ch
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

前往频道在 Telegram

📈 Telegram 频道 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU 的分析概览

频道 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 14 430 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 6 084,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 336

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 14 430 名订阅者。

根据 27 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 543,过去 24 小时变化为 21,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 36.43%。内容发布后 24 小时内通常能获得 N/A% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 252 次浏览,首日通常累积 0 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 33

📝 描述与内容策略

尚未提供频道描述。

凭借高频更新(最新数据采集于 28 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。

14 430
订阅者
+2124 小时
+1247
+54330
帖子存档
"በዙፋኑም በእንስሶቹም በሽማግሌዎቹም ዙሪያ የብዙ መላእክትን ድምፅ ሰማሁ፤ ቍጥራቸውም አእላፋት ጊዜ አእላፋትና ሺህ ጊዜ ሺህ ነበር።" ራእይ 11፡5 እንኳን ለአእላፋት መላእክት ዓመታዊ መታሰቢያ ክ
"በዙፋኑም በእንስሶቹም በሽማግሌዎቹም ዙሪያ የብዙ መላእክትን ድምፅ ሰማሁ፤ ቍጥራቸውም አእላፋት ጊዜ አእላፋትና ሺህ ጊዜ ሺህ ነበር።" ራእይ 11፡5 እንኳን ለአእላፋት መላእክት ዓመታዊ መታሰቢያ ክብረ በዓል በሠላም አደረሳችሁ! የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! መልካም በዓል! ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

https://youtu.be/5Hs2gKQWtKQ?si=IhUu8dESmx5TomrT ትምህርት በሚዲያ ዘወትር ረቡዕ ምሽት በፈለገ ጥበብ የዩቲዩብ ቻናል የሚተላለፍ መርሐ ግብር ሲሆን በሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት መሠረት በየክፍል ደረጃ በትምህርት ዓይነት በመከፋፈል ለተማሪዎች እንደ መርጃ ሆኖ የሚያገለግል ልዩ የትምህርት መርሐ ግብር ነው።

++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++ አፈጻጸም ፦ ሀገራዊ ሰላምን፣ መረጋጋትንና አንድነትን ለማስፈን የታወጀውን የጾምና የጸሎተ ምኅላው አፈጻጸም በቅደሱ ሲኖዶስ በተወሰነው መሠረት ከዚህ በመቀጠል አቀርባለሁ። ቀደም ሲል ብፁዕ ወቅዱስ አባታችን በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ መሠረት በመላው ዓለም ለሚገኙ ሕዝበ ክርስቲያን የታወጀውን አዋጅ አስተላልፈዋል፡፡ በዚሁ መሠረት ያለፈውን በይቅርታና በምህረት ዘግተን በእውነተኛ ንሥሓ ልቅሶና በምህላ፣ በጾምና በጸሎት ወደ ፈጣሪ እንድንቀርብ፣ በመካከላችንም ፍቅርና አንድነት እንዲመጣ ይኽንን ጾመ ነቢያት ወይም የገና ጾም በልዩ ሁኔታ እንድንጾም መንፈሳዊ አዋጅ ተላልፏል፡፡  ይኽ ጥንታዊ የአዋጅ ጾም ሁለት አበይት ታሪኮችን የያዘ ነው፡፡ የመጀመሪያው ክፍል ቅዱስ አብርሃም ሶርያዊ የተባለ ጻድቅ አባት በጸሎት፣ በጾምና በምኅላ ተራራን ከመሬት ከፍ በማድረጉ ኃይለ ጸሎቱና ክብረ አምለኩ የሚዘከርበት ነው፡፡ በሁለተኛው ክፍል ነቢያት የጌታችንን ሰው መሆን እያፈለጉ፣ ድህነትንና ሰላምን በመሻት መጾማቸው ይዘከራል፡፡ (፩ኛ ጴጥ ፩፡፲) እኛም ይኽንን አብነት አድርገን ታላቋ ቤተ ክርስቲያን፣ ኃላፊነቷን እንድትወጣ ስለችግራችን፣ ስለሀገር ሰላምና ስለ ሕዝቡ ደኅንነት በአንድነት ሆነን ወደፈጣሪያች እንድንጮኽ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በጥቅምት ወር ፳፻፲ወ፮ ዓ/ም ወስኖ መግለጫ ሰጥቷል፡፡ ሀገራችን እንድትፈወስ፣ የወገን በወገን ደም መፋሰስ እንዲቀር፣ ያለፈውን በይቅርታና በንሥሓ ዘግቶ ለወደፊቱ ብሩህ ዘመንን እንዲመጣ በንሥሓና በፍጹም ለቅሶ፣ በቁመትና በሰጊድ፣ በሰፊሕና በአንቅአድዎ፣ ወደፈጣሪ እንድንቀርብ የምልኣተ ጉባኤውን ውሳኔ መሠረት በማድረግ ቋሚ ሲኖዶስ በኅዳር ወር ፳፻፲ወ፮ዓ/ም የሚከተለውን ዝርዝር አፈጻጸም አውጥቷል፡፡  ፩ኛ. የጾሙ የመጀመሪያ ሳምንት ከቅዳሜ ኅዳር ፲፭ እስከ ኅዳር ፳፩ ቀን ፳፻፲ወ፮ ዓ/ም በሁሉም የሀገራችን ክፍልና ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ባለችበት በመላው ዓለም የንሥሓ፣ የጾም፣ የጸሎትና የምኅላ ሳምንት እንዲሆን፤   ፪ኛ. በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ በአድባራት አስተዳዳሪዎች፣ በአጥቢያ አለቆችና በገዳም አበምኔቶች መሪነት ሁሉም ዲያቆናት፣ ቀሳውስት፣ መነኰሳት፣ ሰባክያንና ሊቃውንት በሙሉ በየመዐርጋቸው ልብሰ ተክህኖና ወጣት የሰንበት ትምህርት ቤት ዩኒፎርማቸው ለብሰው፣ ሁሉም ምእመናን ጋር በአንድነት በዐውደ ምህረት ጸሎተ ምኅላውን እንዲያደርሱ፤  ፫ኛ. በላው ሕዝበ ክርስቲያን ከሊቅ እስከ ደቂቅ፣ ሕፃናት፣ ወጣቶች፣ እናቶች አባቶች አረጋውያን ሁሉ የቻለ በቤተ ክርስቲያን፣ ያልቻለ በያለበት ሆኖ የተጣላ ታርቆ፣ በፍቅርና በአንድነት፣ በእውነተኛ ንሥሓና ጸጸት በምኅላው እንዲሳተፍ፤ በማእከል የሚደረገው ጸሎተ ምኅላ በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ መሪነት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት በተገኙበት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም ገዳም ሆኖ በመገናኛ ብዙኀን የቀጥታ ሥርጭት ለመላው ዓለም እንዲተላለፍ፤ ፬ኛ. በመጀመሪያው የሱባኤ ቀን ኅዳር ፲፭ ቀንና፣ በሰባተኛው ቀን ኅዳር ፳፩ ቀን በጸሎተ ምኅላው በሚደረግበት ጊዜ ታቦቱ ከመንበሩ ተነሥቶ በዐውደ ምኅረት በቀሳውስት እንዲከብር ሆኖ፤ በሁሉም የምኅላው ቀናት ሥዕለ ማርያም፣ ወንጌልና መስቀል ወጥቶ በአራቱ መዐዝን ሥርዓተ ጸሎተ ምኅላው ከጸሎተ ወንጌል ጋር በየቀኑ በነግህና በሠርክ የሥራ ሰዓትን በማይነካ ሁኔታ እንዲፈጸም፤ ፭ኛ. በየዕለቱ የሚነበቡት የወንጌል ክፍሎችን ስለ ሰላም፣ ስለንሥሓና ጸጸት፣ ስለ ፍቅርና አንድነት፣ ስለ በጎነትና መደማመጥ፣ ስለመሰማማትና ጥላቻን ስለማራቅ እንዲሆን፤ ፮ኛ. በሰፊህና በአንቀዓድዎ፣ በሰጊድና በአስተብርኮ፣ ምኅላው ከደረሰና፣ ጸሎተ ወንጌል ደርሶ ዕለቱ ወንጌል ከተነበበ በኋላ በአንድነት የንሥሓ መዝሙር በመዘመር፣ ሕዝበ ክርስቲያን ስለሀገራቸውና ስለሰው ልጆ ደኅንነት እያሰቡ ወደቤታቸው እንዲሄዱ፤ ፯ኛ. ከመጀመሪው ሳምንት በኋላ እስከ በዓለ ልደት ድረስ የሰርክ ምህላ ሳይቋረጥ መደበኛው ሥርዓተ ጾምና ጸሎት እንዲቀጥል፣ የቤተ ክርስቲያንን ታላቅነት፣ የአበውን ተቀባይነት በሚገለጽ፣ በቀጣይም ሁሉም ኦርቶዶክሳውያን በመንፈሳዊ ጽናት የሰላም ልዑካን ሆነው እንዲቀጥሉ በሚያደርግ ሁኔታ እንዲፈጸም፤    ፰ኛ. አስቀድሞ የደረሰውንና፣ እየደረሰብን ያለው ችግር የጦርነትና የግጭት ብቻ ሳይሆን የረሀብ፣ የድርቅ፣ የኑሮ ውድነት፣ የመፈናቀልና የስደት ጭምር ስለሆነ ከጸሎትና ምኅላችን ጎን ለጎን መረዳዳትና መተዛዘን፣ ርኅራሄና መደጋገፍ አብሮ እንዲፈጸም፤    ፱ኛ. ይኽንኑ መልእክት መላው ዓለም እንዲውቀው፣ በተለይም የኦሬንታል ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት በጸሎት እንዲያስቡን፣ የጸሎታችንና የምኅላችን መነሻ ምክንያቱ የሀገራችን ወቅታዊ ችግር ቢሆንም የምንጸልየው ለመላው ዓለም መሆኑ ተገልጾ በደብዳቤ እንዲላክ እንዲደረግ፣ በማለት ቅዱስ ሲኖዶስ ጥብቅ መመሪያ አስተላልፏል፡፡  እግዚአብሔር አምላካችን በእንባና በንሥሓ የምናቀርበውን ጸሎተ ምኅላችንን በምህረቱ ተቀብሎ ሀገራችንን ሰላም ያድርግልን፣ ሕዝባችንን ይጠብቅልን፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር የኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን  ቅዱስ ሲኖዶስ ኅዳር ፲፩ ቀን ፳፻፲ወ፮ ዓ/ም፡  አዲስ አበባ፡ ኢትዮጵያ ++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++

የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት: ++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!! “ሰላምየ አኀድግ ለክሙ ወሰላመ አቡየ እሁበክሙ፡- ሰላሜን እተውላችኋለሁ፥ የአባቴ ሰላምም እሰጣችኋለሁ” (ዮሐ.14፡27) ሀገራዊ ሰላምን፣ መረጋጋትንና አንድነት ማስፈንን አስመልክቶ በጥቅምቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ በተላለፈው ውሳኔ መሠረት ከቋሚ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ!!! ሰላም፣ ፍቅር፣ አንድነትና ደኅንነት የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ቀዳሚ ተልእኮዎች ናቸው፡፡ በሃገራችን ሰላምን ለማስፈን ቅድስት እናት ቤተ ክርስቲያን ከቀድሞ ጀምሮ ብዙ ጥረት ስታደርግ ኑራለች፡፡ አሁንም ሊኖራት የሚገባውን ተግባራዊ ሚና መወጣት ይኖርባታል፡፡ በተለይም ሰላም በመንፈሳዊ፣ በማኅበራዊ፣ በግለሰብ፣ በተቋም፣ በሰው ሰራሽና በተፈጥሮ ክበብ ውስጥ ያለውን የተሣሠረ ሁለንተናዊ ትርጉም ከግምት ውስጥ ያስገባ ተግባራዊ እንቅስቃሴ የሚያስፈልግበት ጊዜ ላይ እንገኛለን፡፡ ለሰላም መደፍረስና መታጣት ምክንያት የሆኑ ጉዳዮችን በማንሳትና ያስከተሉትን የሰው ልጅ እልቂት፣ ሞትና ስደት፣ የአብያተ ክርስቲያናትና የመንፈሳዊ ቅርሶች ውድመት፣ የካህናትና የሊቃውንት ስደትና መከራ፣ የቋሚና የተንቀሳቃሽ ንብረቶች ውድመት፣ የቤተ ክርስቲያን አንድነት መናጋት፣ በዜጎች መካከል ጥላቻ መስፋት፣ መተማመን መጥፋት፣ የኑሮ ዋስትና ማጣት፣ በስጋት መኖር፣ የማያባራ መከፋፈል፣ የሰብአዊ ክብር ማጣት፣ የመብት ጥሰት፣ የኑሮ ውድነትና የሕዝቦች መፈናቀል በአደባባይ እየታዩ ያሉ ሰብኣዊ ሰቆቃዎች ናቸው፡፡ “ብፁዓን ገባርያነ ሰላም እስመ እሙንቱ ውሉደ እግዚአብሔር ይሰመዩ፡- የሚያስታርቁ ብፁዓን ናቸው፣ የእግዚአብሔር ልጆች ይባላሉና”  (ማቴ.5፡9) በማለት ጌታችን ያስተማረው ትምህርት የቤተ ክርስቲያን መመርያ ነው፡፡  የቤተ ክርስቲያን የሰላምና የአስታራቂነት ድርሻ፣ የሃገር አንድነትና የሕዝብን ሰላም ለመጠበቅ በታሪኳ ያደረገችው አስተዋጽኦ በቀላሉ የሚታይ አይሆንም፡፡  የቤተ ክርስቲያን ታላቅነት፣ የአበውን ተቀባይነትና የሊቃውንቷን ሰላምን የማስፈን ክሂሎት፣ ችግርን የመፍታት ጥበብ አሁንም ተጠናክሮ መተግበር ይኖርበታል፡፡ የሰላምን ወሳኝ ሚና ከግምት ውስጥ በማስገባትና ተገቢውን ትኩረት በመስጠት የሰላምና የዕርቅ ሰነድ በማዘጋጀት የመሪነት ተሳትፎ እንድትፈጽም ገለልተኛና ሰውን ማእከል በማድረግ ታገለግላለች፡፡ ካህናትና መላው አገልጋዮች የሰላም ልዑካን እንዲሆኑ፤ ሰላምን ግንባር ቀደም ሐዋርያዊ ተልእኮዋ አድርጋ ትንቀሳቀሳለች፡፡ በሃገራዊ የሰላምና የዕርቅ ጥረቶች አዎንታዊ ተጽዕኖ ለመፍጠር የሚያስችል ይፋዊ ውክልና እንዲኖራት፣ በሥነ ምግባርና በግብረ ገብነት ትምህርት የራስዋን ኃላፊነት እንድትወጣ፤ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በሃገራዊም ሆነ በራስዋ መዋቅር በሰላም ዙርያ አስተዋጽኦዋን ለማሳደግና የሚጠበቅባትን ለመወጣት ትችል ዘንድ የጥቅምት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በሚገባ ተወያይቶ ውሳኔ አስተላልፏል፡፡ ለቤተ ክርስቲያን መመርያዋ ጽድቅን፣ እምነትን፣ ፍቅርን አጥብቀህ ተከተል ብሎ ቅዱስ ጳውሎስ ለጢሞቴዎስ ያዘዘው መመሪያ ነው፡፡ (፪ኛ ጢሞ. ፪፡ ፳፪) ሰላምን ሳታዳላ በሩቅም በቅርብም ላሉት ትሰብካለች፡፡ • “ርቃችሁ ለነበራችሁ ለእናንተ ሰላምን ቀርበው ለነበሩትም ሰላምን የምስራች ብሎ ሰበከ” እንዲል (ኤፌ.፪፡፲፯)፡፡    ለቤተ ክርስቲያን ሰላም መሣርያዋ፣ ሕይወቷ፣ ጸሎቷ፣ ቀኖናዋና ዶግማዋ ነው፡፡ ለቤተ ክርስቲያን ሰላም ራሱ እግዚአብሔር ነው፡፡  ስለዚህ “ሰላም ከሌላችሁ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር የለም” በማለት የሰው ልጅ ሰላማዊ እንዲሆን ታስተምራለች፡፡ ጥላቻን አጥብቃ ትቃወማለች፡፡ “ጥልን በመስቀሉ ገደለ” የሚለውን መልእክት እንደ ሰንደቅ የምትጠቀምበት መለያዋ ነው፡፡ ስለዚህ በሰዎች መካከል የተከሰተውን ጥላቻ በተሰጣት መንፈሳዊ ጥበብ ማስወገድ ተልእኮዋ ነው፡፡ በሰላም ግንባታ ኢትዮጵያውያንን ያለ ልዩነት በማሳተፍ ቤተ ክርስቲያን የሰላም ሚናዋን በጥበብና በማስተዋል በቋሚነት ትሠራለች፡፡  ሰላምን ያሳጡን ጦርነቶችና ግጭቶች ዘላቂ መፍትሔ እንዲያገኙና በአጭሩ እንዲቋጩ ጥሪዋን ታስተላልፋለች፤ እምቢ ባዮችንም በማውገዝ ዘላቂ መፍትሔ የሚገኝባቸውን ሂደቶችን ትቀይሳለች፡፡  የሰላም ሰነዶችን በማዘጋጀት አስቸኳይ የሆነ ሃገራዊ የሰላም ንቅናቄ በፍጥነት እንዲጀመርና በዚህም ውስጥ ውጤት ሊያመጣ የሚችል ሥልት ተቀይሶ ወደ ሥራ እንዲገባ ማድረግ ለነገ የሚባል ጉዳይ አይደለም፡፡  ቤተ ክርስቲያን የራስዋ የሰላም ከፍተኛ ልዑክ ኖሯት በመዋቅሯ ሁሉ ተዘጋጅቶ ተግባራዊ የሰላም ሥምሪት ለማድረግ የሚያስችል ንቅናቄ ታደርጋለች፡፡  በሃገራዊ የሰላም ጥረቶች፣ የውይይትና የምክክር መድረኮች ባለድርሻ እንድንሆን ከሚመለከተው ጋር ተቀራርቦ መሥራት የሚቻልበትን አሠራር ትዘረጋለች፡፡  በማኅበራዊ ዘርፍ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የቤተ ክርስቲያን የሰላም ጥሪ ተቀባይነት እንዲኖረው በትጋት ትሠራለች፡፡ በሰብአዊ ድጋፍና በእርዳታ ማስተባበር ለወገኖቻችን መድረስ እንዲቻል ልጆቿን አስተባብራ ትንቀሳቀሳለች፡፡  በመግቢያችን እንደተጠቀሰው “ፈኑ እዴከ አንሥእ ኃይለከ” ብለው የለመኑ ነቢያትን የሰማ እግዚአብሔር አምላካችን ጸሎታችንን እንደሚሰማን ከልባችን በማመን በእርሱ ያለንን ትምክህታችን ይህ በመሆኑ ከጽኑ ተስፋና ፍቅር ጋር እንድንፈጽመው አደራ እንላለን፡፡ በተጨማሪ ይህንን መንፈሳዊ ሥርዓትና መደበኛ የቤተ ክርስቲያን ተልእኮ ሁሉም በቅንነት እንዲረዳው በጥብቅ እናሳስባለን፡፡ ዓለማውያን ምሁራን ሃገሮቻቸውን ለመጠበቅ፣ የሕዝባቸውን አንድነት ለማስቀጠል፣ የተረጋጋና እርስ በርሱ የሚተማመን ማኅበረሰብን ለማጽናት በሕግ የሚያስቀጡ “የጥላቻ ንግግርን” የሚያስቀር አዋጅ ያወጣሉ፡፡ ሃገራችንም የጥላቻ ንግግርና ሐሰተኛ መረጃን የሚከለክል አዋጅ አላት፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም ጥላቻንና ሐሰተኛ ትርክቶችን ታወግዛለች፡፡  የአሁኑ ጸሎተ ምኅላ የሚደረገው አለመግባባት በምክክር፣ በውይይት፣ በመደማመጥ እንዲፈታ፤ መከራን በመረዳዳት እንድንሻገር፣ እንደየኃላፊነታችን የሚጠበቅብንን ለመወጣትና የሕዝባችንን ጥያቄ ለመመለስ እንድንችል፣ ችግራችን ሁሉ ተፈትቶ ሰላምና መረጋጋት እንዲመጣ ከሃሊው አምላክ እንዲያግዘን በአንድነት ለመጮኽ ነው፡፡   ስለዚህ ይህ ዓላማው መንፈሳዊ ብቻ የሆነ የጾም፣ የጸሎትና የምኅላ አዋጅ መሆኑን ተረድታችሁ የሚድያ፣ የትምህርትና የፍትሕ፣ መሰል ተቋማት  በሚያስፈልገው ሁሉ እንድትተባበሩን በዚሁ አጋጣሚ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስም አባታዊ ማሳሰቢያን እናቀርባለን፡፡    በአጠቃላይ ቤተ ክርስቲያን በታሪክም ሆነ በትውልድ የሚያኮራ ውጤታማ ሥራን እንድትሠራና ከቃል ወደ ተግባር እንድትሸጋገር ለማድረግ ይህ መግለጫ ተሰጥቷል፡፡ እግዚአብሔር አምላክ  ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን  ይባርክ ይቀድስ። ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!!! አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ  ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ  ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት  ሕዳር 11 ቀን 2016 ዓ.ም    አዲስ አበባ ኢትዮጵያ +++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++

“ከዚህ በኋላ ታላቅ ስልጣን ያለው ሌላ መልአክ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ፥ ከክብሩም የተነሣ ምድር በራች።” ራእይ 18፥1 እንኳን ለመልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በሠላም አደረሳችሁ! የሰንበ
“ከዚህ በኋላ ታላቅ ስልጣን ያለው ሌላ መልአክ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ፥ ከክብሩም የተነሣ ምድር በራች።” ራእይ 18፥1 እንኳን ለመልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በሠላም አደረሳችሁ! የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! መልካም በዓል! ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

"እግዚኡ ረሰዮ ለውእቱ ሚካኤል እምኲሎሙ መላእክት ይትለዓል መንበሩ" እግዚአብሔር አምላክ ፍጥረትን ሳይፈጥር በፊት ባሕርይው ባሕርይውን ያመሰግን ነበር። ክብሩ በባሕርይው እንደቀረ አውቆ ሰው እና መላእክት ስሙን እንዲቀድሱ ክብሩን እንዲወርሱ ፈጠራቸው። ዲያብሎስ በማመስገን ፈንታ መመስገን በመፈለጉ እና እኔ ሥላሴን ከማመስገን ሕጹፅ ነኝ በማለቱ በእግዚአብሔር መልአክ ወደ ምድር ተጥሏል። ይሄኔ ነው ቅዱስ ሚካኤልን ቅሩበ እግዚአብሔር : አኃዜ መንጦላዕት : አቅራቤ ስብሐት : የመላእክት አለቃ አድርጎ ልክ በዛሬው ቀን እንደሾመው ሊቁ ቅዱስ ያሬድ "እግዚኡ ረሰዮ" ጌታው መረጠው በሎ በድርሰቱ የተናገረው። ጌታው ለምን መረጠው ቢሉ የዋኅ ነውና ከእመቤታችን ቀጥሎ እንደእርሱ ያለ የዋኅ የለምና "ወሚካኤልኒ ከማኪ ርህሩህ" እንዲል አንድም "በልማደ ምሕረት ወሣሕል ዘይትማሰለከ አልቦ እንበለ ባሕቲታ እኅትከ ማርያም ድንግል" እንዲል  የዋህነቱ በምን ታውቋል ቢሉ አዳም ስቶ እንደሚወድቅ : ኋላ ማርያም ከምትባል ድንግል ተወልዶ እንደሚያድነው ቢነግራቸው "ይህችን ድንግል ክንፌ ላይ አትምልኝ" ብሎ ነበር። "ሚካኤል መልአክ በክነፈ ጾራ" እንዲል እግዚአብሔር አምላካችን ክብር ይግባው እና ከፍጥረት መገኘት ጀምሮ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤልን ሳያማክር ያደረገው ነገር የለም። ዘካ 1÷12 ለዚህም ሊቃውንቱ "መልአከ ምክሩ" እያሉ ይጠሩታል። ዛሬ በምናስበው ዓቢይ በዓል እስራኤላውያን ከግብጽ ባርነት ለመውጣት መንገድ በጀመሩ ጊዜ ከሙሴ ጋር በመሆን ቀን ፀሐይ እንዳይፈጃቸው ደመና እያደረገ : ሌሊት እንቅፋት እንዳይመታቸው ብርሃን እያበራ የሚመራ : ይህ ብቻም አይደለም “በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለ አንተ ያዝዛቸዋልና” መዝ 91፥11 ተብሎ የተነገረለት ነውና ጌታው መረጠው አለ። "እምኲሎሙ መላእክት ይትለዓል መንበሩ" አለ : ይህም ከሌሎቹ መላእክት በበለጠ በእግዚአብሔር "የተቀባ ኪሩብ" ነውና ክብሩ ከፍ ይላል አለ። ስለምን እንዲህ አለ መልአክ ከመልአክ ይበልጣልን? ቢሉ አዎን ይበልጣል ከጣት ጣት እንዲበልጥ ከመልአክም መልአክ ይበልጣል : የአምላከን እናት ከሚካኤል በቀር ማን ረድቷል? ከነቢያት ለዳንኤል ማን ፈጥኖ ደርሷል? ዳን 10÷21 መካን ለነበሩትስ መሥዋዕት አሳርጎ ማን ልጅ ሰጥቷል? መሳ 13÷17 ለሐዋርያት ሰንሰለቱን ማን በጥሷል? ሐዋ 16÷26 በአንዱ መልአከ እግዚአብሔር በቅዱስ ሚካኤል መላው ምድር ያበራልና። “ከዚህ በኋላ ታላቅ ስልጣን ያለው ሌላ መልአክ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ፥ ከክብሩም የተነሣ ምድር በራች።” ራእይ 18፥1 ዲ/ን መንግሥተአብ ብርሃነ ከአፍሪካ ኅብረት ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ሰንበት ትምህርት ቤት። ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

‹‹መሠረታቲሃ ውስተ አድባር ቅዱሳን፣ መሠረቶቿ በተቀደሱ ታራሮች ናቸው፡፡›› መዝ 86፡1 ጽርሐ ንግሥት ቅድስት ሐና ቤተ ክርስቲያን እንኳን ለእናታችን ለቅድስት ሐና እመ ማርያም በዓለ ዕረፍት በሠላ
‹‹መሠረታቲሃ ውስተ አድባር ቅዱሳን፣ መሠረቶቿ በተቀደሱ ታራሮች ናቸው፡፡›› መዝ 86፡1 ጽርሐ ንግሥት ቅድስት ሐና ቤተ ክርስቲያን እንኳን ለእናታችን ለቅድስት ሐና እመ ማርያም በዓለ ዕረፍት በሠላም አደረሳችሁ! የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! መልካም በዓል! ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

‹‹መሠረታቲሃ ውስተ አድባር ቅዱሳን፣ መሠረቶቿ በተቀደሱ ታራሮች ናቸው፡፡›› መዝ 86፡1 የእናታችን ቅደስት ሐና ሐረገ ትውልድ ከነገደ ሌዊ ከተገኘው ከሊቀ ካህናቱ አሮን ወገን ነው፡፡ ይህም እንደዚህ ነው፣ ቴክታ የተሰኘች ሴት በጥሪቃ የተባለ ወንድ አግብታ በኢየሩሳሌም ይኖሩ ነበር፡፡ በሀብተ ሥጋ የከበሩ ደጋግ የእግዚአብሔር ሰዎች ቢሆኑም በፊታቸው የሚመላለስ፣ ሀብታቸውን የሚወርስ፣ የዓይናቸው ማረፊያ፣ የልባቸው ተስፋ የሚሆን ልጅ ባለመውለዳቸው እያዘኑ ይኖሩ ነበር፡፡ ከእለታት በአንደኛው ቀን ቴክታ ደግ ራእይ ዐየች፤ ራእዩንም ለባለቤቷ በጥሪቃ እንዲህ ስትል ነገረችው፡፡ ‹‹መቼም አምላከ እስራኤል እግዚአብሔር የሚያደርገውን የሚያውቅ የለም በሕልሜ አንዲት ነጭ እንቦሳ ከማሕጸኔ ስትወጣ፣ እንቦሳይቱም ሌላ እንቦሳ እየወለደች እስከ ስድስት ስትደርስ፣ ስድስተኛይቱ ግን ጨረቃን ስትወልድ፣ ሰባኛይቱ ጨረቃ ግን ፀሐይን ስትወልድ ዐየሁ አለችው፡፡ በጥሪቃም ‹‹እኅቴ ሆይ ደግ ራእይ ነው፡፡›› በማለት ወደ ሕልም ፈቺ ዘንድ ሔዶ ቢጠይቅ ‹‹እግዚአብሔር በምሕረቱ ጎብኝቷችኋል፣ በሣህሉ መግቧችኋል፣ ስድስት ሴት ልጆች በየተራ ትወልዳላቸችሁ፣ ሰባተኛይቱ ጨረቃ ግን በጨረቃ የተመሰለች ከሰው ልጆች ሁሉ የበለጠች፣ ከመላእክትም የከበረች ደግ ብላቴና ትወልዳለች፣ የፀሐዩ ምስጢር ግን አልተገለጠልኝምና ጊዜ ይተርጉመው›› ብሎታል፡፡ በጥሪቃም ህልም ፈቺው ያለውን አንድ በአንድ ለባለቤቱ ቴክታ ነገራት እርሷም ደስ ብሏት ‹‹አምላከ እስራኤል ያውቃል›› ብላ ዝም አለች፡፡ ከዚህም በኋላ ቴክታ ፀንሳ ሴት ልጅ ወለደች፤ እግዚአብሔር ፀሎታችንን ሰማን ስትል ሄኤሜን ብላ ጠራቻት፡፡ ሄኤሜንም ዴርዴንን ወለደች፤ ዴርዴንም ቶናህን ወለደች፣ ቶናህም ሲካርን ወለደች፣ ሲካርም ሄርሜላን ወለደች፣ ሄርሜላ ማለት በዕብራይስጥ “ከክቡራን ባለጸጎች የተወለደች” ማለት ነው፡፡ ሄርሜላም ማጣትን አግብታ በጸሎትና በስለት፣በመልአኩ ቅዱስ ራጉኤል ብስራት ፀንሳ ከዓለመ አንእስት ተመርጣ የአምላክ አያት ለመሆን የበቃችውን ቅድስት ሐናን በ5421 ዓመተ ኩነኔ መስከረም ሰባት ቀን ወለደች፡፡ ሐና ማለት “በሃይማት የጸናች፣ በሥነ ምግባር የቀናች፣ በቅድስና፣ በንጽሕና፣ በድንግልና ነፍስም የተሸለመች፣ ቅደስት፣ ክብርት፣ ልዕልት፣ ደግ ሴት” ማለት ነው፡፡ ቅደስት ሐና ቀስ በቀስ አድጋ ሰባት ዓመት ሲሆናት ወላጆችዋ ማጣትና ሄርሜላ ሕርማያኖስ ከሚባል መምህር ዘንድ ወስደዋት ሥርዓተ ኦሪትን ተምራለች፡፡ 15 ዓመት ሲሞላትም ከነገደ ይሁዳ ከቤተ መንግሥት ወገን የቅስራን ልጅ ኢያቄምን አገባች፡፡ ኢያቄምም እንደ እርሷ ሕገ እግዚአብሔርን የተማረ ነበርና ሕጉን አክብረው የሚፈሩ፣ ለድኸ ሰው የሚራሩ፣ ጾም፣ ጸሎትን የሚያዘወትሩ ደጋግ ሰዎች ሆኑ፡፡ ሀብታቸው ግን በጥበበ አምላክ በመጠን ነበር፣ እንዲህ ሆነው በቅድስና ሲኖሩ እንደ ወገኖቻቸው መክነው ለስማቸው ማስጠሪያ፣ ለዐይናቸው ማረፊያ ልጅ አልነበረባቸውም፡፡ ከዚህም የተነሳ ቅድስት ሐናን በዘመኗ የነበረው ሰው ሁሉ ይንቃት፣ ይገፋት፣ ያቃልላት ነበር፡፡ ቅዱስ ኢያቄምና ቅድስት ሐና ግን ልጅ እንዲሰጣቸው እግዚአብሔርን በቀንና በሌሊት ተግተው ሲለምኑና ሲሳሉ በትዕግስት ሲኖሩ ሐምሌ 30 ቀን ራእይን አይተው አልጋና ምንጣፍ ለይተው እስከ ሰባት ቀን ሱባዔ በመያዝ በብሥራተ መልአክ ከሰው ልጆች የበለጠች ከመላእክትም የከበረች፣ ቅደስት፣ ድንግል፤ ንጽሕት ማርያም ነሐሴ ሰባት ቀን ከቅድስት ሐና ተጸነሰች፡፡ ቅድስት ሐና እመቤታችንን በፀነሰች ጊዜ ብዙ ገቢረ ተአምራትን አድርጋለች፡፡ ከነዚህም መካከል ሳምናስ የተባለ የአጎቷ ልጅ ሞቶ ሐዘኗን ለመግለጽ በአልጋው እየተዘዋወረች ስታለቅስ ጥላዋ ቢያርፍበት “አፈፍ” ብሎ ተነስቶ ከእርሷ ስለምትወለደው ስለ እመቤታችን ቅደስት ድንግል ማርያም መስክሮ ሰግዶላታል፡፡ በሌላ በኩልም ቤርሳቤህ የምትባል አንድ ዐይኗ የታወከ አክስት ነበረቻት፣ መጽነሷን ሰምታ ለማረጋገጥ የቅደስት ሐናን አካል ዳስሳ ድንገት ዐይኗን ብትነካው “ቦግ” ብሎ በርቶላታል፡፡ ይህን የተመለከቱት አይሁድ በምቀኝነት በመነሳሳት ቅዱስ ኢያቄምንና ቅድስት ሐናን በድንጋይ ወግረው ሊገሏቸው በተነሱ ጊዜ ‹‹ጸርኁ ጻድቃን ወእግዚአብሔር ሰምዖሙ፣ ወእምኩሉ ምንዳቤሆሙ አድኀኖሙ፤ ጻድቃን ወደ እግዚአብሔር ጮሁ እግዚአብሔር ሰማቸው ከመከራቸውም ሁሉ አዳናቸው›› መዝ 33፡17 እንዳለ እግዚአብሔር መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልን ልኮ እየመራ ወደ ሊባኖስ ተራራ ወሰዳቸው፡፡ በዚያም በ5484 ዓመተ ኩነኔ ግንቦት አንድ ቀን ቅደስት ሐና እንደ ፀሐይ የምታበራ፣ እንደ አንበሳ የምታስፈራ፣ በጨረቃ የተመሰለች ፀሐየ ጽድቅ ጌታችንን የምትወልድ ቅድስት ማርያምን ወለደች ‹‹እምሊባኖስ ትወፅእ መርዓት፤ ሙሽራይቱ ከሊባኖስ ትወጣለች›› መሐል 3፡8 እንዳለ፡፡ ቅዱስ ኢያቄም እና ቅድስት ሐና እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን በመውለዳቸው ለዓለሙ ሁሉ መድኃኒት የሆነ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አያቶች ለመሆን በቅተዋል፡፡ የቅድስና ደረጃቸውም የቅዱሳን ሁሉ መሠረት ሊሆን ችሏል፡፡ በመካንነታቸውም አመካኝተው ሕገ ጋብቻቸውን ያላፈረሱ ንጹሐን፣ ክቡራን፣ ደጋግ ባልና ሚስቶች በመሆናቸውም አባ ሕርያቆስ በመንፈስ ቅዱስ ተቀኝቶ ‹‹ኦ! ድንግል አኮ በፍትወተ ደነሰ ዘተፀነስኪ፣ አላ በሩካቤ ዘበ ሕግ እም ሐና ወኢያቄም ተወለድኪ፤ ድንግል ሆይ! በኃጢአት ፍትወት የተፀነስሽ አይደለሽም፣ በሕግ ከሆነ ሩካቤ ከሐናና ኢያቄም ተወለድሽ እንጂ፡፡›› ሲል በቅዳሴው የቅድስት ሐናንና ንጽሕት ልጅ ያመሰገናት፡፡ ‹‹ዘጻመወ በዓለም የሐዩ ለዝሉፉ፤ በዚህ ዓለም በገድል በትሩፋት የደከመ ፈጽሞ ለዘለዓለም ይድናል፡፡›› መዝ 48፡9 በሚለው በቅዱስ ዳዊት ቃል መሠረት እናታችን ቅድስት ሐና ኅዳር 11 ቀን ከዚህ ኃላፊው ዓለመ ሥጋ፣ ወደ ማያልፈው ዓለመ ነፍስ በሞት ተሸጋገረች፡፡ ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

ባይተዋርነት እስከ መቼ?  መስከረም ፲፭ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም. በአርሲ ሀገረ ስብከት በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ ቤተ ክህነት ኦርቶዶክሳውያን ተገደሉ (ሰባት ኦርቶዶክሳውያን)፡፡ ኦርቶዶክሳውያን ጨቅላ ሕፃና
ባይተዋርነት እስከ መቼ?  መስከረም ፲፭ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም. በአርሲ ሀገረ ስብከት በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ ቤተ ክህነት ኦርቶዶክሳውያን ተገደሉ (ሰባት ኦርቶዶክሳውያን)፡፡ ኦርቶዶክሳውያን ጨቅላ ሕፃናትን ጨምሮ የካህናት ቤተሰብ በአሰቃቂ ሁኔታ በጥይት ተደብድበው ተገደሉ፡፡ በርካቶች ቆሰሉ፡፡  ካህናት እና ቤተሰቦቻቸው ከቤተ ክርስቲያን እስከ ቤታቸው ታድነው ይገደላሉ፡፡  መስከረም ፳፫ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም.) በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት በአዳማ ዙሪያ ወረዳ ቤተ ክህነት በአርቱ መካነ ቅዱሳን ቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች የሆኑት አባ ተክለ አብ እና ቀሲስ መሠረት ተገደሉ፡፡ በደራ፣ በወለጋ፣ በቤንሻንጉል ወዘተ  አሮጌው ዓመት(፳፻፲፭ ዓ.ም.) በስልጤ ዞን የተለመደውን የኦርቶዶክሳውያን ደም በማፍሰስ፣ ሀብት ንብረታቸውን በማቃጠል እና በማሳደድ ነው የተሰናበተን፡፡ አዲሱ ዓመት ደግሞ የአሮጌውን ዓመት የደም ግብር መገበርን አጠናክሮ ቀጥሎበታል፡፡  ካህኑ በዐውደ ምሕረት በአገልግሎት ላይ እያሉ በጥይት የተመቱት ጠረፍ አካባቢ በምትገኘው አጥቢያ አይደለም፡፡ እዚሁ አዲስ አበባ ነው፡፡ .... 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/ባይተዋርነት-እስከ-መቼ/ ባይተዋርነት እስከ መቼ? ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

"የማዳንህን ደስታ ስጠኝ በእሽታ መንፈስም ደግፈኝ።" መዝ 50፡12 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! መልካም ዕለተ ሰንበት! ✍️Youtube �
"የማዳንህን ደስታ ስጠኝ በእሽታ መንፈስም ደግፈኝ።" መዝ 50፡12 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! መልካም ዕለተ ሰንበት! ✍️Youtube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

" ምን ይሻለናል?" የሰው መሻቱ ብዙ ነው በሕይወቱ ለራሱ አብልጦ የሚፈልገውንና የሚሻውን ነገር መርጦ ለእኔ ይላል። ያ ይሻለኛል ይበጀኛል ያለውና የመረጠውን ምርጫ በሌላ ግዜ ደሞ ሊጠላውና ላይመርጠው ሊተወውም ይችላል። እንዲሁም ይሻለኛል ብሎ በመረጠው ነገር በወሰነው ውሳኔ ለራሱ ተጠቅሞ ሌሎችን ሊጠቅም ለራሱም ተጎድቶ ሌሎችንም ሊጎዳ ይችላል። ስለዚህ ከድካሙ የተነሳ የውሳኔ ችግር አለበትና ስህተት ከሌለበት ለእኛ የሚሻለንን ከሚያውቅና በጊዜው ከሚሰጠን ከእግዚአብሔር ዘንድ ሊቀርብ ለሕይወቱ የሚበጀውን እንዲሰጠው ዘውትር ሊለምን ይገባል። ሰው በምድር ባለች አጭር እድሜው (ሕይወቱ) ለራሱም ሆነ ለሰዎች ይበጀኛል ብሎ የሚመርጠውን ያን ምርጫ(ውሳኔ) የሚወስነው ከምን አንፃር ነው? ለነፍስ ነው ለሥጋ? ዘለዓለማዊ ነው ጊዜያዊ? ሕይወት ነው ሞት? ሲኦል ነው ወይንስ መንግሥተ ሰማያት?እነዚህ ሁሉ ጥያቄዎች ከመሻታችን ጋር ምላሽ የሚያስፈልጋቸው ናቸው። ሁልግዜ ልብ ልንል የሚገባና መዘንጋትም የሌለብን ነገር ግን መሻታችን በቃሉ እስካልተቃኘ፣ ፍቃደ እግዚአብሔርንም እስካልጠበቀ ድረስ ትክክል አለመሆኑን ነው። ከቅርብ ግዜ ወዲህ በሕገ ወጥ መልኩ "ብንሄድ ይሻላል" በሚል ፈሊጥ የሕይወትን ጉድለት፣ ቤተሰባዊ ጉዳዮችን፣ የራስንም ድካም፣ የባልንጀራን ክፋት ወዘተ በአደባባይ በመገናኛ ብዙኃን በማስጣት አንዱ በቀደደው ቦይ የሚፈሱ በራሳቸው ላይ ክፉ ውሳኔ የሚወስኑ ብዙዎችን እየተመለከትን እንገኛለን። ለመሆኑ ሊሄዱ ባሰቡበት መንገድ ተጉዘው የነፍሳቸው ማረፊያ የት ሊሆን እንደሚችል አስበውት ይሆንን? አካሄዱስ ትክክለኛና የመጨረሻስ መንገድ ነውን? ለነሱ የመሻሉን ልክ በምን አወቁት? የመሻታቸውስ ምንጭ መንፈስ ቅዱስ ወይስ መንፈሰ ርኲስ? "ብንሄድ (ብንሞት)ይሻላል!" ሞትን መፈለግ በራሱ ኃጢአት አይደለም ሁላችንም ሟቾች ነንና፤ ነገር ግን አበው በተለይም ቅዱሳን ሞትን አብዝተው የሚፈልጉት የሚበልጠውን ስላወቁ የሞትን ከዚህኛው ዓለም ወደ ወዲያኛው መሸጋገርያ ድልድይነት ስለተረዱ ነው። እንደነ ቅዱስ ጳውሎስ አይነት አባቶች መሄድን( መሞትን) ቢሹ በቅድስና ሕይወት ኖረው፣ ከክርስቶስ ጋር መኖርን ናፍቀው፣ በእምነት መነጽር በኋላኛው ዓለም የሚገጥማቸውን ዘለዓለማዊ ሕይወታቸውን ተመልክተው ነው። " በእነዚህም በኹለቱ እጨነቃለሁ፤ ልሄድ ከክርስቶስም ጋር ልኖር እናፍቃለሁ፥ ከሁሉ ይልቅ እጅግ የሚሻል ነውና፤" ፊል፩፥፳፫ እንዲል። ቅዱስ ጳውሎስ ሞትን ሻ እንጂ ወደርሱ በግድ አልጠራትም፣ መግደልና ማንሳት የሚቻለውን እግዚአብሔርን ጠየቀ እንጂ ባልሆነ መንገድም ለማግኘት አልፈለገም አልጣረምምም። ለእንደኛ አይነቱ እድሜውን በአግባቡ ላልተጠቀመ በቅድስና ጎዳና ላልተመላለሰ፣ በንስሓ ራሱን ላላደሰ፣ የሕይወት ጣዕም ላልገባው ሰው ግን ሞትን መሻት ሞት ነው። ይልቅንስ ሟችነትን እያሰቡ በአግባቡ እድሜያችንን በንስሐ መጠቀም ብንችል የበለጠ ከሁሉ ይልቅ እጅግ የሚሻለውን ለራሳችን በመረጥን ነበር። መሄድን የሚሻ ሰው ከክርስቶስ ጋር መኖርን የሚናፍቅ ነው። ከክርስቶስ ጋር መኖርን የሚናፍቅ ያ ሰው ደሞ የናፈቀውን የክርስቶስን ቃል ይጠብቃል፣ መንገዱን በማቅናት አካሄዱንም ያሳምራል፣ ነፍሱን በክብር ለማግኘት ትዕግስትን ያበዛል። መጽሐፍ " በመታገሣችሁም ነፍሳችሁን ታገኛላችሁ።" ሉቃስ ፳፩፥፲፱ ይላልና። ይህም በምድር በሚያጋጥም ማናቸውም መከራ እግዚአብሔርን ከማማረር ይልቅ በትዕግስት በመጠበቅ የሚገኝ ነው። " በቤተ ክርስቲያን ብንኖር ይሻላል!" የሕይወትን ቃል በምንቃርምባት፣ የልብ ጭንቀት በሚቀልባት፣ ፈውሰ ሥጋ ፈውሰ ነፍስ በሚፈጸምባት፣ እግዚአብሔር በሚገኝባት በቅድስት ቤተክርስቲያን መሄድን ባለን ዘመን ሁሉም መኖርን መሻት የብልህ ሰው ልመና ነው። ቅዱስ ዳዊት ለእርሱ የሚሻለውን አብዝቶ እግዚአብሔርን በጠየቀበት ጸሎቱ፦ " እግዚአብሔርን አንዲት ነገር ለመንሁት እርስዋንም እሻለሁ፤ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ በእግዚአብሔር ቤት እኖር ዘንድ፥ እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኘውንም አይ ዘንድ፥ መቅደሱንም እመለከት ዘንድ።" መዝ ፳፯÷፬ አለ ይህም መሻቱን የሚፈጸምበት እድል ቢገጥመው ጥሪም ቢቀርብለት ደስታውን አብዝቶ ሲገልጥ እንመለከታለን። "ወደ ቤተ እግዚአብሔር እንሂድ ባሉኝ ግዜ ደስ አለኝ" እንዲል። መዝ ፻፳፩ የሐዋርያት አለቃ ቅዱስ ጴጥሮስ " ጌታ ሆይ ብትወድስ በዚህ መኖር ለእኛ መልካም ነው" በማለት በደብረ ታቦር አንጻር በቅድስት ቤተክርስቲያን የመኖርን መልካምነት መግለጡ በነፍስ በሥጋ የሚገኝባትን በረከት ተመልክቶ የእግዚአብሔርን ክብር በዐይኑ አይቶ ነው። ማቴ ፲፯ "ብንሄድ ይሻላል" አዎ በምድር ባለች ገነት፣ መልካምን ወደምታስመለክት፣ የክብሩ መገለጫ ወደሆነች፣ የነፍስ ረፍት ወደሚገኝባት፣ በጎ መሻታችን ወደሚፈጸምባት፣ የዓለምን ማዕበል ወደምንሻገርባት፣ መብለ ነፍስ በነፃ ወደሚታደልባት፣ ወደ ቤተክርስቲያን ብንሄድ ይሻላል! የማንጸጸትበት ከሁሉ ይልቅ የምንጠቀምበት ነውና። "ብንቀርብ ይሻላል" ሌላኛው ቅዱስ ዳዊት ለራሱ አብዝቶ ስለሚሻለው ጉዳይ ሲናገር " ለእኔ ግን ወደ እግዚአብሔር መቅረብ ይሻለኛል" መዝ ፸፫÷፳፰ አለ ምክንያቱንም አያይዞ " መታመኛዮ እርሱ ነውና" ሲል ይናገራል። መታመኛውን በእግዚአብሔር ያደረገ ሰው አብዝቶ ወደ እግዚአብሔር መቅረብን ማለትም እንደ እያሱ "እኔና ቤቴ ግን እግዚአብሔርን እናመልካለን" ይላል እርሱን ብቻ ያመልካል፣ ራሱን በንስሓ ንፁህ በማድረግ በትዕዛዙ በመጓዝ በእርሱ ይኖራል እግዚአብሔርም ከእርሱ ጋር ይኖራል። መጽሐፍ " በእኔ ኑሩ እኔም በእናንተ እኖራለሁ፡፡" ዮሐ ፲፭÷፬ እንዲል። ከእግዚአብሔር ጋር የምንኖረው ደግም ስለ እኛ የቆረሰውን ክቡር ሥጋውን ስንበላ ቅዱስ ደሙንም ሰንጠጣ ነው፡፡ " ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ በእኔ ይኖራል እኔም በእርሱ እኖራለሁ።" ዮሐ ፮ ÷፶፮ እንዲል፡፡ " ብንቀርብ ይሻላል! " አዎ ሕይወትን ከሚሰጥ እርሱ ራሱ ሕይወት ከሆነ እግዚአብሔር ብንቀርብ ይሻላል! ትዕዛዙንም ጠብቀን በልጅነት መንፈስ ብንቀርብ ይሻለናል!፣ ወደ እርሱ የቀረቡትን ከቶ ወደ ውጭ የማያወጣ ለክፉም ወደማይሰጥ ወደ እግዚአብሔር ብንቀርብ ይሻለናል። እርሱ ቸር መሐሪ ይቅር ባይ ክፋትን የማያውቅ ጻድቅ አምላክ ነውና። የሚሻለንን ለእኔ የምንለውን እንወቅ ከእኛ በላይ ስለኛ የሚያስብ የሚሻለንን የሚያውቅና መስጠት የሚቻለው አምላክ እንዳለን አንዘንጋ ሐሳባችንን የሚያስጨንቀንንም ነገር ሁሉ የሚቻለው አምላክ ነውና በእርሱ ለእርሱ እንስጠው ብንሰማው ሰውነታችንም ረፍትን ታገኛለችና። "ጆሮአችሁን አዘንብሉ ወደ እኔም ቅረቡ፤ ስሙ ሰውነታችሁም በሕይወት ትኖራለች፤" እንዲል። ኢሳ ፶፭÷፫ ነገር ግን ወደ እርሱ ከመቅረብ ይልቅ ብንርቀው፣ ቃሉንም ባለመስማት በገዛ መንገዳችን ብንጓዝ፣ ሕይወትን ንቀን ሞትን ብንመርጥ " አቤቱ፥ የእስራኤል ተስፋ ሆይ፥ የሚተዉህ ሁሉ ያፍራሉ፤ ከአንተም የሚለዩ የሕይወትን ውኃ ምንጭ እግዚአብሔርን ትተዋልና በምድር ላይ ይጻፋሉ። " ት ኤር ፲፯÷፲፫ እንዲል የዘለዓለማዊ ኑሮአችንን አበላሸን በምድራዊ ሐሳብ ተስበናልና ዋጋችንን በምድር በእጃችን እንቀበላለን። ይቆየን ከሚኪያስ ግዛቸው።