ch
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

前往频道在 Telegram

📈 Telegram 频道 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU 的分析概览

频道 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 14 484 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 6 043,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 334

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 14 484 名订阅者。

根据 30 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 530,过去 24 小时变化为 23,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 39.14%。内容发布后 24 小时内通常能获得 10.20% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 666 次浏览,首日通常累积 1 477 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 33

📝 描述与内容策略

尚未提供频道描述。

凭借高频更新(最新数据采集于 01 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。

14 484
订阅者
+2324 小时
+1447
+53030
帖子存档
መንግስት አባቶችን በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ለማናገር የመጡትን የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች በአድማ በታኝ ፖሊሶች መበተኑና አባላቱን ማሰሩ የመንግስት መዋቅራዊ አድሎ ለመኖሩ ማረጋገጫ ነው። በኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን ሰ/ት/ቤቶች ማ/መ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት በማስተባበር በአዲስ አበባ የሚገኙ ሰ/ት/ቤቶች አባላት ከቋሚ ሲኖዶስ አባቶቻችን ጋር በቤተ ክርስቲያናችን ላይ ባሉ አጠቃላይ ጉዳዮች እና ችግሮች እና በወቅታዊ ቤተክርስቲያን ላይ እየደረሰ ስላሉ በደሎች ላይ ውይይት በማድረግ በጋራ ለመሥራት ሁሉም የቤተ ክርስቲያን አካል የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ለዛሬ 5/9/2014 ዓ.ም በተያዘ ቀጠሮ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ተገኝተዋል። ይሁን እንጂ ከጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ አቡነ ያሬድ እና ከመምሪያው ኃላፊ መ/ብ አባ ተክለያሬድ ከአንድነቱ አመራር ጋር አቅጣጫ በመስጠት በአግባቡ ተጠይቆ የተዘጋጀ ስብሰባ ሙሆኑን ለጸጥታ አካላት የተነገረ ቢሆንም ከየአጥቢያው የመጡ የሰ/ት/ቤት አባላት እንዳይገቡ ያለ አግባብ መንገዱን በመዝጋትና ኃይል ጭምር በመጠቀም ክልከላ አድርገዋል። በዚህም የቋሚ ሲኖዶስ አባላት አባቶቻችን ልጆቻቸውን ለማወያየት ሲፈልጉ የጸጥታ አካላት ማለትም (የአዲስ አበባ ፓሊስ፣ አድማ በታኝ፣ ፌደራል ፓሊስ) አካባቢውን በመክበብ ክልከላ አድርገዋል። ስለዚህ ከሕግ አስከባሪ አካል የማይጠበቅ ተግባር በመፈጸም ከአባቶቻችን ጋር ምክክር ለማድረግ የመጡ የሰ/ት/ቤት ወጣቶችን አሳዝኖ መመለሱ የማይጠበቅ አሳፋሪ ተግባር ፈጽሟል ይህ ክስተት አሁን አሁን ቤተክርስትያንን በተናጥል ምንም አይነት ሕገ መንግስታዊ መብት የሆነውን ሀሳብን በሰላማዊ መንገድ የመግለጽ መብቷን አባቶችን በማሸመቀቅ ፣ወጣቶችን በፖሊስ በመበተን፣ የአምልኮ አደባባያችንን እና የቤተክርስትያንን ይዞታ በጉልበት በመንጠቅ፣ በወይ ብላ ማርያም ታቦታት ወደማደሪያ እንዳይገቡ በመከልከልና የሰንበት ትምህርት ቤት አባላትን በጥይት በጥምቀት በአል ላይ በመግደል፣ በስልጤ ያሉ ምእመናን የታመሙትን የመጠየቅ፣ የተቃጠሉ አብያተ ክርስትያናትን ለመጎብኘት ሀገረ ስብከቱን በመከልከል፣ የእንቁ ልደታን ለመስቀሉ እሮጣለሁ ሰላማዊ እቅስቃሴ በመከልከል ከዛም አልፎ ዛሬ ቤተክርስትያን በራሷ ቅጥር ግቢ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላትን ለማነጋገር የመጡ ሰላማዊ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶችን በመከልከል እና አባላቱን በማሰር የአድሏዊነቱን ጥጉን አሳይቶናል። በመሆኑን ሰ/ት/ቤቶች እና ሁሉም ህዝበ ክርስቲያን ዝርዝር ሁኔታውን እና ቀጣይ ሥራዎችን በመዋቅራችን የምናሳውቅ መሆኑን እንገልጻለን። በመንግስት በተፈጸመው ህገወጥ ድርጊት ማዘናችንን እንገልጻለን "እለት እለት የሚያሳስበኝ የአቢያተ ክርስቲያናት ጉዳይ ነው:: " ፪ኛ ቆሮ ፲፩:፳፰ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg ✍️ FaceBook 👇 http://facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/

እንኳን ለእናታችን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!! "ዮም ፍስሐ ኮነ በእንተ ልደታ ለማርያም ፤ በማርያም መወለድ ደስታ ሆነ!" በሉቃ 1፡ ላይ መልአኩ ቅዱ
እንኳን ለእናታችን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!! "ዮም ፍስሐ ኮነ በእንተ ልደታ ለማርያም ፤ በማርያም መወለድ ደስታ ሆነ!" በሉቃ 1፡ ላይ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ለካህኑ ዘካርያስ የዮሐንስን ልደት አስመልክቶ ሲያበስረው እንዲህ ብሎት ነበር። "በመወለዱ ብዙዎች ደስ ይላቸዋል።" በዮሐንስ መወለድ ብዙዎች ከተደሰቱ ቅድስተ ቅዱሳን ንጽሕተ ንጹሐን የዮሐንስ እመቤት መጥምቀ መለኮት እንዲባል ምክንያት የሆነች የወይን ሐረግ ድንግል ወይን የወይን ፍሬ ክርስቶስን ያስገኘት የድኅነታችን መሠረት በመወለዷ ምን ያህል ሰዎች ደስ ይላቸው ይሆን?????? የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ረድኤት በረከት አማላጅነት ከሁላችን ጋር ይሁን! መልካም በዓል። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመንበረ ፓትርያርክ ዓለም አቀፍ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg ✍️ FaceBook 👇 http://facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/

🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔🔔 #የስብሰባ_ጥሪ_በአዲስ_አበባ_ሀገረ_ስብከት_የሰንበት_ትምህርት_ቤቶች_አንድነት_ሥር_ለምትገኙ_የየሰንበት_ትምህርት_ቤቱ_የሥራ_አመራር_አባላቶች_በሙሉ የፊታችን ቅዳሜ #ሚያዝያ_29_2014_ዓ_ም #ከቀኑ_900_ሰዓት የአዲስ አበባ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት እና የዓለም አቀፍ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት #በአዲስ_አበባ_ሀገረ_ስብከት_የሰንበት_ትምህርት_ቤቶች_አንድነት_ሥር_ከሚገኙ_የየሰንበት_ትምህርት_ቤቱ_የሥራ_አመራር_አባላቶች_ጋር_በሙሉ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ለማወያየት ቀጠሮ ስለተያዘ በተጠቀሰው ዕለት እና ሰዓት #በጠቅላይ_ቤተ_ክህነት_አዳራሽ (5 ኪሎ) እንድትገኙልን እያልን ጥሪያችንን በልዑል እግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን። #የአዲስ_አበባ_ሰንበት_ትምህርት_ቤቶች_አንድነት፣ ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg ✍️ FaceBook 👇 http://facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/

አክራሪዎችና ጽንፈኛ ኃይሎች በወራቤ ቅዱስ ሩፋኤል ቤተክርስቲያን ላይ ምዝበራና ውድመት ፈጸሙ። በመ/ር አቤል አሰፋ ( ኢኦተቤ ቴቪ ሚያዝያ ፳ ቀን ፳፻፲፬ ዓ.ም ) አክራሪዎች የወራቤ ቅዱስ ሩፋኤል ቤተክርስቲያን ላይ ምዝበራና ውድመት ፈጸሙ። አክራሪዎቹ የደብሩን በርና መስኮት በመሰባበር ጉልላቱን በማውረድ መንበሩን እንደገለበጡ ሀገረ ስብከቱ ለኢኦተቤ ቴቪ ገልጿል። የሐዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ሕይወት ቀሲስ ንጉሤ ባወቀ ለኢኦተቤ ቴቪ በስልክ እንደገለጹት አክራሪና ጽንፈኛ ቡድኖቹ የደብሩን የጀነሬተር ቤትና የጥበቃ ቤት ማቃጠላቸውን ገልጸዋል። በሰው ሕይወት ላይ የደረሰ አደጋ ይኑር አይኑር በመጣራት ላይ መሆኑንም ገልጸዋል። ዕለቱ በዓለ ሀምሣ በመሆኑ ምእመናን በየቤታቸው በነበሩበት ሰዓት ድርጊቱ መፈጸሙን የጠቀሱት የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ በስልጤ ዞን ሳንኩራ ቅ/ ገብርኤል ቤተክርስቲያን የማፍረስ እንቅስቃሴ እንዳለ ሀገረ ስብከቱ መረጃው እንደደረሰው ይህንንም ለጸጥታ ኃይል ማሳወቃቸውን ነተናግረዋል። ክስተቱ ከመደበኛው የጸጥታ ኃይል በላይ በመሆኑ በአሁኑ ሰዓት የክልሉ ልዩ ኃይል በስፍራው ደርሶ የማረጋጋት ሥራ እያከናወነ እንደሚገኝ የገለጹት ዋና ሥራ አስኪያጁ ሀገረ ስብከቱም ከጸጥታ መዋቅሩ ጋር በመነጋገር የማረጋጋት ሥራ እያከናወነ ነው ብለዋል ; ከርዕሰ ከተማው ወራቤ ውጪ በሳንኩራ ;ቂልጡ; ቅበት; ሌራ; ዳሎቻ ;ቄራ በተባሉ አካባቢዎች የመንግሥት የጸጥታ ኃይል ምእመናንንና አብያተክርስቲያናትን እንዲጠብቅ ጥሪ አቅርበዋል። በከተማው የወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ላይም ቃጠሎ መፈጸሙን የሐዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ሕይወት ቀሲስ ንጉሤ ለኢኦተቤ ቴቪ ገልጸዋል። በቅርቡ በጎንደር ከተማ የተከሰተውን ችግር ተከትሎ ችግሩን ለማስፋትና አጋጣሚውን ለሌላ ሁከት መጠቀም በእምነት ተቋማት ላይና በንፁሀን ላይ የሚፈጸመው ሕገ ወጥ ድርጊት በአስቸኳይ ይቆም ዘንድ ሁሉም የሚመለከተው አካል ኃላፊነቱን በአግባቡ ሊወጣ ይገባል። EOTC TV +++++++++++++++++++++++++++++++++ የወቅታዊ መረጃ ከትክክለኛው ከቅድስት ቤተክርስቲያን ልሳን ለማግኘት ተከታዮን የዩቲዩብ የፌስ ቡክ ቴሌግራም እና ኢንስታግራም ሊንኮች በመጫን ሰብስክራይብ እና ላይክ ያድርጉ፡፡ ሌሎችም ሰብስክራይብ እንዲያደርጉ በማድረግ መንፈሳዊ ኃላፊነትዎን ይወጡ፡፡ የዩቲዮብ ገጻችን http://www.youtube.com/c/eotctv የፌስ ቡክ ገጻችንን https://www.facebook.com/eotctvchannel ይከታተሉ።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ በመንበረ ፓትርያርክ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቀለሜንጦስ የትንሳኤን በዓል ምክንያት በማድረግ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ። ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን ሙሉውን ይመልከቱ። https://eotc-gssu.org/a/የብፁዕ-አቡነ-ቀሌምንጦስ-የእንኳን-አደረ/

"ወተንሥአ እግዚአብሔር ከመ ዘንቃህ እምንዋም። ኃያል ወኅዳገ ወይን ወቀተለ ፀሮ በድኀሬሁ ፡ እግዚአብሔር ከእንቅልፍ እንደሚነቃ ተነሳ። የወይን ስካር እንደተወው እንደ ኃያልም ሰው ጠላቶቹንም በኋላቸ
"ወተንሥአ እግዚአብሔር ከመ ዘንቃህ እምንዋም። ኃያል ወኅዳገ ወይን ወቀተለ ፀሮ በድኀሬሁ ፡ እግዚአብሔር ከእንቅልፍ እንደሚነቃ ተነሳ። የወይን ስካር እንደተወው እንደ ኃያልም ሰው ጠላቶቹንም በኋላቸው መታ። " መዝ 77(78)፡65 አቤቱ የፍቅርና ቸርነት አምላክ በትንሳኤው ለእኛ ለልጆችህ ብርሃን እንደሰጠህን ለሀገራችን እና ለሰው ልጆች በሙሉ ሰላም እና አንድነትን አውርድልን። በዓሉን ስናከብር ላዘኑ መጽናናትን፣ ለታመሙ ምህረትን ለተቸገሩ በረከትን፣ ሰላም ላጡ ሰላምን ያድልልን። በሁሉም ቦታ የምትገኙ ሰ/ት/ቤቶች ለተቸገሩት ለመድረስ ከበዓሉ ቀድሞ ሲደረግ የነበረው የበረከት ዝግጅት እጅግ ደስ ያሰኛል እንዲሁም ከበዓሉ በኋላም ለተቸገሩት ለመድረስ የበለጠ እንበርታ ከግፉዓን ጎን እንቁም መልእክታችን ነው። "አሁን ግን ክርስቶስ ላንቀላፉት በኵራት ኾኖ ከሙታን ተነሥቶአል። ሞት በሰው በኩል ስለ መጣ ትንሣኤ ሙታን በሰው በኩል ሆኖአልና።" 1ኛ ቆሮ 15÷20 መልካም በዓል ይሁንላችሁ። ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg ✍️ FaceBook 👇 http://facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/

"ኢየሱስንም ይዘው ወሰዱት፤ መስቀሉንም ተሸክሞ በዕብራይስጥ ጎልጎታ ወደ ተባለው የራስ ቅል ስፍራ ወደሚሉት ወጣ። በዚያም ሰቀሉት!" ዮሐ 19፡17 እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ዓለምን ለተቤዠበት
"ኢየሱስንም ይዘው ወሰዱት፤ መስቀሉንም ተሸክሞ በዕብራይስጥ ጎልጎታ ወደ ተባለው የራስ ቅል ስፍራ ወደሚሉት ወጣ። በዚያም ሰቀሉት!" ዮሐ 19፡17 እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ዓለምን ለተቤዠበት በዓለ ስቅለት በሰላም አደረሳችሁ። መልካም በዓል!! ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg ✍️ FaceBook 👇 http://facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/

"ሆሳዕና ለዳዊት ልጅ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው፤ ሆሳዕና በአርያም" ማቴ 21፡9 እንኳን ለበዓለ ሆሳዕና አደረሳችሁ!! በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች
"ሆሳዕና ለዳዊት ልጅ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው፤ ሆሳዕና በአርያም" ማቴ 21፡9 እንኳን ለበዓለ ሆሳዕና አደረሳችሁ!! በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የመንበረ ፓትርያርክ (ዓለም አቀፍ) የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት መልካም በዓል!!!! ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg ✍️ Facebook 👇 https://www.facebook.com/nssu.eotcss ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/

#ኒቆዲሞስ_የሌሊቱ_ተማሪ ቅዱስ ያሬድ የዐቢይ ጾም ሰባተኛውን ሳምንት የአይሁድ አለቃ እና ምሁረ ኦሪት በሆነው በኒቆዲሞስ ስም ሰይሞታል። ኒቆዲሞስ ከጌታችን እግር ሥር ቁጭ ብሎ ሌሊቱን በመማር ያሳል
#ኒቆዲሞስ_የሌሊቱ_ተማሪ ቅዱስ ያሬድ የዐቢይ ጾም ሰባተኛውን ሳምንት የአይሁድ አለቃ እና ምሁረ ኦሪት በሆነው በኒቆዲሞስ ስም ሰይሞታል። ኒቆዲሞስ ከጌታችን እግር ሥር ቁጭ ብሎ ሌሊቱን በመማር ያሳልፍ የነበረ ትግሃ ሌሊትን ለመላው ክርስቲያኖች የሚያስተምር ሰው ነው። ኒቆዲሞስ ሌሊትን ለመማር የመረጠበት ምክንያቶች የሚከተሉት ናቸው። 1ኛ. መምህረ አይሁድ ምሁረ ኦሪት ነበርና ቀን ሲማር ቢያዩት ሳይማር ያስተምረናል ብለው ትምህርቱን ከመቀበል እንዳይዘገዩ ምክንያትን ያሳጣቸው ዘንድ ሌሊት ጌታ ጋር እየመጣ ይማር ነበር። 2ኛ. አይሁድ ከክርስቶስ ጋር ቢያዩት እርሱንም ይቃወሙት ነበርና እነርሱን በመፍራት ሌሊት ይመጣ ነበር። 3ኛ የሌሊት አእምሮ ክት ነው። ቀን በብዙ ሥራ በብዙ ውጣ ውረድ ሲባክን የነበረ አእምሮ ሌሊት ላይ ይሰበሰባልና በትኩረት ትምህርቱን ይቀስም ዘንድ የሌሊቱን ጊዜ መርጧል። 4ኛ ሌሊት የኦሪት ምሳሌ ናት። ብርሃን ወደ ሆነው ክርስቶስ በሌሊትይ መምጣቱ ብርሃን የሆነች ወንጌልን ምትሰጥ አንተ ነህ ሲል በሌሊት እየመጣ ይማር ነበር። ከሌሊቱ ተማሪ ከኒቆዲሞስ ትህትናን ፣ ራስን ዝቅ ማድረግ ፣ በሌሊት መትጋትን ፣ እስከመጨረሻው መጽናትን እንማራለን። ይቆየን! ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/nssu.eotcss ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/

ታማኝ አገልጋይ ማን ው? ከዐቢይ ጾም ሳምንታት መካከል ይህ የያዝነው ስድስተኛው ሳምንት ገብር ኄር ተብሎ ይጠራል ስያሜውን የሰጠው ኢትዮጵያዊ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ነው ። ሊቁ ማኅሌታይ ጾመ ድጓ በተባለ ድርሳኑ ሳምንቱን ገብር ኄር ማለቱ ምዕመናን እንዴት ታማኝ አገልይ ይሆኑ ዘንደ ለማዘከር ነው ። ታሪኩ ጌታችን በወንጌል እንዳስተማረው በማቴዎስ ወንጌል ከምዕራፍ 25÷14 - 31 እንዲህ በምሳሌ ተመዝግቦ ይገኛል ወደ ሌላ ሀገር የሚሄድ ሰው ባሮቹን ጠርቶ ያለውን ገንዘብ እንደ ሰጣቸው እንዲሁ ይሆናልና፤ ለእያንዳንዱ እንደ ዓቅሙ፥ ለአንዱ አምስት መክሊት ለአንዱ ሁለት ለአንዱም አንድ ሰጠና ወደ ሌላ አገር ወዲያው ሄደ። አምስት መክሊትም የተቀበለው ሄዶ ነገደበት ሌላም አምስት አተረፈ፤ እንዲሁም ሁለት የተቀበለው ሌላ ሁለት አተረፈ። አንድ የተቀበለው ግን ሄዶ ምድርን ቈፈረና የጌታውን ገንዘብ ቀበረ። ከብዙ ዘመንም በኋላ የእነዚያ ባሮች ጌታ መጣና ተቆጣጠራቸው። አምስት መክሊት የተቀበለውም ቀረበና ሌላ አምስት መክሊት አስረክቦ፦ ጌታ ሆይ፥ አምስት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እነሆ፥ ሌላ አምስት መክሊት አተረፍሁበት አለ። ጌታውም፦ መልካም፥ አንተ በጎ ታማኝም ባሪያ፤ በጥቂቱ ታምነሃል፥ በብዙ እሾምሃለሁ፤ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አለው። ሁለት መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ፦ ጌታ ሆይ፥ ሁለት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እነሆ፥ ሌላ ሁለት መክሊት አተረፍሁበት አለ። ጌታውም፦ መልካም፥ አንተ በጎ፥ ታማኝም ባሪያ፤ በጥቂቱ ታምነሃል፥ በብዙ እሾምሃለሁ፥ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አለው። አንድ_መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ፦ ጌታ ሆይ፥ ካልዘራህባት የምታጭድ ካልበተንህባትም የምትሰበስብ ጨካኝ ሰው መሆንህን አውቃለሁ፤ ፈራሁም ሄጄም መክሊትህን በምድር ቀበርሁት፤ እነሆ፥ መክሊትህ አለህ አለ። ጌታውም መልሶ እንዲህ አለው፦ አንተ ክፉና ሃኬተኛ ባሪያ፥ ካልዘራሁባት እንዳጭድ ካልበተንሁባትም እንድሰበስብ ታውቃለህን? ስለዚህ ገንዘቤን ለለዋጮች አደራ ልትሰጠው በተገባህ ነበር፥ እኔም መጥቼ ያለኝን ከትርፉ ጋር እወስደው ነበር። ስለዚህ መክሊቱን ውሰዱበት አሥር መክሊትም ላለው ስጡት፤ ላለው ሁሉ ይሰጠዋልና ይበዛለትማል፤ ከሌለው ግን ያው ያለው እንኳ ይወሰድበታል። የማይጠቅመውንም ባሪያ በውጭ ወዳለው ጨለማ አውጡት፤ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል። መክሊት የተበላ ልዮ ልዮ የጸጋ ስጦታ ነው " የጸጋም ስጦታ ልዩ ልዩ ነው መንፈስ ግን አንድ ነው፤ " አገልግሎትም ልዩ ልዩ ነው ጌታም አንድ ነው፤ አሠራርም ልዩ ልዩ ነው፥ ሁሉን በሁሉ የሚያደርግ እግዚአብሔር ግን አንድ ነው ። ለአንዱ ጥበብን መናገር በመንፈስ ይሰጠዋልና፥ ለአንዱም በዚያው መንፈስ እውቀትን መናገር ይሰጠዋል፥ ለአንዱም በዚያው መንፈስ እምነት፥ ለአንዱም በአንዱ መንፈስ የመፈወስ ስጦታ፥ ለአንዱም ተአምራትን ማድረግ፥ለአንዱም ትንቢትን መናገር፥ ለአንዱም መናፍስትን መለየት፥ ለአንዱም በልዩ ዓይነት ልሳን መናገር፥ ለአንዱም በልሳኖች የተነገረውን መተርጎም ይሰጠዋል፤" (1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 12÷ 4-:10) ይህን የጸጋ ስጦታ ግን ብዝዎች እንደ ገብረ አካይ እኔ መች ማገልገል እንዳለብኝ ማንን ማገልገል እንዳለብኝ እንዴት ማገልገል እንዳለብኝ አውቃለው በማለት በድፍረትና በትዕቢት አልያም በማይገባ ፍርሃት በልቦናቸው መሬትነት የቀበሩ ሌሎች ደግሞ አልችልም አልተሰጠኝም የኔ አንድ ብቻ ነው ምን ቸገረኝ አይመለከተኝም ሌላው ይስራው ብለውም በልማድ ብቻ እየተመላለሱ የመንፈስ ቅዱስ ልዮ ልዮ ስጦታ በእነርሱ እንዳይገለጥ የሚዳፍኑና እራሳቸውን ከማንኛውም አገልግሎት የሚከላከሉ የትዬ ለሌ ናቸው። በአርባና በሰማንያ ቀን ተጠምቆ አብተ ወልድና ስመ ክርስትና የተቀበለ ሁሉ የፀጋ ስጦታ አለው። ስለዚህ እኔ አልችልም አልተሰጠኝም ብሎ ከአገልግሎት መዘግየት አግባብ አይደለም " እኛ ሁላችን ከሙላቱ ተቀብለን በጸጋ ላይ ጸጋ ተሰጥቶናልና፤" (የዮሐንስ ወንጌል 1÷16) ያ ማለት ግን ማገልገል አለብን ብለን ብቻ ተነስተን ዐይን ሆነን ሳለ ጆሮ ካልሆንኩ ጆሮ ሆነን ሳለ አንደበት ልሁን ማለት አይገባም" አካል ሁሉ ዓይን ቢሆን መስማት ወዴት በተገኘ? ሁሉም መስማት ቢሆን ማሽተት ወዴት በተገኘ?" እንዲ መጻሕፍ ሐዋርያውም "ሁሉ በጸጋ ይሁን" እንዳለ እንደየ ጸጋችን ልናገለግል ይገባናል ይቆየን በተሰጠን መክሊት እንደ አቅማችን አትርፈን የመንግስቱ ወራሾች የስሙ ቀዳሾች ያድርገን!! ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/nssu.eotcss ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/

#ደብረ_ዘይት እንደ ቅዱስ ያሬድ አስተምሮ ደብረ ዘይት የዐቢይ ጾም አምስተኛ ሳምንት መጠሪያ ሲሆን የዘይት ተራራ የሚል ትርጉም አለው። ደብረ ዘይት ብዙ የወይራ ዛፎች የሚገኙ በት በመሆኑ የዘይት ተ
#ደብረ_ዘይት እንደ ቅዱስ ያሬድ አስተምሮ ደብረ ዘይት የዐቢይ ጾም አምስተኛ ሳምንት መጠሪያ ሲሆን የዘይት ተራራ የሚል ትርጉም አለው። ደብረ ዘይት ብዙ የወይራ ዛፎች የሚገኙ በት በመሆኑ የዘይት ተራራ ለመባል በቅቷል። በዚህ ተራራ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ዳግም ምጽአቱ ለቅዱሳን ሐዋርያት ሰፊ ትምህርት አስተምሯል። ሐዋርያት "ንገረን የመምጣትህ እና የዓለም ፍጻሜ ምልክቱስ ምንድን ነው?" ከሚለው ጥያቄያቸው በመነሳት ስለ ሁለተኛ መምጣቱ እና ከመምጣቱ በፊት ስለሚፈጸሙት ምልክቶች በግልጽ ተናግሯል። ማቴ 24፡1-51 ስንዱዋ እመቤት ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንም በዚህ ሳምንት ይህንኑ የሚያወሱ ምንባባትን ፣ ትምህርቶችን ፣ ስብከቶችን እና መዝሙሮች እያስማማች ልጆችዋ የጌታን መምጣት እያሰቡ ተግባረ ነፍሳቸውን እንዲፈጽሙ እየነገረች ትሰነብታለች። ይቆየን! ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/channel/UC83LE1vp0FBsV2TEfcpSmUg ✍️ Facebook 👇 ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a https://www.facebook.com/nssu.eotcss ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU