4 555
订阅者
+124 小时
-97 天
+630 天
数据加载中...
吸引订阅者
九月 '26
九月 '26
+15
在0个频道中
八月 '26
+114
在0个频道中
Get PRO
七月 '26
+69
在0个频道中
Get PRO
六月 '26
+74
在0个频道中
Get PRO
五月 '26
+77
在0个频道中
Get PRO
四月 '26
+81
在0个频道中
Get PRO
三月 '26
+113
在0个频道中
Get PRO
二月 '26
+112
在0个频道中
Get PRO
一月 '26
+131
在0个频道中
Get PRO
十二月 '25
+96
在0个频道中
Get PRO
十一月 '25
+134
在0个频道中
Get PRO
十月 '25
+182
在1个频道中
Get PRO
九月 '25
+231
在0个频道中
Get PRO
八月 '25
+136
在0个频道中
Get PRO
七月 '25
+126
在0个频道中
Get PRO
六月 '25
+153
在1个频道中
Get PRO
五月 '25
+85
在0个频道中
Get PRO
四月 '25
+130
在1个频道中
Get PRO
三月 '25
+219
在1个频道中
Get PRO
二月 '25
+190
在0个频道中
Get PRO
一月 '25
+303
在0个频道中
Get PRO
十二月 '24
+217
在0个频道中
Get PRO
十一月 '24
+140
在0个频道中
Get PRO
十月 '24
+237
在0个频道中
Get PRO
九月 '24
+195
在0个频道中
Get PRO
八月 '24
+292
在0个频道中
Get PRO
七月 '24
+366
在0个频道中
Get PRO
六月 '24
+223
在0个频道中
Get PRO
五月 '24
+111
在0个频道中
Get PRO
四月 '24
+37
在0个频道中
Get PRO
三月 '24
+45
在0个频道中
Get PRO
二月 '24
+25
在0个频道中
Get PRO
一月 '24
+47
在0个频道中
Get PRO
十二月 '23
+39
在0个频道中
Get PRO
十一月 '23
+58
在0个频道中
Get PRO
十月 '23
+132
在0个频道中
Get PRO
九月 '23
+126
在0个频道中
Get PRO
八月 '23
+125
在0个频道中
Get PRO
七月 '23
+160
在0个频道中
Get PRO
六月 '23
+118
在0个频道中
Get PRO
五月 '23
+113
在0个频道中
Get PRO
四月 '23
+127
在0个频道中
Get PRO
三月 '23
+115
在0个频道中
Get PRO
二月 '23
+134
在0个频道中
Get PRO
一月 '23
+273
在0个频道中
Get PRO
十二月 '22
+202
在0个频道中
Get PRO
十一月 '22
+229
在0个频道中
Get PRO
十月 '22
+223
在0个频道中
Get PRO
九月 '22
+249
在0个频道中
Get PRO
八月 '22
+281
在0个频道中
Get PRO
七月 '22
+186
在0个频道中
Get PRO
六月 '22
+127
在0个频道中
Get PRO
五月 '22
+162
在0个频道中
Get PRO
四月 '22
+129
在0个频道中
Get PRO
三月 '22
+220
在0个频道中
Get PRO
二月 '22
+92
在0个频道中
Get PRO
一月 '22
+116
在0个频道中
Get PRO
十二月 '21
+131
在0个频道中
Get PRO
十一月 '21
+193
在0个频道中
Get PRO
十月 '21
+229
在0个频道中
Get PRO
九月 '21
+172
在0个频道中
Get PRO
八月 '21
+92
在0个频道中
Get PRO
七月 '21
+129
在0个频道中
Get PRO
六月 '21
+67
在0个频道中
Get PRO
五月 '21
+365
在0个频道中
| 日期 | 订阅者增长 | 提及 | 频道 | |
| 04 九月 | +1 | |||
| 03 九月 | +7 | |||
| 02 九月 | +4 | |||
| 01 九月 | +3 |
频道帖子
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
+4
" ህፃናት ልዩ ትኩረት ይሻሉ፤ ...ወላጆች ልጆቻችሁ የሚውሉበትንና የሚጫወቱበትን ቦታ ማወቅና መከታተል ይገባል " - ፖሊስ
👉 " ሰራተኛ ስትቀጥሩ ጥንቃቄ አድርጉ ! "
ህፃን ፊዮና ሰለሞን ነሐሴ 21 ቀን 2018 ዓ/ም ከምሽቱ 12፡30 ሠዓት አካባቢ ከቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 12 ልዩ ቦታው ቦሌ ቡልቡላ በቤት ሰራተኛቸው የእገታ ወንጀል ተፈጽሞባት 3 ሚሊዮን ብር ከተጠየቀባት በኋላ አጋቿ ሰራተኛ ተይዛ ህጻኗ ወደ ቤተሰቦቿ እንድትመለስ ተደርጓል።
መቅደስ ሞገድ የተባለችው ተጠርጣሪ አቶ ሰለሞን ፈንታሁንና ወ/ሮ ሄለን ኃይለሚካሄል ቤት በቤት ሰራተኝነት ለሶስት ወራት ከሰራች በኋላ " ቤተሰብ ልጠይቅ " ብላ ፈቃድ ጠይቃ ከሄደች በኋላ ሳትመለስ ትቀራለች።
ከሁለት ወራት በኋላ ግን ከአንድ ግብረ አበሯ ጋር ወደ ቀድሞ አሰሪዎቿ አካባቢ በመመለስ ህፃን ፊዮና ሰለሞንን ከምትጫወትበት ቦታ ይዛ ትሰወራለች።
ከዚያም ግብረ አበሯ ለህፃኗ ቤተሰቦች በስልክ 3 ሚሊዮን ብር እንዲከፍሉ ይዝታል፤ ቤተሰቡ ዛቻውን በመፍራት 370 ሺህ ብር በባንክ ገቢ ያደርጋል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ከሌሎች የፀጥታ ተቋማት ጋር በቴክኖሎጂ በመታገዝ ባደረገው ክትትል፣ ተጠርጣሪዋ ህፃኗን ይዛ ወደ አማራ ክልል መሄዷን ለይቷል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ከሌሎች የፀጥታ ተቋማት ጋር በመተባበር ባደረገው የተቀናጀ ኦፕሬሽን ተጠርጣሪዋን ከጎንደር ከተማ ማራኪ ክ/ከተማ ዩኒቨርሲቲ ጫካ ውስጥ በጥቆማና ክትትል በቁጥጥር ስር ሊያውል ችሏል።
ታጋችዋ ህፃን ፊዮና ሰለሞን ትላንት ምሽት ላይ ከባህር ዳር አዲስ አበባ ገብታለች።
የአዲስ አበባ ፖሊስ የታክቲክ ወንጀሎች ምርመራ ዋና መምሪያ ኃላፊ ረዳት ኮሚሽነር አድማሱ ኢፋ፣ ህፃናት ልዩ ትኩረት ከሚሹ የህብረተሰብ ክፍሎች ቀዳሚ በመሆናቸው መጠበቅ፣ መንከባከብና ተገቢውን ትኩረት መስጠት እንደሚገባ ተናግረዋል።
ወላጆች ልጆቻቸው የሚውሉበትንና የሚጫወቱበትን ቦታ ማወቅና መከታተል የሚገባ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
የህፃን ፊዮና እናት ወ/ሮ ሄለን ኃ/ሚካኤል፥ ተጠርጣሪዋ መቅደስ ሞገስ በቤት ሰራተኝነት ተቀጥራ ስትሰራ የቆየች በመሆኑ ህጻኗ ስለምታውቃት አጋጣሚ ተጠቅማ የእገታ ወንጀሉን በመፈፀሟ ማዘናቸውን ገልጸዋል።
በወቅቱ የልጃችንን መጥፋት ለአዲስ አበባ ፖሊስ ካመለከትን ጀምሮ ፖሊስ ቀን ከሌሊት ፍለጋውን በማድረግ ልጃችንን በእጃችን በማስገባቱ ወደር የሌለው ደስታ ተሰምቶናል ብለዋል። " በስራው ለተሳተፉ በሙሉ ክብር ይገባቸዋል " ሲሉ ገልጸዋል።
" ማንኛውም ዓይነት ወንጀል ፈፃሚዎች ለጊዜውም ቢሆን ከሰው ዓይንና ጆሮ ቢሰወሩም ከህግ ማምለጥ አይችሉም " ያለው የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ በስራው ተሳታፊ ለነበሩ የአማራ ክልል ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ እና የጎንደር ከተማ ፖሊስ እንዲሁም ሌሎች የፀጥታ ተቋማት ላደረጉት ቀና ትብብር ምስጋናውን አቅርቧል፡፡
ህብረተሰቡ የቤት ሰራተኞችን ሲቀጥር ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርግ እንዲሁም በአካባቢው ላይ የሚያያቸውን ማንኛውም አጠራጣሪ ጉዳዮች ለአቅራቢያ ፖሊስ መረጃ በመስጠት የህግ የበላይነትን ሊያረጋግጥ እንደሚገባም መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡
#AddisAbabaPolice
ነሐሴ 29 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
| 2 | " ' አታሼ' የሚለው የሥራ መደብ የጀማሪ የውጭ ግንኙነት አገልግሎት ባለሙያ የመነሻ የሥራ ደረጃ መጠሪያ ነው " - የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
👉 " ማመልከቻ ሊንኩ ተስተካክሏል"
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ "በአታሼ (Attaché" በተሰኘ የሥራ መደብ 100 አመልካቾችን ለመቅጠር የሥራ ማስታወቂያ ማውጣቱን ይታወቃል።
ይህን ማስታወቂያ ተከትሎ በርካቶች ለመሆኑ "አታሼ" (Attaché) ምንድን ነው ? የሚል ጥያቄ ሲያነሱ እና ሲወዛገቡ ተስተውለዋል።
በሥራው ለመሰማራት ሙከራ ያደረጉ ወጣቶች ደግሞ የሥራ ማስታወቂያው መውጣቱን ተከትሎ የተቀመጠው የመመዝገቢያ ሊንክ "አይሰራም" የሚሉ አስተያየቶችን እያቀረቡ ናቸው።
ይህን ተከትሎ ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ስለ "አታሼ" ምንነት እና ስለመመዝገቢያ ሊንኩ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከፍተኛ ኃላፊን ማብራሪያ ጠይቋል።
እሳቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ምላሽ፣ " በኢፌዴሪ የውጭ ግንኙነት አገልግሎት ባለሙያዎች የሙያ መሰላል መሰረት 'አታሼ' የሚለው የሥራ መደብ የጀማሪ የውጭ ግንኙነት አገልግሎት ባለሙያ የመነሻ የሥራ ደረጃ መጠሪያ ነው " ብለዋል።
ይህ የመጀመሪያው የሥራ መጠሪያ መሆኑን ገልጸው፣ "ከዚያ በኋላ ሦስተኛ ፀሐፊ ይባላል፤ ሁለት፣ አንድ እያለ ይቀጥላል" ሲሉም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
የአመልካቾች መመዝገቢያ ሊንክ አይሰራም በሚል ለሚነሳው ቅሬታ ጠይቀናቸው በሰጡን ምላሽ ደግሞ፣ "የአይሲቲ ባለሙያዎች ቼክ እያደረጉ ነው" የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
ይህን ካሉን ከቆይታ በኋላ ደግሞ፣ "ሊንኩ ተስተካክሏል" ብለዋል።
በ"አታሼ" የሥራ ዘርፍ የሚሰማሩ ባለሙያዎች ምን ምን ይሰራሉ? ስንል የጠየቅናቸው አመራሩ በሰጡን ምላሽ፣ "የመጀመሪያ ደረጃ እንደመሆኑ ሥልጠና የሚሰጥበት የሥራ ላይ ልምምድ የሚደረግበትና አጠቃላይ ከሙያው ጋር ትውውቅ የሚያደርግበት ነው" የሚል አጭር ምላሽ ሰጥተዋል።
"አታሼ" የሥራ አይነት የባህል፣ የሚዲያ ግንኙነት፣ የንግድ ግንኙነት ጨምሮ የተለያዩ ዘርፎች ያሉት ሲሆን፣ በዘርፉ የተሰማሩ አካላት በተመደቡበት የሥራ አይነት የውጭ ዲፕሎማሲያዊ ስራዎችን ማከናወን፣ ሪፖርቶችን ማቅረብ እንደሚጠበቅባቸው ይታመናል።
መመዝገቢያ https://forms.gle/R7PmwCNeqEE3EQBN6 (በማንኛውም የትምህርት መስክ የመጀመሪያ ዲግሪና 0 ዓመት የስራ ልምድ)
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
ነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia | 143 |
| 3 | ተስተካክሏል !
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር 100 አመልካቾችን በአታሼ (Attaché) የሥራ መደብ ለመቅጠር የሥራ ማስታወቂያ አውጥቷል።
- የሥራ መደብ፦ አታሼ (Attaché)
- የሚቀጠሩ ሰዎች ብዛት፦ 100
- ደመወዝ፦ ብር 12,566
- የማመልከቻ ጊዜ፦ 7 ተከታታይ የሥራ ቀናት
➡️ ተፈላጊ ችሎታ ፦ በማንኛውም ትምህርት መስክ የመጀመሪያ ዲግሪና 0 ዓመት የስራ ልምድ
ምዝገባው በወጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አዲሱ ህንጻ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 401 በአካል በመቅረብ ወይም ከዚህ በታች በተቀመጠው የመመዝገቢያ ሊንክ በመጠቀም መመዝገብ ይቻላል https://forms.gle/R7PmwCNeqEE3EQBN6
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የማመልከቻ ሊንኩ መስተከሉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል።
📌 Tikvah Economy and Jobs https://t.me/TikvahEconomy/138
@tikvahethiopia | 117 |
| 4 | #ችሎት
በሽብር ተግባር ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር በዋሉት የኢህአፓ አባላት ላይ የፌደራል ፖሊስ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ የጠየቀ ሲሆን፣ ፍርድ ቤቱ በዋስትና እና በተጨማሪ ቀናት ጥያቄ ላይ ውሳኔ ለመስጠት ለነገ ተቀጥሯል።
ከዚህ ቀደም ነሐሴ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት፣ ፖሊስ ምርመራውን አጠናቆ እንዲያቀርብ ፍርድ ቤቱ ለነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም "ለመጨረሻ ጊዜ" የ7 ቀናት የጊዜ ገደብ መስጠቱን መዘገባችን ይታወሳል።
በዛሬው ዕለት ተጠርጣሪዎቹ አቶ ይስሃቅ ወልዳይ፣ አቶ አበበ አካሉ እና አቶ አበራ ንጉስ ፍርድ ቤት የቀረቡ ሲሆን፣ ፖሊስ የተሰጠው ጊዜ ቢጠናቀቅም ተጨማሪ የ14 ቀናት የምርመራ ጊዜ እንዲሰጠው በድጋሚ ጠይቋል።
ፖሊስ ለተጨማሪ ጊዜ መጠየቂያነት ያቀረባቸው ምክንያቶች፦
- ከአርባ ምንጭ አካባቢ የህክምና ማስረጃ ለማምጣት፣
- የፎረንሲክ እና የቴክኒክ ማስረጃ ውጤቶችን ለመጠባበቅ፣
- የተጨማሪ ምስክሮችን ቃል ለመቀበል፣
- የተያዙ የኤሌክትሮኒክስ ቁሶች (ኤግዚቢት) ምርመራን ለማጠናቀቅ እና
- ከግልና ከመንግስት ባንኮች የተጠርጣሪዎችን የባንክ እንቅስቃሴ ውጤት ለማግኘት የሚሉ ናቸው።
የተጠርጣሪዎቹ ጠበቆች በበኩላቸው ፖሊስ ላለፉት 31 ቀናት ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ ሲያደርግ መቆየቱን በማንሳት፣ የዋስትና መብታቸው እንዲከበር ተከራክረዋል።
የተጠሪዎቹ ጠበቃ በበኩላቸው እስካሁን ስድስት ምስክሮች ቃል መስጠታቸውን ጠቅሰው፣ ፖሊስ ምስክሮችን ሊያባብሉ ይችላሉ በሚል ያቀረበው ስጋት በቂ ማስረጃ የሌለው መሆኑን ገልጸዋል።
በተጨማሪም "ከአገር ሊወጡ ይችላሉ" ለሚለው ስጋት፣ አቶ አበበ አካሉ ፓስፖርት የሌላቸው መሆኑንና ሌሎቹም ቢሆኑ ፍርድ ቤቱ የእግድ ትዕዛዝ ማውጣት ስለሚችል በዋስ ሊፈቱ እንደሚገባ አመልክተዋል።
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አንደኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት፣ የሁለቱንም ወገን ክርክር ካዳመጠ በኋላ ፖሊስ በጠየቀው የ14 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ እና ተጠርጣሪዎቹ ባቀረቡት የዋስትና ጥያቄ ላይ ውሳኔ ለመስጠት ለነገ ነሐሴ 29 ቀን 2018 ዓ.ም ከሰዓት 9 ሰዓት ቀጠሮ መስጠቱን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከተጠርጣሪዎቹ ጠበቃ አቶ ሰለሞን ገዛኸኝ ሰምቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia | 90 |
| 5 | የግብር ስወራ የፈጸሙ የመኪና አስመጪዎች ላይ ዕርምጃ መወሰዱን የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ አሳወቀ።
በመኪና አስመጪነት የንግድ ፈቃድ አውጥተው፤ ያስመጧቸውን ተሽከርካሪዎች በራሳቸው መሸጫ ቦታ ከመሸጥ ይልቅ በኮሚሽን ኤጀንቶች አማካኝነት በመሸጥ የግብር ስወራ የፈጸሙ አስመጪዎች ላይ ዕርምጃ መወሰዱን ቢሮ አስታውቋል።
የቢሮው የሕግ ተገዢነት ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ መሐመድ አብዱራህማን፣ " በሕገ-ወጥ የግብር ስወራ ተግባር መሳተፋቸው በጥናት የተረጋገጠባቸው ግለሰቦችና ድርጅቶች ላይ ሱቆችን ማሸግና ጊዜያዊ ፈቃድ እገዳ ተጥሏል " ብለዋል።
" እነዚህ አካላት የአስመጪነት ፈቃዳቸውን ተጠቅመው ራሳቸው ካስመጧቸው ውጪ ከሶስተኛ ወገን ጭምር ተቀብለው በመሸጥ ሕግን ተላልፈው መገኘታቸው ተረጋግጧል " ሲሉም ገልጸዋል።
በተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ ቁጥር 1341/2017 መሠረት የንግድ ሥራ በተፈቀደለት ቦታና በተመዘገበው የንግድ ዘርፍ ብቻ መከናወን እንዳለበትም አብራርተዋል።
በዚህም መሠረት የመኪና አስመጪዎች ተሽከርካሪዎችን መሸጥ የሚገባቸው በራሳቸው የንግድ ፈቃድ ባወጡበት መሸጫ ቦታ ብቻ መሆኑ ተጠቁሟል።
በተያያዘም ያገለገሉ መኪኖችን የሚሸጡ የኮሚሽን ኤጀንቶች ከአገለገሉ መኪኖች ውጪ አዲስ መኪና ሲሸጡ ከተገኙ በታክስ አስተዳደር አዋጁ መሠረት የቅጣት ዕርምጃ እንደሚወሰድባቸው ቢሮው አስጠንቅቋል።
ኤጀንቶቹ ያገለገለ መኪና ሲሸጡም መረጃውን ለግብር ሰብሳቢው መሥሪያ ቤት በወቅቱ ማሳወቅ ይጠበቅባቸዋል ተብሏል።
ከሕጋዊ መሥመር ውጪ ተንቀሳቅሰዋል የተባሉት አስመጪዎች አሰራራቸውን አስተካክለው በፍጥነት ወደ ሕጋዊ መሥመር እንዲመለሱ ማሳሰቢያ ተላልፏል።
#ኤኤምኤን
ነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia | 87 |
| 6 | ኢትዮጵያ 100 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያለው የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ተቋም ልታቋቁም ነው።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና ዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን (IFC) በኢትዮጵያ የቤት መግዣ ብድር ፋይናንስን ለማስፋፋት የሚያስችል ታሪካዊ የትብብር ማዕቀፍ ዛሬ መፈራረማቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ በ100 ቢሊዮን ብር ካፒታል የሚቋቋመው ተቋም፣ IFC እስከ 200 ሚሊዮን ዶላር የሚደርስ አስተዋጽኦ የሚያደርግበት እንደሚሆን አመልክተዋል።
ተቋሙ በባንክ ዘርፍ ያለውን የገንዘብ ፍሰት አለመመጣጠን ለመቅረፍ እና በመላ አገሪቱ ተደራሽ የሚሆን የቤት መግዣ ብድር ፋይናንስ የሚያስገኝ እንደሆነ ገልጸዋል።
በተጨማሪም አጋርነቱ በተመጣጣኝ ዋጋ 1.5 ሚሊዮን ቤቶችን ለማቅረብ የተያዘውን ግብ ለማሳካት እና በፋይናንስ ስርዓቱ ውስጥ የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ ለማሳደግ የተቀመጠውን ግብ ለማሳካት ወሳኝ እርምጃ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ ፈጣን፣ ጠንካራና ሁሉንም ያካተተ ኢኮኖሚ መገንባቷን እንደምትቀጥል አስታውቀዋል።
#PMOEthiopia
ነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia | 143 |
| 7 | #Update : በሳዑዲ አረቢያ አንድን ኢትዮጵያዊ በድብደባና በአሰቃቂ ሁኔታ የገደሉ 5 ኢትዮጵያውያን በቁጥጥር ሥር ውለዋል።
የሳዑዲ አረቢያ፣ መካ ፖሊስ የድንበር ደህንነት ሕግን በመተላለፍ ሌላኛውን የኢትዮጵያ ዜጋ ወገናቸውን በከፍተኛ ድብደባ እና በአሰቃቂ ሁኔታ ህይወቱ እንዲያልፍ ያደረጉ 5 የኢትዮጵያ ዜጎችን በቁጥጥር ሥር ማዋሉን አስታውቋል።
እንደ ፖሊስ መግለጫ ተጠርጣሪዎቹ ግለሰቡን ሲደበድቡ ፣ ሲያሰቃዩ የሚያሳይ ቪዲዮ በመሰራጨቱ ፈጣን ክትትል ተደርጎባቸው በራንያ ግዛት ውስጥ በቁጥጥር ሥር ውለዋል።
" ሟችም ሆነ ተጠርጣሪዎቹ የሀገሪቱን የድንበር ደህንነት ሕግ ጥሰዋል " ሲል ፖሊስ ገልጿል።
ፖሊስ በጉዳዩ ላይ አደረኩት ባለው የማጣራት ስራ በተጠርጣሪዎቹ እና በሟቹ መካከል ከዚህ ቀደም የነበረ አለመግባባት የነበረ ሲሆን፣ ሁኔታው ተባብሶ ወደ አዘግናኝ ጥቃት አምርቷል።
የመካ ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹ ላይ ሕጋዊ እርምጃ ለመውሰድ አስፈላጊው የምርመራ ሥራ ተጠናቆ ጉዳዩ ወደ ሌላኛው የሕግ አካላት መተላለፉን ገልጿል።
ሳዑዲ አረቢያ ውስጥ ወንጀል ፈጽሞ መገኘት እስከ ስቅላት ሞት የሚያደርስ ቅጣት ሊያስፈርድ ይችላል። አይደለም የሰዎችን ህይወት ያጠፉ የአደንዛዥ እጽ ዝውውር ላይ የሚሳተፉ በሞት የሚቀጡበት ሀገር ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ነሐሴ 27 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia | 172 |
| 8 | የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር 100 አመልካቾችን በአታሼ (Attaché) የሥራ መደብ ለመቅጠር የሥራ ማስታወቂያ አውጥቷል።
- የሥራ መደብ፦ አታሼ (Attaché)
- የሚቀጠሩ ሰዎች ብዛት፦ 100
- ደመወዝ፦ ብር 12,566
- የማመልከቻ ጊዜ፦ 7 ተከታታይ የሥራ ቀናት
➡️ ተፈላጊ ችሎታ ፦ በማንኛውም ትምህርት መስክ የመጀመሪያ ዲግሪና 0 ዓመት የስራ ልምድ
ምዝገባው በወጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አዲሱ ህንጻ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 401 በአካል በመቅረብ ወይም ከዚህ በታች በተቀመጠው የመመዝገቢያ ሊንክ በመጠቀም መመዝገብ ይቻላል https://forms.gle/R7PmwCNeqEE3EQBN6
📌 Tikvah Economy and Jobs https://t.me/TikvahEconomy/138
@tikvahethiopia | 158 |
| 9 | በአዲስ አበባ የመኪና ንግድ ማዕከላት ላይ ሰፊ የግብር ስወራ መኖሩ ተጋለጠ።
የአዲስ አበባ ከተማ ገቢዎች ቢሮ በከተማዋ በሚገኙ የመኪና ንግድ ማዕከላትና የመኪና ድለላ ዘርፍ ላይ ባካሄደው ምርመራ ሰፊ የሆነ የግብር ስወራ መኖሩን እንደደረሰበት ካፒታል ጋዜጣ ዘግቧል።
በመኪና ንግድና ደላላ ሥራ የተሰማሩ አካላት ዓመታዊ የገቢ ግብርና የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ግዴታቸውን በአግባቡ እንደማይወጡ የቢሮው ጥናት አሳይቷል።
ይህን ተከትሎም በመኪና ደላላነት / በኮሚሽን ንግድ የሚሰሩ ነጋዴዎች በግቢያቸው ያስቀመጧቸውን መኪኖች እንዲያስወጡ ጥብቅ ማሳሰቢያ ተሰጥቷቸው ነበር።
ቢሮው እንደገለጸው፣ መኪናዎችን ለሽያጭ በማይፈቀድላቸው ቦታዎች ማስቀመጥና መሸጥ ከሕጋዊ የንግድ ደንቦች ጋር የሚጋጭ ነው።
ቢሮው ባወጣው መመሪያ፣ በሕጋዊ መንገድ የተመዘገቡ የመኪና አስመጪ ድርጅቶች ብቻ በተፈቀደላቸው የንግድ ቦታ መኪና መሸጥ እንደሚችሉ በግልጽ አስቀምጧል።
ከሰሞኑን በአዲስ አበባ በትክክል አስመጪ ያልሆኑና በኮሚሽን የሚሰሩ እጅግ በርካታ የመኪና መሸጫዎች ተዘግተው ነበር።
አሁን ላይ በተሻሻለ መመሪያ ሥራቸውን እንዲቀጥሉ ተፈቅዶላቸዋል። ሆኖም የመኪና ነጋዴዎች የሚሰሩበት ሥርዓት ላይ ገደቦች ተጥለዋል።
በተለይም አዲስና ያልተነዱ "Zero-Mile" መኪኖችን በግል ኮሚሽን ወይም ትርፍ ላይ ተመስርቶ መሸጥ እንዲሁም እነዚህን መኪኖች በራሳቸው ግቢ ውስጥ መሸጥ አይፈቀድም።
አዲስ መኪኖችን የማስመጣትና የመሸጥ መብት ሕጋዊ ፈቃድ ላላቸው አስመጪዎች ብቻ ተሰጥቷል።
በሌላ በኩል፥ የመኪና ደላላዎች በግለሰቦች የተያዙ ያገለገሉ መኪኖችን በኮሚሽን መሸጥ ወይም መኪና በራሳቸው ገዝተው እንደገና መሸጥ ይችላሉ፤ ይህም ግን የተቀመጡትን የግብርና የንግድ ሕጎች በመከተል ብቻ መሆን አለበት።
የመረጃው ባለቤት ካፒታል ጋዜጣ ነው።
ነሐሴ 27 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia | 140 |
| 10 | #ጥናት
በትግራይ የተፈናቃዮች መጠለያ ጣቢያዎች ከፍተኛ የአገልግሎትና የጥበቃ ክፍተት እንዳለ ጥናት አመላከተ።
በትግራይ ክልል የሚገኙ የተፈናቃዮች መጠለያ ጣቢያዎች በምግብ፣ በውሃና ንፅህና፣ በጤና፣ በመጠለያ እና በጥበቃ አገልግሎቶች ላይ ከፍተኛ ክፍተት እንዳለባቸው በቅርቡ ይፋ የሆነ ጥናት አመላክቷል።
ጥናቱ በ5 ዞኖችና በ21 ወረዳዎች የሚገኙ 78 የተፈናቃይ ጣቢያዎችን የሸፈነ ሲሆን፣ ውጤቱ ወደ 307 ሺህ የሚጠጉ ተፈናቃዮችን የሚመለከት መሆኑ ተገልጿል። ጥናቱ በዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (IOM) በበላይነት የተካሄደ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ የካምፕ አስተባባሪነትና አስተዳደር ክላስተር (CCCM) እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል።
በጥናቱ መሠረት 95 በመቶ የሚሆኑት ጣቢያዎች የምግብ ድጋፍ ቢያገኙም፣ ድጋፉ የተፈናቃዮችን ፍላጎት ለመሸፈን በቂ አለመሆኑ ተጠቁሟል። ተመሳሳይ ክፍተት በስነ-ምግብ፣ በጤና፣ በውሃና ንፅህና፣ በትምህርትና በመጠለያ አገልግሎቶችም ታይቷል።
ከ78ቱ ጣቢያዎች 45ቱ ምንም የጥበቃ አገልግሎት የሌላቸው ሲሆን፣ 36 ጣቢያዎች ደግሞ ምንም የመጠለያ ድጋፍ እንደማያገኙ ጥናቱ ያሳያል።
በውሃና ንፅህና ዘርፍም 4 ጣቢያዎች ብቻ በቂ አገልግሎት ሲኖራቸው፣ 27 ጣቢያዎች ምንም አገልግሎት የላቸውም፤ በ47 ጣቢያዎች ደግሞ አገልግሎቱ በቂ አለመሆኑ ተመልክቷል።
በተለይ የጣቢያ አስተዳደርና ማስተባበር ላይ ከፍተኛ ክፍተት መኖሩ ተጠቁሟል። ከተገመገሙት 78 ጣቢያዎች 37ቱ የተፈናቃዮችን ቁጥርና ፍላጎት መከታተል፣ ከሰብዓዊ ድርጅቶች ጋር ማስተባበር፣ መረጃ ማድረስና ቅሬታ መቀበል የሚችል የCCCM አካል የላቸውም።
ችግሩ በማዕከላዊ ዞን ይበልጥ የጎላ ሲሆን፣ በዞኑ የሚገኙ የተፈናቃይ መጠለያ ጣቢያዎች ሁሉም የCCCM አገልግሎት እንደሌላቸው ጥናቱ ጠቁሟል። ዞኑ ከትግራይ አጠቃላይ ተፈናቃይ ህዝብ 19 በመቶ የሚያስተናግድ መሆኑም ተገልጿል።
ከጥበቃ አንፃርም የህጻናት ጥበቃ ስጋት በ64 ጣቢያዎች፣ የሴቶችና ሴት ልጆች ደህንነት ስጋት በ55 ጣቢያዎች እና የፆታዊ ጥቃት ስጋት በ46 ጣቢያዎች መኖሩ ተለይቷል። በተጨማሪም 39 ጣቢያዎች የአካል ጉዳተኞች ተደራሽነት ችግር፣ 14 ጣቢያዎች የመሬትና ንብረት ክርክር፣ 12 ጣቢያዎች ከአስተናጋጅ ማህበረሰብ ጋር ውጥረት እና 10 ጣቢያዎች የሰነድ እጦት እንዳለባቸው ተጠቁሟል።
በአጠቃላይ ከ78ቱ ጣቢያዎች 44ቱ መካከለኛ፣ 22ቱ ከፍተኛ እና 10ሩ ደግሞ ወሳኝ የስጋት ደረጃ ላይ እንደሚገኙ ጥናቱ ደርሷል። 70 በመቶ የሚሆኑት ጣቢያዎች የአካባቢ ስጋት ሲያመለክቱ፣ 43 በመቶዎቹ ደግሞ እንደ ወቅታዊ ጎርፍ ያሉ አደጋዎችን እንደሚጋፈጡ ተገልጿል።
ጥናቱ በኢትዮጵያ ሰብዓዊ ፈንድ (EHF) እና በአውሮፓ ህብረት የገንዘብ ድጋፍ መካሄዱ ታውቋል።
ስለጥናቱ ሂደትና ውጤቶቹ ላይ ግንዛቤ እንዳለው የትግራይ ክልል ጤና ቢሮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia | 147 |
| 11 | በሰሜን ጎንደር ዞን ጠለምት ወረዳ በደረሰ የመሬት መንሸራተት አደጋ የሰው ሕይወት ማለፉና ከ2 ሺህ በላይ ዜጎች መፈናቀላቸው ተገለጸ።
• የመሬት መንሸራተቱ አሁንም ድረስ በቦታው ላይ እየታየና እየተስፋፋ ነው ተብሏል።
በሰሜን ጎንደር ዞን ጠለምት ወረዳ “ግልቤና” በተባለ ቀበሌ ነሐሴ 16 ቀን 2018 ዓ.ም በደረሰ ከባድ የመሬት መንሸራተት አደጋ የአንድ ሰው ሕይወት ማለፉንና ከሁለት ሺህ በላይ ዜጎች ከመኖሪያ ቀያቸው መፈናቀላቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከሚመለከታቸው የወረዳው የሥራ ኃላፊዎች ሰምቷል።
እንደ ወረዳው መረጃ ከሆነ፣ በአደጋው ሳቢያ 411 አባወራዎች ከመኖሪያ ቀያቸው የተፈናቀሉ ሲሆን፣ ይህም በአጠቃላይ ከ2,000 በላይ የሚሆኑ የቤተሰብ አባላትን ለችግር ዳርጓል።
በአደጋው የአንድ ሰው ሕይወት ሲያልፍ፣ አራት ሰዎች ላይ ደግሞ መጠነኛና ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል ተብሏል።
ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖችም በወረዳው የጤና ተቋማት ክትትል እየተደረገላቸው እንደሚገኝ ታውቋል።
የመሬት መንሸራተቱ በንብረትና በእንስሳት ላይም ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል።
እስካሁን ባለው መረጃ መሠረት 26 መኖሪያ ቤቶች ሙሉ በሙሉ የተደረመሱ ሲሆን፣ 31 የቤት እንስሳትም በአደጋው መሞታቸው ተረጋግጧል።
የመሬት መንሸራተቱ አሁንም ድረስ በቦታው ላይ እየታየና እየተስፋፋ ቢሆንም፣ ማህበረሰቡ ቀድሞ አካባቢውን ለቆ ወደ ቀበሌው ማእከል እንዲወርድ በመደረጉ ተጨማሪ የሰው ሕይወት ጉዳት እንዳይደርስ መከላከል መቻሉን ወረዳው ገልጿል።
የአደጋው ሁኔታና የተጎጂዎች ዝርዝር መረጃ ተሰብስቦ ለሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት የተላከ ቢሆንም፣ እስካሁን ድረስ ለተፈናቀሉ ወገኖች የደረሰ ምንም ዓይነት አስቸኳይ እርዳታ አለመኖሩን ተነግሯል።
ተፈናቃዮቹ በአሁኑ ወቅት በቀበሌው ማእከል ተጠልለው የሚገኙ ሲሆን፣ አስቸኳይ የምግብና የቁሳቁስ እርዳታ እንደሚፈልጉም ተጠቁሟል።
ፎቶ፦ ፋይል
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
ነሐሴ 26 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia | 130 |
| 12 | " መሬቱ ነው፣ ዝናቡ አቁሮ ነው፣ ጎርፉ ወደ ፍሳሽ መውረጃ ስላልገባ ነው፣ የኔ ችግር አይደለም፣ የመንገዶች ባለስልጣን ችግር ነው፣ ብሎ ማሳበብ ምክንያት አይሆንም፤ ከተጠያቂነት ነጻ አያደርግም " - አቶ ጥጋቡ ደሳለኝ
በክረምት ወቅት አሽከርካሪዎች መንገድ ላይ የተጠራቀመን የዝናብ ወይም የፍሳሽ ውሃ እግረኞች ላይ ረጭተው ሲያልፉ ማየት የተለመደ ነው።
ነገር ግን በኢፌዴሪ የወንጀል ህግ ከአንቀጽ 820 ጀምሮ እና በተከታዮቹ እንዲሁም የኢፌዴሪ ሚኒስትሮች ምክር ቤት ባወጣው የመንገድ የትራንስፖርት ደንብ ድርጊቱ በደንብ መተላለፍ ወንጀል ተቆጥሮ ከ3 ዓመት በማይበልጥ ቀላል እስራት ወይም በገንዘብ መቀጮ እንደሚያስቀጣ ዓለም አቀፍ የህግ ባለሙያ እና ጠበቃ አቶ ጥጋቡ ደሳለኝ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
የህግ ባለሙያው እና ጠበቃው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በዝርዝር ምን አሉ ?
" አንድ አሽከርካሪ መንገድ ላይ እያሽከረከረ በሚሄድበት ወቅት የእግርኞችን ደህንነት በተጠበቀ ሁኔታ ማሽከርከር እንዳለበት የመንገድ ደህንነት፣ የስነ-ስርዓት ደንብ እና የፌደራል የወንጀል ህግ በግልጽ ይደነግጋል።
በአሽከርካሪዎች እንደዚህ አይነት ጉዳት የሚደርሰው በቸልተኝነት ነው። በእግርኛው ላይ ላደረሰው ጉዳት በደረቅ ወንጀል (ታስቦበት በተፈጸመ ከባድ ወንጀል) ሳይሆን በቸልተኝነት በፍጸመው የደንብ መተላለፍ ወንጀል ተጠያቂ ይሆናል።
እንደዚህ አይነት ወንጀል ሰርተው በፍርድ ቤት ክስ ቀርቦባቸው ጥፋተኛ ከተባሉ በደንብ መተላለፍ ወንጀሎች በመደበኛው የወንጀል ህግ ሶስት አመት በማይበልጥ ቀላል እሰራት ወይም በአማራጭ በገንዘብ መቀጮ ይቀጣሉ።
ይህ ሊሆን የሚችለው ግን ጉዳት የደረሰበት አካል የተሽከርካሪውን የሰሌዳ ቁጥር ይዞ ለፖሊስ አመልክቶ ከሆነ እና በአሽከርካሪው ቸልተኝነት ምክንያት የተጠራቀመው ውሃ በሰውየው ላይ ተረጭቶ እንዳበላሸው በምስክር ማረጋገጥ ሲችል ነው።
የዝናብ ውሃም ይሁን ሌላ ማንኛውም ፈሳሽ በተጠራቀመበት ቦታ ላይ አሽከርካሪው እግረኛውን ቀስ ብሎ ማሳለፍ እና በዝግታ ማሽከርከር ሲገባው ተሽከርካሪው በመጣበት ፍጥነት ግለሰቡን ረጭቶት ከሄደ ተጠያቂ ነው። እንደዚህ አይነት ነገሮች ሲፈጠሩ አሽከርካሪው በረጨበት አካባቢ በሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ ማመልከት ይጠበቃል።
በኢፌዴሪ የወንጀል ህግ ከአንቀጽ 820 ጀምሮ እና በተከታዮቹ ደንብ መተላለፍን በተመለከተ የወጡ የወንጀል ተጠያቂነት ድንጋጌዎች አሉ።
ሌላው የኢፌዴሪ ሚኒስትሮች ምክር ቤት ባወጣው የመንገድ ትራንስፖርት ደንብ አሽከርካሪዎች የመንገድ ደህንነትን ባከበረ፣ በተጠበቀ ሁኔታ ማሽከርከር እንዳለባቸው እና በቸልተኝነት ለሚፈጽሙት ማንኛውም ወንጀል ተጠያቂ እንደሚሆኑ አስቀምጧል።
በተጨማሪም በስልክ እና በላፕቶፕ ላይ ጉዳት ካደረሰ በፍትሐ ብሔር ሁሉ መክሰስ ይቻላል። ግን ምስክሮች ያስፈልጋሉ። በቸልተኝነት ለደረሰ ጉዳት ካሳ የመጠየቅ መብት እንዳላቸው የፍትሐብሔር ህጉም በግልጽ አስቀምጧል።
በክረምት ወቅት በከፍተኛ የዝናብ መጠን አስፋልቶች ላይ ውሃ ሊከማች ይችላል፣ ውሃ የራሱ የፍሰት ስርዓት ስላለው በአንድ ጊዜ ወደ ፍሳሽ መውረጃ ላይ ላይገባ ይችላል። አሽከርካሪዎች በሚንቀሳቀሱበት ወቅት ለእግርኞች ቅድሚያ የሰጠ፣ እግርኞችን ያከበረ እንቅስቃሴ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።
በውሃ እና በመጸዳጃ ቤት ፍሳሽ እግረኛን ረጭተው ቢሄዱ በፈጸሙት የቸልተኝነት ጥፋት በህግ ይጠየቃሉ። የሞራል ኃላፊነትም እንዳለባቸው ማወቅ አለባቸው።
አሽከርካሪዎች ደረጃውን እና ምቾቱን በተጠበቀ ተሽከርካሪ ውስጥ ሆነው ሲሄዱ የእግርኛውን እንቅስቃሴ እና ሁኔታ ደግሞ ያከበረ፣ የጠበቀ እንቅስቃሴ የማድረግ ግዴታ አለባቸው።
' መሬቱ ነው፣ ዝናቡ አቁሮ ነው፣ ጎርፉ ወደ ፍሳሽ መውረጃ ስላልገባ ነው፣ የኔ ችግር አይደለም፣ የመንገዶች ባለስልጣን ችግር ነው ' ብሎ ማሳበብ ምክንያት አይሆንም፤ ከተጠያቂነት ነጻ አያደርግም።
እንደዚህ አይነት ጥፋት የሰራ ተሽከርካሪ የሰሌዳ ቁጥሩ እስከተያዘ ድረስ ተጠያቂ ነው።
አሽከርካሪው ድርጊቱን ቢክድ እንኳ ተጠያቂ ለማድረግ የተበደለው አካል የተሽከርካሪውን የሰሌዳ ቁጥር ይዞ ለፖሊስ ማመልከት እና ሁኔታውን በቅርበት ያየ የአይን ምስክር ማቅረብ ይኖርበታል።
ድርጊቱን የተመለከቱ ሰዎችም የምስክርነት ቃል መስጠታቸው ግለሰቡን እንደ መተባበር ሳይሆን የፍትህ ስርዓቱን እንደ ማገዝ የሚቆጠር በመሆኑ፣ ምስክርነታቸውን መስጠት አለባቸው።
አሽከርካሪዎች እንደዚህ አይነት ነገሮች በህግ ተጠያቂነትን እንደሚያመጡ አውቀው ህጉን አክብረው ሊንቀሳቀሱ ይገባል። "
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
ነሐሴ 26 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia | 199 |
| 13 | #SaudiArabia
በሳዑዲ አረቢያ በቀጥታ የማኅበራዊ ሚዲያ (ቲክቶክ) ስርጭት ላይ የግድያ ወንጀል ፈጽሟል የተባለ ኢትዮጵያዊ ከአምስት ግብረ አበሮቹ ጋር በሳዑዲ የጸጥታ አካላት መያዛቸውን በሪያድ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታወቀ።
ኤምባሲው እንዳለው፣ በሳዑዲ ድንበርና በረሃማ አካባቢዎች በአንዳንድ ኢትዮጵያውያን መካከል ግጭትና ግድያ መፈጸሙን ተከትሎ ጉዳዩ በቅርበት ሲከታተል ቆይቷል።
በተጨማሪም ጉዳዩን በማኅበራዊ ሚዲያ በማሰራጨትና በማራገብ ተጠርጥረው ከ100 በላይ ግለሰቦች መያዛቸውንና ጉዳያቸውም በሕግ እየታየ መሆኑን ኤምባሲው ገልጿል።
ነሐሴ 26 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia | 190 |
| 14 | በትግራይ እና ዓፋር ክልሎች አዋሳኝ አካባቢ ከ12 ሰዓታት በላይ የቆየ የደን ቃጠሎ ጉዳት አደረሰ።
ቃጠሎው ነሐሴ 25 ቀን 2018 ዓ.ም. በትግራይ ምሥራቃዊ ዞን፣ ፃዕዳ እምባ ወረዳ፣ ከዓፋር ክልል ዳሉል ወረዳ ጋር በሚዋሰነው የሐዊለ ቀበሌ አካባቢ መነሳቱን የዞኑ አስተዳደር አስታውቋል።
በእሳቱ 4.125 ሄክታር የሚገመት ደንና የግጦሽ ሳር መውደሙ ተገልጿል። በተለይም የገራህቲ ጥብቅ ደን በቃጠሎው ጉዳት ደርሶበታል።
የቃጠሎው መንስኤ እስካሁን ያልታወቀ ሲሆን፣ ምክንያቱን ለማጣራት ምርመራ መጀመሩ ታውቋል።
የትግራይ ክልል ምሥራቃዊ ዞን አስተዳደር እንዳስታወቀው በአካባቢው ነዋሪዎች ባህላዊ የእሳት ማጥፊያ ዘዴዎች በመጠቀም ነሐሴ 26 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ 5፡30 ላይ ቃጠሎው ሙሉ በሙሉ ማስቆም ተችሏል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ነሐሴ 26 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia | 165 |
| 15 | Got a Telegram channel with 2,000+ subscribers?
Then it’s time to stop posting for free.
With Ads Galaxy, you can monetize your Telegram channel and start earning from the audience you already have.
Your first $500 could be closer than you think.
Link: https://t.me/Ads_Galaxy_bot?start=REF770190998629F
Monetize now! | 179 |
| 16 | " በሕግ ክርክር ላይ ያለ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ የካሳ ጥያቄ አለበን " - ኢ/ር አሸብር ባልቻ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢ/ር አሸብር ባልቻ ተቋሙ የፕሮጀክቶችን ግንባታ ለማፋጠን በሚያደርገው እንቅስቃሴ ውስጥ የካሳ ክፍያ ጉዳይ ዋነኛውና አስቸጋሪው ማነቆ መሆኑን ገልጸዋል።
እንደ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገለጻ፣ ተቋሙ ለካሳ ክፍያ በቢሊዮን የሚቆጠር ብር እያወጣ የሚገኝ ሲሆን አሁንም ድረስ በሕግ ክርክር ላይ ያለ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ የካሳ ጥያቄ እንዳለበት ይፋ አድርገዋል።
ኢ/ር አሸብር በንግግራቸው ወቅት፣ ድሮ የተሰሩ ፕሮጀክቶች ሳይቀሩ አሁንም ድረስ ለተቋሙ ትልቅ የካሳ ክፍያ ጫና እና ችግር እየፈጠሩ መሆኑን ጠቁመዋል።
በተለይም ካለአግባብ በተለያዩ ክፍሎች የሚሰጡ የድጋፍ ደብዳቤዎች እና የሀሰት መረጃዎች ተቋሙን ላልተገባ የካሳ ክፍያ እያጋለጡት መሆኑን ገልጸዋል።
ዋና ሥራ አስፈፃሚው “ካለአግባብ በየክፍሉ የሚሰጡባቸው ድጋፍና የሀሰት መረጃዎች ላልተገባ የካሳ ክፍያ እንድንጋለጥ ያደረጉት ሁኔታ አለ” ብለዋል።
ከአዲሱ የካሳ አዋጅ ጋር ተያይዞ ያሉ ክፍተቶችንም ሲያስረዱ ደግሞ "አዲሱ አዋጅ ክልሎች ለልማት የሚነሱ ሰዎችን የካሳ ክፍያ ራሳቸው እንዲችሉ የሚደነግግ ቢሆንም፣ የአፈጻጸም መመሪያው ባለመውጣቱ ምክንያት ክልሎች ይህንን ኃላፊነት በአግባቡ መወጣት አልጀመሩም" ነው ያሉት።
ይህ መመሪያ አለመኖሩ ደግሞ ተቋሙ ለሚጀምራቸው አዳዲስ ፕሮጀክቶች ተጨማሪ ማነቆ እየሆነበት እንደሚገኝ ኢ/ር አሸብር ጠቁመዋል።
የካሳ ክፍያ አሠራሩና አዲሱ አዋጅ ወደ መሬት ወርዶ ተግባራዊ ባለመሆኑ ምክንያት የኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ፕሮጀክቶች በታቀደላቸው ጊዜ እንዳይጠናቀቁ እንቅፋት እየሆነባቸው እንደሚገኝ ተገልጿል።
ኢ/ር አሸብር ባልቻ አክለውም “አዲሱ የካሳ ክፍያ አዋጅ የሚያሰራ አይደለም፤ ይልቁንም የበለጠ ማነቆ እየፈጠረ ነው” በማለት ተቋሙን ለተደራራቢ የካሳ ክፍያ የዳረገውን ችግር አመልክተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia | 195 |
| 17 | #France
#Paris
በፈረንሳይ፣ ፓሪስ ከተማ " የግብረሰዶማውያን ማህበር ፕሬዚዳንት " እንደሆነ የተነገረለት እና እራሱም የፖሊስ መኮንን የሆነው ፒየር ፒካቬት የተባለ ግለሰብ በጠርሙስ ተቀጥቅጦ ጉዳት ደርሶበት ሆስፒታል መግባቱን ከፍራንስ 24 ዘገባ ተመልክተናል።
ፒካቬት በፓሪስ መሃል በሚገኘው ማራይስ አካባቢ ከአንድ ባር ከወጣ በኋላ በአንድ ግለሰብ በጠርሙስ መቀጥቀጡ ተገልጿል።
ጥቃቱ በሰውነቱ ላይ በርካታ ጉዳቶችን እንዲደርስበት ያደረገ ሲሆን የውስጥ ደም መፍሰስና የጭንቅላት ቁስልም እንደደረሰበት ተዘግቧል።
ፓሪስ ውስጥ የግብረሰዶማውያን መብት ተሟጋች ማህበር ፕሬዝዳንት የሆነው ፒካቬት እራሱን የፖሊስ መኮንን መሆኑን በመግለጽ የፖሊስ መታወቂያውን ቢያሳይም፣ ተጠርጣሪው ጥቃቱን እንዳላቆመ ተመላክቷል።
በጥቃቱ ወቅትም ጥቃት አድራሹ " አጸያፊ ነው " ስላለው የግብረሰዶማዊነት ተግባር በስድብና በኃይለ ቃል ግለሰቡን ሲናገረው እንደነበር ተመላክቷል።
ተጠርጣሪው በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን ከዚህ በፊት የወንጀል መዝገብ እንደሌለው ተገልጿል።
የፓሪስ ከንቲባ ኤማኑኤል ግሬጎዋር ጥቃቱን አውግዘዋል። " ፓሪስ ለሁሉም ሰዎች የነፃነትና የደህንነት ከተማ ሆና ትቀጥላለች " ሲሉ መናገራቸው ነው የተሰማው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ነሐሴ 26 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia | 172 |
| 18 | በ2018 ዓ.ም የሪሚዲያል ፕሮግራም ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ተማሪዎች ውጤት ይፋ ተደርጓል።
ተማሪዎች https://result.ethernet.edu.et ላይ በመግባት Remedial Examination ከሚለው ስር View Results የሚለውን በመጫንና Username በማስገባት ውጤታቸውን በመመልከት ላይ ይገኛሉ።
ከዚሁ ጋር በተያያዘ " ሙሉ ውጤታችን Disqualified ተደርጓል " ያሉ በርካታ ተማሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታ አቅርበዋል።
ተማሪዎቹ " ይፋ በተደረገው የፈተና ውጤት ላይ የገጠመን ከፍተኛ ችግር እንዲሰማልን እንፈልጋለን " ብለዋል።
ቅሬታቸውን ካቀረቡት መካከል በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የተፈጥሮ እና የማህበራዊ ሳንይንስ ተማሪዎች ውጤታቸው " ሙሉ በሙሉ Disqualified " የተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
ከዚህ በተጨማሪ፥ በደብረ ብርሃን፣ ወሎ፣ አርባ ምንጭ፣ ሚዛን ቴፒ፣ ሰመራ፣ ባህርዳር፣ ወልቂጤ፣ ኦዳ ቡልቱም፣ ጎንደር ዩኒቨርሲቲዎች የሚማሩ የተለያዩ ተማሪዎች ውጤት ላይ ተመሳሳይ ችግር እንደገጠማቸው አመልክተዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር ቅሬታቸውን ተመልክቶ ምክንያቱን በመለየትና በማሳወቅ እንዲሁም በመመርመር አስቸኳይ መፍትሄ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።
ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 03/2018 ዓ.ም የተሰጠውን ሀገር አቀፍ የሪሚዲያል ፕሮግራም ፈተና 53,620 ተፈታኞች መውሰዳቸውን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መግለፁ ይታወሳል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ነሐሴ 26 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia | 170 |
| 19 | ግምታዊ ዋጋቸው ከ300 ሚሊዮን ዶላር በላይ የሆኑ ከ4,500 በላይ የሚሆኑ የከባድ ጭነትና የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካዎች በጂቡቲ ወደብ ከ8 ወራት በላይ ቆመው ይገኛሉ።
አስመጪዎቹ፣ ተሽከርካሪዎቹን ወደ አገር ውስጥ ለማስገባት የገንዘብ ሚኒሰቴርንና የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴርን ይሁንታን ባለማግኘታቸው ለከፍተኛ ኪሳራ እየተዳረጉ መሆኑን ጠቁመው ጠ/ሚ ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) መፍትሔ እንዲሰጧቸው ጥያቄ ማቅረባቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል።
ተሽከርካሪዎቹ በጂቡቲ የቆሙበት ምክንያት ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ጋዝ ማምረት በመጀመሯ ምክንያት ከመስከረም 30 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ፣ በቤንዚንና በናፍጣ የሚሠሩ የጭነትና የሕዝብ ማመላለሻ ተሸከርካሪዎች ወደ አገር ውስጥ እንዳይገቡ፣ የገንዘብ ሚኒሰቴር ባስተላለፈው መመሪያው ምክንያት ነው።
ከመቶ በላይ የሚሆኑ አስመጪ ነጋዴዎች፥ ከትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒሰቴር በተሰጣቸው ተሸከርካሪዎችን የማስገቢያ ፈቃድ መሠረት "በነዳጅና ናፍጣ" የሚሠሩ ተሸከርካዎች ወደ አገር ውስጥ እንዳይገቡ ከመከልከሉ በፊት ግዥ ከሚፈጽሙባቸው ተሸከርካሪዎችን አምራች አገሮች ግዥ ፈጽመው ያስጫኑ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡
ገንዘብ ሚኒስቴር ተሸከርካሪዎች እንዳይገቡ በጻፈው ደብዳቤ (መመሪያ) በግዥ ሒደት ላይ ያሉና ግዥያቸው ተጠናቆ የተጫኑ ተሽከርካሪዎች እስከ 6 ወራት ድረስ ክልከላው ሳይመለከታቸው እንዲገቡ መፍቀዱን ሰነዶቹ ያስረዳሉ፡፡
አስመጪዎቹ ገንዘብ ሚኒስቴር መመሪያ ከማስተላለፉ በፊት በተሰጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ የማስገቢያ ፈቃድ አግኝተው ኤልሲ (LC) በመክፈት ከአምራች አገሮች ጋር የግዥ ውል ፈጽመው ተሸከርካሪዎቹ እንዲጫኑ በማዘዝ፣ አንዳንዶቹ ቀረጥና ታክስ ጭምር በመክፈል ተሸከርካሪዎቹን ወደ አገር ውሰጥ የማሰገባት ሂደት አስጀምረው እንደነበር ለጠ/ሚኒሰትሩ ባቀረቡት የአቤቱታ ደብዳቤ ላይ ገልጸዋል፡፡
ተሸከርካሪዎቹን ከወደብ ማንሳት ያልተቻለው በአንድ በኩል የአፈጻጸምና የማጣራት ሂደት ጊዜ በመውሰዱ ተያያዥ በሆኑ አስተዳደራዊ ክፍተቶች ምክንያት በተፈጠረው ችግር ምክንያት መሆኑን አሰረድተዋል።
አስመጪዎቹ፥ በሕጋዊ አሠራር ሂደት አልሲ (LC) በመክፈትና የባንክ የክፍያ ሥርዓት ለውጭ አቅራቢዎችና አምራቾች የተላለፈ በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠር የውጭ ምንዛሪ የተከፈለባቸው ከ4,500 በላይ ከባድ የጭነትና የሕዝብ ማመላለሻ ተሸከርካሪዎች በጂቡቲ ወደብ ቆመው ፦
1. በቀን ከ90,000 ዶላር ላይ ዲሜሬጅ እየተከፈለባቸው መሆኑን፤
2. በየቀኑ ከሚከፈለው የውጭ ምንዛሪ በተጨማሪ፣ ተሸከርካሪዎቹ በጂቡቲ ባለው ከፍተኛ ሙቀትና ጨው ከፍተኛ የቴክኒክና አካላዊ ጉዳት እየደረሰባቸው መሆኑ፤
3. የዴሜሬጅ ክፍያ ባለመከፈሉ የጂቡቲ መንግሥት ተሸከርካሪዎቹን በጨረታ የመሸጥ አደጋ እንደተጋረጠባቸው፤
4. ተሸከርካሪዎቹን ለመግዛት ከተለያዩ ባንኮች ለወስዱት የውጭ ምንዛሪ በዋስትና ያስያዙት ንብረት (ኮላተራል) በሐራጅ የመሸጥ አደጋ እየደረሰባቸው መሆኑን፣
5. በብሔራዊ ባንክ በForeign Exchange Delinquent List ውስጥ የመመዝገብ አደጋ እያጋጠማቸው መሆኑን፤
...በመጠቆም ጠቅላይ ሚኒሰትሩ መፍትሄ እንዲሰጧቸው ተማጽነዋል፡፡
መንግሥት ተሽከርካሪዎቹ ወደ አገር ውስጥ እንዲገቡ ቢያደርግ፣ ከታክስና ቀረጥ (ባለፉት ወራቶች) ከ1.8 ቢሊዮን ብር በላይ ያገኝ የነበረውን ገቢ ማጣቱን በጉምሩክ ኮሚሽን በተጣራ መረጀ መረጋገጡን አክለዋል።
ከተሽከርካሪዎቹ ጋር በተያያዘ ጉምሩክ ኮሚሽንም በጂቡቲና በአገር ውስጥ ስለቆሙት ተሸከርካሪዎች በሚመለከት ግንቦት 11/2018 ዓ.ም. ለገንዘብ ሚኒስቴር ደብዳቤ ፅፎ ነበር።
በቤንዚንና ናፍጣ የሚሠሩ የጭነትና የሕዝብ ማመላለሻ ተሸከርካሪዎች፣ ከመስከረም 30 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እንዳይገቡ መከልከሉን፣ ቀደም ብሎ በሂደት ላይ የነበሩትንና በተፈቀደው 6 ወራት ውስጥ ጂቡቲ ደርሰው የቆሙ ተሸከርካዎችን በሚመለከት መፍትሔ እንዲሰጠው ጠይቋል።
ኮሚሽኑ ከባድ የጭነትና የሕዝብ ማመላለሻ አስመጪዎች ከትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒሰቴር የማስገቢያ ፈቃድ እንደተሰጣቸው በደብዳቤው አረጋግጧል፡፡
ግዥ የፈጸሙ፣ ቀረጥና ታክስ የከፈሉና ትራዚት የተፈቀደላቸው፤ ማስገቢያ ፈቃድ ተሰጥቷቸው ዲክላራሲዮን ያልቀረበባቸው መኖራቸውን፣ እንዲሁም አገር ውስጥ ገብተው በጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች በኩል የማስገቢያ ፈቃዶች ከትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር በኩል ተጣርተው እንዲላኩ በተደጋጋሚ ቢጠይቅም ምላሽ ማግኘት እንዳልቻለ ገልጿል፡፡
ተሸከርካሪዎቹ በጂቡቲ ፍሪ ዞን ለረዥም ጊዜ በመቆየታቸው፣ ከፍተኛ የዲሜሬጅ ክፍያ እየተጠየቀባቸው መሆኑንና ወደ አገር ውሰጥ ማምጣት ካልተቻለ የጂቡቲ መንግሥት በጨረታ እንደሚሸጣቸው ማሰጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው አስመጪዎች እንደነገሩት ኮሚሽኑ አረጋግጧል፡፡
በመሆኑም ተሽከርካሪዎቹ ወደ አገር ውስጥ ገብተው በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር በኩል ማረጋገጫ እስከሚሰጣቸው ድረስ በጉምሩክ ቁጥጥር ሥር እንዲቆዩ አስመጪዎች መጠየቃቸውን ኮሚሽኑ ለገንዘብ ሚኒስቴር በጻፈው ደበዳቤ አስታውቋል።
በጂቡቲ ከቆሙት ተሸከርካሪዎች ውስጥ አብዛኛዎቹ ቀረጥና ታክስ የተከፈለባቸው መሆኑን፣ አገር ውስጥ ገብተው ያለተለቀቁትና ከሌሎች ተመሳሳይ ተሽከርካሪዎች መንግሥት ከ1.8 ሚሊዮን ብር በላይ ከቀረጥና ታክስ ሊሰበስብ እንደሚችል ኮሚሽኑ አረጋግጦ፣ በተሰጣቸው የማስገቢያ ፈቃድ መሠረት የጉምሩክ ሥነ ሥርዓት ተፈጽሞባቸው ወደ አገር ውሰጥ እንዲገቡ ውሳኔ እንዲሰጥበት ገንዘብ ሚኒስቴርን የጠየቀ ቢሆንም ምላሽ አላገኘም።
ጉምሩክ ኮሚሽን ነሐሴ 2/2018 ዓ.ም. በድጋሚ ለገንዘብ ሚኒስቴር በጻፈው ደብዳቤ፣ ቀደም ብሎ በግንቦት ወር የተጻፈውን ደብዳቤ አስታውሶ፣ አስመጪዎቹ ከተለያዩ ንግድ ባንኮች የባንክ ፈቃድ አግኝተው የትራንዚት ፈቃድ ያላቸውና የሌላቸው መሆናቸውን ጠቁሞ፤ አገር ውስጥ ያለገቡ በነዳጅ የሚሠሩ፦
- ከባድ የጭነትና የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡሶች፣
- በአገር ውስጥ ለመገጣጠም ተገዝተው አገር ውስጥ ያልገቡ (CKD እና SKD) ተሸከርካሪዎች፣
- በመልቲ ሞዳል ሥርዓት ተጓጉዘው በአገር ውስጥ ባሉ የተለያዩ ደረቅ ወደቦች ውስጥ የሚገኙ ተሸከርካሪዎችን ማስተናገድ ስለሚቻልበት ሁኔታ ውሳኔ አንዲሰጠው ጠይቋል።
አስመጪዎቹም በተደጋጋሚ ገንዘብ ሚኒስቴርን ተመላልሰው በአካልና በደብዳቤ ቢጠይቁትም፣ አንድ ጊዜ የሚመለከተው ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴርን መሆኑንና እሱን እንደማይመለከተው በመግለጽ ሌላ ጊዜ ደግሞ ጉዳያቸው የሚፈታው በጠ/ሚ ጽ/ቤት በኩል እንደሆነ ከመግለጽ ባለፈ መፍትሔ የሚሰጣቸው በማጣታቸው ጠ/ሚ ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) መፍትሄ እንዲሰጧቸው ጠይቀዋል።
አስመጪዎቹ ከባንኮች ለወሰዱት ብድር ያስያዟቸው ንብረቶች ለጨረታ ሊቀርቡ እንደሚችሉና በስራቸው ያሉ በሺዎች የሚቆጠሩ ሠራተኞችም ሥራ ሊያጡ እንደሚችሉ በማመልከት የማስገቢያ ጊዜው እንዲራዘምና ተሽከርካሪዎቹ ወደ ኢትዮጵያ ገብተው በጉምሩክ ኮሚሽን ቁጥጥር ስር እንዲሆኑ ጠይቀዋል።
በተጨማሪም፣ የኢትዮጵየ ብሔራዊ ባንክ በ " Foreign Exchange Delinquent List " እንዳያስገባቸው እንዲያርጉላቸው ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)ን ተማጽነዋል።
ከተቻለ በአካል ቀርበው በተሟላ ማስረጃ በአጭሩ እንዲያስረዷቸውና እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል፡፡
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሪፖርተር ጋዜጣ ነው።
ነሐሴ 25 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia | 233 |
| 20 | " በድርቁ ምክንያት በደረሰባቸው ከፍተኛ የኑሮ ጫና እና የተስፋ መቁረጥ ስሜት ሰባት ወንዶች በአንድ ቀን መርዝ ጠጥተው ራሳቸውን ለማጥፋት ሙከራ አድርገው የሁለቱ ህይወት አልፏል " - ጃን አሞራ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት
• ከ4 ሺህ በላይ ነፍሰጡርና አጥቢ እናቶች ለምግብ እጥረት ተጋልጠዋል።
• ከ3 ሺህ በላይ እንስሳት በመኖ እና በውሃ እጥረት ምክንያት ሞተዋል።
(ቲክቫህ ኢትዮጵያ)
በሰሜን ጎንደር ዞን በጃና ሞራ ወረዳ የተከሰተው አስከፊ ድርቅ በአካባቢው ማህበረሰብ ላይ መጠነ ሰፊ ሰብአዊ ቀውስ እያስከተለ እንደሚገኝ ተገልጿል።
በወረዳው ስር ከሚገኙ 38 ቀበሌዎች መካከል 18ቱ በድርቅ የተጎዱ ሲሆን፣ በዚህም ምክንያት ከ96 ሺህ በላይ ሰዎች ለከፋ የምግብ እና የውሃ እጥረት መጋለጣቸውን የወረዳው ግብርና ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ሷሊህ ሃሰን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
በአካባቢው የተከሰተው የዝናብ እጥረት ለችግሩ ዋነኛ መንስኤ መሆኑን ሃላፊው አመልክተዋል።
በአካባቢው በተለምዶ በግንቦት ወር መጀመር የነበረበት ዝናብ እስከ ሃምሌ 19 ቀን ድረስ በመዘግየቱ አርሶ አደሩ ሰብሉን በወቅቱ ለመዝራት አልቻለም።
በወረዳው ካሉ አጠቃላይ 38 ቀበሌዎች ውስጥ 5ቱ ለመጀመርያ ጊዜ ዝናብ ያገኙት ሐምሌ 19 ቀን ሲሆን ክረምት ከገባ 4 ቀን ብቻ ዝናብ ያገኙ 5 ቀበሌዎችም ስለመኖራቸው ጠቁመዋል።
ከተዘራው 25 ሺ ሄክታር በላይ መሬት ውስጥም ከ8 ሺህ 1 መቶ ሄክታር በላይ የሚሆነው ጭራሽ ሳይበቅል የቀረ ሲሆን፣ በተለይም የጤፍ ሰብል ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ መውደሙን ታውቋል ይህም በአካባቢው ከፍተኛ የምግብ ዋስትና እክል መፍጠሩ ተገልጿል።
ተዘርቶ ከበቀለው ሰብልም 4 ሺ ሄክታር የሚሆነው የጠወለገ ነው ያሉ ሲሆን በአጠቃላይ ወረዳው ካለው 26 ሺ 659 ሄክታር የእርሻ መሬት ላይ የበቀለው 12 ሺ 126 ሄክታር የሚሆነው ማሳ የተጎዳ መሆኑን እና ምናልባት ለዘር እና ለመኖ ካልሆነ በቀር ለምግብነት በማይሆን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
ይህ የድርቅ አደጋ በሰው ህይወትና በስነ-ልቦና ላይ እያደረሰ ያለው ጉዳት እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱንም አቶ ሷሊህ ነግረውናል።
በወረዳው ከሚገኙ ቀበሌዎች አንዱ በሆነው በዋሰል ቀበሌ ውስጥ በድርቁ ምክንያት በደረሰባቸው ከፍተኛ የኑሮ ጫና እና የተስፋ መቁረጥ ስሜት ሰባት ወንዶች በአንድ ቀን ውስጥ መርዝ ጠጥተው ራሳቸውን ለማጥፋት ሙከራ ማድረጋቸው ተሰምቷል።
ከእነዚህም መካከል የሁለቱ ህይወት ወዲያውኑ ሲያልፍ፣ አምስቱ በህክምና እርዳታ መተርፋቸውን የጽ/ቤቱ ሃላፊ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
ከምግብ እጥረት ጋር ተያይዞም በአሁኑ ወቅት 71 ህጻናት በከፍተኛ የምግብ እጥረት፣ 5029 ህጻናት ደግሞ በመካከለኛ ደረጃ የምግብ እጥረት ላይ ይገኛሉ።
በተጨማሪም ከ4 ሺህ በላይ ነፍሰጡርና አጥቢ እናቶች ለተመሳሳይ ችግር ተጋልጠዋል።
የወንዞች ፍሰት ከ90 በመቶ በላይ በመቀነሱ፣ ህዝቡ ቆሻሻ ውሃ ለመጠጣት ተገዷል። በዚህም ምክንያት እንደ እከክ፣ ወባ እና የደም ተቅማጥ ያሉ ተላላፊ በሽታዎች በወረዳው በስፋት እየተከሰቱ መሆኑ ተመላክቷል።
እስካሁን ባለው መረጃ ከ3 ሺህ በላይ እንስሳት በመኖ እና በውሃ እጥረት ምክንያት የሞቱ ሲሆን፣ ቁጥራቸው ወደ 4 ሺህ የሚጠጉ እንስሳት ደግሞ የተሻለ ሳርና ውሃ ፍለጋ ወደ ጎረቤት አካባቢዎች ተሰደዋል።
በተጨማሪም የአባ ሰንጋ (Anthrax) በሽታ በአካባቢው መከሰቱ የታወቀ ቢሆንም፣ ወረዳው ላይ ምንም አይነት የመድሃኒት ክምችት ባለመኖሩ እና በክልል ደረጃም መድሃኒት ጠፍቶ በገንዘብ ለመግዛት ባለመቻሉ የእንስሳቱ እልቂት ሊባባስ እንደሚችል ስጋት ተፈጥሯል።
እስካሁን ድረስ የመንግስትም ሆነ የሌሎች ተራድኦ ድርጅቶች ድጋፍ በቂ አለመሆኑን የገለጹት አቶ ሷሊህ፣ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በሁለት ቀበሌዎች ላይ ጥናት መጀመሩን ጠቅሰዋል።
ይሁን እንጂ ችግሩ ካለው ስፋትና ጥልቀት አንጻር አፋጣኝ የምግብ፣ የመድሃኒት እና የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት ካልተመቻቸ ሁኔታው ወደማይመለስ ጥፋት ሊያመራ እንደሚችል በማሳሰብ፣ የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ አስቸኳይ ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ነሐሴ 24 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia | 283 |
