የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU 的分析概览
频道 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 14 484 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 6 043,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 334 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 14 484 名订阅者。
根据 30 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 530,过去 24 小时变化为 23,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 39.14%。内容发布后 24 小时内通常能获得 10.20% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 666 次浏览,首日通常累积 1 477 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 33。
📝 描述与内容策略
尚未提供频道描述。
凭借高频更新(最新数据采集于 01 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
14 484
订阅者
+2324 小时
+1447 天
+53030 天
帖子存档
ጴጥሮስ ወጳውሎስ /ጴጥሮስ እና ጳውሎስ/
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በየአመቱ ሐምሌ 5 ቀን ጴጥሮስ ወጳውሎስ ወይም ጴጥሮስና ጳውሎስ በማለት ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስና እና ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ መልካሙን የክርስትና ገድል ተጋድለው ሰማዕትነትየተቀበሉበት ቀን በታላቅ ድምቀት ታከብራለች።
የክርስቶስን ትምህርት /ክርስትናን/ በማስተማር እና ለዓለም በማዳረስ ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ ያደረጉት እነዚህ ቅዱሳን አባቶች ዞረው ከማስተማር እና ከማገልገላቸውም በተጨማሪ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ መልእክታትን በመጻፍ እና ለተለያዩ ሀገራትም በመላክ ጭምር ወንጌልን አስፋፍተዋል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ ስምንት ምዕራፎችን የያዘ ሁለት መልእክታትን ሲጽፍ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ደግሞ አንድ መቶ ምዕራፎችን የያዘ አስራ አራት መልእክታትን ጽፈዋል።
ቅዱስ ጴጥሮስ
ከአስራሁለቱ ሐዋርያት አንዱ እና በቀድሞ ስሙ ስምዖን ተብሎ ሲጠራ የነበረ ሲሆን በኃላ ግን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ኬፋ ብሎ ሰይሞታል፡፡ ኬፋ ማለት በአራማይክ ቋንቋ ዐለት ማለት ሲሆን ጴጥሮስ ማለትም በግሪክ ቋንቋ ዐለት ማለት ነው፡፡ ዮሐ 1፡43 ማቴ 16:18፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ የትውልድ ቦታው ቤተ ሳይዳ ሲሆን ብዙ በትምህርት የገፋ ሰው አልነበረም፡፡ አሳ እያጠመደ ኑሮውን የሚመራ እና ባለትዳር የነበረ ሰው ነው፡፡ ማር 14፡70 ዮሐ 1፡45 ሐዋ. ስራ 4፡13
ከሐዋርያቱ መካከል ጌታችን ከሚያቀርባቸው እና የሚስጥር ሐዋርያት ከሚባሉት አንዱ ይሄው ሐዋርያ ቅዱስ ጴጥሮስ ሲሆን ጌታችን የኢያኢሮስን ልጅ ከሞት ሲያስነሳ፣ በታቦር ተራራ ላይ ብርሃነ መለኮቱን /ክብሩን/ ሲገልጽ፣ በጌቴ ሴማኒ ጸሎት ሲያደርግ አብሮ የነበረ ሐዋርያ ነው፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ ብዙ ጊዜ ጌታችን ጥያቄ ሲያነሳ ፈጥኖ መልስ በመስጠት የሚታወቅ ሲሆን በተለያዩ ነገሮች ላይ ፈጣን እና አንዳንዴም ችኩል ነበረ፡፡ ማር 5፡35 ማር 9፡2 ማር 14፡32
በጌታችንም ሞት ጊዜ ሊይዙት ከመጡት ወታደሮች የአንዱን ጆሮ በሰይፍ የቆረጠና ጌታችን ከተያዘ በኋላ ሦስት ጊዜ ጌታን አላውቀውም ብሎ ክዷል፡፡ ከትንሳኤው በኋላ ግን ክርስቶስ አምላክ እንደሆነና አይሁድ በግፍ ያለበደሉ እንደሰቀሉት እና እንደገደሉት በአደባባይ ያልምንም ፍርሐት ምስክርነቱን ሰጥቷል፡፡ በተለያዩ ጊዜያቶች ስለክስርቶስ በመመስከሩ ታስሯል፣ ብዙ መከራም ተቀብሏል፡፡ የማሰርና የመፍታት (የክህነት ስልጣን) ስልጣነ ክህነት ላላቸው አገልጋዮች ሁሉ ይሰጥ እንጂ ክርስቶስ በቀጥታ የተናገረውና የሰጠው ግን ለቅዱስ ጴጥሮስ ነበር፡፡ እንዲሁም የሐዋርያት አለቃም አድርጎ ሾሞታል፡፡ ዮሐ 18፡10 ዮሐ 2፡14 ማቴ 16፡18፡፡
በመጨረሻም ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ በ67 ዓ.ም ሐምሌ 5 ቀን በሮም ከተማ በኔሮን ቄሳር እጅ ተይዞ ሊሰቀል ሲል እንድጌታዬ ልሰቀል አይገባኝም ጭንቅላቴን ወደታች አድርጋችሁ ስቀሉኝ ብሎ ቁልቁል ተሰቅሎ ሰማዕትነትን ተቀብሏል፡፡
ቅዱስ ጳውሎስ
ቅዱስ ጳውሎስም ሁለት ስሞች ነበሩት፡፡ የመጀመሪያው የዕብራይስጥ ስሙ ሳውል ሲሆን ይህንን ስም በጳፉ ከበርያሱስ ጋራ እስኪከራከር ድረስ ተጠቅሞበታል፡፡ ከዚያ በኋላ ግን በሮማዊ ስሙ ጳውሎስ ተብሎ ተጠርቷል፡፡ የሐ. ስራ 13፡9 የትውልድ ሐገሩ ጠርሴስ ከተማ ሲሆን እዚያም ድንኳን በመስፋት ይተዳደር ነበር፡፡ አባቱ ፈሪሳዊና ከብንያም ወገን የነበረ ሲሆን የሮም ዜግነትንም ያገኘው በአባቱ በኩል ነበር፡፡ የሐ.ስራ 18፡3፣ 22፡26
በትምህርት ደረጃ ወደኢየሩሳሌም ተልኮ በመሔድ ስመጥር ከሆነው አስተማሪ ከገማልያል የሙሴን ሕግና የአይሁድን ወግ ጠንቅቆ ተማረ፡፡ ከዚህም በኋላ የክርስቶስ ተከታይ የሆኑ ክርስቲያኖችን ያሳድድ ነበረ፡፡ ሊያጠፋቸውም የሚቻለውን ሁሉ ያደርግ ነበረ፡፡ ሰማእቱ ቅዱስ እስጢፋኖስ በድንጋይ ሲወገር በመገደሉ ተስማምቶ የወጋሪዎቹን ልብስ ይጠብቅ ነበረ፡፡ የሐ.ስራ 22፡3 የሐ.ስራ 7፡59፣ 9፡1
ከዚህም በኋላ አማኞችን ለማሳሰር ወደ ደማስቆ ሲሄድ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሰማይ ጠራውና አይኖቹ ታወሩ፡፡ ሰዎችም ይዘው ወደ ሐናንያ ወስደውት አይኖቹን ከከፈተለት በኋላ ለአገልግሎት እግዚአብሔር እንደሚፈልገው ነገረው፡፡ እርሱም በደስታ ተቀብሎ በዚያ ተቀመጠ፡፡ ወደ ምኩራብም ገብቶ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ መሰከረ፡፡የሐ.ሥራ 9፡1፣ 22፡4፣ 26፡9
ይሔ ሐዋርያ ታላላቅ 3 አለም አቀፍ ጉዞውችን በማድረግ የክርስቶስን ወንጌል አስተምሯል፡፡ ብዙ ጊዜ ታስሯል የተለያዩ እንግልቶችም ደርሰውበታል፡፡ በወንጌል አገልግሎት ከቅዱስ ጳውሎስ የበለጠ አይገኝም፡፡ በመጨረሻም በኔሮን ቄሳር ዘመነ መንግስት በ67 ዓ.ም ሐምሌ 5 ቀን አንገቱን ተሰይፎ በሰማዕትነት አርፏል፡፡
ሁለቱንም ሐዋርያት የሚያመሳስላቸው ብዙ ነገሮች ቢኖሩም ከነዚህ መካከል ጥቂቶቹን ብንመለከት ሁለቱንም ስማቸውን ለውጦላቸዋል፣ ሁለቱም ሙት አስነስተዋል፣ ሁለቱም የሰማዕትነት አክሊል ተቀብለዋል፣ ሁለቱም መልዕክትን ጽፈዋል፣ ሁለቱም ስለስሙ ታስረዋል፣ ወንጌልንም ዞረው አስተምረዋል፡፡ በመጨእሻም በተመሳሳይ ዕለት አርፈዋል፡፡ የቅዱሳኑ በረከትና አማላጅነት በሁላችንም ላይ ይደር፡፡
✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg
✍️ Facebook 👇
http://facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
በሰመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
"ወጣትነትና ጾም"
* * *
-- ቅድስት ቤተክርስቲያን ማንኛዉም ክርስቲያን የጾም ና የፀሎት ሕይወት እንዲኖረው ሥርዓትን ደንግጋ በጾም የሚገኘውን ጥቅም እየዘረዘረች ዘወትር ታስተምራለች ።
-- የወጣትነት ዕድሜ የጉልበት ፣ የኃይል ፣ የብርታት ፣ ያሰቡትን የመፈፀምያ፣ አሸናፊነትን ለመጎናጸፍ ሩጫ የሚበዛበት ዕድሜ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ "የጉብዝና ጊዜ " ብሎ እንዲጠራው። " የጭንቀት ቀን ሳይመጣ በጕብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ፤ ደስ አያሰኙም የምትላቸውም ዓመታት ሳይደርሱ፤ "እንዲል (መጽሐፈ መክብብ 12፥1) ለዚያም ነው አበው ከአራቱ ባሕርያተ ሥጋ መካከል አንዱ በሆነው በእሳት መስለው "የእሳትነት እድሜ" ብለው የሚጠሩት።
-- ይህ የጉብዝና ዕድሜ ለዓለማዊም ይሁን ለመንፈሳዊ ነገር ሊውል ይችላል፤ ዓለምን ወድዶ፣ ስሜቱን አዳምጦ ገንዘብ እያሳደደ ለስጋዊ ነገር ብቻ የጎበዘ እንዳለ ሁሉ ሥጋዊ ፍላጎቱን ገትቶ ፣ ገንዘቡንና ጊዜውን ሰውቶ፣ በመንፈሳዊ ምግባራት እየተጋ ፣በእምነት ፈጣሪውን አያስደሰተ ፣ አባቶቹን እያከበረ ይህን የእሳትነት ዕድሜውን የሚሻገር ብዙ አለ።
* * **
--- ይህን የእሳትነት ዕድሜ በብልሀትና በጥበብ ከመሻገርያ መንገዶች አንዱ ጾም ነው። በተቃራኒው እንዳንጾም ፈተና የሚሆንብን ደግሞ ስለ መብል ማሰብና ሆድን መውደድ ነው። ቅዱስ ጳውሎስ ሆዳቸውን ስለሚወዱና ስለ መብል ሲሉ ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን ለሚጥሱ ለሚያቃልሉ ሰዎች " መጨረሻቸው ጥፋት ነው፥ ሆዳቸው አምላካቸው ነው፥ ክብራቸው በነውራቸው ነው፥ አሳባቸው ምድራዊ ነው።" ብሎአቸዋል (ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 3፥19) በተጨማሪ /ጾም አይጠቅምም፣ ዋናው የልብ ንጽህና ነው፤ ዓሳ ብንመገብ ችግር የለውም / እያሉ ስለ ወንጌል ሳይሆን ለከርሳቸው ጠበቃ ስለሚቆሙ ሰዎች " እንዲህ ያሉት ለገዛ ሆዳቸው እንጂ ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ አይገዙምና፥ በመልካምና በሚያቆላምጥ ንግግርም ተንኮል የሌለባቸውን ሰዎች ልብ ያታልላሉ።" ይላል። (ወደ ሮሜ ሰዎች 16፥18)
**
--- የወጣትነት ዕድሜ የሩጫ ጊዜ ነውና አንዳንድ ወጣቶች ለምን አትጾምም ተብለው ሲጠየቁ /ሥራ ላይ ስለሆንኩኝ ፣ ስለሚደክመኝ፣ ቦታው ስለማይመች ወዘተ ... አልጾምም ብለው/ ተራ ምክንያቶችን እያቀረቡ ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን ጥሶ በጠዋቱ መመገብ ፋሽን እየሆነ መጥቷል። በዚህ ዘመን እንደ ቅዱስ ያሬድ ቃል አንደበቱን ከሀሜት ከስድብ ከልክሎ፣ ዐይኑን ከፉ ከማየት ገትቶ፣ ጆሮውን ክፉ ከመስማት ከልክሎ ፣እጁንም ያልተፈቀደለትን ከመዳሰስ አቅቦ፣ እግሩንም ወደ ኃጢአት ስፍራ ከመጓዝ ከልክሎ፣ ሥርዓተ ቤተክስቲያንን አክብሮ ቢችል እስከ ምሽት ባይችል እስከ 9 የሚጾም፣ የስርዓተ ቅዳሴ ተካፋይ የሆነ ፣ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ሥጋውን የሚበላ ደሙንም የሚጠጣ ወጣት በትክክልም ይህን የእሳትነት ዕድሜ የሚያሻግረውን መንገድ ይዟል ያሰኛል።
** ለአንድ ለሚጾም ሰው የሥጋ ድካም ግድና አስፈላጊ ነው። ያለድካም የሚገኝም ጸጋ የለምና። ጾም ሥራን አይከለክልም ሥራም ጾምን አያግድም ቤተክርስቲያን በጾም ሥራ አትስሩ የሚል አስተምህሮ የላትም። እንደውም ሥጋን ለማድከም አመቺ ነው። በገዳም ያሉ አበው በጾማቸው አዘውትረው ይሰራሉ ለባልንጀሮቻቸው ይታዘዛሉ። እንደውም ሥራ መፍታት እንደማይገባ ለማስተማር "ሥራ ቢጠፋ ቆባቸውን ቀደው ከእንደገና ይሠፋሉ" የሚል ብሒል አላቸው። ይህም በሥራ መፍታት ውስጥ የሚከሰተውን የዲያብሎስ ፈተና ለማሸነፍ ነው። በተጨማሪ ላለመጾም ቦታ የአካባቢ ሁኔታ ምክንያት ከቶ አይሆንም።
ለምሳሌ በአድዋ ድል ጀግኖች አባትና እናቶቻችን በዚያ ጦርነት ውስጥ እንኳን ሁነው በመጾማቸው ከፈጣሪ ኃይል እንደሚያገኙ በማመን እየጾሙ ይዋጉ ነበር እንጂ ጮማውን እንቁረጥ ወይኑን እንጎንጭ አላሉም በሀገርና በሃይማኖት ላይ የመጣ ጠላት ያለ ጾምና ጸሎት ሊወጣ አይችልምና።
* ****
--- የወጣትነት ዕድሜ የሥጋ ፍትወታት የሚበረቱበት በተለይም ንፅህናችንን እንድናጎድፍ የዝሙት ፆር የሚበረታበት ስለሆነ በማስተዋል ሊያልፉት የሚገባ ጊዜ ነው። ታድያ ለዚህ መድኃኒቱ ጾምና ፀሎት ነው። ራሱን ለጾም የሚያተጋ ወጣት እርጋታን ዝምታን ይማራል ገንዘብም ያደርጋል፤ ለዛ ነው አበው
"ጾም ትፌውስ ቁስለ ነፍስ
ወታጸምም ኩሉ ፍትወታተ ዘሥጋ
ትሜሕሮሙ ለወራዙት ጽሙና" ትርጓሜ (ጾም የነፍስን ቁስል ትፈውሳለች የሥጋን ፍትወታት /ፆር/ ታስታግሳለች ለወጣቶችም ከልብ የሆነ ዝምታን ታስተምራለች) /የኪዳነ ምሕረት ዚቅ / በማለት የተናገሩት።
--- የሰውነት ቅርጹን ለመጠበቅ ያገኘውን እያግበሰበሰ ጾም ሳይል አርብ ሮብ ሳይተው ከሚመገብ ወጣት ይልቅ በሃይማኖት ሁኖ ሥርዓት እየጠበቀ እየጾመ ጥሬ የሚቆረጥም ወጣት እንደ ሦስቱ ሕፃናት ደምግባቱ ያማረ ልምላሜ ሥጋ ልምላሜ ነፍስ ያልተለየው ይሆናል።
--- በአጠቃላይ ጾም በወጣትነት ይበልጥ ልንለማመደውና ልንተገብረው የሚገባ መንፈሳዊ ሕይወትን የሚያሳድግ የወጣቶች በሽታ ለተባለው ዝሙት ሁነኛ መድኃኒት ነው። /ዮሐንስ 2 ትርጓሜ/
ጾሙን ከፈጣሪ የምንታረቅበት ያድርግልን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ዲያቆን ሚክያስ ግዛቸው
https://youtu.be/Ys-F4TxAIfU ✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg
✍️ Facebook 👇
http://facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
የቅዱስ ሚካኤል ስምና የስሙ ክብር
‹ሰላም ለዝክረ ስምከ ምስለ ስመ ልዑል ዘተሳተፈ
ወልደ ያሬድ ሄኖክ በከመ ጸሐፈ ሶቦ እጼውእ ስምከ ከሢትየ አፈ-----››>
(የያሬድ ልጅ ሄኖክ እንደጻፈው ከልዑል ስም አጠራር ጋር ለተባበረ ስም አጠራርህ ሰላም እላለሁ፡፡) ይለዋል፡፡
✿✿✿✿✿✿✿✿
★★★ ስለ ቅዱሳን መላእክት ስም፣ተልእኮና፣ተግባር ከሰማንያ አሐዱ መጽሐፍ ቅዱስ አንዱ በሆነው በመጽሐፈ ሄኖክ ላይ ተጠቅሶ እናገኛለን፡፡ ሄኖክ በዘመነ አበው ከነበረው ከያሬድ የተወለደ ሲሆን የያሬድ አባትና የሄኖክ አያት መላልኤል ይባላል፡፡ ዘፍ ፭፥፲፭‐፳ ሄኖክ ማለት ሐዲስ ማለት ሲሆን አባታችን አዳም አትብላ የተባለውን ዕፀ በለስ በልቶ እርጅናን(ብልየትን) ለልጆቹ እንዳወረሰ ሄኖክም ደግሞ በዚህ ዓለም ከኃጢአት በቀር አዲስ ነገር እንደሌለ አውቆ አካሄዱን ከፈጣሪው አድርጎ ከእግረ ገነት ወድቆ በጾም፣በጸሎት፣በትሕርምት ተወስኖ ህዳሴ ነፍስን አምጥቷልና በኋላ ሥራው ሐዲስ ተብሏል፡፡ ሄኖክ ከአዳም ጀምሮ ሰባተኛ ትውልድ ሲሆን ከእግዚአብሔር ጋር ስለነበረው ግንኙነት ሙሴ በኦሪት መጽሐፉ ‹‹ሄኖክ አካሄዱን ከእግዚአብሔር ጋር ስላደረገ አልተገኘም እግዚአብሔር ወስዶታል›› ብሎ ቅድስናውንና አለመሞቱን የመሠከረለት ከሃያ ሁለቱ አርዕስተ አበው አንዱ የሆነ ታላቅ አባት ነው ዘፍ ፭፥፳፪ ይሁዳ ቁጥር ፲፬፡፡
✿✿✿✿✿✿✿✿✿
★★★ ሄኖክ በመጽሐፉ በዐይኖቹ ያየውን በጆሮዎቹ የሰማውን ስለ ቅዱሳን መላእክት ስምና ተልዕኮ፣ስለ መሲሕ (ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ)፣ስለ ፀሐይና ጨረቃ ዑደት ጽፎ ለትውልድ ያስተላለፈ አባት ነው፡፡ ስለ ቅዱሳን መላእክት ስምና ተልዕኮ ሲናገር ‹‹የትጉኃን ቅዱሳን መላእክት ስማቸው ይህ ነው፡፡ ከቅዱሳን መላእክት አንዱ ዑራኤል በመብረቅና በነጎድጓድ ላይ የተሾመ ነው፡፡ ከቅዱሳን መላእክት አንዱ ሩፋኤል በሰዎች ነፍሳት ላይ የተሾመ ነው፡፡ ከቅዱሳን መላእክት አንዱ ራጉኤል ስለ ዓለምና ስለ ብርሃናት የሚበቀል ነው፡፡ ለሰው በሚያደርገው በጎነት ላይ ለሕዝቡ ታዛዥ ነውና ከቅዱሳን መላእክት አንዱ ሚካኤል ነው፡፡ አዕምሮአቸውን ባጡ ሰዎችም ላይ የተሾመ ከከበሩ መላእክት አንዱ ሠረቃኤል ነው፡፡ በእባቦችም ላይ በገነትም ባሉ ጻድቃን ላይ የተሾመ ከከበሩ መላእክት አንዱ ገብርኤል ነው›› ሄኖክ ፮፥፩‐፲ በማለት አስፍሯል፡፡
✿✿✿✿✿✿❀❀✿✿
★★★ ሚካኤል የሚለው ቃል የዕብራይስጥ ሲሆን “ሚ” ማለት መኑ “ካ“ ማለት ከመ “ኤል” ደግሞ አምላክ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡ አጠቃለን በአንድነት ስንጠራው ‹‹መኑ ከመ አምላክ›› ማን እንደ አምላክ (እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው?) ማለት ነው፡፡ ይህን የቅዱስ ሚካኤል ስም በጠራን ቁጥር የምንመሠክረው ስለ መልአኩ ብቻ ሳይሆን ስለ ቅዱስ ሚካኤል አምላክ ስለ እግዚአብሔርም ጭምር ነው፡፡ ይህም ማለት ሚካኤል ስንል እግዚአብሔርን በባሕርይ የሚመስለው በሥልጣንም የሚተካከለው በሰማይም በምድርም እንደሌለ የሚናገር፣ ግብሩን የሚገልፅ፣ ኃለዎቱን የሚያስረዳ ስመ እግዚአብሔር የታወቀ የተገለጠ የባሕርይ ልዩ ክቡር ስም መሆኑን የሚገልጥ ነው፡፡
❀❀❀❀❀❀❀✿✿✿❀
★★★ የቅዱስ ሚካኤልን ስም ትርጉም የእግዚአብሔርንም ታላቅነት በዓይኖቹ የተመለከተ ሊቀ ነቢያት ቅዱስ ሙሴ እግዚአብሔርን የሚመስለው እንደሌለ ሲናገር ‹‹አቤቱ በአማልክት መካከል አንተን የሚመስልህ ማን ነው? በቅዱሳን ዘንድ እንደ አንተ የከበረ ማን ነው?›› ብሏል ዘጸ ፲፭፥፲፩፡፡ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት እንዲሁ ‹‹አቤቱ ከአማልክት የሚመስልህ የለም›› በማለት መስክሯል መዝ ፹፭፥፰፡፡ የመልክአ ሚካኤል ጸሐፊ ‹‹ከልዑል ስም አጠራር ጋር ለተባበረ ስምህ ሰላም እላለሁ›› ያለው የልዑላን ልዑል የተባለ የእግዚአብሔርን ስም እንደ ሌሎች መላእክት ሁሉ ቅዱስ ሚካኤልም ስለተሸከመው ነው፡፡ እግዚአብሔር ለእሥራኤል ዘሥጋ በሙሴ አማካኝነት የተስፋውን ምድር እንዲወርሱ ቃል ኪዳን በሰጣቸው ወቅት ‹‹በመንገድህ ይጠብቅህ ዘንድ ወዳዘጋጀሁልህም ሥፍራ ያገባህ ዘንድ እነሆ እኔ መልአኬን በፊትህ እሰድዳለሁ፡፡ ራስህን ጠብቅ፣ ስማው፣ እምቢም አትበለው ስሜም በእርሱ ስለሆነ ኃጢአትን ብትሠሩ ይቅር አይልምና አታስመርሩት›› በማለት የእግዚአብሔር ስም በመልአኩ ስም ውስጥ እንዳለ በግልጥ ተናግሯል ዘጸ ፳፫፥፳‐፳፩፡፡
£✿❀✿❀£❀£€
★★★ በሌላም የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ራሱ ቅዱስ ሚካኤል እንደተናገረው የአምላኩ ስም በስሙ በመኖሩ ስሙን ድንቅ አሰኝቶታል፡፡ በመጽሐፈ መሳፍንት ምዕራፍ ፲፫ ሰፍሮ በምናገኘው የማኑሄና የሚስቱ ታሪክ ላይ ከዳን ወገን ማኑሄ የሚባል አንድ ሰው እንደነበረ ሚስቱም ልጅ መውለድ ያልቻለች መካን ስለነበረች ልጅ መውለድ ባለመቻሏ በምታዝንበት በዚያን ወራት መልአከ እግዚአብሔር ቅዱስ ሚካኤል ተገልፆ እንደምትፀንስ ወንድ ልጅም እንደምትወልድ ልጁም ከእናቱ ማኅፀን ጀምሮ ለፈጣሪው የተለየ ናዝራዊ እንደሚሆን እርሷም የሚያሰክር መጠጥ እንዳትጠጣና፣የረከሰም ነገር እንዳትመገብ፣በልጁም ላይ ምላጭ እንዳያርፍበት አስጠነቀቃት፡፡ እርሷም ተመልሳ የሆነውንና ከቅዱስ ሚካኤል ጋር የተነጋገረችውን መልአኩም ያላትን ሁሉ ለባሏ ለማኑሄ ‹‹የእግዚአብሔር ሰው ወደ እኔ መጣ መልኩም እንደ እግዚአብሔር መልአክ እጅግ የሚያስደነግጥ ነበር ከወዴትም እንደመጣ ጠየቅሁት እርሱም ስሙን አልነገረኝም›› አለችው፡፡
£✿✿✿✿✿✿££
★★★ ማኑሄም የእግዚአብሔር መልእክተኛ ዳግመኛ ይመጣና ለእርሱም ይነግረው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ለመነ፡፡ እግዚአብሔርም የማኑሄን ቃል ሰምቶ መልአኩን ላከ፡፡ የእግዚአብሔርም መልአክ የማኑሄ ሚስት በእርሻው ውስጥ ሳለች እንደገና ወደ እርሷ መጣ፡፡ እርሷም ፈጥና ባሏን ጠራችው አብረውም ሳሉ መልአከ እግዚአብሔር ተገለጠላቸው፡፡ ማኑሄ ‹‹ከሚስቴ ጋር የተነጋገርህ አንተ ነህን?›› ብሎ ቢጠይቀው መልአኩ እርሱ እንደሆነ ገለጠለት፡፡ ማኑሄም ስለሚወልደው ልጅና ሊያደርገው ስለሚገባው ነገር ለሚስቱ እንደነገራት ለእርሱም እንዲነግረው ጠየቀው፡፡ መልአኩም ከመለሰለት በኋላ የሚያነጋግሩት መልአከ እግዚአብሔር መሆኑን ሁለቱም አላወቁም ነበርና ‹‹ነገርህ በደረሰ ጊዜ እንድናከብርህ ስምህ ማን ነው?›› በማለት ማኑሄ ቢጠይቀው ቅዱስ ሚካኤል ስሜ ድንቅ ነው ለምን ትጠይቀኛለህ? ብሎታል፡፡
ሊቃውንቱ ይህን የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል አብነት በማድረግ ‹‹ሚካኤል ብሂል ዕፁብ ነገር›› ትርጓሜ (ሚካኤል ማለት ዕፁብ ነገር) ማለት ነው ብለው ተርጉመውታል፡፡ ይህንንም ይዛ ቅድስቲቱ ቤተክርስቲያን ድንቅ የሆነ ስሙን ‹‹ሰላም ለዝክረ ስምከ›› እያለች ባመረ ዜማ፣ በተወደደ ምስጋና ዘወትር ስታመሰግን ታድራለች፡፡
✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg
✍️ Facebook 👇
http://facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
11ኛው ዓለም አቀፍ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ ባለ 9ኝ የጉባኤው አቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቀቀ፡፡
"የአምላካችን ቤት ከቶ አንተውም!!!" {መጽ.ነኅ.10፥39 }
11ኛው ዓለም አቀፍ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ በተገኙበት በይፋ ተጀመረ !!
በቅዱስ ሲኖዶስ ጸድቆ በየዓመቱ በበዓለ ጰራቅሊጦስ ሰንበት የሚከናወነው ይኸ ጉባኤ ከየአህጉረ ስብከቱ የተወከሉ አባላት የሚታደሙበት እና በሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት እና የአገልግሎት ሂደት ላይ የሚመክር ጉባኤ ነው።
ጉባኤው በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት በጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ እየተካሄደ የሚገኝ ሲሆን በነገው ዕለት ምልዓተ ጉባኤው የአቋም መግለጫ በማውጣት የሚጠናቀቅ ይሆናል።
በጉባኤው መክፈቻ ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ፤ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር ) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊና የኒውዮርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፤ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የየሰንበት ትምህርት ቤቶች ተወካዮች ተገኝተዋል።
https://youtu.be/Tuw7XiJLt8U
✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg
✍️ Facebook 👇
http://facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
"የአምላካችን ቤት ከቶ አንተውም!!!" {መጽ.ነኅ.10፥39 }
የ11ኛው የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጉባኤ ዝግጅት መጠናቀቁ ተገለጸ!
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ፣ 11ኛው ዓለም አቀፍ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ከሰኔ 4 – 5 ቀን 2014 ዓ.ም. ድረስ ይካሄዳል፡፡
በመሆኑም በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት አዘጋጅ ዐቢይ ኮሚቴው ማምሻውን ዝግጅቱን ማጠናቀቁ ገልጸዋል።
https://youtu.be/Tuw7XiJLt8U
✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg
✍️ Facebook 👇
http://facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
https://youtu.be/Tuw7XiJLt8U
✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg
✍️ Facebook 👇
http://facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ በዓመት ሁለት ጊዜያት እንዲሆን በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ቁጥር 164 በተደነገገው መሠረት ምልዓተ ጉባኤው የመክፈቻው ሥርዓተ ጸሎት ከተፈጸመበት ግንቦት 9 ቀን 2014ዓ.ም. ጀምሮ የተለመደውን ዓመታዊ መደበኛ ስብሰባ ሲያካሂድ ሰንብቶ ለቤተ ክርስቲያናችንና ለሀገራችን የሚበጁ ማህበራዊና መንፈሳዊ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡
በዚሁ መሠረት፡-
የ2014ዓ.ም. የግንቦቱ ርክበ ካህናት ጉባኤ መክፈቻ ንግግር በቤተ ክርስቲያናችንና በአገራችን የተከሰተውን የሰላም እጦት ተከትሎ የደረሰው የሰው ሕይወት ሕልፈትና የአብያተ ክርስቲያናት መቃጠል የካህናትና የምእመናንን ህልፈተ ሕይወት ላይ ያተኮረ ሲሆን በዚሁ ላይ የተነጋገረው ምልዓተ ጉባኤ በሰፊው ተነጋግሮ ችግሩ መፍትሔ እንዲያገኝ ለሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት እንዲቀርብ ተደርጓል፡፡
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት የተከናወነው የመንፈቅ ሪፖርት፣ ምልዓተ ጉባኤ ያዳመጠና የገመገመ ሲሆን በስድስት ወራት ውስጥ ተወስነው ፍጻሜ ያላገኙ ጉዳዮች አስፈላጊው ክትትል እየተደረገ ፍጻሜ እንዲያገኙ ጉባኤው መመሪያ ሰጥቷል፡፡
ሀገራዊ ሰላምን አስመልክቶ፣ በችግሩ ዙሪያ የተነጋገረው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በአሁኑ ደረጃ በአገራችን ያለው የሰላም እጦት ላይ በሰፊው ተወያይቶ በቀጣይ ጦርነትና የእርስ በርስ ግጭት ተወግዶ አጠቃላይ ሰላም በሚሰፍንበት መልኩ ተነጋግሮ ችግሩን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ መፍታት እንዲቻል፣ ቤተ ክርስቲያናችን የአስታራቂነት ሚናዋን መጫወት እንድትችል ለማድረግ ለፌዴራል መንግሥት ጥያቄ እንዲቀርብ ተደርጓል፡፡
ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በአገራችን በተከሰተው የሰላም እጦት ምክንያት በቤተ ክርስቲያናችንና በካህናት አገልጋዮቻችን እንዲሁም በምእመናኖቻችን ላይ የደረሰውና እየደረሰ ያለው የሰው ሕይወት መጥፋትና የአብያተ ክርስቲያናት መቃጠል፣ የበዓል ማክበሪያ ቦታዎች መነጠቅ አስመልክቶ ጉባኤው የተነጋገረ ሲሆን አጥፊዎች ለሕግ እንዲቀርቡ፣ በቀጣይም በመንግሥት በኩል አስፈላጊው ጥበቃ እንዲደረግልን በመጠየቅ፣ እስከአሁን በቤተ ክርስቲያናችን ላይ ደረሰ የተባለው ችግር በዓይነትና በቁጥር ተለይቶ ለሚመለከታቸው የፌዴራልና የክልል መንግሥት አካላት እንዲቀርብ ተደርጓል፡፡
በአገራችን በተከሰተው ወቅታዊ ችግር ምክንያት ችግር ለደረሰባቸው ለተፈናቀሉና ለተሰደዱ ወገኖች፣ ለፈረሱና ለተቃጠሉ አብያተ ክርስቲያናት ማቋቋሚያ፣ ለተዳከሙ የአብነት ት/ቤቶች መደጐሚያ የሚሆን የገንዘብ ድጋፍ እንዲደረግ ተወስኗል፡፡
በክልል ትግራይ የሚገኙ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ቤተ ክርስቲያኒቱን አስመልክተው በ30/04/2014 እና በ3/06/2014 ዓ.ም. ባወጡት መግለጫ ምልዓተ ጉባኤው ገምግሞ በቀጣይ የክልሉ አባቶች በማዕከል እንደ ቅዱስ ሲኖዶስ አባልነታቸው ለአገር አንድነትና ሰላም በጋራ እንዲሠሩ ምልዓተ ጉባኤው ጥሪውን አቅርቧል፡፡
ቤተ ክርስቲያናችን በዘመናት በርካታ የልማት ተግባራትን ስታከናውን የቆየች ቢሆንም ለቤተ ክርስቲያኒቱ አገልግሎት የሚሰጥ የሕክምና ማዕከል ሳታቋቁም መቅረቷ ተገቢ አለመሆኑን በመገምገም፣ በቀጣይ የሕክምና ማዕከሉ ቅድሚያ ተሰጥቶት እንዲገነባ ጉባኤው ወስኗል፡፡
በየሦስት ዓመቱ የሚደረገው የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ አስመልክቶ በተደረገው ምርጫ፡-
1. ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የሰሜን አሜሪካ ኒውዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ (ዶ/ር) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣
2. ብፁዕ አቡነ አብርሃም የባሕርዳር ከተማ ልዩ ዞን ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ አድርጐ በመምረጥ ለቀጣይ ሦስት ዓመታት እንዲሠሩ ሰይሟል፡፡
በአጠቃላይ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በጉባኤ ላይ በቆየባቸው ቀናት ባደረገው ሰፊ ውይይት፡-
ለቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ አገልግሎት መጠናከር፣
ለአገራችን፣ ለሕዝባችንና ለመላው ዓለም ሰላም መገኘት፣
ለተሰደዱና ከቄያቸው የተፈናቀሉ መረጋጋትና ወደቄያቸው መመለስ፣
በአገራችን ጦርነትና የሰላም እጦት በሚወገድበት ሁኔታ በሰፊው በመምከርና ለዘለቄታዊ ሰላም አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ በርካታ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡
በመሆኑም መላው ሕዝባችንና የመንግሥት መሪዎች ሁሉም ለአገራችን ሰላምና አንድነት ከምንጊዜወም በላይ በአንድነት በመነሳት በትኩረት እንዲሠሩ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ጥሪውን አቅርቧል፡፡
በመጨረሻም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ከግንቦት 9-25 ቀን 2014ዓ.ም. በቤተ ክርስቲያኒቱ መንፈሳዊና ማህበራዊ እንዲሁም አገራዊ ሰላምን አስመልክቶ ሲወያይ በመቆየት በዛሬው ዕለት ስብሰባውን በጸሎት ዘግቷል፡፡
እግዚአብሔር አምላክ ለአገራችንና ለቤተ ክርስቲያናችን
እንዲሁም ለመላው ሕዝባችን ሰላሙንና አንድነቱን ይስጥልን፡፡
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን፡፡
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም
ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ግንቦት 25 ቀን 2014ዓ.ም.
አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ
✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg
✍️ Facebook 👇
http://facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
ሔኖክ አካሄዱን ከእግዚአብሔር ጋር ቢያደርግ እግዚአብሔር ስለወሰደው አልተገኘም። ዘፍ 5፡24 ነብየ እግዚአብሔር ኤልያስም እግዚአብሔርን በማስደሰቱ በእሳት ሰረገላ ወደ ሰማይ አረገ። 2ኛ ነገ 2፡1 ከአሥራ ሁለቱ ሐዋርያት አንዱ ፍቁረ እግዚእ የተባለ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ሞትን እንዳያይ በአምላኩ ተነገረው። ዮሐ 21፡22 እንደዚሁ ኢትዮጵያዊው የዜማ ሊቅ ፣ የመጽሐፍት ደራሲ ፣ ካህን ፣ የነገረ ሃይማኖት ሊቅ ምሑር ቅዱስ ያሬድም በዚህች ዕለት በግንቦት 11 ወደ ብሔረ ሕያዋን የሄደበት የተሰወረበት ዕለት ነው። በረከቱ ከኛ ጋር ትሁን ለዘለዓለሙ አሜን!!
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመንበረ ፓትርያርክ ዓለም አቀፍ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት
✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg
✍️ FaceBook 👇
https://www.facebook.com/nssu.eotcss
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
በመጨረሻም ለሁሉም ኢትዮጵያውያን ልጆቻችንና ወገኖቻችን የምናስተላልፈው መልእክት ሰላምንና አንድነትን ለማረጋገጥ ጕልበትን እንደ አማራጭ መውሰድ አቁመን፣ የተከሠቱብንን ችግሮች በውይይትና በድርድር ለመፍታት ለሚደረገው ጥረት የላቀ ድጋፍ በመስጠት በጦርነትና በረኃብ፣ በድርቅና በበሽታ እያለቁ ያሉ ልጆቻችንንና ወገኖቻችንን እንድንታደግ በእግዚአብሔር ስም በመማፀን መንፈሳዊ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን ፤
እግዚአብሔር ጉባኤያችንን ይባርክ ፤
ኢትዮጵያንንና ሕዝቦችዋንም ይቀድስ!!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
አሜን ፤
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም
ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ግንቦት ፲ ቀን ፳፻፲፬ ዓመተ ምሕረት
አዲስ አበባ -ኢትዮጵያ ። ✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg
✍️ Facebook 👇
http://facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
በ፳፻፲ወ፬ ዓ.ም የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ መክፈቻ ሥነሥርዓት ላይ ብፀዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ መልዕክት አስተላለፉ።የመልዕክቱ ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ይነበባል፦
መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ ፦
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ፤
• ብፁዕ አቡነ ያሬድ
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የምሥራቅ ጎጃምና የአርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እንዲሁም የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ የበላይ ኃላፊ፤
• ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ
የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የሲዳማ፣ የጌድኦ፣ የአማሮና ጉርጂ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤
• ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት፣
• በአጠቃላይ በዚህ ታላቅ ቅዱስ ጉባኤ የተገኛችሁ በሙሉ፦
በዓለም ውስጥ የሰላምና የአንድነት ማእከል ሆና ታገለግል ዘንድ ቤተክርስቲያንን በክቡር ደሙ ቀድሶ የሰጠን ጌታችን፣ አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን ለሁለት ሺሕ ዐሥራ ዐራት ዓ.ም የረክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ስብሰባ አደረሳችሁ !!
“ወሩፁ ኀበ ሰላም ምስለ ኵሉ ፤ከሁሉ ጋር ወደ ሰላም ሩጡ” (ዕብ.፲፪፥፲፬)፤
ሁላችንም እንደ ምንገነዘበው የቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዚህ ዓለም መመሥረት ዋና ዓላማ ሕዝብንና አሕዛብን በክርስቶስ ትምህርተ ሰላም፣ አገናኝታ፣ አቀራርባና አንድ አድርጋ በሃይማኖት ለእግዚአብሔር መንግሥት ንጹህ ወገንን ማቅረብ ነው፡፡ ለዚህ ለተቀደሰ መለኮታዊ ዓላማ እውን መሆን ሲባል ከራሱ ከባለ ቤቱ ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ አንሥቶ ብዙ ቅዱሳን አበው የደም ዋጋ ከፍለዋል፡፡
ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዚህ ክቡር ደም አማካኝነት ድል በድል እየተሻገረችና እየተራመደች እስካሁን ደርሳለች ዛሬ በክብር የተቀመጥንበት ወንበርም የዚህ ደም ውጤት እንደ ሆነ አሳምረን እናውቃለን፡፡
በየጊዜው በኃላፊነት የተቀመጡ ቅዱሳን አበው መከራ መስቀሉን ፈርተውና ተሰቅቀው ቢያፈገፍጉ ኖሮ ይህ እኛ ዛሬ የተሰየምንበት ክብረ መንግሥተ እግዚአብሔር የሚገኝ አልነበረም፡፡ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ጉዞ አንድ ተብሎ ሲጀመር በፍኖተ መስቀል ስለ ሆነ ፍኖተ መስቀሉ ተቋርጦ አያውቅም፤ ለወደፊትም ይቋረጣል ተብሎ አይጠበቅም፡፡
በዚህ ፍኖት የሚጓዙ ቅዱሳንም አይታጡም ብቻ ሳይሆን እጅግ በጣም ብዙ ናቸው፤ ፍኖተ መስቀል በልዩ ልዩ ዕንቅፋቶችና መሰናክሎች የተሞላ፣ አባጣ ጐርባጣ፣ ወጣ ገባ ቢሆንም መጨረሻው ስኬትና ድል ነውና ለፍጹም ዘለዓለማዊ ሰላምና አንድነት ሲባል የሚጓዙበት መንገድ ነው፡፡
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት፣
የዘመናችን ፍኖተ መስቀልም መሰናክሉንና ዕንቅፋቱን በሀገራችን፣ በቤተ ክርስቲያናችንና በምእመናን ልጆቻችን ጫናው እያበረታ እንደ ሆነ መጠራጠር ያለብን አይመስለንም፡፡
የምእመናን፣ የካህናትና የአብያተ ክርስቲያናት ጉዳት አሁንም ገዝፎና ሰፍቶ እየቀጠለ ነው፡፡ ስጋትና ጭንቀት፣ አለመተማመንና ቀቢፀ ተስፋ ተንሰራፍቶአል፤ አብሮ ተከባብሮ፣ ከመኖር ይልቅ ሌላውን ጥሎ ኮርቻ ላይ ለመውጣት የሚደረገው እሽቅድምድም በሰፊው እየተሠራበት እንደሆነ እየታዘብን ነው፡፡
ይህንን አደገኛ አካሄድ ለማሳካት ሲባል የሚደረገው ያልነበረ ልማድም ቤተ ክርስቲያናችንን እየተጋፋ ነው፤ ምእመናንንም እያሳዘነ ነው፤
ቤተ ክርስቲያናችን በሃይማኖት ነጻነት መከበር ችግር ባይኖርባትም በአጉል ፉክክር የሚደረጉ፣ ካሁን በፊት ያልነበሩ የሥርዓተ ሃይማኖታችን አደባባዮችን ለመቀራመት የሚደረገው አካሄድ ተገቢ ነው አንልም፡፡
ይህ ሁኔታ ለሁሉም በሚበጅና ሁሉም በየራሱ የሚስተናገድበት የየራሱ የሆነ ክቡር ስፍራ አግኝቶ ሊስተናገድ የሚችልበት ሁኔታ ካልተፈጠረ ጥሩ ሊሆን አይችልም፤ ችግሩም በግልፅ እየታየ ስለ ሆነ የሚመለከተው አካል ፈጣን መፍትሔ ሊያበጅበት ይገባል፡፡
ከታሪክ፣ ከነባር ባህል ጥበቃ፣ ከሃይማኖት ክብርና መብት ባሻገር በአንድ ስፍራ ሁለት የተለያዩ ሃይማኖታውያን እንዲገለገሉ የሚደረግ ከሆነ ሁለት የተለያየ እምነት ያላቸው ሃይማኖታውያን በዓላቸው በአንድ ቀን ቢውል ምን ሊፈጠር እንደሚችል መገመት አያስቸግርም፡፡
ሃይማኖታውያንም ለራሳቸው ሲሉ ይህንን ችግር ራሳቸው የመፍትሔ አካል መሆን የኖርባቸዋል፤ የሰላም ጠበቆች መሆናቸውንም በዚህ ሊያሳዩ ይገባል፡፡
ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት !!
የሰላም አስፈላጊነት በየቀኑ ብቻ ሳይሆን በእያንዳንዷ ሰከንድ ለሃይማኖታችን መጠበቅና ለሕዝባችን ደኅንነት መረጋገጥ ትልቅ ዋጋ አላት፡፡
ሰላም በደፈረሰ ቍጥር የምናጣው ብዙ ነው፤ እንደ እውነቱ ከሆነ ሰው ሁሉ ከማንም ተግባር በፊት ሰላምን መጠበቅ ላይ ቢሠራና ሰላምን ገንዘብ አድርጎ ቢመላለስ በሁሉም ነገር ስኬታማ መሆን ይችላል፡፡
በተለይም ሕዝብን በኃላፊነት በመምራት የምንገኘው ዓለማውያንም ሆን ሃይማኖታውያን ከማናቸውም ተግባር በፊት ሰላምን ማረጋገጥ ላይ መሥራት ይጠበቅብናል፤ ምክንያቱም ሃይማኖታዊም ሆነ ሀገራዊ ጥቅም ያለ ሰላም በምንም ተአምር ሊመጣ አይችልምና ነው፡፡
ሰላም ከሞላ ጐደል ፍጥረት ሁሉ የሚፈልጋት ውድ ነገር ብትሆንም መገኛዋን በተመለከተ ግን ብዙ አናውቀውም፡፡ እንደ እውነቱ ከሆነ ግን ሰላም በጕልበት አትገኝም፤ በሀብትም አትገኝም፤ በሥልጣንም ሆነ በነጠላ ዕውቀትም አትገኝም፡፡
እውነተኛዋና ዘላቂነት ያላት ሰላም የምትገኘው “ክፉውን በመልካም አሸንፍ እንጂ በክፉ አትሸነፍ” በሚለው ትምህርተ እግዚአብሔር ብቻ ነው፤ ሰው ሌላውን ቸል ብሎ ራሱን ሲያስቀድም የሰላም ፀር ይሆናል፤ ራሱን ሳይሆን ሌላውን ሲያስቀድም ግን የሰላም ጠበቃ ይሆናል፡፡
በሀገራችን ተከሥቶ ሕዝባችንን እያንገላታ የሚታየው ክሥተት ይህ ራስን ማብለጥ ሌላውን ማንጓጠጥ ነው፤ ይህንን በአግባቡ አርመን አንተ ትበልጣለህ አንተ ትሻላለህ ወደ ሚል ፍና ትሕትና ካልተመለስንና ነገሮችን በፍቅር ለመለወጥ ካልጣርን የሕዝባችንን መከራ ማሳጠር አንችልም፡፡
“ዕርቅ ደም ያደርቅ” እንዲሉ የዕርቅን ጥቅም በመቀበል ወደ ተሻለ ነገር መራመድ ጊዜው የሚጠይቀን ተግባር ነው፡፡
ይህንን በማስተማርና በመምከር ሕዝቡን ወደ ዕርቅና ወደ ይቅርታ ማምጣት ደግሞ የኛው የሃይማኖት አባቶች ተቀዳሚ ተግባር ሊሆን ይገባል፤ ምክንያቱም “ወደ ሰላም ሩጡ” ተብለናልና!
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!!
በአሁኑ ጊዜ ከምንም ጊዜ በላይ ቤተ ክርስቲያናችን በፈተና ላይ የምትገኝበት ወቅት መሆኑን መዘንጋት የለብንም፤ ደማቸው በየአቅጣጫው እንደ ጐርፍ እየፈሰሰ ያለው የልጆቻችን ብሎም የወገኖቻችን ደም ነው፡፡
በጦርነትና በድርቅ፣ እንደዚሁም በተለያዩ ግጭቶች በረኃብ እየረገፉ ያሉት እኛ አጥምቀን የሥላሴ ልጅነትን አሰጥተን በልጅነት ያከበርናቸው፣ እግዚአብሔር ጥብቅ በሆነ አደራ ያስረከበን የመንፈስ ልጆቻችን ናቸው፡፡
የእነሱ ልሳን ሆነን ዛሬ ከጎናቸው ካልቆምን ነገ የኛ አባትነት ጥያቄ ውስጥ የሚከት ነገር ሊመጣ ይችላል፡፡
ስለ ሆነም ይህ ቅዱስ ጉባኤ፣ ራሱን ከማናቸውም አደረጃጀት ነጻ አድርጎ የሰላም ጥሪን በማሰማት ለሁሉም ኢትዮጵያውያን ሰላም መረጋገጥ ለሰላም በሰላም መሥራት መጣርና ውጤት ማምጣት ይጠበቅበታል፡፡
በዚህ ዙርያ ይህ ዓቢይ ጉባኤ በስፋት ተወያይቶ አቅጣጫ እንደሚያስቀምጥም ይጠበቃል፤
🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔
ግንቦት 5/2014 ዓ.ም ቀድሞ በተያዘ መርሐግብር ብጹአን አባቶቻችን ለማነጋገር ቤተክህነት ተገኝተው የነበሩት እና በዕለቱ ያለአግባብ ለእስር ከተዳረጉት መካከል የነበሩት
#ቃለአብ_ታመነ እና #ዓለምነህ_ዳኘው ከኮልፈ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት በ200 ብር ዋስ እንዲወጡ ቢወሰንም ይግባኝ ተጠይቆባቸው ልደታ ፍርድ ቤት ውሳኔ በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ ብለን መዘገባችን ይታወቃል።
በዛሬው ዕለት በልደታ ፍርድ ቤት ቀርበው ጉዳያቸው ታይቶ ፍርድ ቤቱም ጉዳዩ ለእስር የሚዳርግ አይደለም ብሎ በመወሰኑ ቀድሞ በእስር ፍርድ ላይ #በ200 ብር ዋስ እንዲወጡ የተወሰነውን ፍርድ ቤቱም በማጽናት ወንድሞቻችን #ከእስር_ተፈተዋል።
ይህንኑ ጉዳይ ከተፈጠረበት ዕለት ጀምሮ ምዕመናን ፥ መላው ሰንበት ት/ቤቶች በማሕበራዊ ገጻችሁ በማጋራት ፤ በእስር ቤት በመሄድ በመጠየቅ እና የሚያስፈልገውን በማሟላት ለወንድሞቻችሁ ያላችሁን ድጋፍ እና አጋርነት ላሳያችሁ በሙሉ አንድነቱ ምስጋናውን ያቀርባል።
#የአዲስ_አበባ_ሰንበት_ትምህርት_ቤቶች_አንድነት
🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔
መንግስት አባቶችን በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ለማናገር የመጡትን የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች በአድማ በታኝ ፖሊሶች መበተኑና አባላቱን ማሰሩ የመንግስት መዋቅራዊ አድሎ ለመኖሩ ማረጋገጫ ነው።
በኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን ሰ/ት/ቤቶች ማ/መ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት በማስተባበር በአዲስ አበባ የሚገኙ ሰ/ት/ቤቶች አባላት ከቋሚ ሲኖዶስ አባቶቻችን ጋር በቤተ ክርስቲያናችን ላይ ባሉ አጠቃላይ ጉዳዮች እና ችግሮች እና በወቅታዊ ቤተክርስቲያን ላይ እየደረሰ ስላሉ በደሎች ላይ ውይይት በማድረግ በጋራ ለመሥራት ሁሉም የቤተ ክርስቲያን አካል የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ለዛሬ 5/9/2014 ዓ.ም በተያዘ ቀጠሮ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ተገኝተዋል።
ይሁን እንጂ ከጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ አቡነ ያሬድ እና ከመምሪያው ኃላፊ መ/ብ አባ ተክለያሬድ ከአንድነቱ አመራር ጋር አቅጣጫ በመስጠት በአግባቡ ተጠይቆ የተዘጋጀ ስብሰባ ሙሆኑን ለጸጥታ አካላት የተነገረ ቢሆንም ከየአጥቢያው የመጡ የሰ/ት/ቤት አባላት እንዳይገቡ ያለ አግባብ መንገዱን በመዝጋትና ኃይል ጭምር በመጠቀም ክልከላ አድርገዋል።
በዚህም የቋሚ ሲኖዶስ አባላት አባቶቻችን ልጆቻቸውን ለማወያየት ሲፈልጉ የጸጥታ አካላት ማለትም (የአዲስ አበባ ፓሊስ፣ አድማ በታኝ፣ ፌደራል ፓሊስ) አካባቢውን በመክበብ ክልከላ አድርገዋል።
ስለዚህ ከሕግ አስከባሪ አካል የማይጠበቅ ተግባር በመፈጸም ከአባቶቻችን ጋር ምክክር ለማድረግ የመጡ የሰ/ት/ቤት ወጣቶችን አሳዝኖ መመለሱ የማይጠበቅ አሳፋሪ ተግባር ፈጽሟል ይህ ክስተት አሁን አሁን ቤተክርስትያንን በተናጥል ምንም አይነት ሕገ መንግስታዊ መብት የሆነውን ሀሳብን በሰላማዊ መንገድ የመግለጽ መብቷን አባቶችን በማሸመቀቅ ፣ወጣቶችን በፖሊስ በመበተን፣ የአምልኮ አደባባያችንን እና የቤተክርስትያንን ይዞታ በጉልበት በመንጠቅ፣ በወይ ብላ ማርያም ታቦታት ወደማደሪያ እንዳይገቡ በመከልከልና የሰንበት ትምህርት ቤት አባላትን በጥይት በጥምቀት በአል ላይ በመግደል፣ በስልጤ ያሉ ምእመናን የታመሙትን የመጠየቅ፣ የተቃጠሉ አብያተ ክርስትያናትን ለመጎብኘት ሀገረ ስብከቱን በመከልከል፣ የእንቁ ልደታን ለመስቀሉ እሮጣለሁ ሰላማዊ እቅስቃሴ በመከልከል ከዛም አልፎ ዛሬ ቤተክርስትያን በራሷ ቅጥር ግቢ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላትን ለማነጋገር የመጡ ሰላማዊ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶችን በመከልከል እና አባላቱን በማሰር የአድሏዊነቱን ጥጉን አሳይቶናል። በመሆኑን ሰ/ት/ቤቶች እና ሁሉም ህዝበ ክርስቲያን ዝርዝር ሁኔታውን እና ቀጣይ ሥራዎችን በመዋቅራችን የምናሳውቅ መሆኑን እንገልጻለን። በመንግስት በተፈጸመው ህገወጥ ድርጊት ማዘናችንን እንገልጻለን
"እለት እለት የሚያሳስበኝ የአቢያተ ክርስቲያናት ጉዳይ ነው:: " ፪ኛ ቆሮ ፲፩:፳፰
ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት
✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg
✍️ FaceBook 👇
http://facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇
https://eotc-gssu.org/a/
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
