ch
Feedback
ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ

ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ 

前往频道在 Telegram

ስለቴክኖሎጂ አዳዲስ መረጃዎች እና ሶፍትዌር የሚያገኙበት ቻናል፡፡ 🕳Professional Hack Tips and tricks 💡Cracked Softwares 🌎 ዘመኑ የቴክኖሎጂ ነው ከዘመኑ ጋር አብረው ይዘምኑ YouTube channel https://youtube.com/c/MkTechZoneETH

显示更多

📈 Telegram 频道 ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ  的分析概览

频道 ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ  (@computer_android_tricks) 是活跃参与者。目前社区聚集了 11 983 名订阅者,在 教育 类别中位列第 17 269,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 838 位。

📊 受众指标与增长动态

自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 11 983 名订阅者。

根据 04 三月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -107,过去 24 小时变化为 0,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 0%。内容发布后 24 小时内通常能获得 N/A% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 0 次浏览,首日通常累积 0 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 0。

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“ስለቴክኖሎጂ አዳዲስ መረጃዎች እና ሶፍትዌር የሚያገኙበት ቻናል፡፡ 🕳Professional Hack Tips and tricks 💡Cracked Softwares 🌎 ዘመኑ የቴክኖሎጂ ነው ከዘመኑ ጋር አብረው ይዘምኑ YouTube channel https://youtube.com/c/MkTechZoneETH”

凭借高频更新(最新数据采集于 05 三月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 教育 类别中的关键影响点。

11 983
订阅者
无数据24 小时
-337 夊
-10730 夊
帖子存档
#NewsAlert ‼️ #Coronavirus የዩናይትድ ኪንግደም አልጋወራሽ ልዑል ቻልረስ የኮሮና ቫይረስ ተገኘባቸው። INDEPENDENT

🖍COVID19 - ጠቅለል ያለ መረጃ‼️ የኮቪድ-19 የመጀመሪያ ኬዝ ከተገለፀበት ጊዜ ጀምሮ ያሉ ቁጥራዊ መረጃዎች 🖍በቫይረስ የተጠቁ ብዛት: 408,892 🖍በቫይረሱ የተከሰተው ሞት : 18,259
🖍COVID19 - ጠቅለል ያለ መረጃ‼️ የኮቪድ-19 የመጀመሪያ ኬዝ ከተገለፀበት ጊዜ ጀምሮ ያሉ ቁጥራዊ መረጃዎች 🖍በቫይረስ የተጠቁ ብዛት: 408,892 🖍በቫይረሱ የተከሰተው ሞት : 18,259 🖍በቫይረሱ ተይዘው ያገገሙ: 107,073 🔶በጣሊያን ዛሬ በ24 ሰዓት ውስጥ 743 ዜጎቿን አታለች። በስፔን በተመሳሳይ 24 ሰዓት ውስጥ 489 በቫይረሱ ምክንያት ዜጎቿን በሞት ተነጥቃለች። 🔶የሕንዱ ጠ/ሚ ናሬንድራ ሞዲ በህንድ እየተስፋፋ ያለውን የኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] ወረርሽኝ ለመግታት 1̀.2 ቢሊዮን ዜጎች ለ21 ቀናት በቤት ውስጥ እንዲቆዩ ማወጃቸውን ቢቢሲ ዘግቧል:: 🔶በኬንያ የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ቁጥር 25 ደረሰ። የኬንያ ጤና ሚኒስቴር ዛሬ በሰጠው መግለጫ ተጨማሪ 9 ሰዎች ቫይረሱ እንደተገኘባቸው ይፋ አድርጓል። 🔶ዛሬ ሱዳን 1 የኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] ተጠቂ ማግኘቷን ሪፖርት አድርጋለች። ሀገሪቱ የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመግታት ሁሉም ድንበሮቿ እንዲዘጉ ትዕዛዝ አስተላልፋለች። 🔶 #የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል ላልተወሰነ ጊዜ ወደ ቤተሰቦቻቸው እንዲመለሱ ተወስኗል።ተማሪዎች ወደ ቤተሰቦቻቸው ሲመለሱም በትራንስፖርት እጥረት እና መሰል ችግሮች እንዳይስተጓጎሉ ዩኒቨርሲቲዎች ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስበዋል። #share #share #መረጃዎችን ለወዳጅዎ ያጋሩ። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

Rest in home🏠 or rest in peace⚰ ምርጫው የራሳችን ነው!! ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

ውድ Tech Zone ተከታታዮች አሁን ባለው ወቅታዊ ሁኔታ ምክንያት የኮሮና ቫይረስን አሳሳቢነት እየጨመረ ስለመጣ የተጣሩ መረጃዎችን የምናደርሳችሁ ስለሆነ ለጊዜው በፊት የነበሩን ትምህርቶች በመሃል የምንለቅላችሁ ይሆናል። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

#ታዋቂው ካሜሮናዊ የጃዝ ሙዚቃ ንጉሥ ማኑ ዲባንጎ በኮሮና ቫይረስ ህይወቱ ማለፉ ተሰምቷል። ካሜሮናዊው ሳክስፎኒስትና የጃዝ ሙዚቃ ንጉስ ማኑ ዲባንጎ በ86 ዓመቱ ነው በኮሮና ቫይረስ ተይዞ በፈረንሳይ
#ታዋቂው ካሜሮናዊ የጃዝ ሙዚቃ ንጉሥ ማኑ ዲባንጎ በኮሮና ቫይረስ ህይወቱ ማለፉ ተሰምቷል። ካሜሮናዊው ሳክስፎኒስትና የጃዝ ሙዚቃ ንጉስ ማኑ ዲባንጎ በ86 ዓመቱ ነው በኮሮና ቫይረስ ተይዞ በፈረንሳይ ፓሪስ ሆስፒታል የህክምና ክትት ላይ ሳለ መሞቱ የተነገረው። ዓለምን ያሳሰበው የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ተከትሎ የማኑ ዲባንጎን የቀብር ሥነ ሥርዓት ቤተሰቡ ጨምሮ ከ20 የማይበልጡ ሰዎች በተገኙበት እንደሚከወንና አሁን ላይ ያለው ሁኔታ ሲስተካከል የማስታወሻ ሥነ ሥርዓት እንደሚሰናዳ ቤተሰቦቹ አስታውቀዋል. ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

በኮሮና ቫይረስ ስጋት ምክንያት ዝምቧቤ ለመጪዎቹ ሁለት ወራት ሰርግ ከልክላለች ። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━
በኮሮና ቫይረስ ስጋት ምክንያት ዝምቧቤ ለመጪዎቹ ሁለት ወራት ሰርግ ከልክላለች ። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

#COVID19 "ዩንቨርሲቲዎች ተማሪዎቻቸውን እንዲያሰናብቱ ተወስኗል" - የሳይንስ እና የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ዩንቨርሲቲዎች ተማሪዎቻቸውን እንዲያሰናብቱ መወሰኑን የሳይንስ እና የከፍተኛ ትምህር
#COVID19 "ዩንቨርሲቲዎች ተማሪዎቻቸውን እንዲያሰናብቱ ተወስኗል" - የሳይንስ እና የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ዩንቨርሲቲዎች ተማሪዎቻቸውን እንዲያሰናብቱ መወሰኑን የሳይንስ እና የከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል። ውሳኔው የተወሰነው በኮሮና ቫይረስ መክንያት ተማሪዎች የከፋ ችግር እንዳይደርስባቸው እንደሆነ ተገልጿል። ዩንቨርሲቲዎች ተማሪዎቻቸውን በራሳቸው ትራንስፖርት ወጪ አጓጉዘው ወደ የቤተሰቦቻቸው አንዲያደርሱ መወሰኑን በሚኒስቴሩ የኮሙኑኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ደቻሳ ጉርሙለኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ተናግረዋል። ዩንቨርሲቲዎቹ ተማሪዎቹን የሚያሰናብቱት ለምን ያህል ጊዜ ነው? በሚል ከሬድዮ ጣቢያው ለተነሳላቸው ጥያቄ አቶ ደቻሳ አሁን ላይ ለዚህ ያህል ጊዜ ማለት የሚከብድ በመሆኑ የቫይረሱ ስርጭት ሰዎችን በማይጎዳበት ጊዜ ለተማሪዎቹ ጥሪ ይደረግላቸዋል፣ አስከዛው ግን ከቤተሰቦቻቸው ጋር ይቆያሉ ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል። ምንጭ፦ ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

#DrLiaTadesse - በኮሮና ቫይረስ የተያዘ አንድ ተጨማሪ ሰው በመገኘቱ አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 12 ደርሰዋል። - ይህ ታማሚ የ34 ዓመት ኢትዮጵያዊ ነው፤ መጋቢት 10 ነው ከዱባይ ወ
#DrLiaTadesse - በኮሮና ቫይረስ የተያዘ አንድ ተጨማሪ ሰው በመገኘቱ አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 12 ደርሰዋል። - ይህ ታማሚ የ34 ዓመት ኢትዮጵያዊ ነው፤ መጋቢት 10 ነው ከዱባይ ወደ ኢትዮጵያ የገባው። - ግለሰቡ የህመም ምልክት ያሳየው መጋቢት 13/2012 ዓ/ም ነው። በተደረገለት ምርመራ በቫይረሱ መያዙ ተረጋግጣል። - ከታማሚው ጋር ግንኙነት የነበራቸው 15 ሰዎች በክትትል ላይ ይገኛሉ። #መረጃዎችን ለወዳጅዎ ያጋሩ። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

🖍የውጪ ዜና-Corona Virus‼️ ‼️ #ሰበር : የቶክዮ 2020 ኦሎምፒክ ኮረና ቫይረስ ምክንያት መራዘሙን ኢንተርናሽናል ኦሎፒክ ኮሚቴ አስታውቋል። ኦሎምፒኩ መቼ እንደሚካሄድ በቀጣይ ድርጅቱ መ
🖍የውጪ ዜና-Corona Virus‼️ ‼️ #ሰበር : የቶክዮ 2020 ኦሎምፒክ ኮረና ቫይረስ ምክንያት መራዘሙን ኢንተርናሽናል ኦሎፒክ ኮሚቴ አስታውቋል። ኦሎምፒኩ መቼ እንደሚካሄድ በቀጣይ ድርጅቱ መግለጫ እንደሚያወጣ ገልጿል። ‼️ #በጣልያን በ24 ሰዓት ውስጥ ተጨማሪ 602 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መሞታቸው ሪፖርት ተደርጓል። አጠቃላይ የሟቾች ቁጥርም 6,078 ደርሷል። በቫይረሱ የተጠቁትም 63,928 ደርሰዋል። ‼️ #አሜሪካ ኒውዮርክ እና ዋሽንግተንን በመሳሰሉ ከተሞች የበረታውን ወረርሽኝ ለመቆጣጠር ጥብቅ ያለቻቸውን እርምጃዎች እየወሰደች ነው። á‰ áŠ’á‹ ዮርክ ከተማ ብቻ በኮሮና መያዛቸው የተረጋገጠ ሰዎች ቁጥር ከ20 ሺሕ በላይ ደርሷል። ‼️ #የጀርመኗ መራሄተ መንግሥት #አንጌላ መርክል በምርመራ ከኮሮና ቫይረስ ነጻ መሆናቸው መረጋገጡን የጀርመን መንግሥት ቃል አቀባይ ተናገረ። ‼️#SouthAfrica የኮሮና ስርጭትን ለመግታት ከመጪው ሀሙስ ጀምሮ ለ21 ቀናት ማንኛውም ዜጋ አስፈላጊ ለሆኑ ጉዳዮች ካልሆነ በቀር ከቤቱ እንዳይወጣ የደቡብ አፍሪካ መንግስት ትዕዛዝ አስተላለፈ። በደቡብ አፍሪካ 402 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ እንደተያዙ ይታወቃል:: ‼️ #ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም “በኮሮና ቫይረስ የተያዘው የመጀመሪያ ሰው ሪፖርት ከተደረገ በኋላ፤ የመጀመሪያዎቹ 100ሺህ ሰዎች በቫይረሱ ለመያዝ 67 ቀናት ወስደዋል። ቀጣዮቹ 100ሺህ ሰዎች የተያዙት በ11 ቀናት ውስጥ ሲሆን፤ ሦስተኛ 100ሺህ ሰዎች የተያዙት ደግሞ በ4 ቀናት ውስጥ ነው” ‼️ #ስፔን 4517 አዲስ ተጠቂዎች የተገኘባት ሲሆን 462 አዲስ ሞት ከትናንት ጀምሮ ባለው ጊዜ ተመዝግቧል። እስካሁን በቫይረሱ የተጠቁት ቁጥር 33,089 ሲሆን የሟቾች ቁጥር ደግሞ 2182 ደርሷል ። ━━━━━━ @Computer_Android_tricks

#የ24_ሰዓት_የኮሮና_ቫይረስ_ስርጭትና_አጠቃላይ_ኬዝ ▪️▪️▪️▪️▪️▪️▪️▪️▪️▪️▪️▪️▪️ ✔️ሰኞ መጋቢት 14 እስከ ጠዋቱ 02:08 ሰዓት ድረስ ✅እንደምን አደራችሁ ክቡራን የሰው ልጆች ፣ አለማችን 7.7 ቢልየን ሰዎች እንዳሉባት የሚገመት ሲሆን ወሬው ሁሉ ኮሮና ቫይረስ ሆኗል ፣ ምክንያቱም 192 ሀገራትን አዳርሷልና ✅32,440 ሰዎች በ24 ሰዓት ብቻ በቫይረሱ ተጠቅተዋል ✅1,631 ሰዎችም በ24 ሰዓት ውስጥ ብቻ በቫይረሱ ሞተዋል ✅338,879 ሰዎች እስካሁን በኮሮና ቫይረስ ተጠቅተዋል ✅14,688 ሰዎች ደግሞ በቫይረሱ ምክንያት ሞተዋል ✅99,011 ሰዎች አገግመው ከሆስፒታል ወጥተዋል ✅225,180 ሰዎች አሁን ላይ ቫይረሱ ይገኝባቸዋል ✅214,627 ሰዎች በመካከለኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ ✅10,553 ሰዎች ደግሞ በአሳሳቢ ደረጃ ላይ ናቸው ✅ ባለፉት 24 ሰዓት በርካታ ሰው የሞተባቸውን 5 ሃገራትን ከታች ተመልከቱ። እንዲሁም በጠቅላላው እስካሁን ያለውን የቫይረሱን ስርጭት በምስሉ ላይ ታገኛላችሁ። በተከታይነት በአፍሪካ ያለውን ወቅታዊ ቁጥራዊ መረጃን ፖስት እናደርጋለን ይጠብቁን። ─────────────────────────── 🇮🇹 በጣልያን ቫይረሱ አሁንም የበርካታ ሰዎችን ሕይወት እየቀጠፈ ይገኛል። ባለፉት 24 ሰዓት ብቻ 651 ሰዎች ሲሞቱባት +5,560 ሰዎች ደግሞ በቫይረሱ ተጠቅተዋል። ─────────────────────────── 🇪🇸 ስፔን ባለፉት 24 ሰዓት በርካታ ሰው የሞተባት 2ኛዋ ሀገር ነች +391 ሰዎች ሲሞቱባት +3,272 አዳዲስ ኬዞችንም አስተናግዳለች። በጠቅላላው 25,496 ኬዞችን አስተናግዳ 1,378 ሰዎች ሞተዋል። ─────────────────────────── 🇮🇷 በኢራን ባለፉት 24 ሰዓት ብቻ 129 ሰዎች ሞተው +1,028 አዳዲስ ተጠቂዎችንም አስተናግዳለች። ─────────────────────────── 🇺🇸 ቫይረሱ በአሜሪካ ከፍተኛ የሆነ አስፈሪ መስፋፋት ላይ ይገኛል። ያባለፉት 24 ሰዓት ብቻ +9,339 በቫይረሱ የተያዙ ሰዎችን እንዳገኘች ስታሳውቅ 117 ሰዎች ደግሞ ሞተውባታል። ─────────────────────────── 🇬🇧 በብሪታኒያ ባለፉት 24 ሰዓት ብቻ 56 ሰው የሞተ ሲሆን +1,035 ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል። በጠቅላላው 5,018 ሰዎች ተጠቅተው 233 ሰዎች ሞተዋል። ─────────────────────────── 🇫🇷 ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በርካታ ሰው የሞተባት 5ኛ ሀገር ነች 112 ሰዎች ሲሞቱባት 1,847 አዲስ ኬዝ አስተናግዳለች። ─────────────────────────── 🔴 በጠቅላላ በኮሮና ቫይረስ ብዙ ሰው የሞተባቸው ሀገራት 🇮🇹 5,476 ጣልያን 🇨🇳 3,270 ቻይና 🇪🇸 1,772 ስፔን 🇮🇷 1,685 ኢራን 🇫🇷 674 ፈረንሳይ ─────────────────────────── 🔵 በርካታ የኮሮና ቫይረስ ኬዝ ያስተናገዱ ሀገራት 🇨🇳 81,093 ቻይና 🇮🇹 59,138 ጣልያን 🇺🇸 34,717 ዩናይትድ ስቴትስ 🇪🇸 28,768 ስፔን 🇩🇪 24,873 ጀርመን ─────────────────────────── #የጥንቃቄ_መረጃዎችን_ሁሌም_እንተግብር ✅ እባካችሁ እጅ የማስታጠብ ፋሽን ላይ ያለን አታስመስሉት ማንም ሰው ማስታጠቢያ ይዞ በቅርበት እጅ ማስታጠብ አደጋ አለው። ላስታውሳችሁ ቫይረሱ የሚተላለፈው እጅ በመታጠብ ብቻ አይደለም ከሚያስሉ እና ከሚያስነጥሱ ሰዎች ቢያንስ 2 የአዋቂ እርምጃ መራቅ አለብን። ተቀራርበን ከማስታጠብ ይልቅ አነስተኛ ጀሪካን ላይ ቧንቧ በመግጠም ሰው እራሱ እየሔደ እንዲታጠብ እናድርግ። በዚህ መሐል በቫይረሱ የመጠቃት ዕድል ያለው የሚያስታጥበው ሰው መሆኑን ልብ በሉ። √ አስፈላጊውን ጥንቃቄ በማድረግ የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን በጋራ እንከላከል። #በቅድመ_ጥንቃቄ_እና_በፀሎት_እንበርታ √ መረጃ አይናቅም ስለዚህ ለሌሎች እንዲደርስ ሼር አድርጉ √ ቁጥራዊ መረጃዎቹን ያገኘሁት :- ስፒዶሜትር ዌብሳይት ላይ ነው #መረጃዎችን ለወዳጅዎ ያጋሩ። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

‍ ‍ ኢመደኤ “የኢትዮጵያ የተቀናጀ የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ19) መከታተያና መቆጣጠሪያ ሲስትም” አዘጋጀ አዲስ አበባ፡ መጋቢት 13 ቀን 2012 ዓ/ም: ኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ19) ሥርጭትን ለመግታት የምታደርገውን ጊዜ የማይሰጥ ርብርብ ለማገዝ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ (ኢመደኤ) “የኢትዮጵያ የተቀናጀ የኮቪድ19 መቆጣጠሪያ ስርአት - Ethiopian COVID-19 Monitoring Platform” አዘጋጅቷል:: ኤጀንሲው ያዘጋጀው ሲስተም የተለያዩ መረጃዎችን የሚሰጥ ሲሆን፤ ከእነዚህ መካከልም፦ • ሃገራዊ፣ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ የሆኑ ወቅታዊ የ covid-19 መረጃዎችን ለመከታተል፤ • ገላጭ በሆኑ የቦታ ማሳያ መረጃዎች ለማየት፤ • ስለ covid-19 ምልክቶች፣ ጥንቃቄዎች፣ ህክምናዎች እና ሌሎች መረጃዎችን ለማግኘት፤ • ዜጎች በራሳቸውም ሆነ በሌሎች ላይ የሚያጋጥሟቸውን ጥርጣሬዎች ሪፖርት ለማድረግ፤ • የተለያዩ ሙያ እና አቅም ያላቸውን በጎ ፈቃደኞች ለመመዝገብ፤ • የተለያዩ እርዳታዎችን (በአይነትም ሆነ በገንዘብ) ለመሰብሰብ፤ • ለማህበረሰቡ የሚጠቅሙ መረጃ ያላቸውን ምንጮችን (ሊንኮችን) ለመጠቆም፤ • አስፈላጊ የሆኑ መሰረተ-ልማቶችን (ሆስፒታል፣ ፋርማሲ፣ ፖሊስ ጣቢያ) ለማመላከት፤ እንዲሁም ሌሎችን መረጃዎች ለማሰራጨት የሚያገለግል ሲስተም ነው፡፡ የመከላከያና መቆጣሪያ ሲስተሙ ቫይረሱ ሊያስከትል የሚችለውን የከፋ ሁኔታ ከወዲሁ ለመከላከልና ጥንቃቄ ለማድረግ በሚል የተዘጋጀ ሲሆን፤ በነገው ዕለት መጋቢት 14 ቀን 2012 ዓ/ም የጤና ሚኒስቴር እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በይፋ አገልግሎት መስጠት የሚጀምር ይሆናል፡፡ በዚሁ አጋጣሚ የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ19) ስርጭትን ለመግታት በሚደረገው ሃገራዊ ርብርብ ላይ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኢጀንሲ-ኢመደኤ የሚያደርገውን አስተዋጽኦ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ይገልጻል፡፡ #መረጃዎችን ለወዳጅዎ ያጋሩ። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

😭Feeling sad😭 በመጨረሻም ጣሊያን እጇን ሰጠች «በአካልም በአእምሮም ሞተናል፣ከዚህ በሁዋላ ምን እንደምናደርግ አናውቅም በምድር ሁሉንም ሞከርን መፍትሄ የለም ከዚህ በኋላ ከሰማይ እንጠብቃለ
😭Feeling sad😭 በመጨረሻም ጣሊያን እጇን ሰጠች «በአካልም በአእምሮም ሞተናል፣ከዚህ በሁዋላ ምን እንደምናደርግ አናውቅም በምድር ሁሉንም ሞከርን መፍትሄ የለም ከዚህ በኋላ ከሰማይ እንጠብቃለን» #መረጃዎችን ለወዳጅዎ ያጋሩ። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ቁጥር 11 ደረሰ! - አንደኛው ታማሚ የ28 ዓመት ወጣት ኢትዮጵያዊ ሲሆን በሽታውን ሪፖርት ወዳደረጉ ሀገራት ቤልጂየም እና ኔዘርላንድ ተጉዞ የነበረና መጋቢት 5/
በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ቁጥር 11 ደረሰ! - አንደኛው ታማሚ የ28 ዓመት ወጣት ኢትዮጵያዊ ሲሆን በሽታውን ሪፖርት ወዳደረጉ ሀገራት ቤልጂየም እና ኔዘርላንድ ተጉዞ የነበረና መጋቢት 5/2012 ዓ/ም ከቤልጂየም ወደ ኢትዮጵያ የገባ ነው። - ሁለተኛው ግለሰብ የ34 ዓመት ኢትዮጵያዊ ሲሆን መጋቢት 10/2012 ዓ/ም ከዱባይ ወደ ኢትዮጵያ ሲገባ በቦሌ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ በሚደረገው የመንገደኞች የሙቀት ልየታ የኮሮና ቫይረስ ምልክቶች በማሳየቱ በለይቶ ማቆያ እንዲቆዩ በማድረግ በላብራቶሪ ምርመራ በኮሮና ቫይረስ መያዙ ተረጋግጧል። #መረጃዎችን ለወዳጅዎ ያጋሩ። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

የዓለም ጤና ድርጅት /WHO/ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም ለወጣቶች መልዕክት አስተላልፈዋል። ያዳምጡ! #መረጃዎችን ለወዳጅዎ ያጋሩ። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

ሞባይሎን ማጽዳት አይርሱ! የእጅ ስልኮችን የራሳቸው ማጽጃ ያላቸው ሲሆን ይህንን ማግኘት ካልቻሉ ግን የእጅ ስለኮትን በቀላሉ በውሃና በሳሙና በተነከረ በጥጥ ወይም ጥጥ ባለው በጨርቅ የስልክዎን ስክሪ
ሞባይሎን ማጽዳት አይርሱ! የእጅ ስልኮችን የራሳቸው ማጽጃ ያላቸው ሲሆን ይህንን ማግኘት ካልቻሉ ግን የእጅ ስለኮትን በቀላሉ በውሃና በሳሙና በተነከረ በጥጥ ወይም ጥጥ ባለው በጨርቅ የስልክዎን ስክሪንም ሆነ ጀርባ እንዲሁም ጎኖች ማጽዳት ይችላሉ። በዚህ ወቅት ግን የሚያጸዱበት ፈሳሽ በስልኮቹ ክፍተቶች በኩል እንዳይገባ ጥንቃቄ ያድርጉ። ምንጭ፡- BBC ~ INSA #መረጃዎችን ለወዳጅዎ ያጋሩ። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

💢ስለዚህ ዜና ትንሽ ነገር ለማለት እፈልጋለሁ‼️ ✅በመጀመሪያ ትምህርት ሚኒስትር #በታብሌት ፈተና በመፈተን ቀላሉን መንገድ ስለመረጠ፤ ቴክኖሎጂን መጠቀም ስለመረጠ ደስ ብሎኛል። ✅ከኢኮኖሚ እንዲሁም ካለው Process አንፃር #ከወረቀቱ ፈተና የተሻለ ነው። ⚠️ይሁን እንጂ... 1⃣. Security በደንብ ሊታሰብበት ይገባል። secure ባልሆነ ሲስተም ውስጥ ፈተና እፈትናለሁ ብሎ መነሳት ከጥቅሙ ጉዳቱ ይበልጣል ባይ ነኝ። ሲጀመር computer security, Internet security ላይ የተማረ ሀይል በሌለበት ሀገር ላይ ፈተናውን ከሀከሮች ማነው ሚጠብቀው? ➡️1ጊዜ እንኳን ኮምፒውተር አይቶ የማያውቅ ልጅ ባለበት ሀገር ውስጥ፤ በሌላ በኩል ደግሞ ገና 8ኛ ክፍል ሆኖ ስለ ሀኪንግ፣ ፕሮግራሚንግ ጠንቅቆ የሚያውቅ ተማሪ መኖሩን እንዴት አላሰባችሁትም? (ገና 8ኛ ክፍል ሆኖ C++, Java, Python, Html, Css, Javascript, PHP ጠንቅቆ የሚያውቅ ልጅ አጋጥሞኛል ሀኪንግ ማወቅም ይፈልጋል Kali linux ሰጥቼውም ተመልሼ ስሄድ እሱን ጨርሶ ሀኪንክ ውስጥ ሰምጦ አግኝቼዋለሁ።) ለዚህ ልጅ Biology, Chemistry.... ሌሎችንም አጥንቶ መፈተን ወይስ ሀኪንጉን ጠንክሮ ሰርቶበት ከተሳካለት በቀላሉ ፈተናውን ሰርቆ ወይንም ውጤቱን ቀይሮ ማለፍ? ➡️ፈተናው በታብሌት እስከሆነ ድረስ የውጭም የውስጥም ሀከሮች አይናቸው ፈተናው ላይ ነው መረሳት የለበትም። ✔️አየር መንገድ ለ Security ሲባል VPN እና BYOD ይጠቀማል። 🔹 VPN➡️ (ማናችንም የምንጠቀመውን ኢንተርኔት + #VPN ይጠቀማል፤ ኢንተርኔቱ በVPN ይሸፈናል ሀከር መጥቶ ፋይሉን ለማግኘት ሲሞክር የሚያገኘው ሽፋኑን ነው፤ ልክ እንደ ችንኩርት ቁጠሩት ኮሯን ለማግኘት ስንት ጊዜ እንልጣለን?) 🔹 BYOD (Bring your own device) policy (እዛ ሲስተም ላይ መግባት የሚችለው የተመዘገበ Device ብቻ ነው) ⚠️ነገር ግን የኛን MAC address ወደተመዘገበው MAC address በመቀየር መግባት እንችላለን።✅ ➡️ፈተናውም ላይ እነዚህንና ሌሎችን #Techniques ሊጠቀሙ ይችላሉ ነገር ግን ማወቅ ያለባቸው በደንብ Secure እስካልሆኑ ድረስ Professional ሀከር እስከሆነ ድረስ ሁሉንም ማለፍ አያቅተውም።✅ 2⃣. ሌላው ሀሳቤ 1 ቀን እንኳን #ታብሌት አይቶ የማያውቅን ልጅ በጥቂት ቀናት ወይንም ሰአታት ልምምድ ብቻ እንዴት ከሌላው እኩል ይፈተናል የሚል ነው። ይሄ እንኳን ከ 2, 3 አመት በላይ የሚቸገሩበት አይመስለኝም። ⚠️በተቃራኒ ከ2,3 አመት በኋላ እያንዳንዷ ክፍተት ስለምትታወቅ ሀከሮችን መቋቋም ትችላላችሁ ወይስ እንደለመዳችሁት ፈተና ይደገም ልትሉ ነው? #Hacking ቀላል ነገር አይደለም፤ የማይቻል ነገርም አይደለም። ⚠️⚠️እዚህ ሀገር #Professional_Hacker ካለ እስከዛሬ ለምን ባንኮች Hack ተደረጉ ሲባል አንሰማም ልትሉ ትችላላችሁ... ሁሉ አይነገርም ሁሉ ሚዲያ ላይ አይወጣም እንጂ እስከዛሬ ባንኮች ATM ማሽኖች ብዙ ጊዜ ጥቃት ይደርስባቸዋል፤ እከሌ እከሌ ባልላችሁም 2ሰዎችን አውቃለሁ ባንክ #Hack ያደረጉ.... 1 ባንክ ተደረኩ አለ ማለት በተዘዋዋሪ #Hack ማድረግ እንደሚቻል ነገራችሁ ማለት ነው ያ ከሚሆን እስከዛሬ ምንም ጥቃት እንዳልደረሰበት በማስመሰል በጣም ከባድ ነገር እንደሆነ ቢያሳምናችሁ ለሱ የተሻለ የደህንነት ሲስተም ነው። 👍ለማንኛውም መልካም ፈተና✍ ለማለት እወዳለሁ፤ ለፈታኙም ለተፈታኙም። 🙏 ሰርቆ ሳይሆን ሰርቶ ማለፍ የሚፈልግ ተማሪ ይብዛልን። 🙏 © @ethiotechs #መረጃዎችን ለወዳጅዎ ያጋሩ። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

"የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል ፈተና በታብሌት በመጠቀም የምንፈትን እንደሆነ ላበስር እወዳለሁ" - ዶ/ር ኢንጂነር ጌታሁን መኩሪያ [የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር] #ArtsTv #መረጃዎችን ለወዳጅዎ ያጋሩ። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

https://t.me/tiens_ethiopia_bot?start=vJX9EBB 🚫TIENS - ኢትዮጵያ ወርሓዊ ገቢ Bot በመጠቀም በአዲስ እንዲሁም እጅግ ቀላል በ ሆነ እና በ አጭር ጊዜ ውስጥ የ ቁዋሚ ወርሓዊ ገቢ (እስከ 38, 000 ብር በወር) ባለቤት ይሁኑ በማለት 6553 ok ብለው ያስሉካልኳችሁ እና ብራችሁን ይወስዳሉ። ⚠️እንዳትጠቀሙት።

#fake የኮሮና ቫይረስ መረጃ አፕሊኬሽኖች በዝተዋል እና ወደ ስልክዎ የሚጭኗቸዉን አፕሊኬሽኖች እንደ Google Play ካሉ ታማኝ ምንጮች ብቻ በመጫን ይጠቀሙ! . #fake ከተባሉት አፕሊኬሽኖች
#fake የኮሮና ቫይረስ መረጃ አፕሊኬሽኖች በዝተዋል እና ወደ ስልክዎ የሚጭኗቸዉን አፕሊኬሽኖች እንደ Google Play ካሉ ታማኝ ምንጮች ብቻ በመጫን ይጠቀሙ! . #fake ከተባሉት አፕሊኬሽኖች መካከል አንዱ ስልክዎ ላይ እንደተጫነ ስልክዎን በመቆለፍ በ48ሰዓት ዉስጥ $100 በቢትኮይን እንዲከፍሉ ካልሆነም ስልክዎ ላይ የሚገኙትን ማንኛዉም አይነት መረጃዎች እንደሚያጠፋ ያስፈራራል። #መረጃዎችን ለወዳጅዎ ያጋሩ። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━

ሳምሰንግ ከኮሮና በሽታ ጋር በተገናኘ ለደንበኞቹ ነፃ የስልክ ማፅጃ "ሳኒታይዘር" ማቅረቡን አስታውቋል። የስልክ ማፅጃ ሳኒታይዘሮቹን በተመረጡ 19 ሃገራት ለ Galaxy ስልክ ባለቤቶች ሲሆን ያቀረበ
ሳምሰንግ ከኮሮና በሽታ ጋር በተገናኘ ለደንበኞቹ ነፃ የስልክ ማፅጃ "ሳኒታይዘር" ማቅረቡን አስታውቋል። የስልክ ማፅጃ ሳኒታይዘሮቹን በተመረጡ 19 ሃገራት ለ Galaxy ስልክ ባለቤቶች ሲሆን ያቀረበው ኢትዮጵያ በዝርዝሩ ዉስጥ አትገኝም። #መረጃዎችን ለወዳጅዎ ያጋሩ። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks ━━━━━━━━━━━━━━━