ch
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

前往频道在 Telegram

📈 Telegram 频道 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU 的分析概览

频道 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 14 309 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 6 167,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 365

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 14 309 名订阅者。

根据 21 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 502,过去 24 小时变化为 16,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 48.88%。内容发布后 24 小时内通常能获得 13.10% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 0 次浏览,首日通常累积 1 875 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 0

📝 描述与内容策略

尚未提供频道描述。

凭借高频更新(最新数据采集于 22 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。

14 309
订阅者
+1624 小时
+1117
+50230
帖子存档
በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤት በሊቃውንት ጉባኤ አዘጋጅነት ለሦስት ተከታታይ ቀናት በዘርፈ ብዙ የቤተክርስቲያን ጉዳዮች ላይ ሲመክር የቆየው የሊቃውንት የምክክር ጉባኤ ባለ 14 አንቀጽ የጋራ የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቋል። የመግለጫው ሙሉ ሐሳብ እንደሚከተለው ይነበባል። ============================ ሚያዚያ 22 ቀን 2017ዓ.ም አዲስአበባ እኛ ሊቃውንት እንደምንረዳው ጉባኤ ኒቅያ በምንልበት ጊዜ በቤተ ክርስቲያን አነጋገር ጉባኤ ተደረገ ሲባል ሰዎች ተሰብስበው ይህን ማመን አለብን ያንን መተው አለብን ብለው በድምጽ ብልጫ ተስማምተው የጋራ መግለጫ አወጡ ማለት ሳይሆን ሰፊ እርሻ /ሁዳድ/ ያለው ገበሬ በአዝመራው መሐል እህሉን መስሎ አዝመራውን የሚጎዳ የሚያበላሽ አረም ሲበቅልበት ከእህሉ መካከል አረሙን በጥንቃቄ ነቅሎ እንደሚጥል ሁሉ ቤተ ክርስቲያንም ክርስቶስን በዓይኗ ዓይታ ትምህርቱን በጆሮዋ ሰምታ በአጠቃላይ ቤተ ክርስቲያን በአባቶቻችን በሐዋርያት አማካይነት የቃሉን ትምህርት የእጁን ተአምራት ዓይታ በምታውቀውና በምታምነው እውነተኛ ሃይማኖት መሐል የራሷን እምነት ሳይሆን ተመሳስሎ የሚጎዳትን የመናፍቃን የአስተሳሰብ አረም ነቅላ ለመጣል አረሙን ነቅላ ትምህርት አዝመራዋን ትከላከላለች፡፡በኒቅያ ጉባኤም የተደረገው ይኸው ነው አረም አርዮስ ተነቀሎ የክርስቶስ አምላክነት በምላት በስፋት ተነገረ የሃይማኖት መግለጫ የሆነው ጸሎተ ሃይማኖት ጸደቀ ፡፡ እኛም የሠለስቱ ምዕት የልጅ ልጆች የኢትዮጵያ ሊቃውንት በቤተ ክርስቲያናችን ላይ የበቀለውንና እየበቀለ ያለውን አረም በትምህርት የአረም ማጥፊያ መድኀኒትነት ለመንቀል ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ለመጠበቅ ምእመናንን ለማጽናት በዚህ በመንበረ ፓትርያርክ ቅጽረ ግቢ ተሰብስበን መክረን ተወያይተን- 1. ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በጉባኤው መክፈቻ የሰጡትን ቃለ ምእዳን አባታዊ መመሪያና ቡራኬን በመቀበል የሰጡትን አባታዊ መመሪያ በየመጣንበት ጉባኤ ቤት ሥራ ላይ ለማዋል ቃል እንገባለን፡፡ 2. ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፤የባሕር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በጉባኤው መክፈቻና በየመርሐ ግብሩ መካከል ያስተላለፉትን የሥራ መመሪያ ወቅቱ በሚጠይቀው ቤተ ክርስቲያን በምትፈልገው ምእመናን ለሚጠይቁት ጥያቄ ሁሉ ምላሽ ለመስጠት በየጉባኤ ቤታችን ከማስተማር ከማገልገል ባሻገር እንደአባቶቻችን ለሃይማኖታችን አለኝታና ጠበቃ ሆነን ለመሥራት ቃል እንገባለን፡፡ 3. ጥንታዊት ሐዋርያዊት የሆነችውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በረጅም ታሪኳ ውስጥ ባሳለፈቻቸው አጋጣሚዎች ሁሉ ያካበተችውን የእቅበተ እምነት (ሃይማኖት) ልምድ ከመጀመሪያው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ያሉትን የዐቃብያነ ሃይማኖት ተጋድሎዎች በመረዳት ቅብብሎሹን ለማስቀጠል ቃል እንገባለን፡፡ 4. አሁን ባለንበት ክፍለ ዘመን ከሚከሠቱት አሉታዊ ግድፈቶችና ሥርዋጾች መካከል በቅዱሳት መጻሕፍት፣ በገድላት፣በድርሳናትና በታአምራት የቤተ ክርስቲያን አዋልድ መጻሕፍት በመከለስ በመሸቀጥና በመበረዝ መንፈሳዊነታቸውን ለቀው የተዛባ ሐሳብ እንዲኖራቸው ከእግዚአብሔር ፈቃድና ሐሳብ እንዲወጡ የሚደረገው ሴራ እጅግ አደገኛ ነው፡፡ስለሆነም ጥንታውያን በቀኖና መጻሕፍት የተሠፈሩና የተመዘኑ መጻሕፍቶቻችን ባሉበት ሁኔታ ተጠብቀው ይቀጥሉ ዘንድ እኛ የጉባኤ መምህራን የመጻሕፍቱ ጠበቃ በመሆን በሊቃውንት ጉባኤ በኩል ያላለፉ በትንሣኤ ማሳተሚያ ድርጅት አሳታሚነት ያልታተሙ መጻሕፍት ባለመጠቀም ደቀ መዛሙርትና ምእመናን እንዳይገለገሉባቸው ለማስተማር ቃል እንገባለን፡፡ 5. የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሥዕላት፣መስቀል፣ሥነ ሕንፃና ኪነ ጥበብ ይዘትና ቅርጽ በቀኖና ቤተ ክርስቲያን የተለካ ሃይማኖታዊ ምሳሌነታቸው እንደ መጻሕፍት የሚነበብ እንደሰው የሚናገሩ እንደ መምህራን የሚያስተምሩ ንዋያት ናቸው፤ስለሆነም እነዚህን ንዋያተ ቅድሳት በየዘመኑ የሚነሱ የውስጥና የውጭ አጽራረ ቤተ ክርስቲያን የተለያየ ስሜት እንዲፈጥሩ የሚሰጡት ትርጉም እንዲዛባ ለማድረግ የሚያደርጉት ሙከራ እጅግ ብዙ ነው አባቶቻችን በብዙ ውጣ ውረድ ያቆዩልንን የስገኙልንን እነዚህን ንዋያተ ሃይማኖት ጠብቀን በማስጠበቅ ጥቅማቸውን በማስተማር ባሉበት ሁኔታ ለትውልድ ለማስተላለፍ ምትክ የሌለውን ድርሻችንን ለመወጣት ቃል እንገባለን፡፡ 6. አጽራረ ቤተ ክርስቲያን የሀገሪቱን የውስጥ ሁኔታ በማጤን ራሳቸው በሚሰጡን አጀንዳ በሚፈጠር የተዛባ የፖለቲካ አመለካከት የመሪዎችን አቋምና ትከሻ በመለካት በሚገኝ አጋጣሚ ሁሉ በመጠቀም ሠርጎ በመግባት ኑፋቄን በመዝራት በቀኖና፣በታሪክና በትውፊት በምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን በዜማ በቅዳሴ በትርጓሜ በበዓላት አከባበር ላይ ሁሉ ኦርቶዶክሳዊ ያልሆኑ እንግዳ ነገሮችን ሊያሸክሙን እንደሞከሩና አንዳንዶቹም አዳዲስ ትርክት እንደጫኑብን ታሪክ እንደቀየሩብን በማኅበረሰቡ ውስጥ ቅራኔ እንደፈጠሩብን ከቀረቡት ጥንታዊ ጽሑፎች ተረድተናል፡፡ስለሆነም የደረሱብን ችግር የቀኖና የትውፊት የታሪክ ተፋልሶ ስህተቶችን በማኅብረሰቡ ውስጥ ሠርጎ የገባ የትርክት አረሙን ከስንዴው በጥንቃቄ በመለየት ወደ ጥንታዊ ማንነታችን ለመመለስ የሚጠበቅብንን ሁሉ ረድኤተ እግዚአብሔርን አጋዥ በማድረግ ለመሥራት ቃል እንገባለን፡፡ 7. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከተመሠረተች ጀምሮ መከፋፈል ያልገጠማት የተማከለ የአስተዳደር መርሕ ስለምትከተልና ወጥ በሆነ የአሰራር መዋቅር ስለምትመራ መሆኑ የታወቀ ነው፤ስለሆነም ከቤተ ክርስቲያናችን ኣንጻር የተማከለ ኣሰራር የተሻለ ውጤት እንዳለው ለቤተ ክርስቲያናችን ሃይማኖትና ሥርዐት መጠበቅ ጠቃሚ መሆኑን ስለተገነዘብን ማእከላዊ መዋቅራችንን ለመጠበቅና ለማስጠበቅ የበኩላችንን ድርሻ ለመወጣት ተስማምተናል፡፡ 8. በአምስት ሊቃውንት ቅዱሳን ስም በቡድን ተከፋፍሎ በየርእሱ የተደረገው ውይይትና የመፍትሔ ሐሳብ ቀርቧል፡፡ቡድኑ የተወያየበት ሠነድ የዚህ ቃለ ጉባኤ አካል በማድረግ ጥቅል ሠነዱ ለቅዱስ ሲኖዶስ እንዲቀርብ የሚድረግ ሆኖ ለማሳያ ያህል በክብዙ በጥቂቱ በአቋም መግለጫ እንዲወጣበት አድርገናል፡፡በዚህም መሠረት ሀ. በነገረ ማርያምንና በነገረ ክርስቶስን ዙሪያ በጉባኤው ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን በዚህ ዙሪያ ውይይት ያደረገው ቡድን ለሚነሱ ጥያቄዎች ሰፊ ምላሽ የሚሰጡ ከቅዱሳት ማጻሕፍት በማጣቀስ የውይይቱን ውጤት አቅርቧል በዚህም መሠረት፡- እመቤታችን በተመለከተ ጊዜውን ተደራሽ ያደረጉ ጥያቄዎች ጥንተ አብሶን፣ ቤዛዊተ ዓለም፣ አማላጅነት፣የጌታችን ወንድሞችና የእመቤታችን ትንሣኤና ተያያዝ ጥያቄዎች በቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ መሠረት ሰፊ ውይይትና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል ስለሆነም ቅዱሳት መጻሕፍትን መሠረት በማድረግ አባቶቻችን ነቢያት፣ አባቶቻችን ሐዋርያት ቀደምት ሊቃውንት ያቆዩልንን የነገረ ማርያም ትምህርት ዛይበረዝ ተጠብቆ ለትውልድ እንዲተላለፍ ጠንክረን እናስተምራለን፡፡

ቋሚ ሲኖዶስ ልዩልዩ ውሳኔዎችን አስተላለፈ። *********************************** ሚያዚያ ፳፪ ቀን ፳፻ ፲ዘ፯ ዓ.ም +++++++++++++++++++ አዲስአበባ -ኢትዮጵያ """"""""""""""""""""""""""" ቋሚ ሲኖዶስ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ከቤተክርስቲያናችን የነገረ ማርያም አስተምህሮ ውጪ በፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበር አዳራሽ የሰጡትን ትምህርትና በማኅበሩ ሚዲያ የተላለፈበትን ሁኔታ በተመለከተ በዛሬው መደበኛ ጉባኤው በሰፊው ተወያይቶ ለመወሰን በያዘው ቀጠሮ መሰረት በጉዳዩ ዙሪያ ጥልቅ ውይይት ካደረገ በኋላ የሚከተሉትን ውሳኔዎችን አስተላልፏል። 1. ፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማህበር በተለያዩ ጊዜያት ከቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ ውጪ በሚዲያው ያስተላለፈው የስሕተት ትምህርት የቤተክርስቲያናችንን አባቶች፣ሊቃውንቱንና መላው ሕዝበ ክርስቲያኑን ያሳዘነ በመሆኑ በማህበራት ምዝገባ ክትትልና ቁጥጥር መምሪያ በኩል ጊዜያዊ የእገዳ ደብዳቤ እንዲደርሰው እና በመምሪያው በኩል አስፈላጊው ጥብቅ ክትትል እንዲደረግ ሆኖ በጉዳዩ ላይ የመጨረሻ ውሳኔ መስጠት ይቻል ዘንድ አምስት አባላት ያሉት ኮሚቴ እንዲቋቋም አድርጓል። በዚህም መሰረት ቋማ ሲኖዶስ ያቋቋማቸው አጣሪ ልዑካን አጠቃላይ የማህበሩን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ እና በሚዲያው ያስተላለፋቸውን የስህተት ትምህርቶች በተመለከተ ከጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት እና ከማህበራት ምዝገባ፣ ቁጥጥርና ክትትል መምሪያ ጋር በመነጋገር በሚገባ መርምርውና አጣርተው በአጭር ጊዜ ውስጥ ከውሳኔ ሐሳብ ጋር ለቋሚ ሲኖዶስ እንዲያቀርቡ፣ 2. ብፁዕ አቡነ ገብርኤል “ማርያም ቤዛዊተ ዓለም” አትባልም በማለት ከቤተ ክርስቲያናችን የነገረ ማርያም አስተምህሮ ውጪ የሰጡት ሕጸጽ ያለበት ትምህርት በሊቃውንት ጉባኤ በኩል በሚገባ ተመርምሮና ተጣርቶ ከመፍትሔ ሐሳብ ጋር ለቋሚ ሲኖዶስ በአስቸኳይ እንዲቀርብ ብፁዕነታቸውም ጉዳዩ ተጣርቶ የመጨረሻ ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው በተአቅቦ እንዲቆዩ፣ 3. ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የደቡብ ኦሞና አሪ ዞኖች ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት እና ብፁዕ አቡነ በርናባስ የደቡብ ካሊፎርኒያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ያስተላለፏቸው የስሕተት ትምህርቶችና በሌሎችም መምህራን የተላለፉ ነቀፋ ያለባቸው ትምህርቶች ካሉ የሊቃውንት ጉባኤ ከቤተ ክርስቲያኒቱ አስተምህሮ አንጻር በሚገባ መርምሮና አጣርቶ ከመፍትሔ ሐሳብ ጭምር በአጭር ጊዜ ውስጥ ለቋሚ ሲኖዶስ እንዲያቀርብ፣ 4. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መገናኝ ብዙኃን ስርጭት ድርጅት ለፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማህበር ሚዲያ የአየር ሰዓት የሰጠበትን ዝርዝር ሁኔታና ከማኅበሩ ጋር በተያያዘ አየር ላይ ያዋላቸውን ትምህርቶች የሚያሳይ ሪፖርት እንዲያቀርብ ይደረግ በማለት ቋሚ ሲኖዶስ ወስኖ የዕለቱን ጉባኤ በቅዱስነታቸው ጸሎተ ቡራኬ አጠናቋል። መረጃው የ/ኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ/Department of Public Relation ,EOTC ነው።

3. በሕግ ከተሰጣቸው መብት ውጪ በማስተማር የሚሰማሩ ማኅበራትን በሕግ አግባብ ወደ መስመር አለማስገባት የሰሞኑ ስሁት ትምህርት በሕጋዊ ዕውቅና ስም የሚንቀሳቀሱ ማኅበራት እኩይ ተግባር ከትናንት የቀጠለ የብልሹ አስተዳደር መገለጫ ነው። የማኅበራት አስተዳደር ደንብ ፀድቆ ሥራ ላይ ከመዋሉ በፊት ደንቡ ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን በማስረጃ በማስደገፍ የማሻሻያ ሐሳብ ብናቀርብም ተቀባይነት ሳያገኝ ቀርቷል። በመሆኑም የፈራነው ደርሶ ፤ ደንቡን ለማስፈፀም የተቀመጠው የማኅበራት ምዝገባ ክትትል እና ቁጥጥር መምሪያ፤ በማኅበራት አስተዳደር ደንብ አንቀጽ ፲ ላይ የማኅበራት ዓለማ "ለትምህርት ተጠሪ ተቋማት ድጋፍ መስጠት ነው" በሚል የተደነገገ ቢሆንም እንደ ‹‹ፍኖተ ጽድቅ›› ያለ ማኅበር ድጋፍ ሰጪ ሳይሆን ፈፃሚ ሆኖ፣ ማኅበሩ ከተመሠረተበት ዓላማ ውጭ ትምህርተ ወንጌልን በአዳራሽ ውስጥ ሲሰጥ፤ በሚዲያ ትምህርት ሲያስተላልፍ አልፎ ተርፎ የቤተ ክርስቲያን መዝሙሮቿን ከሥርዓቷና ከቀኖናዋ ውጪ በሆነ ሁኔታ በሚዲያ እያቀናበረ ሲያስተላልፍ ተገቢው አስተዳደራዊም ሆነ ቀኖናዊ እርምጃ እንዲወሰድ ከማድረግ ይልቅ በማኅበርነት በመመዝገብ እንዲሁም በደንቡ የተሰጠውን የመቆጣጠር ሓላፊነት የማኅበራት ማደራጃ ምዝገባ ክትትል እና ቁጥጥር መምሪያ ባለመወጣቱ ዛሬ ለደረሰው ስሑት ትምህርት ዝግጅትና ስርጭት አብቅቶናል፡፡ ይኽ ማኅበር ከኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተህምሮ ውጪ ስሑት ትምህርት የሚሰጥበት ተቋም እንደሆነ በተጨባጭ እየታወቀ እና በአካል ቀርበው አረጋግጠው እንኳን ቅዱስ ፓትርያርኩን በዚያ ሥፍራ እንዲገኙ በማድረግ ቤተ ክርስቲያንን አሳልፈው የሰጡ የቤተክርስቲያኒቱ አገልጋዮች መኖራቸው የአደባባይ ሐቅ ነው፡፡ በመሆኑም ከዚህ በታች የዘረዘርናቸው ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ተገቢው ትኩረት እንደሚሰጣቸው እና የእርምት እርምጃ እንደሚወሰድባቸው እናምናለን። 1. የሊቀ ጳጳሱ ኢ-ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮ በቅዱስ ሲኖዶስ ቀኖናዊ እርምጃ እንደሚወሰድበት ብናምንም በሚገባ እና በትኩረት ጉዳዩ እንዲታይና መፍትሔ እንዲሰጠው፡፡ እንዲሁም በተመሳሳይም ስሑት ትምህርቶችን የሚያስተምሩ እና ያስተማሩ ሌሎች ጳጳሳት እና መምህራን ጉዳይም አብሮ እንዲታይ፣ ይኽን አጋጣሚ ተጠቅሞ የሊቃውንት ጉባኤም በስሑት አስተምህሮዎች ላይ ተገቢውን ምላሽ እንዲሰጥ ቢደረግ፡፡ 2. ሓላፊነቱን በአግባቡ ያልተወጣው የማኅበራት ምዝገባና ክትትል እና ቁጥጥር መምሪያ ከሊቀ ጳጳሱ ጀምሮ በየደረጃው ያሉ ሓላፊዎች እንዲጠየቁ፡፡ 3. የማኅበራት ምዝገባ ክትትልና ቁጥጥር መምሪያ የዕውቅና ሰርተፊኬት ከመቸርቸር ወጥቶ፣ ደንቡና አሠራሩን ዳግመኛ በመፈተሽ፣ የዕውቅና አመዘጋገብ፣ ክትትልና ቁጥጥር ሒደቱም ንጥር ያለ እና መስፈርቶች የወጡለት እንዲሆን፡፡ 4. ቅዱስ ፓትርያርኩን በማሳሳት " ፍኖተ ጽድቅ " በተባለው ማኅበር ዝግጅት ላይ እንዲገኙ ያደረጉ የቅዱስ ፓትርያርኩ ልዩ ጽ/ቤት ሓላፊና የፖትርያርኩ የፕሮቶኰል ሹም እንዲጠየቁ፡፡ 5. ‹‹ፍኖተ ጽድቅ›› የተሰኘው ማኅበር በቤተክርስቲያን ላይ እያደረሰ ያለውን የተሐድሶ ኑፋቄ ትምህርት ባለማረሙ ምክንያት ማኅበሩ የምዝገባ ፈቃዱ ተሰርዞ ባስተላለፈው ትምህርቶች በቀኖና እንዲጠየቅ እና በዚሁ አጋጣሚ ከመምህራን እስከ ሊቃነ ጳጳሳት “ፍኖተ ጽድቅ” ከተባለ ማኅበር ጋር የጀመሩት በነዋይ ላይ የተመሠረተ ግንኙነት በአስቸኳይ እንዲቆም እንዲደረግ። እንዲሁም በቤተ ክህነቱ የበላይ ሓላፊዎች በኩል እናት ቤተ ክርስቲያናችን አንዳች ሳይጎድልባት ባልተገባ መሻት ከባለ ጸጋ እጅ ለማኝ በማድረግ ቅድስት ቤተክርስቲያንን የማዋረድ እና አሳልፎ የመስጠት እኩይ ተግባር እንዲቆም። 6. የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ኦርቶዶክሳዊት ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ አገልግሎቷን እንዳታሰፋ እጅ ተወርች ቀፍድዶ የያዛት ደካማ፣ ብልሹ አስተዳደር እንዲስተካከል በልጅነት መንፈስ በተደጋጋሚ የችግሮቹን ማሳያና መፍትሔዎቹን፣ ሥርዓተ መዋቅርን በመጠበቅ እስከ ቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ድረስ ቢያቀርብም ተጨበጭ ምላሽ አልተሰጠውም ። ይህም ጉዳይ ከግንዛቤ ገብቶ አፋጣኝ መፍትሔ ሊሰጠው ይገባል። ነገር ግን አሁንም እንደ ቀድሞው ተሸፋፍኖ የሚታለፍ እና መፍትሔ ከመስጠት ይልቅ ታላቋን ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስትያን የማይመጥነው ብልሹ አስተዳደር የሚቀጥል ከሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከሚገኙ ሊቃውንት፣ ምእመናን፣ እና የሰንበት ት/ቤት አባላት ጋር በመሆን የምንረከባትን እና ለትውልድ የምናሰረክባትን እናት ቤተ ክርስቲያን የምንታደግበትን መንገድ የምንከተል መሆኑን በዚሁ አጋጣሚ ለመግለፅ እንወዳለን። የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ሚያዚያ ፳፩ቀን ፳፻፲ወ፯ ዓ.ም አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

ወቅታዊ መልእክት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ (ሀገር አቀፍ) የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከውጪና ከውስጥ የሚቃጡባትን ፈተናዎች በመቋቋም ከውጭ የሚቃጡባትን ፈተናዎች ሰማዕትነትን በሚቀበሉ ልጆቿ ምስክርነት፣ ምንፍቅናን በቃል የመጣውን በቃል በመጻሕፍት የመጣውን በመጻሕፍት በመመከት ሐዋርያዊ ቅብሎሿን ጠብቃ መሠረተ እምነቷን፣ ዶግማና ቀኖናዋን ቅዱስ ትውፊቷን ለትውልዱ እያስተማረች ጸንታ ቆይታለች፤ ወደ ፊትም ትኖራለች፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን ዛሬ በልዩ ልዩ ውጫዊ ፈተናዎች ዋጋ እየከፈለች ያለች ቢሆንም ከሁሉ የከፋው ግን ከክብር በላይ የላቀ ክብር ባጎናጸፈቻቸውና እረኛና ጠባቂ እንዲሆኑ ባሰማራቻቸው ልጆቿ በተደጋጋሚ እየገጠማት ያለው የቀኖና ጥሰት ነው። የጥር ፲፬ ጳጳሳት ሹመት፣ የትግራይ ሲኖዶስ፣ የቅባት ጳጳሳት ሹመት ፤ ፖለቲካን ተጠግቶ ቤተክርስቲያንን የማጥቃት ክፉ ግብር ሳያንሳት ፤በተገኘው አጋጣሚ ኹሉ የምንፍቅና ትምህርቶች የሚያስተላፉትን በዝምታ መመልከት እየበዛና በዚህም በጎቿን ከበረቷ ለማስነጠቅ ለሚሠሩ ሁሉ ተባባሪ በመሆን የሚኬድበት ርቀት ቤተክርስቲያኒቱን ዋጋ እያስከፈለ በመሆኑ በቃ ሊባል ይገባዋል፡፡ ለማሳያ ይሆን ዘንድ በአቡነ በርናባስ መባልእትንና ነገረ ክርስቶስን አስመልክቶ፤ በአቡነ ፊልጶስ እመቤታችንና ሥላሴን አስመልክቶ የተናገሩትን የስሕተት ትምህርቶች ቅዱስ ሲኖዶስም ሆነ የሊቃውንት ጉባኤ በወቅቱ ማስጠንቀቂያም ሆነ የእርምት እርምጃ ባለመውሰዳቸው ዛሬ በአቡነ ገብርኤል እመቤታችንንና ነገረ ክርስቶስን አስመልክቶ ያውም በዐውደ ምሕረት፣ እንዲሁም በዕለተ ስቅለት በተደረገ የአዳራሽ ጉባኤ ለተናገሩት የኑፋቄ ትምህርት አድርሶናል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ቤተ ክርስቲያን ገፊ እንደሆነች እና ስለክርስቶስ የሚዘምሩትን እንደምታባርር እርሷም ስለ ክርስቶስ እንደማትዘምር በአደባባይ በጉባኤ ያለምንም ፍርሀት ሲናገሩ ተደምጠዋል፡፡ ከዚህም ባለፈ የማኅበራት ምዝገባ ክትትልና ቁጥጥር መምሪያን ጨምሮ የተለያዩ ሊቃነ ጳጳሳት በኑፋቄ ትምህርት ማስፋፋት ላይ የተሰማራውን “ፍኖተ ጽድቅ” ማኅበርን በገንዘቡ በሚሠራቸው የስቱዲዮ ግንባታ፣ የመጽሐፍ ኅትመት እና የመሳሰሉት ተግባራት በመማረክ የቤተክርስቲያንን ክብር አሳልፈው ሰጥተዋል፡፡ በዚህ ሂደት ላይ አንዳንድ መምህራን እና ማኅበራትም ተሳታፊ መሆናቸው በእጅጉ አሳዛኝ ነው፡፡ ይህ እንዲሆን ምክንያት ከሆኑ ነገሮች መካከል የሚከተሉት በዋናነት ተጠቃሽ ናቸው። 1. የአስተዳደር ብልሹነት የወለደው ዘርፈ ብዙ ችግር በእኛ መረዳት አሁናዊው ፈተና እና ችግር ከውጪያዊው የዝግጅት ጥቃትና ፈተናም በላይ የበረታው የውስጥ ችግር ነው። ለዚህም ዋናውና አንደኛው የሁለንተናዊ ድካማችን ምክንያት የቤተ ክህነቱ ብልሹ አስተዳደር ነው። አሁን ላይ ያለው የቤተ ክህነት አስተዳደር ዘመኑን በመዋጀት የቤተ ክርስቲያንን መንፈሳዊ ተልዕኮ በማስፈፀም ነፍሳትን ለመንግሥተ እግዚአብሔር ለማብቃት የሚያስችል ቁመና እና ብቃት ላይ አይገኝም ። ሕግ አውጪ፣ ሕግ ፈፃሚ እና ሕግ ተርጓሚ አንድ አካል በመሆን፣ ተጠቅልሎ በተያዘ ሥልጣን ቤተ ክርስቲያኒቱ እጅ ተወርች ተቀፍድዳ ወደ ትውልዱ እንዳትደርስ እየተሠራ ይመስላል። ቤተ ክርስቲያን በማይመጥናት ደካማ አስተዳደር ምክንያት ከተመሠረተችበት ነፍስ የማዳን መንፈሳዊ ተግባር ተናጥባለች። አስተዳደሩ ምእመናንን ለመንፈሳዊ ፍሬ ከማብቃት ይልቅ ለውድቀታቸው ምክንያት ሆኗል። በተለያዩ ጊዜያት ተጠንተው የቀረቡ ልዩ ልዩ የአስተዳደር ማሻሻያዎች እየተኮላሹ ጉዞው ከድጡ ወደ ማጡ ሆኗል:: በ ፳፻ወ፬ ዓ.ም ለሲኖዶስ የቀረበው የመሪ ዕቅድ ትግበራ ጥያቄ ፲፫ ዓመታት ሲገፋ ቆይቶ አሁንም ቦታ ተነፍጐታል። አስተዳደራዊ ለውጥ ጠልነቱ ተባብሶ ቀጥሏል። እኔ ብቻ በሚሉ ፣ ቤተ ክርስቲያን እንደ ግል ተቋማቸው በሚያዩ አካላት ተወራለች:: በሃይማኖት ችግር ፣ በቀኖና ጥሰት እና በሙስና ተጠያቂ መሆን የሚገባቸው አካላት የተሻለ ሹመትና ሽልማት ይሰጣቸዋል፡፡ 2. ለሊቃውንት ጉባኤ ትኩረት መነፈጉ የሊቃውንት ጉባኤ ተገቢው ትኩረት ሳይሰጠው በመቅረቱ ፣ እንዲሁም ሊቃውንት ክብራቸው ባለመጠበቁ እና ከውሳኔ ሰጪነት ድርሻ በመገለላቸው ፤ ለስሑት ትምህርት በሚገባው መልኩ ምላሽ መስጠት የማይችል ሆኗል:: እንዲሁም በቤተክርስቲያኒቱ ስም ለሚታተሙና ለሚሰራጩ መጻሕፍትና ልዩ ልዩ የምስልና የድምፅ እንዲሁም የኅትመት ውጤቶች የመገምገምና ዕውቅና የመስጠት ሥልጣኑ ተነጥቋል። የአደረጃጀትና የመከላከል አቅሙ በመዳከሙ፤ በመዋቅሩ ውስጥ የተሰገሰጉ ሐሰተኛ መምህራን በአፍም በመጽሐፍም ስሁት ትምህርታቸውን በቤተ ክርስቲያኒቱ ዐውደ ምሕረት እያሰራጩ ይገኛሉ። ትናንት አባቶች ያቆዩትን ሀብት መንዝሮ መጠቀም እንጂ የራሳቸውን አሻራ የማያኖሩ፣ ሀብት ንብረቷን ጠብቀው ከማቆየት ይልቅ ለግል መዝብረው ቀሪውን ለዘራፊ አሳልፈው የሰጡ ከመንፈሳዊ ክብር በጐደሉ፣ በሥጋ ሐሳብ ጨርሶውኑ በተወሰዱ፣ ምግባር በጎደላቸው ከአጥቢያ ጀምሮ እስከ ሊቃነ ጳጳሳት ድረስ ባሉ አገልጋዮች እየተፈተነች ትገኛለች። ያለ ዋጋ ከሚሰጠው መንፈሳዊ ሹመት ጀምሮ የቤተ ክርስቲያንን መንፈሳዊ አገልግሎት የሚጎዳ እኩይ ተግባር በእጅ መንሻ የሚፈጽሙ አካላት በሁሉም መዋቅር ውስጥ ተሰግስገው ቤተ ክርስቲያን የተመሠረተችበትን ዓላማ እንዳታሳካ ሳንካ ሆነውባታል። ስንዱዋ እመቤት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በሕግ እና በሥርዓት ዝግጅቷ እንከን አይወጣላትም። ነገር ግን ከሕግና ከሥርዓት ባፈነገጡ፣ ሐሰተኛ ትምህርት በሚያሰራጩ እና ኢ-ክርስቲያናዊ በሆነ ሕይወት ወስጥ በሚመላለሱ በተለይ በሁሉም መዋቅር ወስጥ በሚገኙ አገልጋይ ሠራተኞች ላይ ተግባራዊ ርምጃ አለመወሰዱ ለምእመናን ተስፋ መቁረጥ እና ፍልሰት ምክንያት ሆኗል ።

በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ የዝክረ ኒቂያ የሊቃውንት ጉባኤን ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ
+2
በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ የዝክረ ኒቂያ የሊቃውንት ጉባኤን ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በጸሎት ተጀመረ። በምክክር ጉባኤው ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፤ የባሕር ዳር እና ሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስን ጨምሮ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ; የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነትና የሥራ ኃላፊዎች; ከመላው ኢትዮጵያ የተሰባሰቡ ሊቃውንት ታድመውበታል። የሊቃውንት ምክክር ጉባኤውን ያሰናዳው የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የሊቃውንት ጉባኤ ነው። ምንጭ ፡ የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

እንኳን ለዳግማዊ ትንሣኤ በሰላም አደረሳችሁ! ክርስቶስ ተንሥአ እም ሙታን በዓቢይ ኃይል ወሥልጣን አሠሮ ለሰይጣን አግዐዞ ለአዳም ሰላም እምይእዜሰ ኮነ ፍስሐ ወሰላም ምንባባታ 1ኛ ቆሮ 15፡1-20
እንኳን ለዳግማዊ ትንሣኤ በሰላም አደረሳችሁ! ክርስቶስ ተንሥአ እም ሙታን በዓቢይ ኃይል ወሥልጣን አሠሮ ለሰይጣን አግዐዞ ለአዳም ሰላም እምይእዜሰ ኮነ ፍስሐ ወሰላም ምንባባታ 1ኛ ቆሮ 15፡1-20 1ኛ ዮሐ 1:1-ፍጻሜ ምዕራፍ የሐዋ. ሥራ 23፡1-10 ምስባክ "ይትነሣእ እግዚአብሔር፤ ወይዘረዉ ፀሩ፤ ወይጒየዩ ጽላዕቱ እምቅድመ ገጹ፤ ከመ የሐልቅ ጢስ ከማሁ ይሐልቁ። እግዚአብሔር ይነሣ፤ ጠላቶቹም ይበተኑ፤ የሚፈሩትም ከፊቱ ይሽሹ፤ ጢስ እንደሚበንን እንዲሁ ይብነኑ።" መዝ 67፡1-2 ወንጌል ዮሐ 20፡19-ፍጻሜ ምዕራፍ ቅዳሴ ዘዲዮስቆሮስ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

ለፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበር ተሰጥቶት የነበረው የዘገባ ፍቃድ ለጊዜው መታገዱ ተገለጸ። ሚያዝያ ፲፮/፳፻፲፯ ዓ.ም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥር የሚሰሩ ኦርቶዶክሳውያን የሚዲያ ተቋማት በአንድ ማዕከል  እንዲያገለግሉ፣ የመረጃ ፍሰቱ ወጥነት ያለውና ተቋማዊ መሆን ይችል ዘንድ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ የሁለት ቀናት ሥልጠና ተሰጥቶ የቤተ ክርስቲያን መሠረት እምነት፣ ሥርዓተ አምልኮና ትውፊት አክብረው በቤተ ክርስቲያን ዙሪያ ዘገባ ማከናወን የሚችሉበት ፈቃድ ከመምሪያው መሰጠቱ ይታወሳል። ከእነዚህ የሚዲያ ተቋማት መካከልም የፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበር ፍኖተ ጽድቅ ቴሌቪዥን አንዱ ሆኖ ዘገባዎችን ሲያሰራጭ ቆይቷል። ሆኖም ግን በፍኖተ ጽድቅ ቴሌቪዥን በዕለተ ስቅለት "ቅድስት ድንግል ማርያም ቤዛዊተ ዓለም አትባልም።" በሚል ርእስ  የተላለፈው ትምህርትን ውዝግብ በማሰነሳቱና ቋሚ ሲኖዶስ በጉዳዩ ዙሪያ ተወያይቶ ውሳኔ ለመስጠት ለረቡዕ ሚያዚያ 22 ቀን 2017 ዓ.ም ቀጠሮ የያዘ በመሆኑና ጉዳዩ በሚገባ ተጣርቶ ውሳኔ እስከሚሰጠው ድረስ ከመምሪያችን ለፍኖተ ጽድቅ ቴሌቪዥን የተሰጠው የዘገባ ፍቃድ ለጊዜው የታገደ መሆኑን እንገልጻለን።                ምንጭ:-   የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን  ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

“ኢሀሎ ዝየ ዳእሙ ተንሥአ በከመ ይቤ - ከዚህ የለም እንደ ተናገረው ተነሥቷል፡፡” ማቴ.28፡6 በጌታችን በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መቃብር በራስጌና በግርጌ የነበሩ ቅዱሳን መላእክት ማልደው ወደ ጌታ መቃብር ለሄዱ ሴቶች ሕያውን ከሙታን መካከል ስለምን ትፈልጋላችሁ ከዚህ የለም እንደ ተናገረው ተነሥቷል በማለት መልሰውላቸዋል፡፡ ሴቶቹ ወደ መቃብሩ መሄድ የጌታችንን ሥጋ ሽቱ ለመቀባት ነበር፡፡ ነገር ግን እንደ ጠበቁት ሦስት ቀን የሞላው ጠረኑ የተቀየረ ሥጋ ሳይሆን ባዶ መቃብር ነበር ያገኙት፡፡ ማስተዋል አቅቷቸው እንጂ ጌታችን ከሞቱ አስቀድሞ “ይህንን ቤተ መቅደስ አፍርሱት በሦስተኛው ቀን አነሣዋለሁ” ብሎ በሥልጣኑ በሦስተኛው ቀን እንደሚነሣ ነግሯቸው ነበር፡፡ (ዮሐ.2፡18) በሌላም የወንጌል ክፍል “ያለ እኔ ፈቃድ ነፍሴን ከሥጋዬ የሚለያት የለም፤ እኔ ወድጄ እለያታለሁ እንጂ በመቃብር ላኖራት አዋሕጄም ላስነሣት ሥልጣን አለኝ፡፡” በማለት ስለሞቱና ስለ ትንሣኤው ተናግሮ ነበር፡፡ (ዮሐ.10፡18) የጌታችን ሥጋ በመቃብር መፍረስ መበስበስን ሊያጠፋል ወደ መቃብር ወረደ እንጂ እስከ ክርስቶስ ድረስ በነበሩ ሙታን ሲሆን እንደነበረው መፍረስ መበስበስ ያለበት በሦስተኛውም ቀን ሽቱ መቀባት የሚያስፈልገው አይደለም፡፡ አይሁድ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ካንተ ምልክት ማየት እንሻለን ባሉት ጊዜ “አመጸኛና አመንዝራ ትውልድ ምልክትን ትሻለች ከነቢዩ ከዮናስ ምልክት በቀር ሌላ ምልክት አይሰጣትም፡፡ ዮናስ በአሳአንበሪ ሆድ ውስጥ ሦስት መዓልትና ሦስት ሌሊት እንደቆየ የሰው ልጅም በምድር ሆድ ውስጥ ሦስት መዓልትና ሦስት ሌሊት ይቆያል፡፡” በማለት መቃብር እንደማያስቀረው ሙስና መቃብርን አጥፍቶ በሦስተኛው ቀን እንደሚነሣ አስቀድሞ ተናግሮ ነበር፡፡ (ማቴ.12፡39) ወደ መቃብሩ የሄዱ ሴቶች በተደጋጋሚ በሰሙት የአይሁድ የውሸት ወሬ ምክንያት አስቀድሞ የሰሙትን የጌታ የትንሣኤውን ነገር በሙሉ እምነት መቀበል አልቻሉም ነበርና ሽቱ ለመቀባት ሄዱ፡፡ በለሊት ከወንዶቹ ቀድመውና ጨክነው ወደ መቃብሩ የሄዱበት ጥንካሬ ግን የሚደንቅ ነው፡፡ ቀድመው በመሄዳቸው ቀድመው የትንሣኤውን ብስራት ሰሙ፤ በዓይናቸውም አይተው አረጋገጡ፡፡ ጌታችን ከሙታን መካከል እንደሌለ፣ መሞቱ ሞታችንን ሊያጠፋ፣ ወደ መቃብር መውረዱም በመቃብር ፈርሶ በስብሶ መቅረትን ሊያስወግድ እንደሆነ ተረዱ፡፡ የጌታችን የሞተው ሞታችንን ለመግደል የተነሣውም እኛን ለማሥነሳት ነውና የጌታችን ትንሣኤን ስናከብር የምናከብረው ትንሣኤያችንን እንደሆነ መረዳት ያስፈልጋል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “ዘተሰቅለ በእንተ ኃጢአትነ ከመ ያጽድቀነ ወትንሥአ ከመ ያንሥአነ - ሊያጸድቀን ስለኃጢአታችን ተሰቀለ፤ ሊያነሣንም ተነሣ” ይላል፡፡ (ሮሜ.4፡25) ስለዚህ የትንሣኤን በዓል ስናከብር የተነሣንበት በዓል እያከበርን ነውና በዓሉ ሙት በሆነ ሕይወት እንዳናከብር በትንሣኤ ልቡና ተነሥተን ስለእኛ ሕይወት የተቆረሰውን የክርስቶስ ሥጋን በመብላት ደሙንም በመጠጣት ሊሆን ይገባል፡፡ በዓለ ትንሣኤ የመነሣት በዓል ነውና ለፍቅር ለአንድነት ለሰላም ከመነሣት ጋር በዓሉን ማክበር ይገባል፡፡ ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ “ወአድኃነነ በርደቱ እመስቀሉ ውስተ ሲኦል ወፈትሐ እለሀለዉ ሕየ ጻድቃነ ሙቁሐነ በኃጢአተ አዳም አቡሆሙ - ከመስቀሉ ወደ ሲኦል በመውረዱ አዳነን በዚያም በአባታቸው አዳም ኃጢአት ምክንያት የታሰሩ ጻድቃንን ፈታ፡፡ ብሎ እንዳስተማረ የምናከብረው በዓል የመፈታት በዓል ስለሆነ ከኃጢአት፣ ከክፋት ከዘረኝነትና መሰል እስራቶች ተፈትተን ልናከብረው ይገባል፡፡ በመጨረሻም በመላው ዓለም የምትገኙ ኦርቶዶክሳውያን፣ በሀገር ውስጥም ከሀገር ውጭም ያላችሁ በሰንበት ትምህርት ቤት የምታገለግሉ ወጣቶችና ሕጻናት በዓሉ ለንስኃ፣ ለአገልግሎትና ለመልካም ነገር የመነሣትና ከተለያዩ የዓለም እስራቶች የመፈታት በዓል እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ፡፡ እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው አደረሳችሁ! መልካም የትንሣኤ በዓል ይሁንላችሁ! መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወ/ትንሣኤ በመ/ፓ/ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሓላፊ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

ክርስቶስ ተንሥአ እም ሙታን ሞተ ወኬዶ ለሞት። ለእለ ውስተ መቃብር ወሀበ ሕይወተ ዘለዓለም ዕረፍተ። ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ተነሣ። ሞቶ ሞትን አጠፋው። በመቃብር ላሉትም የዘላለም ዕረፍት የሚሆን
ክርስቶስ ተንሥአ እም ሙታን ሞተ ወኬዶ ለሞት። ለእለ ውስተ መቃብር ወሀበ ሕይወተ ዘለዓለም ዕረፍተ። ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ተነሣ። ሞቶ ሞትን አጠፋው። በመቃብር ላሉትም የዘላለም ዕረፍት የሚሆን ሕይወትን ሰጠ። እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችሁ!! መልካም በዓል! የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

ስለሆነም የመጨረሻው ዕድላችን የተንጠለጠለው እምነትን ተከትለን በምንሰራው ስራ ላይ መሆኑን ለኣፍታ እንኳ መዘንጋት የለብንም፤ ዛሬ ከሰው ኣእምሮ በእጅጉ እየራቀ የሚገኘው ይኸው እምነትና ሥነ-ምግባር ነው፤ ሰዎች ከእምነትና መልካም ሥነ-ምግባር በራቁ ቊጥር ሕይወት መራራ እንድትሆን ትገደዳለች፡፡ እኛ ኢትዮጵውያን ከጥንት ጀምሮ በእምነትና ሥነ-ምግባር እየተመራን፣ በደልን በይቅርታ እየዘጋን፣ እስከ ጋብቻ በሚዘልቅ ባህለ-ዕርቅ ደምን እያደረቅን፣ በወንድማማችነት ፍቅር ተስማምተን በሺሕ ለሚቆጠሩ ዘመናት እንዳልኖርን፣ እነሆ ዛሬ ለታላቅነታችን በማይመጥን ሆናቴ መለያየትና መጣላት ብሎም እርስ በርስ መገዳደል ዕለታዊ ተግባራችን ኣድርገን እንገኛለን፡፡ ይህ በጣም ኣሳዛኝ ክሥተት ነው፤ ይህንን ሳናስተካክል የምናከብረው በዓለ ትንሣኤም እዚህ ግባ የሚባል ደስታ ሊያስገኝልን እንደማይችል የታወቀ ነው፡፡ እየሆነ ያለው ሁሉ ማንንም ኣይጠቅምም፤ በዕርቅ፣ በይቅርታና በውይይት የማይፈታ ችግር ያለ ይመስል ይህን ያህል መጨካከን እንዴት እንደ መፍትሔ ተደርጎ ይወሰዳል? አሁንም ለሁሉም ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን የምንማፀነው፡- እባካችሁ እኛው ራሳችን ሸምጋይና ተሸምጋይ ሆነን ችግሮቻችንን ለመፍታት በብርቱ እንስራ፤ መፍትሔም እናምጣ፤ መሳሪያ ኣንሥታችሁ እርስ በርስ በመገዳደል የምትገኙ ወገኖቻችን እባካችሁ ቆም ብላችሁ ኣስቡና ሰላምና ዳቦ ኣጥቶ ለተቸገረው ሕዝባችሁ ስትሉ ለሰላማዊ መፍትሔ ዕድል ስጡ፤ ኢትዮጵያ የምትባለው ሀገር የሁሉም ኢትዮጵያውያን መሆኗን በትክክል የሚያረጋግጥ ሰላማዊ መፍትሔ በማስቀመጥ ለአንድነትዋና ለዕድገትዋ አጥብቃችሁ ጣሩ፤ ግጭትና መለያየት ከሚያጠፋን በቀር ምንም ዓይነት ጥቅም ሊሰጠን እንደማይችል ብዙ ማብራሪያ የሚያስፈልገው ኣይደለም፤ ስለሆነም ገዳዩን መሳሪያ ኣስቀምጡና በሃይማኖት፣ በኣንድነት፣ በስምምነትና በጭንቅላት ኃይል ሰላምን ኣምጡ፤ ይህ የቤተ ክርስቲያናችን ወቅታዊ ጥሪ ነው፤ በመጨረሻም፡- በልዩ ልዩ ምክንያት ከሞቀ ቤታቸው ተፈናቅለው በየኣካባቢው በረኃብ ኣለንጋ እየተገረፉ የሚገኙት ወገኖቻችን በትንሣኤው በዓል ተጽናንተውና እፎይ ብለው በደስታ እንዲያሳልፉ ካለን ከፍለን በመመገብና በማልበስ እንድንደርስላቸው በእግዚአብሔር ስም ኣባታዊ መልእክታችንን እናስተላልፋለን፤ በድጋሚ እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችሁ!! መልካም በዓለ ትንሣኤ ያደርግልን! “እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ” ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!! አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ሚያዝያ ፲፪ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም አዲስ አበባ ኢትዮጵያ፣ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ ዘተናገረ በበዓለ ትንሣኤሁ ለእግዚእነ ወኣምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘዕሥራ ምእት ዐሠርቱ ወሰብዓቱ ዓመተ ምሕረት፤ በስመ ኣብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ ኣምላክ አሜን! በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፣ ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፣ የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፣ በሕመም ምክንያት በየፀበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፣ እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያት በሙሉ፣ በትንሣኤው የሕይወት መንገድን ያሳየን ጌታችን ኣምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን ለሁለት ሺሕ ዐሥራ ሰባት ዓመተ ምሕረት በዓለ ትንሣኤው በሰላም ኣደረሰን ኣደረሳችሁ! “ወኣርኣይከኒ ፍኖተ ሕይወት፡- የሕይወትን መንገድ ኣሳየኸኝ” (መዝ.፲፭÷፱-፲፩)፤ ሕይወት በዓለመ ፍጡራን ውስጥ ከሚገኘው ድንቅ ነገር ሁሉ ተወዳዳሪ የሌላት ድንቅ ነገር ናት፤ ሕይወት ኣካልን የማንቀሳቀስ፣ የማመዛዘን፣ የመወሰንና የመስራት ሀብተ ጸጋ ያላት ልዩ ፍጥረት ናት፡፡ በዚህም ምክንያት ሕይወት ወደ እግዚአብሔር የሚቀርብ ወይም የሚመስል ጠባይ ኣላት፤ ሰው የእግዚአብሔር መልክና ኣምሳል ኣለው የሚለው መጽሓፍ ቅዱሳዊ ኣስተምህሮም ከዚሁ ጋር የሚስማማ ነው፤ ሕይወት ከእግዚአብሔር ጋር በቀጥታ የተጣበቀ ወይም የተሳሰረ ግንኙነት ኣላት፤ “ወኅብእት ሕይወትክሙ ምስለ ክርስቶስ፡- ሕይወታችሁ ከክርስቶስ ጋር የተሳሰረች ናት” የሚለው ሐዋርያዊ አባባልም ይህንን ያመለክታል፡፡ ሕይወት ፈጣሪንና የፈጣሪ ርዳታን ስትሻ የመኖርዋ ምስጢርም ከእግዚአብሔር ጋር የሚገናኝ ጸጋ ስላላት ነው፤ ሕይወት መልካም ስትሰራ ደስተኛ፣ ክፉ ስትሰራ ደግሞ ስቅቅተኛ የምትሆንበት ምክንያትም ከእግዚአብሔር ጋር የሚያገናኛት ጸጋ ስለሚነግራት ነው፡፡ ምክንያቱም መልካምን መውደድ፣ ክፉን መጥላት የእግዚአብሔር የማይለወጥ ጠባይ ስለሆነ፣ ክፉን ሰርታ ከእርሱ ጋር በደስታና በነጻነት መኖር በፍጹም ኣትችልምና ነው፡፡ የመጀመሪያው ሰው ኣዳም ክፉውን ከሰራ በኋላ ወዲያውኑ መሸሸግና መደናገጥ ሊወረው የቻለው ከእግዚአብሔር ጋር በቀጥታ ግንኙነት ያላት ውሳጣዊት ሕይወቱ ከእግዚአብሔር ጋር ኣብራ መቀጠል የማትችልበት ደረጃ እንደደረሰች ስለተረዳች ነው፡፡ ከዚህ ኣንጻር ሕይወት የመኖር ጸጋ ብቻ ሳይሆን ከእግዚአብሔር ተሳስሮ የመኖር ጸጋም ያላት መሆኑን እንገነዘባለን፡፡ ሕይወት የማትጠፋ ብትሆንም የመሞት ስጋት ያልተለያት ፍጡር ናት፤ በተለይም እግዚአብሔርን የበደለች ዕለታ ከባድ የሞት ኣደጋ ያጋጥማታል፤ ይህም ሞት የሥጋ ሳይሆን ከእግዚአብሔርና የእግዚአብሔር ከሆነው ሁሉ መለየት ነው፤ የሕይወት ከባዱ ሞትም ይኽ ነው፡፡ የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት! እኛ ሰዎች በኃጢኣት ጠንቅ ያጣነው ሕይወት እንዳለ ቅዱስ መጽሓፍ “በኣንድ ሰው በደል ኃጢኣት ወደ ዓለም ገባ፤ በዚህም ምክንያት ሰው ሁሉ ሞተ ወይም ከእግዚአብሔር ተለየ” በማለት የእኛ ከእግዚአብሔር መለየት ዋናው ሞት እንደሆነ ያስረዳል፡፡ይህ ገለጻ ከእግዚአብሔር ጋር የመኖር ሕይወታችን በበደል ምክንያት ማጣታችንን የሚያሳይ ነው፡፡ እኛ በደለኞች ሆነን ከእግዚአብሔር የተለየንበት የመጀመሪያው ምክንያት በደለኞች ከሆኑ ኣዳምና ሔዋን የተገኘን መሆናችን ነው፡፡ በመሆኑም የሁላችንም ሥጋዊና መንፈሳዊ ኣካል የተከፈለው ከነሱ እንደመሆኑ መጠን ያለን ሁሉ እንደነሱ ቀድሞውኑ የሞተና የተፈረደበት ነው፡፡ በሌላ ኣባባል በጥንተ ኣብሶ ምክንያት ከእግዚአብሔርና የእግዚአብሔር ከሆነው ሁሉ የተለየን ሆን ማለት ነው፤ ስለዚህም ነው በኣንድ ሰው በደል ምክንያት ሁሉም ሞቱ ብሎ እግዚአብሔር ያሳወቀን፤ ጥንተ ኣብሶ ወይም የውርስ ኃጢኣት የሚባለውም ይኽ ነው፡፡ ከዚህም ጋር ከእግዚአብሔር የለየን የውርሱ ኃጢኣት ሳይበቃን በየሰዓቱ በምንፈጽመው ክፉ ተግባር በበደል ላይ በደል እየጨመርን በመቀጠላችን በጨለማ ላይ ተጨማሪ የጨለማ ጥላ ኣክለንበታል፡፡ ይህ ሁሉ ተደማምሮ ሞታችን ወይም ከእግዚአብሔር መለየታችን የሰፋና የከፋ እንዲሆን ኣድርጎታል፤ የተወዳዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናትና ምእመናት! ከእግዚአብሔር የለያየን ኣበሳ - ኃጢኣት በእግዚአብሔር ፊት እጅግ ከባድ ቢሆንም እግዚአብሔር እኛን ለማዳን ያለው ፈቃድ በተስፋ ጭላንጭል ማሳየቱን ኣላቋረጠም፡፡ ይኸውም የበደላችን ዕዳ ከመጀመሪያው ኣንሥቶ የማዳን ተስፋውን በተነገረለት በኢየሱስ ክርስቶስ ቤዛዊ ሞት እንደሚሰረዝ፣ በእርሱም ጽድቅ እንደ ጻድቃን ተቈጥረንና ያጣነውን ሕይወት እንደገና ኣግኝተን ወደ እግዚአብሔር እንደምንቀርብ፣ ይህም ከትንሣኤ በኋላ እውን እንደሚሆን እግዚአብሔር ለእኛ ደጋግሞ ይፋ ኣድርጎኣል፡፡ ይህንን ተስፋ - ትንሣኤ በመንፈስ ቅዱስ የተረዳ ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት በምስጋና መዝሙሩ እንዲህ ብሎ ይገልጸዋል፤ “ዳግመኛም ሥጋዬ በተስፋው ኣደረ፤ ነፍሴን በመቃብር ኣትተዋትምና፤ ጻድቅህንም በመቃብር ተጥሎ፤ ፈርሶና በስብሶ ይቀር ዘንድ ኣሳልፈህ ኣትሰጠውም፤ የሕይወትንም መንገድ እንዲህ ኣሳየኸኝ” በማለት የሕይወታችን ተስፋ-ትንሣኤን በሚያስደንቅ ኣገላለጽ አስረድቶናል፡፡ ገለጻው የክርስቶስንና የኛን ትንሣኤ እንደሚመለከት በቅዱሳን ሓዋርያት ተርጓሚነት በቅዱስ መጽሓፍ ተብራርቶ ይገኛል፡፡ በመሆኑም የእኛ መጨረሻ የሚጠናቀቀው በመቃብር ተጥሎ፤ ፈርሶና በስብሶ በመቅረት ሳይሆን እንደገና ተነሥቶና ከእግዚአብሔር ጋር በተሳሰረ ኃይለ ሕይወት ለዘላለም በመኖር እንደሆነ ቃሉ ያስረዳናል፡፡ ቅዱስ ዳዊት ከትንሣኤ በኋላ የሚሆነውን ይህን ጣዕመ ሕይወትን ነው ኣሳየኸኝ ብሎ የገለጸው፤ ጌታችን የዚህ ሕይወት የትንሣኤ በኵር ሆኖ ተነሥቶኣል፤ ከትንሣኤውም በኋላ ለዘላለም በሕይወት ይኖራል፡፡ በቀጣይም ጊዜው ሲደርስ እኛ ተከታዮቹ የእርሱን ዓይነት ትንሣኤ ተነሥተን በማያልቅ ኃይለ ሕይወት ከሱ ጋር ለዘላለም በሕይወት እንኖራለን፤ ጌታችን ያሳየን የሕይወት መንገድ ይኸው ነው፡፡ ይኽ ሕይወት ከሁሉም ህላዌ - ሕይወት የላቀና የበለጠ ጣዕም ያለው ዘላለማዊና ድንቅ ሕይወት ነው፤ ይኽ ሕይወት ከስጋት፣ ከስሕተት፣ ከቅጣትና ከሞት - ፍርሓት ነጻ የሆነ፣ በፍጹም ነጻነትና ደስታ ከእግዚአብሔር ጋር ለዘላለም የሚያኖር ሕይወት ስለሆነ ሁላችንም ወደዚህ ሕይወት ለመድረስ በእምነት እንተጋለን፡፡ የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት! ዘር ሳይኖር ፍሬ እንደማይገኝ ሁሉ ሕይወታዊ ትንሣኤም ያለ ሃይማኖትና ሥነ - ምግባር ሊገኝ ኣይችልም፡፡ ጌታችንም ይህንን ኣስመልክቶ ሲያስተምረን “መልካም ያደረጉ ለሕይወት ትንሣኤ ይነሣሉ፤ ክፉም ያደረጉ ለፍርድ ትንሣኤ ይነሣሉ›› ብሎ ኣሳውቆናል፡፡ ከዚህ አኳያ የሕይወትን ትንሣኤ የሚያገኝ ያመነ፣ የተጠመቀና መልካም ስራን የሰራ እንጂ የተነሣው ሁሉ ኣለመሆኑ ግልጽ ነው፤ መነሣቱ ሁሉም የግድ ይነሣል፤ ነገር ግን ከትንሣኤ በኋላ የሚጠብቀን ሕይወት በዚህ ዓለም በሕይወተ ሥጋ ሳለን በሰራነው ስራ የሚወሰን እንደሆነ ጌታችን በማያሻማ ሁኔታ ኣረጋግጦልናል፡፡

መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ ዘር ሳይኖር ፍሬ እንደማይገኝ ሁሉ ሕይወትም ያለ ሃይማኖትና ሥነ ምግባር ሊገኝ አይችልም። ጌታችንም ይህንን አስመልክቶ ሲያስተምረን "መልካም ያደረጉ ለሕይወት ትንሣኤ ይነሣ
መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ ዘር ሳይኖር ፍሬ እንደማይገኝ ሁሉ ሕይወትም ያለ ሃይማኖትና ሥነ ምግባር ሊገኝ አይችልም። ጌታችንም ይህንን አስመልክቶ ሲያስተምረን "መልካም ያደረጉ ለሕይወት ትንሣኤ ይነሣሉ፤ ክፉም ያደረጉ ለፍርድ ትንሣኤ ይነሣሉ።" ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችሁ!! የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ ዘር ሳይኖር ፍሬ እንደማይገኝ ሁሉ ሕይወትም ያለ ሃይማኖትና ሥነ ምግባር ሊገኝ አይችልም። ጌታችንም ይህንን አስመልክቶ ሲያስተምረን "መልካም ያደረጉ ለሕይወት ትንሣኤ ይነሣሉ፤ ክፉም ያደረጉ ለፍርድ ትንሣኤ ይነሣሉ።" ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት እንኳን አደረሳችሁ!! ቅዳም ስዑር (ገብረ ሰላም) የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok