተ እግዚአብሔር ብፅዓት አድርገን እንስጥ ልጃችን ቤተ እግዚአብሔርን እንድታገለግል እንጂ በዚህ ዓለም እኛን ልታገለግል እንዳልተሳልን አስብ አለችው። ኢያቄምም ይህን ከሚስቱ በሰማ ጊዜ ፈጽሞ ደስ አለው።" በዚህም ስእለታቸው መሠረት ታኅሣሥ 3 ቀን ወደ ቤተ እግዚአብሔር ወሰዷት። አባቷ ዳዊት በመዝሙሩ "ልጄ ሆይ ስሚኝ እዪ ጆሮሽንም አዘንብዪ ወገንሽን የአባትሽንም ቤት እርሺ ንጉሥ ውበትሽን ወዷልና።" መዝ 44(45) ፡10-11 እንዳለ የአባት የእናቷን ቤት ትታ የንጉሡ እግዚአብሔር ቤተ መንግሥት ወደ ምትሆን ወደ ቤተ መቅደስ ገባች። እናት አባቷም በቤተ መቅደስ ካህናትን ጠርተው ስእለታችንን ተቀበሉን አሏቸው። ካህናትቱም እንቀበላለን ብለው ቢመጡ እመቤታችን ከፀሐይ ሰባት እጅ አብርታ ታይታቸዋለች። እነርሱም ይህችን የመሰለች ደግ ፍጥረት ተቀብለን ምን እናበላታለን ፣ ምንስ እናጠጣታለን ፣ በምን እናኖራታለን ፣ ምንስ እናነጥፍላታለን ፣ በምንስ እንጋርዳታለን ብለው ሲጨነቁ መልአኩ ፋኑኤል ከሰማይ ሕብስት ሰማያዊ ጽዋዕ ሰማያዊ ይዞ በራሳቸው ላይ ረቦ ታይቷል። እነርሱም ለካህኑ ለዘካርያስ ክብር መልአክ የመረደ መስሏቸው ነበርና ዘካርያስን ጠርተው "አባታችን ሆይ ይህ ክብር የወረደልህ ለአንተ ለደጉ አባታችን ነውና ተነስተህ ተቀበል።" አሉት። እርሱም ሊቀበል ቢወጣ መልአኩ ወደ ሰማይ ራቀው። መልአኩ የተገለጠው ለሐና እና ለኢያቄም ስለ እናንተ ክብር ነው ቢሏቸው መልአኩ መልሶ ወደ ሰማይ ርቋል። ኋላም ካህኑ ዘካርያስ እግዚአብሔር ሚሠራውን የሚያውቅ የለም ሕፃኗን ትታችሁ እናንተ ወደ ኋላ ተመለሱ ብሎ ለሐና እና ለኢያቄም አሳወቃቸው። መልአኩም እመቤታችን ወዳለችበት ወርዶ ቀኝ ክንፉን ጋርዶ ግራ ክንፉን አንጥፎ የያዘውን ሰማያዊ ሕብስትና ሰማያዊ ጽዋ መገባት። አባ ሕርያቆስ በቅዳሴ ማርያም ላይ "ድንግል ሆይ ምድራዊ ሕብስትን የተመገብሽ አይደለሽም ከሰማየ ሰማያት የበሰለ ሰማያዊ ሕብስትን ነው እንጂ። ድንግል ሆይ ምድራዊ መጠጥን የጠጣሽ አይደለሽም ከሰማየ ሰማያት የተቀዳ ሰማያዊ መጠጥ ነው እንጂ።" ብሎ እንዳመሰገነ። ይህስ እንዴት ይሆናል ሰማያዊ ሕብስት እና ሰማያዊ ጽዋ ማን ሊበላ ማን ሊጠጣ ይችላል ቢሉ አይደለም እመቤታችን የአምላክ እናት ቀርቶ በምድረ በዳ እሥራኤል ዘሥጋ ከሰማይ መና ወርዶላቸው ተመግበዋል። ዘጸ 16 የእግዚአብሔር ሰው ነቢዩ ኤልያስም እንዲሁ ሰማያዊ መብል እና ሰማያዊ መጠጥ መልአኩ እንደመገበው መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል። 1ኛ ነገ 19፡5- 8 ካህናቱም የምግቧስ ነገር ከእግዚአብሔር ዘንድ ከሆነልን ከሰው ጋር ምን ያጋፋታል ቦታዋ ወይም መኖርያዋ በቤተ መቅደስ ይሁን እንጂ ብለው ዙፋን ዘርግተው ስጋጃ አንጥፈው አክብረው እግዚአብሔርን እያመሰገኑ ወደ ቤተ መቅደስ አገቧት። በዚያም ለ12 ዓመት ተቀመጠች። "ድንግል ሆይ አንገታቸውን እንደሚያገዝፉ እንደ ዕብራውያን ሴቶች ልጆች በዋዛ ያደግሽ አይደለም በንጽሕና በቅድስና ቤተ መቅደስ ኖርሽ እንጂ።" ቅዳሴ ማርያም የእናታችን የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት የልጇም ቸርነት በዚህም ዓለም በወዲኛውም ዓለም ይጠብቀን። ይቆየን!

የምህረት እናት አማላጃችን ቅድስት ሆይ የአሥራት ሀገርሽን ኢትዮጵያን በምህረቱ እንዲጎበኛት ለምኝልን፡፡ https://t.me/EOTCNSSU https://www.facebook.com/nssu.eotcss
የምህረት እናት አማላጃችን ቅድስት ሆይ የአሥራት ሀገርሽን ኢትዮጵያን በምህረቱ እንዲጎበኛት ለምኝልን፡፡ https://t.me/EOTCNSSU https://www.facebook.com/nssu.eotcss

“ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ።” ዳን 10፡13 👉🏻 #ሚካኤል ማለት መኑ ከመ አምላክ እንደ እግዚአብሔር ያለ ማነው የሚል ትርጉም አለው። ይህም እንደ እግዚአብሔር ያለ በባሕርይው ቅዱስ የሆነ ፣ እንደ እግዚአብሔር ያለ ንጹሐ ባሕርይ ፣ እንደ እግዚአብሔር ያለ ፍጹም ማነው የሚል ነው። ቅድስና ፣ ንጽሕና እና ፍጹምነት የባሕርይ ገንዘቡ የሆነ ከእግዚአብሔር በቀር የለምና። 👉🏻 ሚካኤል ፍጥረቱ በዕለተ እሑድ ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ዘፍ 1፡3 ላይ “እግዚአብሔርም ብርሃን ይሁን አለ።” ብሎ ብርሃንን በፈጠረ ጊዜ ሕልውና መላእክት ታውቋል። እንዴት ቢሉ ሰሚ በሌለበት ተናጋሪ አይናገርና እንዲሁ ልዑል እግዚአብሔር አስቀድሞ ሰሚአን የሆኑ መላእክትን ስለፈጠረ ብርሃንን በነቢብ (በመናገር) ፈጥሯል። የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም በዛሬው ዕለት ኅዳር 12 ቀን በዓለ ሲመቱ ይታሰባል። ይህ ቅዱስ መልአክ መጋቤ ብሉይ እየተባለ ይጠራል። በብሉይ ብዙ ገቢረ ተዓምራትን እየሠራ በጎላ በተረዳ አበው ነቢያትን ስለተራዳና ከእግዚአብሔር ተልኮ ድንቅ ድንቅ ሥራዎችን በማድረጉ ይህ ስያሜ ተሰጥቶታል። 👉🏻 በዘኁ 22፡21-35 ላይ የእግዚአብሔርን ሕዝብ እሥራኤል ዘሥጋን ያለአግባብ ሊራገም የወጣውና ሀብተ መርገም የተሰጠው በልአምን የተቋቋመው እሥራኤል ዘሥጋን ከእርግማን ያዳናቸው ይህ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነው። 👉🏻 ኢያ 5፡13-15 ላይ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል በጌልጌላ ለነቢዩ ኢያሱ ወልደ ነዌ ተገልጦለት ነበር። ኢያሱም የመልአኩን ማንነት ሲያረጋግጥ “ከእኛ ወገን ወይስ ከጠላቶቻችን ወገን ነህን?” አለው። መልአኩም መልሶ “እኔ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ ሆኜ አሁን መጥቼአለሁ” ቢለው ኢያሱ በመልአኩ ፊት በፍርሃት ሰግዷል። “እኔና ቤቴ ግን እግዚአብሔርን እናመልካለን።” በሚለው ታላቅ የእምነት ንግግሩና ምክሩ የምናውቀው ነቢይ ዝቅ ብሎ ለመልአኩ የሰገደው ስለምንድን ነው ብለን ብንጠይቅ ለቅዱሳን መላእክት የጸጋ ስግደት ስለሚገባ ነው። ቀድሞ ከሊቀ ነቢያት ሙሴ ጋር ሆኖ ሕዝቡን ሲመራ የነበረው ይህ ቅዱስ መልአክ ከኢያሱም ሳይለይ እስራኤል ዘሥጋ በጠላቶቻቸው እንዳይዋረዱ ሲረዳቸው ነበር። ዛሬም ይህ መልአክ ክርስቲያኖች በጠላት ዲያብሎስ እንዳይዋረዱ ሲራዳቸው ይቆያል። 👉🏻 ዘጸ 23፡20-22 ላይ እግዚአብሔር አምላክ ለእርሱ የሚታዘዙትን ሁሉ በመንገዳቸው እየጠበቃቸውና እየተራዳቸው ወደ ርስት መንግሥተ ሰማይ መርቶ ለክብር እንዲያበቃቸው እንዲሁም አመጸኞችን ይቀጣ ዘንድ ለዚህ ቅዱስ መልአክ ክብርና ሥልጣን ሰጥቶታል። “በመንገድህ ይጠብቅህ ዘንድ ወደ አዘጋጀሁትም ስፍራ ያገባህ ዘንድ መልአኬን በፊትህ እሰዳለው።” እንዲል። በዚህ ቃል መሠረት እግዚአብሔር በመልአኩ በቅዱስ ሚካኤል አማካኝነት እሥራኤል ዘሥጋን ከግብጽ ባርነት ወደ ምድረ ርስት ከንአን እንደሚያስገባቸው ተናግሯል። ታዲያ እሥራኤል ዘነፍሥ የሆንን እኛ ክርስቲያኖችን ደግሞ በግብጽ ከተመሰለች ሲኦል በምድረ ርስት ከንዐን ወደ ተመሰለች ገነት ርስት መንግሥተ ሰማይ በአማላጅነቱ በተራዳኢነቱ እንደ ምን አያገባን? ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በመልአኩ አማላጅነትና ተራዳኢነት ፈጣን አገልግሎቱም ርስቱን እንደምንወርስ ሲናገር “ሁሉ መዳንን ይወርሱ ዘንድ ስላላቸው ለማገዝ የሚላኩ የሚያገለግሉም መናፍስ አይደሉምን?” ብሏል። ዕብ 1፡14 እኛም ከቅዱሳን መናፍስት ወገን አንዱና አለቃቸው የሆነ ቅዱስ ሚካኤል መዳን መንግሥተ ሰማይን እንወርስ ዘንድ የሚላክ የሚያገለግል አይደለምን እንላለን። ወደ ቀደመው ነገራችን ስንመለስ ገጸ ንባቡ እንዲህ ብሎ ይቀጥላል “በፊቱ ተጠንቀቁ፥ ቃሉንም አድምጡ፤ ስሜም በእርሱ ስለ ሆነ ኃጢአት ብትሠሩ ይቅር አይልምና አታስመርሩት።” የእግዚአብሔር ስም በስሙ ላይ ላለ ለዚህ ታላቅ መልአክ የመፍረድንም ሥልጣን ከአምላካችን እንደተሰጠው ትመለከታላችሁን? ከማማለድም በላይ ኃጢአት የሚሠሩትን አመጸኞችን የመቅጣት ሥልጣንን ከእግዚአብሔር ዘንድ የተቸረው ደግ ሩህሩህ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነው። በአንጻሩ ቃሉን የሚሰሙትን እርሱን የሚያከብሩትን ደግሞ በረድኤት በበረከት ይሞላቸዋል ፣ ምድራቸውን ከበሽታ ይፈውስላቸዋል ፣ እህሉንም ውኃውንም ይባርካል ፣ ጠላቶቻቸው የሆኑ አጋንንትን ከእግራቸው በታች ይቀጠቅጥላቸዋል። በተጨማሪም መልአሉ ቅዱስ #ሚካኤል 👉🏻 ድኅነተ ሥጋ ወነፍስ ያሰጣል። መዝ 33፡7 ፣ ዘፍ 48፡16 ፣ ዕብ 1፡14 👉🏻 ከክፉ ሁሉ ይራዳል። ዳን 10፡13 ፣ ዳን 12፡1 👉🏻 ያማልዳል ያስታርቃል። ዘካ 1፡12-13 👉🏻 ለሰው ሁሉ በጎን የሚያደርግ መልአክ ነው። ሔኖክ 6፡1-2 👉🏻 የከበረ መልአክ ነው። ከክብሩ የተነሳም ምድር ሁሉ ትበራለች። ራእ 10፡1 ፣ ራእ 18፡1 👉🏻 የትሕትና አባት ነው። ይሁ 1፡9 👉🏻 በሰዎች ድኅነት ሀሴት ደስታን የሚያደርግ ነው። ሉቃ 15፡7 👉🏻 በተጨነቅን ጊዜ የሚያበረታን የሚያረጋጋን የሚያጽናናን መልአክ ነው። ሉቃ 22፡43 ፣ ዳን 10፡20 የመልአኩ የቅዱስ ሚካኤል ረድኤቱ አማላጅነቱ ፈጣን ተራዳኢነቱ ዘወትር ከኛ ጋር ይሁን!!! ይቆየን።

ከቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በዓመት ሁለት ጊዜያት እንዲሆን በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ቁጥር 164 በተደነገገው መሠረት ምልዓተ ጉባኤው የመክፈቻው ሥርዓተ ጸሎት ከፈጸመበት ከጥቅምት 11 ቀን 2014ዓ.ም. ጀምሮ የተለመደውን ዓመታዊ መደበኛ ስብሰባ ሲያካሂድ ሰንብቶ ለቤተ ክርስቲያናችንና ለሀገራችን የሚበጁ ማህበራዊና መንፈሳዊ ውሳኔዎችን አሳልፎአል፡፡ በዚሁ መሠረት፡- 1️⃣ የ2014 ዓ.ም. የጥቅምቱ ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ መክፈቻ መልእክት አሁን በአገራችን እየታየ ባለው ጦርነት እና የርስበርስ ግጭት ላይ ያተኮረ ሲሆን፡- ▶️ጦርነቱ በወንድማማቾች መካከል እየተደረገ ያለና ሀዘኑን የከፋ ያደረገው መሆኑ፣ ▶️በዚሁ ጦርነትና ግጭት በርካታ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን ለሞት ለስደትና ለረሀብ መዳረጋቸው፣ ▶️በዚህም ምክንያት በአገሪቱ እየታየ ያለው የኑሮ ውድነት አገራዊ ልማት ላይ እያደረሰ ያለው ተጽእኖ ከፍተኛ መሆኑን በመገንዘብ ይህ ጦርነትና ግጭት ተወግዶ በአገሪቱ ሰላምና አንድነት እንዲሰፍን ከሁሉም በላይ ወደ እግዚአብሔር በመጸለይ ይቅርታ ምሕረት መጠየቅ አስፈላጊ መሆኑን የሚያስገነዝብ በመሆኑ ጉባኤው ይህንኑ መልእክት ተቀብሎ በመላ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ተግባራዊ እንዲሆን ወስኗል፡፡ 2️⃣ በአገራችን በኢትዮጵያ አሁን ያለው የሰላም እጦትና ጦርነት ወደፊትም ሊያስከትል የሚችለው ችግር ከፍተኛ መሆኑ ስለታመነበት በተቻለ አቅም ዜጐች ሁሉይ ለአገራዊው አንድነትና ሰላም መገኘት ዘብ እንዲቆሙ የየበኩላቸውን ጥረት እንዲያደርጉ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ 3️⃣ በዚሁ አገራዊ የሰላም እጦት እየተደረገ ያለውን ጦርነት ምክንያት አድርገው ከአገር ውጭ የሚገኙ አንዳንድ አብያተ ክርስቲያናትና ካህናት አገራዊ ሰላም ላይ ጥላ በሚያጠላ አገራዊና ሕዝባዊ አንድነትን በሚያፈርስ መልኩ ቅስቀሳ ማድረጋቸው ከቤተ ክርስቲያንና የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች ነን ከሚሉ በፍጹም የማይጠበቅ ሆኖ አግኝቶታል፡፡ በመሆኑም በአውስትራልያ፣ በካናዳ፣ በአውሮፓና በአሜሪካ ሁነው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስም እየፈጸሙ ካለው አገራዊና ሕዝባዊ አንድነት ከሚያደፈርስ ተግባራቸው እንዲቆጠቡ ቅዱስ ሲኖዶስ እያሳሰበ አሁንም ወደ ሰላሙና አንድነቱ እንዲመለሱ ጥሪውን ያቀርባል፡፡ ይህንንም የሰላም ተልዕኮ የሚያስፈጽም በውጭው ዓለም የሚገኙ ብፁዓን አባቶች የሚመሩት የጋራ የሰላም ልዑክ እንዲቋቋም ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ 4️⃣ በአገራችን በኢትዮጵያ በተከሰተው ጦርነት ምክንያት ከቄያቸው ለተፈናቀሉና በተፈጥሮና ሰው ሠራሽ ችግር ለደረሰባቸው ወገኖቻችን ዕርዳታ እንዲሆን ብር50,000,000.00(ሃምሳ ሚሊየን ብር) በቤተ ክርስቲያናችን ስም ችግሩ ለደረሰባቸው ወገኖች እንዲሰጥ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡ 5️⃣ የአገራችንን ቀጣይ የዕድገት ደረጃ በእጅጉ ከፍ ያደርጋል የሕዝቦችን አኗኗር በመቀየር ከድኀነት ያወጣል በሚል ታስቦበት ከዓመታት በፊት ግንባታው የተጀመረው የሕዳሴ ግድብ እየተጠናቀቀ ያለበት ምዕራፍ ላይ መድረሱና 2ኛ ሙሌት መከናወኑ ለአገራችን ለኢትዮጵያ ትልቅ የድል ምዕራፍ በመሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስ አድንቋል፡፡ በቀጣይም ለመጨረሻው የድል ምዕራፍ ለመድረስ መላው ኢትዮጵያውያን በጉልበት በገንዘባቸውም በሐሳብም ጭምር ድጋፋቸውን እንዲያደርጉ ቅዱስ ሲኖዶስ አሳስቧል፡፡ 6️⃣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሚገኙ መንፈሳውያን ኮሌጆችን አሁን ቤተ ክርስቲያኒቱ ከደረሰችበት የእድገት ደረጃ ጋር ለማመጣጠንና ተጨማሪ ኮሌጆች በማስፈለጉ በደቡብ ክልል የሚገኙ ሁለት ካህናት ማሠልናዎች ወደ መንፈሳዊ ኮሌጅ እንዲያድጉ አስፈላጊውም በጀት እንዲመደብላቸው ጉባኤው ወስኗል፡፡ 7️⃣ ለመንበረ ፓትርያርክና ለየአህጉረ ስብከት የሚያገለግል የ2014ዓ.ም. ዓመታዊ በጀት ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ተደልድሎ በቀረበው መሠረት ዝርዝሩን ተመልክቶ በጀቱ እንዲፀድቅ በማድረግ በሥራ ላይ እንዲውል ጉባኤው ወስኗል፡፡ 8️⃣ የ4ዐኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ የጋራ መግለጫ ላይ የተነጋገረው ጉባኤ በመግለጫው ላይ በመወያየት አንዳንድ ማሻሻያዎችን በማድረግ እና በማጽደቅ የ2014ዓ.ም. በጀት ዓመት የሥራ መመሪያ እንዲሆን ጉባኤው ወስኗል፡፡ 9️⃣ በአገራችን በኢትዮጵያ የተደረገው 6ኛ አገራዊ ምርጫ ነጻና ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ መከናወኑና በተለይም ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው በመመረጣቸው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የተሰማውን ደስታ እየገለጸ፤ ቀጣዩ አገራዊ ሥራቸውም ለአገርና ለወገን የሚጠቅም የተሳካ የአመራር ዘመን እንዲሆንላቸው በሥራቸውም እግዚአብሔር አብሮአቸው እንዲሆን ቤተ ክርስቲያን ትፀልያለች፡፡ በአጠቃላይ ቅዱስ ሲኖዶስ በጉባኤ በሰነበተባቸው ቀናት ስለ አብነት ት/ቤቶች እና ስብከተ ወንጌል መስፋፋት፣ ስለ ሰንበት ት/ቤቶች መጠናከር ስለ አገራዊ ሰላምና አንድነት ሰፊ ምክክርና ውይይት ያደረገ ከመሆኑም በላይ በአገራችን በተከሰተው የሰላም እጦት የደረሰው ጦርነት ረሀብና የጤና ማጣት አብቅቶ ሰላም እንዲሰፍን ቅዱስ ሲኖዶስ ለሰባት ቀናት ጸሎት ያደረገ ሲሆን በቀጣይም መላው ካህናትና ምዕመናን ስለ አገራችን ሰላምና አንድነት እንዲጸልዩ ቅዱስ ሲኖዶስ አጥብቆ አሳስቧል፡፡ በመጨረሻም ቅዱስ ሲኖዶስ ለ8 ቀናት ሲያከናውን የቆየውን የጥቅምቱ 2014 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ስብሰባ ዛሬ ጥቅምት 18 ቀን 2014ዓ.ም. በጸሎት ዘግቷል፡፡ እግዚአብሔር አምላክ ለአገራችን ሰላሙን ለመላው ሕዝባችን አንድነቱን ይስጥልን፡፡ ጥቅምት 18 ቀን 2014ዓ.ም. አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ https://t.me/EOTCNSSU

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ተጀምሯል። ቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ በመክፈቻ መልእክታቸው "ቆመህ ቃሉን ትሰብክ ዘንድ የተቀበልከውን አደራ ጠብቅ" ፩ኛ ጢሞ 4:14 በሚል የመጻሕፍ ቅዱስ ቃል የ
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ተጀምሯል። ቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ በመክፈቻ መልእክታቸው "ቆመህ ቃሉን ትሰብክ ዘንድ የተቀበልከውን አደራ ጠብቅ" ፩ኛ ጢሞ 4:14 በሚል የመጻሕፍ ቅዱስ ቃል የቅዱስ ሲኖዶስ ኃላፊነት ምድራዊ ብቻ ሳይሆን ሰማያዊ በመሆኑ ለሁሉም አስተምሩ የተባልነው ስለዚህ ምዕመናንን በነፍሳቸውና በስጋቸው በምልአት መጠበቅ እንደሚገባ አሳስበዋል። በተለይም በሀገራችን ያለው የሰላም ማጣት እየፈጠር ያለው ጉዳት ሁሉም የሚረዳው በመሆኑ እግዚአብሔርን መጠየቅ እኛም ድርሻችንን መወጣት እንደሚገባ አባታዊ መመሪያ ሰጥተው ጉባኤውን ከፍተዋል። https://t.me/EOTCNSSU

14. በውጪ ዓለማት በሰሜናዊና ደቡብ አሜሪካና ካናዳ በአውሮፓና በአፍሪካ በአውስትራሊያ በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች በሚገኙ አህጉረ ስብከት በተመደቡት ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትና የሥራ ሓላፊዎች አስተባባሪነት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ዶግማ ቀኖናና ሥርዓተ አምልኮን መዋቅራዊ ሰንሰለትን በጠበቀ መልኩ በየአህጉሩ ለሚኖሩ ኦርቶዶክሳውያን አገልግሎት በመሥጠት ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች ተከታታይ ትምህርተ ሃይማኖት ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ዶግማ ቀኖና ታሪክ ትውፊትና ባህል የአብነት ትምህርት እንዲያውቁ በማስተማር መሬት በመግዛት ሕንጻ ቤተ ክርስቲያንን በመገንባት ቤተ ክርስቲያን በመግዛት ያሉትን በማደስ የሥራ መዋቅሩን በማጠናከር የሀገረ ስብከትና የወረዳ ቤተ ክህነት ጽ/ቤቶችን በመክፈት ስብከተ ወንጌልን ለምእመናን ለማድረስ እንደ የአካባቢው ሁኔታ በአካል በስልክና በኢሜል በማስተማር የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በውጪው ዓለም ጎልታ እንድትታይ ኢትዮጵያውያን ባሉበት ሁሉ እንዲገለገሉ ጉልህ ሚና ከማበርከት በተጨማሪ በሀገር ውስጥ በተከሠቱ ግጭቶች ለደረሰ ጉዳት ለችግሩ ተጠቂ ወጎኖች ለገዳማትና አድባራት ለአብነት ት/ቤቶች በገንዘብና በቁሳቁስ ያደረጉት አስተዋጽኦና እጅግ የሚያመሰግንና አለኝታነትን ያረጋገጠ ተግባር በመፈጸማቸው ጉባኤው ምስጋናና አድናቆቱን ገልጿል፡፡ ለወደፊትም ችግሩ ከሀገራችን እስከሚወገድ ድረስ የጀመሩትን ሃይማኖታዊና ወገናዊ አለኝታና ድጋፋቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ከፍ ባለ አክብሮት እንጠይቃለን፡፡ 15. በውጭው ዓለም በተለይም በአውስትራሊያና በሰሜን አሜሪካ ትውልደ ኢትዮጵያውያን የሆኑትን ኦርቶዶክሳውያን የትግራይና የሌላ ክፍለ ሀገር ተወላጆች በሚል እየከፋፈሉ ከሚገኙት መካከል አባ ሰረቀ ብርሃን ወ/ሳሙኤል ከአውስትራሊያ አህጉረ ስብከት ከቀረበው ሪፖርት ጉባኤ ግንዛቤ አግኝቷል፡፡ በተከሰተውም ግጭት ምክንያት በውጭ ዓለም የሚኖሩትን ኢትዮጵያውያንና የውጭውን አህጉረ ስብከት እንዲሁም የቤተ ክርስቲያኗን አንድነት የሚንድ በመሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስ በጥልቀት ተወያይቶ ውሳኔ ይሰጥበት ዘንድ እንጠይቃለን፡፡ 16. የምዕራቡ ዓለምና የአውሮፓ ሕብረት አባል ሀገራት እያደረሱ ያለውን ተጽእኖ ለሀገራችንና ለሕዝባችን አንድነት ከፍተኛ ጉዳት የሚያስከትልና የተጠቀሱት ሀገራትም ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸውን ታሪካዊ ወዳጅነት የሚያሻክር መሆኑን በመረዳት በውጭው ያሉት ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ነጩ ቤተ መንግሥት በመግባት ድምጻቸውን በማሰማታቸው ጉባኤው ያለውን አክብሮት እየገለጸ ቀጣዩ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በጉዳዩ ላይ ተወያይቶ የኢትዮጵያን እንድነትና ሉዓላዊነት ለማስከበር ያለውን አቋም ለዓለም ማኅበረሰብ እንዲያሳውቅ እንጠይቃለን፡፡ 17. በቤተ ክርስቲያኗ መዋቅራዊ አሠራር ውስጥ የሚከሰቱት የመልካዊ አስተዳደር ችግሮችና ብልሹ አሠራሮች የቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ አስተምህሮ የሚፈታተንና እናት ቤተ ክርስቲያን በምእመናን ልቡና ያላትን ተቀባይነት የሚያሳጣ በመሆኑ ይህ ችግር ተስተካክሎ በመልካም ዓርዓያነት ለመሥራት በቅዱስ ሲኖዶስ በየጊዜው የሚወሰኑ ውሳኔዎችን በመፈጸም የሚጠበቅብንን ድርሻ እንወጣለን፡፡ 18. በእንግሊዝና በመላው ዓለም ሀገር የሚገኙት ቅርሶች፣ ታቦታትና ልዩ ልዩ ንዋየ ቅድሳት ወደ ሀገራቸውና መንበረ ክብራቸው እንዲመለሱ የተጀመረው ያላሰለሰ ጥረት ተጠናክሮ እንዲቀጥል እንጠይቃለን፡፡ 19. የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ ሰበካ ጉባኤን ለማቋቋምና ለማጠናከር አባቶቻችን ለአርባ አመታት ሥምሪት በማድረግ ሥልጠናዎችን በማካሄድ በመውጣት በመውረድ በብዙ ድካም ለፍሬ የበቃበትን ዘመን ለማሰብ አርባኛ አመት ልዩ መርሐ ግብር ሲዘጋጅ ሙሉ ታሪኩን የሚገልጥ መድብለ መጽሐፍ በማዘጋጀትና በማሳተም የአርባ ዓመቱን ሙሉ ውጣ ውረድ ስብሰባዎች ሴሚናሮች ውይይቶች የፎቶግራፍ ዐውደ ርእይ በማደራጀትና ለእይታ በማብቃት ይህ መደበኛ ስብሰባ በልዩ ይዘትና ቅርጽ እንዲከናወን መምሪያው ያደረገውን አስተዋጽኦ ጉባኤው ልዩ ምስጋናና አክብሮቱን ይገልጻል፡፡ ለወደፊቱ የቤተክርስቲያኗን በሚገልጽና በሚመጥን መልኩ እንዲያስቀጥል አደራ እንላለን፡፡ 20. የ ፵ኛውን ዓመት ጠቅላላ ዓለም አቀፍ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ስብሰባ ስናደርግ ከእናት ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ጋር ሲነጻጸር በርካታ ትርጉም ቢኖረውም ለዚህ ጉባኤ ምሳሌ የሚሆን የእስራኤል ሕዝቦች በ40 ዓመት የበረሀ ጉዞ ወደ ቅድስት ሀገር እንደገቡ እኛም የቃለ ዐዋዲውን ሕግ በማስፈጸምና የቤተ ክርስቲያኗን መዋቅራዊ አሠራር ለማጠናከር በብዙ ውጣውረድ ቆይተንና የሰበካ ጉባኤን የሥራ እንቅስቃሴ አጠናክረን ለዚህ መድረሳችን እግዚአብሔርን የምናመሰግንበት ሲሆን ከዚህ በኋላ ከመጣንበት ተምረን የቤተ ክርስቲያኗን መዋቅራዊ አሠራር አጠናክረን ቤተ ክርስቲያናችን በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍ ብላ እንድትታይ በመልካም አርአያነት ጠንክረን እንሠራለን፡፡ ጥቅምት 11/2014 ዓ.ም ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!! https://t.me/EOTCNSSU .

ታይቶና ተሰምቶ በማይታወቅ ፆታ ሳይለይ እመጫቶችን ነፍሰጡሮችን ግራና ቀኝ ፊትና ኋላ እሳትና ውኃ የማይለዩ ሕፃናት በአሰቃቂ ሁኔታ እንዲገደሉና ብዙዎች ሀብት ንብረታቸው ወድሞባቸው ለስደት እንዲዳረጉ ሆኗል፡፡ ለብዙ ዘመናት የተገነቡ ከተሞች የሕዝብና የሀገር ሀብት ወድሟል፡፡ የተቀጠፈው የሰው ሕይወት የወደመው የሐብት መጠን በውል ማወቅ ካልተቻለበት ሁኔታ በቤተ ክርስቲያን ላይ ሊተካ የማይችል ዘግናኝ ኪሳራ ደርሷል፡፡ ይኽ ክስተት በ3ኛው ምእት ዓመት ዘመነ ሰማዕታት ተብሎ በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ተመዝግቦ ከምናነበው ታሪክ ጋር ተመሳሳይ የሚመሰልበት ክርስቲያኖች በዋሉበት እንዳያድሩ በአደሩበት እንዳይውሉ የተደረገበትን ታሪክ የሚያስተውልና የሚያረጋግጥ ቤተ ክርስቲያንን የሚፈትን በሰቆቃ የታጀበ አባቶችንና ሁላችንን ለዋርያዊ ለሰማዕትነት የሚያዘጋጅ ዘመን ነው፡፡ ስለሆነም እንዲህ ዓይነቱ ክፉ ዘመን አሁን በምናየው የአህጉረ ስብከት የመተባበርና የመረዳዳት መንፈስ በመተጋገዝ በመተዛዘን እግዚአብሔር አምላክ የምሕረትና የሰላም እጁን ይልክ ዘንድ በጾም በጸሎት በስግደት ንጹሕ መሥዋዕትን በማቅረብ ምህረትን መጠየቅ ስለሚገባ በዚህ ዘርፍ ያለመታከት ጠንክረን ለመሥራት ቃል እንገባለን፡፡ 9. ቤተ ክርስቲያናችን በመላው ትግራይ የሚገኙ አህጉረ ስብከት ጽ/ቤቶች የገዳማትና አድባራት አገልጋይ ካህናትና ተገልጋይ ምእመናንን የምትመራና የምታስተዳድር መሆኗ ዓለም ያወቀው ፀሐይ የሞቀው እውነት ነው፡፡ ሕዝቡም በኢትዮጵያዊነቱ የማይደራደር የክርስትና ምንጭ ንጹሕ አማኝ ፍጹም ኢትዮጵያዊ መሆኑን ቤተ ክርስቲያናችን ታምናለች፡፡ መላው ሕዝባችንም ይኽኑ ያምናል፡፡ የትግራይን ሕዝብ ከኢትዮጵያዊነቱ ነጻ እናወጣለዋለን የሚሉ የተለዩ ወገኖች አመለካከትና አስተሳሰብ ልጆቻቸውን ጭምር ሲገብሩና ጸዋትወ መከራ እንዲቀበል ሲያደርጉ ኖረዋል፡፡ ይሁንና ከመጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም ጀምሮ ሀገሪቱን ይመራ በነበረው ፓርቲ ውስጥ በተደረገው የሥልጣን ሽግግር ሂደት ከተወሰነ በኋላ የትግራይን ክልል የሚመራው አካል ከማእከላዊው አመራር ጋር ልዩነት በመፈጠሩ ተግባብተውና ተመካክረው ሀገራቸውን እና ሕዝባቸውን በሰላም እንዲመሩ የሚያደርግ ውሳኔ ላይ እንዲደርሱ በተለያዩ ጊዜያት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ፣ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት የበላይ ሓላፊ አባቶችና አባሎቻቸው እንዲሁም ከልዩ ልዩ ማኅበረሰብ የተውጣጡ ታዋቂና የተከበሩ የሀገር ሽማግሌዎች ሰላምና ፍቅርና አንድነት እንዲመጣ እስከ ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም ሲያደርጉት የነበረውን ውጣውረድና መንገላታት ጉባኤው በታላቅ አክብሮት የሚያስታውሰው ነው፡፡ ይሁን እንጂ ከተጠቀሰው ቀን ጀምሮ ባለው ችግር የተነሳ የሰሜን ወሎና የዋግ ኽምራ አህጉረ ስብከት ተወካዮች በትግራይ ውስጥ የሚገኙ አህጉረ ስብከት ተወካዮች ሊቃነ ጳጳሳት የዚህ የ40ኛው ጉባኤ ተሳታፊ ሊሆኑ አልቻሉም፡፡ ስለሆነም ከላይ በተጠቀሱ አካባቢዎች ለጠፋው ክቡር የሰው ሕይወት ለተቃጠሉ ገዳማትና አድባራት ለተፈናቀሉ ወገኖች ለወደመ ቅርስ ንብረት ልባዊ ኀዘናችንን እንገልጻለን፡፡ በይቀጥላልም ቅዱስ ሲኖዶስ ለጉዳዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራበትና እየተነጋገረበት የሚገኝ መሆኑን ብንገነዘብም ለወደፊቱ የበለጠ ትኩረት ተሰጥቶበት የጥናት ቡድን በመሰየም ከመንግሥት ጋር በመነጋገር የወደመ ንብረት እንዲካስ ቤተሰቦቻቸቸውን በሞት ያጡ እንዲቋቋሙ የተፈናቀሉ ወደ ቀያቸው እንዲመለሱና የመኖር ዋስትና የሕግ ከለላ እንዲያገኙ ጥረት እንዲደረግ እንጠይቃለን፡፡ እኛም የጉባኤው ተሣታፊዎች የሚጠበቅብንን ድርሻ ለመወጣት ቃል እንገባለን፡፡ 10. የኦሮሚያ ቤተ ክህነት አደራጅ ኮሚቴ በሚል ይንቀሳቀስ ከነበረው ክፍል ጋር የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ባለፈው ጥቅምት 2013 ዓ.ም ባካሄደው ጉባኤ ችግሩ እንደ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮና እንደ አባቶቻችን ልማድ በውይይት እንዲፈታ በሳልና ጥበብ የተመላበት ውሳኔ መወሰኑ ይታወሳል፡፡ ይሁን እንጂ ውይይቱና ውሳኔው በአህጉረ ስብከት በወረዳዎችና በአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ተላልፎ ያልተቋጨና የተንጠለጠለ በመሆኑ አሁንም በአንዳንድ አህጉረ ስብከት ውስጥ በወረዳዎችና በአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ውዝግብ መኖሩን በሪፖርቱ ተደምጧል፡፡ በመሆኑም ቅዱስ ሲኖዶስ የሰጠውን ውሳኔ አፈጻጸሙን እስከታች በማውረድ የሚታዩ ልዩነቶችን ሁሉ በውሳኔው መሠረት እንዲፈጸም እንዲደረግ እንጠይቃለን፡፡ 11. በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ የአብነት ት/ቤቶችና ገዳማትን ከማስፋፋት አንጻር በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ከተመደበው የድጎማ በጀት በተጨማሪ በርካታ አህጉረ ስብከት ልዩ ልዩ የገቢ ማስገኛ ግንባታዎችን በራሳቸው ገቢ በመገንባትና ከኪራይ ከሚገኘው ገቢ ለአብነት ት/ቤት ለመምህራንና ለደቀ መዛሙርት በቅዳሴና በማሕሌት ለሚያገለግሉ ዲያቆናትና ቀሳውስት ቋሚ ወርኃዊና ዓመታዊ በጀት በመመደብ ቤተ ክርስቲያን እንድትገለገል እንዲሁም ካህናት በአካባቢው ቋንቋ እየሰለጠኑ ለወንጌል አገልግሎት ራሳቸውን እንዲያበቁ የካህናት ማሰልጠኛዎችን በማቋቋም በማጠናከር ከፍተኛ ውጤት መገኘቱን ከቀረቡ ሪፖርቶች መረዳት ተችሏል፡፡ ይህ ተግባር የቤተ ክርስቲያንን ተልእኮ በሚጠበቀው ልክ ለማከናወን አማራጭ የሌለው መፍትሔና ወቅቱ የሚጠይቀው ግዴታ በመሆኑ በዚህ ዘርፍ በቁጥርጠኝነት ለመሥራት ቃል እንገባለን፡፡ 12. በየደረጃው ያሉ አህጉረ ስብከት የወረዳ ቤተ ክህነት ጽ/ቤቶች የሰበካ ጉባኤያት በመንፈሳዊና ሐዋርያዊ አገልግሎት ማሟያ የገንዘብ ገቢ ያስገኙ ዘንድ በርካታ ሕንጻዎች ማስገንባታቸውን በየዓመቱ በሚቀርበው የሥራ ፍሬ ሪፖርት እየተገለጹ ይገኛሉ፡፡ ግንባታዎችም ከጊዜ ወደ ጊዜ መቀጠላቸውን የሚያስመሰግን ለቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ ዕድገት ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን ጉባኤው ተገንዝቧል፡፡ ስለሆነም እነዚህ ቋሚ የቤተ ክርስቲያን ሀብቶች ተሰፍረውና ተቆጥረው ተመዝግበው የሚያስገኙት ገቢ ጭምር በግልጽ ታውቆ መረጃው እስከ ዋናው መ/ቤት እንዲደርስ ቅዱስ ሲኖዶስ በአጀንዳነት ይዞና ተነጋግሮ ውሳኔ ይሰጥበት ዘንድ እንጠይቃለን፡፡ 13. በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ውሳኔ መሠረት በ2013 ዓ.ም በተለያዩ አርእስተ ትምህርት በተመረጡ ሊቃውንት በየአህጉረ ስብከቱ ለሚመለከታቸው የሥራ ሓላፊዎች የተሰጠው ትምህርታዊ ሴሚናር በከፍተኛ ደረጃ ያነቃቁ የተለያዩ ሐሳቦች የመነጩበት ነበር፡፡ ይህ ትምህርታዊ ሴሚናር ከዛሬ 40 ዓመታት በፊት ክብርና ምሥጋና ይግባቸውና አባቶቻችን ቅዱሳን ፓትርያርኮች ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ሊቃውንት የጀመሩት የወጡበት የወረዱበት የደከሙበት ነገር ግን አባት ያበጀው ለልጅ ይበጀው እንዲሉ አበው በነርሱ ድካም እኛ የበረታንበት ያለደመወዝ ሠርተው እኛ ደመወዝ ተከፋይ የሆንበት አሁን ለደረሰበት ደረጃ ያበቃው ይህ የሰበካ ጉባኤ ሥምሪት ነው፡፡ የ40ኛ ዓመት ጉዞ ስንል የ40 ዓመት ታሪክ በመድበል መጽሐፍ ታሪኩን ስናስቀምጥ የቤተ ክርስቲያናችን ታሪክ ማለታችን ሳይሆን ለሰበካ ጉባኤ መጠናከር ሥምሪት የተደረገበትን ዓመት ማለታችን ነው፡፡ ስለዚህ ይህ የሰበካ ጉባኤ ሥምሪት ውጤት ያስገኘ ከመንበረ ፓትርያርክ እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ድረስ በየደረጃው የሚገኙ ሓላፊዎችን የሚያገናኝ ሐሳብ ለሐሳብ የሚያለዋውጥና የሚያስተሳስር የሚያናብብ በአንድ ሐሳብ እንድራመድና እንድንፀና የሚያደርግ ወሳኝ መርሐ ግብር ስለሆነ ለወደፊቱም በቅዱስ ሲኖዶስ በኩል ትኩረት ተሰጥቶት እንዲቀጥል እንዲደረግ አበክረን እንጠይቃለን፡፡