የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU 的分析概览
频道 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 14 484 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 6 043,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 334 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 14 484 名订阅者。
根据 30 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 530,过去 24 小时变化为 23,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 39.14%。内容发布后 24 小时内通常能获得 10.20% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 666 次浏览,首日通常累积 1 477 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 33。
📝 描述与内容策略
尚未提供频道描述。
凭借高频更新(最新数据采集于 01 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
14 484
订阅者
+2324 小时
+1447 天
+53030 天
帖子存档
የኢ/ኦ/ቤ/ክ 40ኛ ዓመት ጠቅላላ ዓለም አቀፍ ጉባኤ ባለ 20 አቋም መግለጫ አወጣ
1. ቤተ ክርስቲያናችን ባለፉት ፵ኛ ዓመታት በየደረጃው ባቋቋመቻቸው የሰበካ ጉባኤያት አያሌ ሥራዎች በታሪኳ ላይ ከማስመዝገቧም በላይ ለክርስቲያናዊ ዕድገትና ለሁለንተናዊ የካህናትና የምእመናን ተሳትፎን የገነባ ጠንካራ መሠረት ለመጣል የሚያስቸለንን አመቺ ሁኔታ ፈጥሯል፡፡ በተለይም ቅዱስ ሲኖዶስ የቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎቷ ይሣለጥ ዘንድ በሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ አስተዳደራዊ ሥርዓት መሠረት የየአጥቢያው ቤተ ክርስቲያን ሐዋርያዊ ተልእኮን መሟላትና እውን መሆን በየአህጉረ ስብከቱ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት መሪነት ዐረፍተ ዘመን የገታቸው በልዩ ልዩ ዘርፍ የተወከለ ሓላፊዎች አገልጋይ ሠራተኞች ባደረጉት ውጣ ውረድ የጎለበተና የታነጸ በመሆኑ በቀጣዩም የሥራ ዘመናችን እግዚአብሔር ቢፈቅድ የበለጠ ለቤተ ክርስቲያናችን ሁለንተናዊ ዕድገት ለማምጣት የሚጠይቀውን አስፈላጊ መስዋዕትነት ሁሉ እንከፍላለን፡፡
2. ባለፉት ፵ኛ ዓመታት በየደረጃው ያሉ የቤተ ክርስቲያኒቱን ሁለንተናዊ ተልእኮ ለማሟላት የቃለ ዐዋዲው ድንጋጌ በየአጥቢያው ቤተ ክርስቲያን ከዓላማውና ከተግባሩ በመነጨ አንድነት ከላይ እስከታች ባለው የሥራ መዋቅር በመናበብ በርካታ ሥራዎችን አከናውነናል፡፡ ለወደፊቱም በወሬ የማይፈታ ፈተናን የሚቋቋም ትውልድ በማነጽ ይህንኑ አንድነታችንን በማጠናከርና በማስተማር የቤተ ክርስቲያናችንን የሕልውና አንድነት ክብርና ልዕልና ለማስጠበቅ መንጋውን የመከታተልና የመቆጣጠር ሥራ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ በአርቆ አሳቢነት በመሥራት አደራችንን እንወጣለን የቃለ ዐዋዲውም ሕግ በተጀመረው አግባብ በልዩ ልዩ ቋንቋዎች ተተርጉሞ ለሀገር ውስጥና ለውጭው ዓለም በበቂ ሁኔታ እንዲሠራጭ እየጠየቅን ቅዱስ ሲኖዶስም የቃለ ዐዋዲው መመሪያ በውጭው ሀገራት ሙሉ በሙሉ ሥራ ላይ እንዲውል ጥብቅ መመሪያ እንዲሰጥ እንጠይቃለን።
3. ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት እስከ ሀገረ ስብከት የተዘረጋውን ልዩ ልዩ ማስፈጻሚያ ተቋማት የየአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናቱ ተግባራዊ ለማድረግ በየደረጃው ለሚገኙ ኃላፊዎች፣ የየወረዳው ሊቃነ ካህናት፣ የየአጥቢያዎቹ አስተዳዳሪዎችና አገልጋይ ካህናት የአጥቢያውን አብያተ ክርስቲያናት የመንፈሳዊ አገልግሎትና የመገልገያ ንዋያተ ቅድሳት በማሟላት ፣የአብነት ት/ቤቶችን በማቋቋምና በማደራጀት የመምህራንና የደቀ መዛሙርቱን መኖሪያ ቤት በመሥራት፣የሥልጠና ወጪ በመሸፈን በተደረገው ጥረት ከፍተኛ ውጤት መመዝገቡን ከሪፖርቶቹ ተረድተናል፡፡ ስለሆነም በመጪው በ2014/15 ዓ.ም ሕዝበ ክርስቲያኑንና የበጎ አድራጊ ወገኖች ተሳትፎ የበለጠ ዳብሮና ተጠናክሮ እንዲቀጥል የበኩላችነን ጥረትና የማስተባበር ሥራ ለመሥራት ተስማምተናል፡፡
4. በየደረጃው የሚገኘውን የቤተ ክርስቲያቱን ሀብትና ገንዘብ ካለው የሰው ኃይል ጋር በማቀናጀት በቁጠባና በማብቃቃት በመጠቀም ብኩንነትን የሚጋበዙ አሠራሮችን በማስወገድ ገንዘብና የቤተ ክርስቲያን መገልገያ ንዋያተ ቅድሳትን ከመዝባሪዎች የመከላከል አስፈላጊነቱ በተለያዩ ጊዜያት በተካሄዱ ጉባኤያት ተነስተው መመሪያ የተሰጠባቸው ቢሆንም አሁንም አልፎ አልፎ ምርመራ በተደረገባቸው ቦታዎች በዚህ ዘርፍ ያለው ችግር አለመቀረፉን የሚያሳይ ሪፖርት በንባብ ተሰምቷል፡፡ ስለሆነም የአስተዳደራዊ ሓላፊነታችንን ከፍ በማድረግ የቤተ ክርስቲያንን ሀብት በቆጣቢነት ለመጠቀምና ውሳኔና መመሪያን በማክበር በባለአድራነት ተግባራዊ እናደርጋለን፡፡
5. ሐዋርያዊትና ኩላዊት ቤተ ክርስቲያናችን በሀገራችን ሕዝብ ዘንድ በሚነገሩ ቋንቋዎች ለማስተማርና ለማገልገል በተጀመረው ጥረት በርካታ የአገልግሎት፣ የትምህርትና የመዝሙር መጻሕፍት ተተርጉመው ተሠራጭተዋል፡፡ የየቋንቋው ተናጋሪ ወጣቶችና ካህናት የአጫጭር የመካከለኛና የረጅም ጊዜ ሥልጠናዎች እየወሰዱ ምእመኑ የሚጠይቀውን በቋንቋ የመገልገልን ፍላጎት በማበርከት ላይ በመንግሥት ሚዲያዎች፣ በእኛ ቤተ ክርስቲያን፣ በማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥንና በባለሀገሩ ቴሌቪዥን የመገናኛ ብዙኀን ሲተላለፉ የነበሩት መርሐ ግብሮች የቤተ ክርስቲያኒቱን ሁለንተናዊ ሐዋርያዊ ተልእኮ ለዓለም አቀፉ ሕብረተሰብና ለመላው የእምነቱ ተከታዮች በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር የሚያስተላልፈው መልእክት፣ ትምህርትና ጸሎት በሀገሪቱ ውስጥ በሚገኙ ልዩ ልዩ ቋንቋዎች በምልዓተ ክህነት ሲያገለግሉበትና ሲያስተምሩበት ከመገኘቱም በላይ በኮቪድ 19 ዐለማቀፋዊ ወረርሽኝ የተደናገጠውን ሕዝብ ቃለ እግዚአብሔር በመጥቀስ የማጽናኛ የማበረታቻ ትምህርት ሲሰጥ መታየቱ ቤተ ክርስቲያናችን ምን ያህል ዝግጁ መሆኗን የገለጠ ከመሆኑም በላይ ዓለም አቀፋዊ አድናቆትን አስገኝቷል፡፡ በአርያነት የሚጠቀስ ሆኖ በታሪክ የሚዘገብ ሥራ ሆኖ ይኖራል፡፡ ይኽንንም ሥራ ለማጠናከር በየአህጉረ ስብከቱ ዜና ዘጋቢ የሰው ሓይል በቂ በጀት እንዲመደብ ቅዱስ ሲኖዶስ አጽንኦት ሰጥቶ አንዲመለከተው እንጠይቃለን፡፡
7. የመላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የሀገር ውስጥና ውጭ ሀገር ሲኖዶስ ተብሎ የላይ ፈሪና የታች ፈሪ ሲባባል ቆይቶ የቤተ ክርስቲያኗን ሲኖዶሳዊ አንድነት ለማስመለስ ብዙዎች ሊቃነ ጳጳሳት ሊቃውንትና ታዋቂ ሰዎች የደከሙበት ተግባር ቢሆንም ጊዜ ሲደርስ አምባ ይፍረስ እንዲሉ አበው ክቡር ጠቅይ ሚኒስቴር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በአግዚአብሔር ፈቃድ ራሳቸው በሄዱበት አውሮፕላን ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ ክርስቲያን 4ኛ ፓትርያርክና በመላው ዓለም በሐዋርያዊ አገልግሎት ላይ የነበሩ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን ሐምሌ 25 ቀን 2010 ዓ.ም በክብር ይዘው በመምጣት የቤተ ክርስቲያን ሲኖዶሳዊ አንድነት ተመልሶ ቤተ ክርስቲያናችን ደስታዋን በቅዱስ ያሬድ ዝማሬ በምእመናን እልልታ በሚሊኒየም አዳራሽ ሐምሌ 28 ቀን 2010 ዓ.ም በማክበር ላይ ሳለች በዚን ዕለት የቤተ ክርስቲያናችን አንድነት የማይዋጥላቸው የውስጥና ውጪ ጠላቶች እንዲሁም ነጭ በጥቁር የመሸነፍ ምሥጢር የምሥጢሩ ባለቤት የሆነችው የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንም ሕዝቡን በአንድነት በሰላምና በፍቅር ገመድ አሥተሳስ ያቆየች መሆኗ እንደበደል ተቆጥሮባት ባሳደገቻቸው ልጆቿ በጠላትነት ተነስተው በጅግጅጋና በአካባቢው የሚገኝ አብያተ ክርስቲያናትን ካህናትና ምእመናን በእሳት ካቃጠሉ ንብረታቸው ተዘረፈው ጥለው እንዲሰደዱ ተደረገ መንግሥትም በጊዜው የጥፋት አመራር ሰጥተዋል የተባሉ ባለሥልጣናትንና ድርጊት ፈጻሚዎች ለሕግ ማቅረቡን ተመልክተናል፡፡ ከዚያ ወዲህ ግን እምነትንና ማንነትን መሠረት ያደረገ ጥፋት በቡራዩ ይኽን ተከትሎ በምሥራቅና ምዕራብ ወለጋ በሻሸመኔ በዝዋይ በመተከል በጉራ ፈርዳ ፣ምዕራብ አርሲ በባሌ፣በምዕራብ ሐረርጌ፣ድሬዳዋ ተከታታይ ጭካኔ የተሞላበት በተለያየ ቀን ጭፍጨፋ በመደረጉ ቤተክርስቲያኗን አሳዝኗል፡፡
8. በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሑመራ ማይካድራ ምዕራብ ጎንደር መተማ ሰሜን ጎንደር ጭና አቡነ ተክለ ሃይማኖት ማእከላዊ ጎንደር በደቡብ ጎንደር ጨጨሆ መድኃኔዓለም ሰሜንና ደቡብ ወሎ ዋግ ሕምራ ራያና ኮረም በጅማ በሊሙ ኮሳ በሊሙሰቃ ወረዳዎች ፤በሰሜን ሸዋ በአጣዬ በሸዋሮቢት በካራ ቆሬ በማጀቴ አካባቢዎች አብያተ ክርስቲያናት ተቃጥለዋል፡፡ የቤተ መቅደስ ካህናት ካህኑ ዘካርያስ በቤተ መቅደስ በተሰዋበት አምሳል በአገልግሎት እንዳሉ ጭምር ታርደዋል፡፡ ምእመናንና ምእመናት በሀገራችን ታሪክ
💦💢💦💢💦💢💦💢💦💢💦💢💦💢💦💢💦💢💦💢💦💢
40ኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰበካ መንፈሳዊ ዓለም አቀፍ ጉባኤ በቅዱስ ፓትርያርኩ ቃለ በረከት በይፋ ተከፈተ !!!
💦💢💦💢💦💢💦💢💦💢💦💢💦💢💦💢💦💢💦💢💦💢
መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ
***********
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ
ራብዓይ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ብፁዕ አቡነ ያሬድ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ የበላይ ኃላፊ፣ የአርሲ ሀገረ ስብከት እና የምሥራቅ ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የሲዳማ ክልል፣ የጌዴኦ አማሮና ቡርጂ ዞኖች አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፡፡
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት፣
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት የየመምሪያውና የየድርጅቱ ኃላፊዎች፣
ከሀገር ውስጥና ከውጭ አህጉር የመጣችሁ የየሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጆች፣
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የየክፍሉ ኃላፊዎች፣
የአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣
ከሁሉም አህጉረ ስብከት የመጣችሁ ተወካዮች በአጠቃላይ፤
የተበታተኑትን የሚሰበስብ፣የተራራቁትን የሚያቀራርብ እግዚአብሔር አምላካችን ከልዩ ልዩ አጽናፈ ዓለም የመጣችሁትንና ከዚህ ከቅርብ የቆየነውን በአንድነት አሰባስቦ ስላገናኘን ክብርና ምስጋና ለአምላካችን እናቀርባለን&
“ወአናቅጸ ሲኦል ኢይኄይልዋ፤ ወኢያንቀለቅልዋ፤ የሲኦል በሮች አይበረቱባትም፤ አያናዋውጧትምም” /ማቴ06፡08/፡፡
ይህን ዓረፍተ ነገር ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ኃይልና ጽናት አስመልክቶ ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያስተማረን ትምህርት ነው፤ ዓረፍተ ነገሩ እንደሚያመለክተው ቤተ ክርስቲያን ፈተና የሚያበዙባት ፈታኞች እንደማይለዩዋት ነው፤ ፈተናውን የሚያመጡባት አካላት በስም ባይጠሩም በተግባራቸው የሲኦል በሮች ተብለው ስለ ተጠቀሱ ሞትና መቃብር እንደዚሁም የእነሱ ዘበኞች የሆኑ ሠራዊተ አጋንንት እንደሆኑ መረዳቱ አያዳግትም፤ ጌታችን የቤተ ክርስቲያን ፈታኞች እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ በሙሉ ዓቅማቸው ቤተክርስቲያንን ቢታገሏትም ሊያሸንፏት ግን አይችሉም ማለቱ በራእየ ዮሐንስ እንደተገለፀው መቃብር በትንሣኤ ዘጉባኤ፣ ሠራዊተ አጋንንት ደግሞ በደመ በግዑ በመጨረሻ የሚሸነፉና ከነካቴው የሚወገዱ መሆናቸውን ለመግለጽ እንደሆነ እናስተውላለን፡፡
ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት
ክቡራን የጉባኤው ታዳሚዎች
ሊቀ ኖሎት በሆነው በአምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም የተቋቋመውና የተሰበሰበው ይህ ዓለም አቀፍ ጉባኤ፣ የሲኦል በሮች የማያናውጧትን ቤተ ክርስቲያን ለመጠበቅ እንደሆነ ሁላችንም የምንገነዘበው ነው፤ ቤተ ክርስቲያን ለሁለት ሺሕ ዘመናት ያህል በመከራ እየተፈተነች እስካሁን ድረስ ከዕለት ወደ ዕለት እየሰፋችና ሁሉንም እያዳረሰች የመጓዟ ምሥጢር መድኃኒታችን ከላይ የገባላትን ቃል ኪዳን ሊቀለብስ የሚችል ኃይል በሰማይም ይሁን በምድር የሌለ በመሆኑ እንደሆነ አንዘነጋውም፤ ይሁን እንጂ ዋናውና ላዕላዊው ጠባቂ እሱ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ እኛም የጥበቃው ተሳታፊዎች አድርጎ ሹሞናልና አደራ ጭምር ያለበት የጥበቃ ተልእኮና ኃላፊነት አለብን፡፡ በዚህም “አማልክት አንትሙ ወደቂቀ ልዑል ኲልክሙ፤ እናንተ አማልክት ናችሁ፤ ሁላችሁም የልዑል ልጆች ናችሁ” ብሎ ያናገረው የጸጋ አምላክነት በእኛ ላይ እንዴት ተፈጻሚ እንደሆነ ማጤኑ ተገቢ ነው፤ ከዚህ አንጻር
በአሁኑ ጊዜ የቤተ ክርስቲያን ፈተና በምን ደረጃ ላይ ይገኛል?
በየአካባቢው የሚገኙ ኖሎትስ ቤተ ክርስቲያንን ለመጠበቅ ያደረጉት ጥረት ምን ይመስላል?
ለወደፊቱስ የቤተ ክርስቲያንን ፈተና ለማቅለል ምን ማድረግ ይገባል? የሚሉትን መሪ ሐሳቦች በማንሣት ይህ ጉባኤ የማየት ኃላፊነት አለበት፡፡
ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት
ክቡራን የጉባኤው ታዳሚዎች፣
ቤተ ክርስቲያን በአየር የተንሳፈፈች ነገር ሳትሆን በማኅበረ አማንያን ልቡና ውስጥ ተጠልላ የምትገኝ መንፈሳዊት መንግሥተ እግዚአብሔር ናት፤ ይህም ባሕርይዋ ከአማንያን ህልውና ጋር ያቆራኛታል፤ አማንያንም ያለ ሀገር ህልውና ስለሌላቸው ቤተ ክርስቲያን በተከታዮቿ አማካኝነት ከሀገር ሰላም ጋር ትተሣሠራለች፣ ይህ ብቻም አይደለም፤ የዓለሙን ሰላምና ፍቅር አስተማሪ፣ ሰባኪና ተምሳሌት በመሆን የሰው ልጆችን ሁሉ የመጠበቅ ኃላፊነትም አለባት፤ ይህንም ስታደርግ እንደ እናትም እንደ መምህርም እንደ ሽማግሌም ማዕከላዊት ሆኖ ሥራዋን በለብዎ ማከናወን እንዳለባት ይታወቃል፡፡ ይሁንና ቤተ ክርስቲያናችን በአሁኑ ጊዜ በፈተና ተከባ፣ ልጆችዋም እርስ በርስ እየተጣሉ እንደሚገኙ ዓለም ሁሉ የሚያውቀው ነው፤ እነዚህ ወገኖቻችን ቤተ ክርስቲያን ልጆቼ ብላ የተቀበለቻቸው፣ በልጅነት ያከበረቻቸውና ለእግዚአብሔር መንግሥት ዕጩ ያደረገቻቸው፣ ያም ባይሆን በአርአያ እግዚአብሔር የተፈጠሩ ክቡራን ሰዎች ናቸው፤ ቤተ ክርስቲያን በዚህም በዚያም ያሉ ሁሉ ልጆቿ ናቸውና ስለነሱ ይገዳታል፤ ይሰማታል፣ ያሳስባታልም፤ በመሆኑም ብትችል መክራና አስተምራ፣ ገሥጻና ተrጥታ፣ ካልሆነም ልባዊ የሆነ ጸሎት ወደ እግዚአብሔር በማቅረብ ከእርስ በርስ ጠብ ተላቀው በአንድነት፣ በሰላምና በፍቅር እንዲኖሩ በጸሎትና በምህላ ፈጣሪን መማፀን አለባት፤ ይህን ስናደርግ የኖላዊነት ኃላፊነታችንን በአግባቡ እየተወጣን ነው ማለት እንችላለን፤ በመሆኑም ቅዱስ ሲኖዶስ በሚያስተላልፈው ቀኖናዊ መልእክት ገዳማቱ አድባራቱና አብያተ ክርስቲያናቱ በጸሎትና በምህላ ተጠምደው ስለ ሕዝብ ስለ ምእመናንና ስለሀገር ደኅንነት አጥብቀው ፈጣሪን እንዲማፀኑ በዚህ ጉባኤ ፊት አባታዊ መልእክታችንን እናስተላልፋለን፡፡
በመጨረሻም አርባኛው ዓለም አቀፍ የሰበካ መንፈሳዊ ጠቅላላ ጉባኤ በዛሬው ዕለት ተከፍቶ በፈቃደ እግዚአብሔር የተጀመረ መሆኑን እናበስራለን፡፡
እግዚአብሔር የተባረከ የተቀደሰ ጉባኤ ያድርግልን
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
አሜን
አባ ማትያስ
ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት
ጥቅምት ፰ ቀን ፳ ፻ ወ ፲ ፬ ዓ.ም.
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ
💦💢💦💢💦💢💦💢💦💢💦💢💦💢💦💢💦💢💦💢💦💢
የሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ትግበራ በሁሉም አጥቢያዎች እንዲተገበር ስለማሳወቅ:
በሀገር አቀፍ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ በተወሰነው ውሳኔ መሠረት ሁሉም አኅጉረ ስብከት ተዘጋጅቶ የቀረበውን የአንድኛ ክፍል መጽሐፍት ተግባራዊ እንዲያደርጉ ለሁሉም አኃጉረ ስብከቶች ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ደብዳቤ የውጣ ሲሆን ሁሉም እስከ አጥቢያ በማሳወቅና ያልደረሳቸው እንዲደርሳቸው በማሳወቅ በትኩረት እንዲሠራ መመሪያ ተላልፏል፡፡
መጻሕፍቶቹን ለማግኘት ይህን ሊንክ ይጠቀሙ
https://eotc-gssu.org/a/
ስለ አተገባበር መልእክት ለመላክ የአንድነቱን አድራሻች ይጠቀሙ
https://t.me/EOTCNSSU
የሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ትግበራ በሁሉም አጥቢያዎች እንዲተገበር ስለማሳወቅ:
በሀገር አቀፍ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ በተወሰነው ውሳኔ መሠረት ሁሉም አኅጉረ ስብከት ተዘጋጅቶ የቀረበውን የአንድኛ ክፍል መጽሐፍት ተግባራዊ እንዲያደርጉ ለሁሉም አኃጉረ ስብከቶች ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ደብዳቤ የውጣ ሲሆን ሁሉም እስከ አጥቢያ በማሳወቅና ያልደረሳቸው እንዲደርሳቸው በማሳወቅ በትኩረት እንዲሠራ መመሪያ ተላልፏል፡፡
መጻሕፍቶቹን ለማግኘት ይህን ሊንክ ይጠቀሙ
https://eotc-gssu.org/a/
ስለ አተገባበር መልእክት ለመላክ የአንድነቱን አድራሻች ይጠቀሙ
https://t.me/EOTCNSSU
የምሥራች በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሠረት የአንደኛ ክፍል የሰ/ት/ቤቶች መማርያ መጽሐፍ መሠራጨት ጀመረ። በአንድነቱ ዌብሳይት ሊንክ ታገኙታላችሁ።https://eotc-gssu.org/a/%e1%88%a5%e1%88%ad%e1%8b%93%e1%89%b0-%e1%89%b5%e1%88%9d%e1%88%85%e1%88%ad%e1%89%b5/
እንኳን ለመስቀል በዓል አደረሳችሁ እያልን እግዚአብሔር አምላካችን ለሀገራችንብሰላም ለተቸገሩት ሁሉ መጽናናትን ይስጥልን።
🌹🌻💐🌹🌻💐🌹🌻💐🌹🌻💐🌹
''በእግዚአብሔር ቤት መረቅናችሁ'' መዝ ፻፲፯፥፳፮
🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓
#በአዲስ_አበባ_ሀገረ_ስብከት_የሰንበት_ትምህርት__ቤቶች_አንድነት_የአዲሱ_ካሪኩለም_ቅድመ_ትግበራ_ከጀመሩ #57_ሰንበት_ትምህርት_ቤቶች_ውስጥ_ሐምሌ 25/2013 ዓ.ም ያስፈተናቸውን #የ4ኛ, #የ6ኛ እና #10ኛ ክፍል #ተማሪዎችን_ለመጀመሪያ_ጊዜ_በአንድነት_መስከረም_9_2014 ዓ.ም እውቅና ሊያሰጥ ነው‼
🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓
🌹🌻💐🌹🌻💐🌹🌻💐🌹🌻💐🌹🌻💐🌹🌻🌹💐🌻🌹💐🌻🌹💐🌻🌹💐🌻💐🌹
በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት #የአዲሱ_ካሪኩለም_ቅድመ_ትግበራ_ከጀመሩ #57 ሰንበት ት/ቤቶች ውስጥ #የ4ኛ, #የ6ኛ እና #10ኛ ክፍል ተማሪዎችን ሐምሌ 25/2013 ዓ.ም ያስፈተነ ሲሆን የተፈተኑት ተማሪዎቹን #መስከረም_9_2014 ዓ.ም ከቀኑ 7:00 ጀምሮ በጠቅላይ ቤተክህነት አዳራሽ (5 ኪሎ) እውቅና የሚያሰጥ ሲሆን በመርሐግብሩ ላይ ብጹዓን ሊቃነ ጳጳሳት ፥ የጠቅላይ ቤተክህነት የመምሪያ ኃላፊዎች ፥ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሥራ ኃላፊዎች ፥ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥር የሚገኙ የየሰንበት ት/ቤቶች የሥራ አመራሮች ፥ የተመራቂ ተማሪዎች ወላጆች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የሚገኙ ይሆናል።
በ10ኛው ሀገር አቀፍ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባዔ ላይ በተወሰነው መሠረት ሁሉም ሰንበት ት/ቤቶች በየክፍሉ በአዲሱ ካሪኩለም እንዲያስተምሩ መወሰኑ የሚታወቅ ነው ::
👉 ለማስታወሻ ያህል ፦ መርሐ ግብሩ በቅድስት ስላሴ ካቴድራል የነበረው በተለያዩ ምክንያቶች ወደ ጠቅላይ ቤተክህነት አዳራሽ የተዘዋወረ መሆኑን እየገለጽን በዕለቱም በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ የተተኪ መምህራን ስልጠና ሲከታተሉ የነበሩ ሰልጣኞችን የማስመረቅ መርሐ ግብር የሚኖር መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን።
🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓🎓
በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት
🌹🌻💐🌹🌻💐🌹🌻💐🌹🌻💐🌹🌻💐🌹🌻🌹💐🌻🌹💐🌻🌹💐🌻🌹💐🌻💐🌹
መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ
ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ፣ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ዘተናገረ በበዓለ ርእሰ ዐውደ ዓመት ዘዕሥራ ምእት ዐሠርቱ ወዐርባዕቱ ዓመተ ምሕረት፡፡
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን !
- በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትገኙ፤
- ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትኖሩ፤
- የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፤
- በሕመም ምክንያት በየፀበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፤
- እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ
ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት
ሰማይንና ምድርን፣ በውስጣቸው የሚገኙ ፍጥረታትን የሚታዩትንና የማይታዩትን የፈጠረ እግዚአብሔር አምላካችን እንኳን ከዘመነ ማቴዎስ 2013 ዓመተ ምሕረት ወደ ዘመነ ማርቆስ ወንጌላዊ 2014 ዓመተ ምሕረት በሰላምና በጤና አደረሳችሁ ፡፡
#ዘይሔድሳ ለምድር በበረከቱ$
‹እግዚአብሔር አምላክ ምድርን በበረከቱ ያድሳታል /ድጓ/›
ቅዱሳት መጻሕፍት እንደሚነግሩን እኛም እንደምንገነዘበው እግዚአብሔር አምላክ በፍጡራን አእምሮ ሊመጠን በማይችል በረከቱ ምድርንና በውስጧ ያሉትን ፍጥረታት ሁሉ በማያቋርጥ ሒደት እያደሰ ይኖራል ፡፡
እግዚአብሔር አምላክ ፍጥረታት እየታደሱ እንዲተካኩ በማድረጉ የቀደመው ሲያልፍ አዲሱ ሲተካ የሕይወት ጉዞ የማያቋርጥ ሆኖ እንዲቀጥል አድርጎአል ፡፡
ከጌታችን ከአምላካችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በፊት የነበረው አሮጌ ዘመን ዓመተ ፍዳ፣ ዓመተ ኩነኔ በእርሱ መሥዋእትነት ሲያሳልፍ ከልደተ ክርስቶስ ጀምሮ ያለውንም የምሕረት ዘመን ብሎ አድሶታል ፡፡
ወደፊትም በዳግም ምጽአቱ ሰማይንና ምድርን በማሳለፍ የተሻለ ሕይወት ለሰው ልጆች መስጠቱ የእግዚአብሔር ፈቃድ መሆኑን ከቅዱስ ወንጌል ተምረናል፡፡ (ማቴ. 24-25)
በመሆኑም ፍጥረታትን የማሳለፉ ተግባር የእግዚአብሔር ቀዋሚ ሥራ ሆኖ እናገኘዋለን ፡፡
እግዚአብሔር አምላካችን በባህርዩ ማርጀትና ኅልፈት የሌለበት ነው፤ በመጻኢው ዓለም ለሰው ልጆች ያዘጋጀው ሕይወትም ማርጀትና ኅልፈት የሌለበት፣ ሁል ጊዜ ሐዲስ ሆኖ የሚኖር ነው፡፡
የሃይማኖታችን ጽኑ ተስፋም በአዲሱ ዓለም ላይ የተመሠረተ ነው፡፡
ይሁንና ወደ አዲሱ ዓለም ለመድረስ በየዘመኑ አዳዲስ ሥራዎችን በመሥራት እግዚአብሔርንና ፍጡራኑን በትጋት ማገልገል ያስፈለጋል፡፡
በዚህ ዓለም በፍጡራን ዓቅም ሊታደስ የማይችል ነገር ቢኖር ሃይማኖት ብቻ ነው፡፡ ከሃይማኖት በቀር ሌላው ሁሉ ለሰው ልጅ በሚጠቅም መንገድ ሊሻሻል፣ ሊስተካከልና ይበልጥ ሊጠቅም የሚችልበትን ዘዴ ተከትሎ ማሻሻል ተገቢ ይሆናል ፡፡
ዓለም ከተፈጠረ፣ ዘመን ከተቆጠረ አንሥቶ እስካሁን ባለበት ብቻ ቆሞ የኖረበት ዘመን የለም፤ በየጊዜው አዳዲስ የአሠራር ስልቶች እየተፈጠሩ፣ በቀጣይም በሌላ አዲስ ስልት እየተተኩ ይኖራሉ፤ ይህም ቀዋሚ የሆነ የእግዚአብሔር ጸጋ ነው ፡፡
ከዚህ አኳያ በተሰናባቹ በ2013 ዓመተ ምሕረት ማብቂያና በአዲሱ 2014 ዓ.ም. መግቢያ ላይ ቆም ብለን ልናስበው የሚገባ ነገር አለ ፡፡
ይኸውም በተሰናባቹ ዓመት የነበረንን አጠቃለይ ሥጋዊና መንፈሳዊ ተግባር መመርመር ሲሆን ያልሠራንባቸው አጋጣሚዎች ካሉም በአዲሱ ዘመን አካክሰን በመሥራት ያመለጠንን ሁሉ በእጥፍ ሠርቶ ለመተካት ጠንክሮ መሥራት ያስፈለጋል ፡፡
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅድስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት፦
አዲሱ ዓመት ሲመጣ የደስታና የተሐድሶ ልቡና ዘመን እንዲሆንልን ከመመኘቱ ጋር በብሩህ ተስፋ መቀበላችን መልካም ነው፤ ይሁንና የሰላምና የእድገት ምኞታችን ወደ ተጨባጭ ፍሬ ሊደርስ የሚችለው በሥራ ብቻ ነው ፡፡
በዓለማችን፣ እንዲሁም በአካባቢያችን የምናያቸው ውብና ድንቅ ነገሮች ሁሉ የሥራ ውጤት መሆናቸውን ለአንድ አፍታ እንኳ ቢሆን ልንዘነጋው አይገባም ፡፡
እግዚአብሔር እኛን የፈጠረ ለሥራ እንጂ እንድንተኛ አይደለም፤ በሥራ ላይ ቸልተኛነትን የምናሳይ ከሆነ ኑሮአችን መመሰቃቀል ብቻ ሳይሆን በእግዚአብሔር ፊት መክሊት ቀባሪ ተብሎ መጠየቅም እንዳለ ማሰብ ይገባናል ፡፡ እንደሚባለውም ‹‹ሰው ለመብላት አይኖርም፤ ለመኖር ይበላል እንጂ፤ እንዲሠራ፡፡››
ለሥራ ክብርን አለመስጠት፣ እግዚአብሔር እኛን የፈጠረበትን ዓላማ እንደመዘንጋት የሚያስቆጥር ይሆናል፤ ይህ ደግሞ ለእኛ የሚበጅ አይደለም ፡፡ (ዘፍ. 1፡3)
እግዚአብሔር ከበረከቱ ያጎደለብን አንዳችም ነገር የለም፤ በየጊዜው አዲስ የሆነ ራዕይ፣ አዲስ የሆነ አሠራር፣ አዲስ የሆነ ጥበብ፣ አዲስ የሆነ ዘመን፣ አዲስ የሆነ ጤንነት ወዘተርፈ ከመስጠት ያቋረጠበት ጊዜ የለም ፡፡
ይሁንና እርሱ የሰጠንን አዲስ የዘመን ስጦታ በአዲስ አስተሳሰብና አሠራር ተቀብለን ካልተጠቀምንበት አዲስ ዘመን ማለቱ ብቻ ከምኞትና ከቃላት ያለፈ ትርጉም ሊኖረው አይችልም፡፡
ዘመኑ አዲስ ሊሆን የሚችለው እኛ በምናበረክተው ሥራ እንጂ ዘመን በራሱ አዲስ ሊሆን አይችልምና እግዚአብሔር አምላክ የሚወዳችሁና እግዚአብሔርን የምትወዱ ልጆቻችንና ወገኖቻችን በሙሉ አዳዲስ ሥራዎችንና አሠራሮችን በመፍጠር አዲሱን ዓመት በሁለመናው አዲስ አድርገን እናክብረው ፡፡
እግዚአብሔር አምላካችን በዓሉን የደስታና የጤና፣ዘመኑን የምሕረትና የሰላም ያድርግልን፡፡ ለሀገራችንና ለመላው ዓለም ሰላምን ይስጥልን፡፡ሕዝባችንን በፍቅርና በአንድነት ያጽናልን፡፡ የተዘራውን ዘር፣ የተተከለውን ተክል ይባርክልን፡፡የተወለዱትን ሕፃናት ያሳድግልን፡፡
መልካም የሥራ ዘመን ያድርግልን !!
እግዚአብሔር አምላካችን ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ ይቀድስ፤
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ
ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም፤
ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
መስከረም 1 ቀን 2013 ዓ.ም
አዲስ አበባ-ኢትዮጵያ
“አይዞህ እነሱ ሞቴን አይተዋል እንጂ እርገቴን አላዩም”
ጌታችን ከሞት መነሳቱን ዘግይቶ የተረዳውና ያመነው ከአስራ ሁለቱ ሐዋርያት አንዱ የሆነው ቶማስ ከሃገረ ስብከቱ ከህንድ ከአገልግሎት በደመና ተጭኖ ሲመለስ እመቤታችን ከሞት ተነስታ ስታርግ መንገድ ላይ ያገኛትና ይደነግጣል። በመቀጠልም የልጅሽንም ትንሳኤ ሌሎቹ አስቀድመው ሲያዩ እኔ ግን ዘግይቼ አየሁ አሁንም ያንቺን ትንሳኤ እና እርገት ሳላይ ልቀር ነበር። ምን አይነት ኃጢአተኛ ብሆን ነው ብሎ በጣም አዘነ።
ያን ጊዜ እመቤታችን ከላይ በርእሳችን ያነሳነውን ሃሳብ “አይዞህ እነሱ ሞቴን አይተዋል እንጂ እርገቴን አላዩም” በማለት አጽናናችው። ማጽናናትም ብቻ አይደለም በስእል ላይ የምናየውን የተገነዘችበትን ጨርቅ ወይም ሰበን ሰጠችው። እርሱም ይህን ደብቆ ይዞ ወደሐዋርያት በመሔድ መነሳቷን ሲነግራቸው ቅዱስ ጴጥሮስ ያኔም ጌታችን ተነሳ ስንል ተጠራጠርክ አሁን ደግሞ የእናቱ ሥጋ በመቃብር መኖሩን አላመንክም ብሎ ወቀሰው።
ከዚያም ተያይዘው ወደ መቃብሩ ቢሄዱ ባዶ ሆኖ አገኙት። እርሱም መነሳቷን እንዲያምኑ የመግነዟን ጨርቅ አውጥቶ አሳያቸው ለበረከትም ቆራርጠው ተከፋፈሉት። ዛሬ ካህናት በእጅ መስቀላቸው ስር የሚያደርጉት ጨርቅ የዚያ ምሳሌ ነው። እመቤታችን እንደልጇ ተነስታ አርጋለች። መፍረስና መበስበስንም አላየችም። ሐዋርያትም ቶማስ ያየውን የትንሳኤዋን ምስጢር እንዴት ሳናይ እንቀራለን ብለው በአመቱ ሱባኤ ገቡ ይህንንም ምስጢር ለመመልከት በቁ።
ዛሬም ሞቷን ያዩ ትንሳኤና እርግማን ለማየት ያልታደሉ ብዙዎች ይኖራሉ። ብዙ ነገርም ሲናገሩ ይሰማሉ። ይሄ ግን የሚሆነው እግዚአብሔር ሲፈቅድ ነው እና ይፍቀድላቸው ከማለት ውጪ ምን እንላለን። እግዚአብሔር ቢፈቅድ የትንሳኤዋን ነገር መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርት በቀጣይ እንማራለን። የአማላጅነቷ ጸጋ አይለየን
እግዚአብሔርን መፍራት
እግዚአብሔርን መፍራት ሲባል በፊቱ መሳቀቅ እና መሸማቀቅ ሳይሆን በፍቅር ሆኖ ትእዛዛቱንን መጠበቅና ማክበር ነው፡፡ ቅዱስ መጽሐፍ እግዚአብሔርን ስለመፍራት ሲገልጽ “የጥበብ መጀመሪያው እግዚአብሔርን መፍራት ነው” ይለናል፡፡ ምሳ 1፡7 ሰው አዋቂ ነኝ ብሎ ካሰበ በመጀመሪያ አዋቂነቱ የሚለካው እግዚአብሔርን በመፍራቱ ነው፤ ምክንያቱም የጥበብ ሁሉ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ስለሆነ፡፡ እግዚአብሔርን መፍራት የሌለበት ዕውቀት፣ ሀብት፣ ስልጣን እና የትኛውም ከፍታና ክብር ሁሉ ከውርደት አይለይም በኋላ ላይ ፍጻሜው በኃጢአት ባህር ሳያሰጥመን አይቀርምና፡፡ ከእግዚአብሔር ባህርያት ውስጥ አንዱ ርሕራሔው ሲሆን ሌላኛው ደግሞ እውነተኛ ፈራጅነቱ ነው፡፡ ዓለም የተንጋደደ ፍርዷን ብትፈርድም፣ ለአስመሳዮች እና ለአታላዮች ለጊዜው ምቾት ብትሰጥም ጊዜው ሲደርስ ግን እውነተኛው ዳኛ ሲነሳ ሁሉም ነገር ይቀያየራል፡፡ የሳቁ ያለቅሳሉ፣ የገፉ ይወድቃሉ፣ ገንዘብና ወርቅን የወደዱ ይነቀላሉ፣ እግዚአብሔርን በመፍራት ራሳቸውን የገዙና ፍላጎታቸውን የተቆጣጠሩ ደግሞ ይከብራሉ የተባረከ ዘመንንም ይጎናጸፋሉ፡፡
ለዚያም ነው ጠቢቡ ሰሎሞን በዚሁ በመጽሐፈ ምሳሌ 10፡27 ላይ “እግዚአብሔርን መፍራት ዘመንን ታረዝማለች፤ የኃጥአን እድሜ ግን ታጥራለች” በማለት የተናገረው፡፡ ንጉስ በዙፋኑ፣ ነጋዴ በንግዱ፣ የስራ ኃላፊ በሹመቱ፣ ሁሉም በያለበት እግዚአብሔርን ፈርቶ ካልታመነ ምድራውያኑን አታልሎ ቢያልፍ እንኳን በእግዚአብሔር መጠየቁ አይቀርም፡፡ ማንም እና ምንም ነገር በእርሱ ፊት የተሰወረ አይደለምና፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ይህን ሃሳብ ሲያጠናክርልን በዕብ 4፡13 “እኛን በሚቆጣጠር በእርሱ አይኖች ፊት ሁሉ ነገር የተራቆተ እና የተገለጠ ነው እንጂ በእርሱ ፊት የተሰወረ ፍጥረት የለም” ብሏል፡፡
ሰው እግዚአብሔርን ከሚፈራ ይልቅ ሰዎችን ይፈራል፤ እግዚአብሔር አየኝ ከሚል ይልቅ ሰው አየኝ ብሎ ይሳቀቃል፡፡ ነፍስንም ስጋንም የሚገድለው እግዚአብሔር እያለ እኛ ግን ደካማውን የሰውን ልጅ እንፈራለን የሰራነውን ነውር እና ኃጢአት ከሰው ለመደበቅ እንሞክራለን፡፡ ሰውን ማክበር እንጂ መፍራት አይገባም ሲባል ብዙ ጊዜ እንሰማለን፡፡ ሰዎች ግን በአባባል ደረጃ ቢናገሩትም እውነታው የተገላቢጦሽ ነው ከእግዚአብሔር ይልቅ ሰዎችን እንፈራለን፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይለናል “ሁሉን አክብሩ፤ ወንድሞችን ውደዱ፤ እግዚአብሔርን ፍሩ፤ ንጉስን አክብሩ” 1ኛ ጴጥ 2፡17
እግዚአብሔርን የምንፈራው በሕይወት ለመኖር እና ለራሳችን ጥቅም እንጂ ለእርሱ የምንጨምረው ነገር ኖሮ አይደለም፡፡ ከሞት ወጥመድ ለማምለጥ እና የመከራንም ዘመን ለማለፍ እርሱን መፍራት ምርጫ የሌለው መንገድ ነው፡፡ ከሁሉ ነገርም ቀዳሚው ተግባር ነው፡፡ ይልቁንም አሁን ባለንበት በዚህ ክፉ የሞት ዘመን ጨለማውን አቆራርጦ ከመንገድ ሳይቀሩ ብርሃኑ ጋር ለመድረስ እግዚአብሔርን መፍራት የሁሉም ነገር መሰረት ነው፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞን በመጽሐፈ ምሳ 14፡27 “ሰው ከሞት ወጥመድ ያመልጥ ዘንድ እግዚአብሔርን መፍራት የሕይወት ምንጭ ነው” እንዲል፡፡ ዛሬ በሃገራችን የምናየው እና የንሰማው ሞትና መተላለቅ፤ ዝርፊያ፤ ውሸት፤ ራስወዳድነት ሁሉ መነሻው ምን ይመስላችኋል? እግዚአብሔርን የሚፈራ ንጉስ፣ እግዚአብሔርን የሚፈራ ሕዝብ ወይም አማኝ፣ እግዚአብብሔርን የሚፈራ አገልጋይ በመጥፋቱ ነው፡፡ ቅዱስ ዳዊት በመዝ 14፡6 “እግዚአብሔርን መፍራት በአይናቸው ፊት የለም” እንዳለ፡፡ አንድ ሰው እግዚአብሔርን መፍራት ካልቻለ ተዳፍሯል ማለት ነው፡፡ እርሱን መዳፈር ደግሞ መጨረሻው ምን ሊሆን እንደሚችል ማሰብ ቀላል ነው፡፡ እንደበደላችን ሳይሆን እንደቸርነቱ የታገሰን ቅዱስ አምላካችን እግዚአብሔር ምስጋና ይድረሰው፡፡ እኛም እርሱን መፍራት በልባችን ኖሮ በቅድስና እንድንኖር ያበርታን፡፡
=+=+=+=+=+=+=+=+=+=+=+=+=+=
ዋኖቻችሁን አስቡ =+= ዕብ ፲፫÷፯
=+=+=+=+=+=+=+=+=+=+=+=+=+=
ይህን ኃይለ ቃል ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለጊዜው ለዕብራውያን ሰዎች የላከላቸው መልዕክቱ ላይ ያስተላለፈው ሲሆን ፍጻሜው ግን በክርስቶስ ክርስቲያን ለተሰኘን ለኛ ለምዕመናን ሁሉ ነው።
ዋኖቻችን እነማን ናቸው ቢሉ ሐዋርያው «የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሯችሁ» በማለት መልሶልናል። እነርሱም ከቀደምት አበው ጀምሮ ነቢያት ሐዋርያት ጻድቃን ሰማዕታት በሙሉ ቅዱሳን ናቸው።
ሙሉውን ጹሑፍ ለማንበብ ፌስቡክ ሊንኩን ይንኩ፡- 👉 Facebook 👇👇👇👇 https://www.facebook.com/nssu.eotcss
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
