ch
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

前往频道在 Telegram

📈 Telegram 频道 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU 的分析概览

频道 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 14 403 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 6 084,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 336

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 14 403 名订阅者。

根据 26 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 541,过去 24 小时变化为 19,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 34.65%。内容发布后 24 小时内通常能获得 N/A% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 988 次浏览,首日通常累积 0 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 33

📝 描述与内容策略

尚未提供频道描述。

凭借高频更新(最新数据采集于 27 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。

14 403
订阅者
+1924 小时
+1197
+54130
帖子存档
''''''''''''ከቅ/ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል እይታዎች''''''' እንኳን ለታላቁ መላእክ ቅዱስ ገብርኤል በዓል በሠላም አደረሰን አደረሳችሁ ። '''''''' እንደሚታወቀው በመጸሐፍ ቅዱስ ““ ሲድራቅንና ሚሳቅን አብደናጎንም ” በሌላ ስማቸው አናንያ አዛርያ ሚሳኤል በትንቢተ ዳንኤል 3፥22 ላይ ተመዝግቦ እንደምናገኘው ከእግዚአብሔር ተልኮ ከእቶን እሳት ያዳነበት ቀን የሚዘከርበት ነው ።!!! ወድ ክርስቲያኖች እነዚህ ወጣቶች ሁለት ግብዣ ቀርቦላቸው ነበር ! ናቡከደነፆር ላቆመው የራሱ ምስል መስገድ አልያም ወደ እቶን እሳት መጣል ሁሌም በዓለም ሳለን የሚቀርብልን ግብዣ ይህ ነው ትልቁ ነገር በምርጫችን ላይ ማንነታችን ይወሰናል። እነዚህ ወጣቶች ግን ምርጫቸው ሳይሆን የሚያስደንቀው በአምላካቸው ላይ ያላቸው ፍጹም እምነት ነው። ለንጉሥ ናቡከደነፆር የመለሱለት ምን ያህል በአምላካቸው ላይ እምነታቸው ፍጹም እንደሆነ የሚያረጋግጥ ነው!!!  ዳን 3፡16 -18 "ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም መለሱ ንጉሡንም፦ ናቡከደነፆር ሆይ፥ በዚህ ነገር እንመልስልህ ዘንድ አስፈላጊያችን አይደለም። የምናመልከው አምላካችን ከሚነድደው ከእሳቱ እቶን ያድነን ዘንድ ይችላል፤ ከእጅህም ያድነናል፥ ንጉሥ ሆይ! ነገር ግን፥ ንጉሥ ሆይ፥ እርሱ ባያድነን፥ አማልክትህን እንዳናመልክ ላቆምኸውም ለወርቁ ምስል እንዳንሰግድለት እወቅ አሉት።" ውድ ክርስቲያኖች እደምን ያለ እምነት! እንደምን ያለ መደገፍ! እንደምን ያለ ጽናት! ነው። እቶን እሳት እያዩ አለመፍራት! አለመንቀጥቀጥ! አለመራድ! ያድነናል በሚል ቃል ብቻ ያልተደገፈ ልዩ የሆነ እምነት ታየባቸው! ይኸውም ባያድነን እንኳ አንተ ላቆምከው ምስል አንሰግድም የሚል ፍጽምና ያለው በሥራ የተገለጠ እምነት ነው። ለዚህ እምነታቸው መልአኩ ብስራታዊው መልአክ ቅ/ገብርኤልን ልኮ ከሚነድ እቶን እሳት አዳናቸው!!! ወድ ክርስቲያኖች እዚህ ላይ ልብ ልንለው የሚገባ ዛሬ ዓለም በብዙ መማለጃ ከአምላካችን እንድንርቅ በእርሱም ላይ መታመን እንዳይኖረን ልታደርገን ትቃትታለች። እርሱም ከአምላካችን ይልቅ ሥልጣንን ፣ ሀብትንና የዓለም ምኞትን ሌላው ቢያቅታት ራስ ወዳድነትን  እርስ በእርስ መጨካከን ብሎም ዘረኝነትን በባልንጀራ ላይ ከፉ ማድረግን እንድንመርጥ ታደርገናለች ለዚህ ምላሻችን ሊሆን የሚገባው ''ዓለም ለምታቀርበው ግብዣ ሁሉ አንሰግድም ሥልጣን ባይኖረን በላይ በመንግስቱ ቦታ አለን ሀብት ባይኖረን ሰማያዊ ሀብት ክርስቶስ አለን! ብለን ዛሬ ታይቶ ነገ ለሚጠፋ አልገዛም በደሙ የዋጃትን ነፍሴን አላቆሽሻትም እነዚህ  ሁሉ ባይኖሩኝም መልአኩን ልኮ ነፍሴን በእቅፉ ሊያኖራት የታመነ ነው!!! ብሎ በእርሱ ላይ መደገፍ  እንዲሁም በመዝሙር 33(34):7 ላይ ቅ/ዳዊት  እንደተናገረው “የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል።” ሊያድኑን የሚችሉ በተሰጣቸው አምላካዊ ጸጋ ስናከብራቸው እና ስንፈራቸው  ሊታደጉን የሚችሉ የእግዚአብሔር ሰራዊቶች መላእክት ዛሬም በእኛ መዳን ውስጥ ደስተኞች እንደሆኑ ልንገነዘብ ይገባል!!!! መላእክት እንኳን በእግዚአብሔር የተደገፈውን ይቅርና በአንድ ኃጥዕ መመለስ ፍጹም ደስተኞች ለአምላካቸውም ምስጋና አቅራቢዎች ናቸው “እላችኋለሁ፥ እንዲሁ ንስሐ ከማያስፈልጋቸው ከዘጠና ዘጠኝ ጻድቃን ይልቅ ንስሐ በሚገባ በአንድ ኃጢአተኛ በሰማይ ደስታ ይሆናል።” ሉቃ 15፥7 እንዲል ወንጌል።  ውድ ክርስቲያኖች በዚህ በዓል ከምንማራቸው ቁም ነገሮች  ውስጥ እምነታችንን ዓለም ሁሉ አንድ ሆኖ ቢገዳደርብን ዓለም በፍትወቷ አንከተልሽም ስንላት ስቀለው ስቀለው  የምትለን ቢሆን እንኳ ''እሷ ጋር ካለው እኛ ጋር ያለው ይበልጣል'' ብለን እምነት ጽናት ሊኖረን ይገባል ከኢያሱ ጋር ሆነን በአንድ ቃል " እኔና ቤቴ ግን እግዚአብሔርን እናመልካለን እናንተ የምታመልኩን ዛሬ ምረጡ" ብለን ጽናትን በሥራ የተገለጠ እምነትን እንዲሁም ስለ አምላካችን መስክሮ መከራን ተቀብሎ የድል አክሊል መቀዳጀትን ተገን ማድረግ እና መላእክት እኛን ለማዳን የሚላኩ የሚያግዙ መሆናቸውን እና በመዳን ሕይወታችን ላይ ድርሻ ያላቸው መሆኑን ማጤን ይገባናል። “ሁሉ መዳንን ይወርሱ ዘንድ ስላላቸው ለማገዝ የሚላኩ የሚያገለግሉም መናፍስት አይደሉምን?” ዕብ 1፥14  እንዲህ ከሆነ የሚያስፈራን ነገር አይኖርም ከእንባቆም ጋራ ይህንን መዝሙር በጋራ እንዘምራለን። ዕንባ 3፡16-19 "እኔ ሰምቻለሁ፥ ልቤም ደነገጠብኝ፤ ከድምፁ የተነሣ ከንፈሮቼ ተንቀጠቀጡ፤ መንቀጥቀጥ ወደ አጥንቶቼ ውስጥ ገባ፤ በስፍራዬ ሆኜ ተናወጥሁ፤ በሚያስጨንቁን ሕዝብ ላይ እስኪመጣ ድረስ የመከራን ቀን ዝም ብዬ እጠብቃለሁ። ምንም እንኳ በለስም ባታፈራ፥ በወይንም ሐረግ ፍሬ ባይገኝ፥ የወይራ ሥራ ቢጐድል፥ እርሾችም መብልን ባይሰጡ፥ በጎች ከበረቱ ቢጠፉ፥ ላሞችም በጋጡ ውስጥ ባይገኙ፥ እኔ ግን በእግዚአብሔር ደስ ይለኛል፤ በመድኃኒቴ አምላክ ሐሤት አደርጋለሁ። ጌታ እግዚአብሔር ኃይሌ ነው፤ እግሮቼን እንደ ዋላ እግሮች ያደርጋል፤ በከፍታዎችም ላይ ያስሄደኛል።" ወስብሐት ለእግዚአብሔር ይቆየን ላእከ ወንጌል ዳርዮስ ፈቃዱ ታኅሣሥ 19 ቀን 2016 ዓ.ም ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/SSUGlobal ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

"እርሱም፦ እነሆ፥ እኔ የተፈቱ በእሳቱም መካከል የሚመላለሱ አራት ሰዎች አያለሁ፤ ምንም አላቈሰላቸውም፤ የአራተኛውም መልክ የአማልክትን ልጅ ይመስላል ብሎ መለሰ።" ዳን 3:25 እንኳን ለሊቀ መልአኩ
"እርሱም፦ እነሆ፥ እኔ የተፈቱ በእሳቱም መካከል የሚመላለሱ አራት ሰዎች አያለሁ፤ ምንም አላቈሰላቸውም፤ የአራተኛውም መልክ የአማልክትን ልጅ ይመስላል ብሎ መለሰ።" ዳን 3:25 እንኳን ለሊቀ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በሠላም አደረሳችሁ! በዚህ ዕለት መልአኩ ሠልስቱ ደቂቅን ከእቶን እሳት ያዳነበት መታሰቢያ ነው! የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! መልካም በዓል! ✍️Youtube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

++ በሦስቱ ወጣቶች እምነት የእሳት ኃይል በእሳት ጠፋ ዳን 3÷1-30!! ++ እግዚአብሔርን የካደ በጉልበቱ የተመካ ሥልጣንን ክብርን ባዕለጠግነትን መፈራትን የሰጠውን ፈጣሪውን የዘነጋ ሰው ንጉሥ ናቡከደነጾር በባቢሎን ምድር በዱራ ሜዳ ላይ ቁመቱ ስድሳ ክንድ ወርዱም ስድስት ክንድ የሆነ የወርቅ ምስል አቁሞ ሕዝቡ በሙሉ ለእርሱና ለጣዖት ይሰግዱ ዘንድ አዋጅን አወጀ ፡፡ ሕዝቡም አዋጁን ተከትለው ንጉሥ ላቆመው ጣዖት እንደ ግንድ እየተረበረቡ እንደ ሻሽ እየተነጠፉ ይሰግዱ ጀመር ፡፡ እግዚአብሔር ሀገርን ዘመንን ያለ ደጋግ ሰዎች አይተውምና ስቶ በጣዖት ፍቅር ነድዶ ተጨልጦና ተገርኝቶ በጠፋው ሕዝብ መካከል በእድሜያቸው ለጋ የነበሩ ሦስቱን ወጣቶች ለምሥክርነት አገኘ ፡፡ ሦስቱ ወጣቶች እንደተቀረው ሕዝብ ንጉሥ ንጉስ ላቆመው ምስል ሰግደው ለምን? ሲባሉ እምነት በልብ ነው አስመሰልን እንጂ አልሰገድንም ያለነው በባዕድ ሀገር ያውም በምርኮ ነው በባዕድ ሀገር ያለ ሰው ደግሞ ቢጭኑት አህያ ቢለጉሙት ፈረስ ነው ስለዚህ ብንሰግድ ምንም ማለት አይደለም የሰገድነው ወጣትነታችን አታልሎን አፍላነታችን ገፍትሮን ነው እንኳን እኛ ሮጠን በልተን ያልጠገብነው ጎልማሶቹ ሽማግሎቹ አዛውንቱ ሰግደው የለምን? ኋላ ንስሐ እንገባለን ይገድሉናል ብለን ፈርተን ነው የሚሉና ሌሎች ብዙ ሰንካላ ምክንያቶችን ማቅረብ ይችሉ ነበር፡፡ እነርሱ ግን ለስህተትና ለጥፋት ምክንያት አበጅተው ፈጣሪያቸውን ክደው ለጣዖት አልሰገዱም ፡፡ በዚህም ታላቅ እምነታቸውና ተጋድሏቸው ቅዱስ መጽሐፍ ለዘላለም ሲያወሳቸው እውነተኛ ክርስቲያኖችም ሲመሰክሩላቸው ይኖራሉ፡፡ +++ የሦስቱ ወጣቶች ታላቅ እምነት +++ በዚህ ዘመን ያለን ሰዎች እግዚአብሔርን የምናመልከው የምናገለግለው አስከሞላልን እስከተሳካልን እስከጠገብንና እስከተመቸን ብቻ እንጂ ከጎደለብን ካጣን ከተቸገርን እርሱን ለማምለክና ለማገልገል ፈቃደኞች አይደለንም ፡፡ እነዚህ ወጣቶች በንጉሡና ባነደደው እሳት ፊት ቆመው "ንጉሥ ሆይ አምላካችን ከሚነደው እሳት ሊያድነን ይቻላል ባያድነን እንኳ አንተ ላቆምከው ምስል አንሰግድም " ዳን 3÷17-18 በማለት ሲሞላልን ብቻ ሳይሆን ሲጎድልብንም ፤ ስናገኝ ብቻ ሳይሆን ስናጣም ፤ ጤና ስንሆን ብቻ ሳይሆን ጤናችን ሲናጋና ስንታመምም ፤ ሲሰጠን ብቻ ሳይሆን ሲነሣንም ፤ እርሱን በእውነት በሙሉ ልብና በመንፈሳዊ ደስታ ማምለክ ማመስገን እንደሚገባ አስተማሩን ፡፡ ኢዮባዊ እምነት ይህ ነውና ፡፡ +++ እነርሱ በእምነት መንግሥታትን ድል ነሡ +++ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ጦር ሳይሰብቁ ዝናር ሳይታጠቁ በጦር አንደበት በፈረስ አንገት ሳይዘምቱ ንጉሥ ናቡከደነጾርንና መኳንንቱን እግዚአብሔርን ይዘው ድል የነሱ እነዚህን ወጣቶች "እነርሱ በእምነት መንግሥታትን ድል ነሡ" ዕብ 11÷33 ብሎ ይመሠክርላቸዋል ፡፡ በዚህም "ዓለምን የሚያሸንፈው እምነታችን ነው" 1ኛ ዮሐ 5÷4 የሚለውን ቃል አማናዊነት አረጋገጡልን ፡፡ ቤተክርስቲያንም የሐዋርያውን ቃል ቃል አድርጋ ይህን እምነታቸውንና ተጋድሏቸውን ለዓለም ሁሉ ትመሠክራለች ቤተክርስቲያን (ምእመናን) በፈተናና በመከራ ያለች ተጋዳይ (millitant) እንዲሁም ድል አድራጊ መሆኗንም ከእነርሱ ተጋድሎና ድል አድራጊነት ተምረናልና ፡፡ ዛሬ የመጠጥ ሱስ ߹ የወሬ ሱስ ߹ ሰውና ሰው የማጋጨት ሱስ ሰውነታችንን ድንኳን ልቡናችንን ዙፋን አድርጎ መንግሥት የሆነብን እንዲሁም የዚህ ዓለም (ፈጣሪውን የካደ ዓለም) ገዥ የተባለ ዲያብሎስ ከእምነት ሊያስወጣን ስፍራችንን ሊያስለቅቀን በመጨረሻም እንደ መንግሥት በራሳችን ላይ ነግሦ ወደ ወረደበት ጥልቅ ሊያወርደን የሚታገለን ሰዎች ካለን በእምነት ሁሉን ማሸነፍ እንደሚቻል ሦስቱ ወጣቶች የተግባር መምህራን ይሆኑናል ፡፡ +++ የእሳትን ኃይል አጠፉ +++ ሠለስቱ ደቂቅ ለጣዖት ባለመስገዳቸው ወደ እቶን እሳት እንዲወረወሩ ተፈረደባቸው ተወረወሩም ፡፡ ያመኑት የታመኑበት ፈጣሪያቸው መልአኩን ልኮ የእሳቱን ኃይል አጠፋላቸው ፡፡ የእነርሱ ሰናፊላቸውን እንኳ ሳይለበልብ እነርሱን የጣሉ በእሳቱ ወላፈን ነድደው ሞቱ ፡፡ ይህን የሚንበለበል እሳት እግዚአብሔር መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ያጠፋው በእነዚህ ወጣቶች እምነት ምክንያት እንደሆነ ሐዋርያው ሲመሰክር "በእምነት የእሳትን ኃይል አጠፉ" ዕብ 11÷ 34 ብሏል :: ክፉዎች ባቀጣጠሉት እሳት ሲነድዱ በወላፈኑም ሲለበለቡ ደጋጎቹ ግን በእምነት የዘረኝነትን የዕብሪትን የዝሙትን የጥንቆላን የመተትንና ሌሎች እንደ እሳት የሚፈትኑ ነገሮችን ሊያጠፉ እንደሚችሉ ሐዋርያት አስተምረውናል 1ጴጥ 4÷12 ፡፡ +++ እሳት የእሳትን ኃይል አጠፋ +++ ቅዱሳን መላእክት እሳታውያን ናቸው ዕብ 1÷7 ፡፡ እሳታውያን በመሆናቸውም አንድ መልአክ ሲገለጥ ከክብሩ የተነሳ ምድር እንኳን ይበራል "ሌላም ብርቱ መልአክ ደመና ተጎናጽፎ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ ፊቱም እንደ ፀሐይ እግሮቹም እንደ እሳት አምዶች ነበሩ " ራእይ 10÷1 "ከዚያ በኋላ ታላቅ ሥልጣን ያለው ሌላ መልአክ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ ከክብሩም የተነሣ ምድር በራች" ራእይ 18÷1 ተብሎ እንደተጻፈ ፡፡ ሊቀ መላእክት መጋቤ ሐዲስ አብሣሬ ትስብዕት የሆነ ቅዱስ ገብርኤልም ከእነዚህ እሳታውያን ቅዱሳን መላእክት አንዱ ነውና ወደ እቶን እሳት ከተወረወሩት ሦስቱ ወጣቶች ጋር አራተኛ ሆኖ በመግባት እሳቱ እየነደደ የእሳቱን ኃይል አጠፋ እሳቱ እየነደደ የማቃጠል ኃይሉን አበረደው ፡፡ ይህ እንዴት ያለ ተአምር ነው ? እንግዲህ ምን እንላለን ? በዚህ ዘመን እንደ እሳት እየነደደ ከሚፈትነን ነገር ሁሉ የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ያድነን የጌታ መልአክ በሚፈሩት ዙርያ ይሰፍራል ያድናቸውማልና መዝ 33÷7 ፡፡ የሠለስቱ ደቂቅ በረከታቸው እምነታቸው ይደርብን መልአኩም ጥበቃ አይለየን !! ቢትወደድ ወርቁ ታኅሣሥ 18 ቀን 2011 ዓ.ም ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/SSUGlobal ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

"እነሆ፥ እውነትን ወደድህ፤ የማይታይ ስውር ጥበብን አስታወቅኸኝ።" መዝ 50፡5 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️Youtube 👇 https
"እነሆ፥ እውነትን ወደድህ፤ የማይታይ ስውር ጥበብን አስታወቅኸኝ።" መዝ 50፡5 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️Youtube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

"ቅድስትና ያለ ነውር ትሆን ዘንድ ክብርት የሆነችን ቤተ ክርስቲያን ለራሱ እንዲያቀርብ ፈለገ።" ኤፌ 5፡27 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት!
"ቅድስትና ያለ ነውር ትሆን ዘንድ ክብርት የሆነችን ቤተ ክርስቲያን ለራሱ እንዲያቀርብ ፈለገ።" ኤፌ 5፡27 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️Youtube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

"የአማልክትን አምላክ አመስግኑ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።" መዝ 135፡2 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️Youtube 👇 https://w
"የአማልክትን አምላክ አመስግኑ፤ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና።" መዝ 135፡2 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️Youtube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት የደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ሰ/ት/ቤት የልዩ ፍላጎት የአገልግሎት ክፍል 9ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን አከበረ ፤ 15-04-2016 ዓ.ም (የሰንበት ት/ቤቶ
+8
በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት የደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ሰ/ት/ቤት የልዩ ፍላጎት የአገልግሎት ክፍል 9ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን አከበረ ፤ 15-04-2016 ዓ.ም (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) በመርሐ ግብሩ ላይ የደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ የሆኑት መልአከ ብርሃን ቆሞስ አባ ይትባረክ የተገኙ ሲሆን ከኅዳር 21 2007 ዓ.ም ጀምሮ በከተማው የሚገኙ መስማት የተሳናቸው ክርስቲያኖች ባቀረቡት ጥያቄ መሠረት ሰንበት ት/ቤቱ የልዩ ፍላጎት አገልግሎት እንደጀመረ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተቀዳሚ ምክትል ሰብሳቢ ዲ.ን ስንታየው ማሩ ገልጸዋል። በአሁንም ሰዓት ከ30 የሚበልጡ የልዩ ፍላጎት አገልጋዮች የሚገኙ ሲሆን የተለያዩ መንፈሳዊ ተከታታይ ትምህርቶችን በምልክት ቋንቋ እየተማሩ ፣ መዝሙራትንም እያጠኑ በማገልገል ላይ ይገኛሉ። በትላንትናውም ዕለት ቁጥራቸው 20 የሚሆን መስማት የተሳናቸው አባላት ትምህርታቸውን አጠናቅቀው ተመርቀዋል። በምረቃ መርሐ ግብሩም ላይ ዓባላቱ መዝሙር ፣ የጥያቄ እና መልስ ውድድር እንዲሁም መንፈሳዊ ተውኔት ለታዳሚዎች አቅርበዋል። (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

"ቤቱም የእውነት ዓምድና መሠረት፥ የሕያው እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ነው።" 1ኛ ጢሞ 3፥15 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! መልካም ዕለተ
"ቤቱም የእውነት ዓምድና መሠረት፥ የሕያው እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ነው።" 1ኛ ጢሞ 3፥15 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! መልካም ዕለተ ሰንበት! ✍️Youtube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

"የመቅደሳችን ስፍራ ከጥንት ጀምሮ ክፍ ያለ የክብር ዙፋን ነው።" ኤር 17፡12 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️Youtube 👇 https
"የመቅደሳችን ስፍራ ከጥንት ጀምሮ ክፍ ያለ የክብር ዙፋን ነው።" ኤር 17፡12 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️Youtube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu