ch
Feedback
ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ

ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ 

前往频道在 Telegram

ስለቴክኖሎጂ አዳዲስ መረጃዎች እና ሶፍትዌር የሚያገኙበት ቻናል፡፡ 🕳Professional Hack Tips and tricks 💡Cracked Softwares 🌎 ዘመኑ የቴክኖሎጂ ነው ከዘመኑ ጋር አብረው ይዘምኑ YouTube channel https://youtube.com/c/MkTechZoneETH

显示更多

📈 Telegram 频道 ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ  的分析概览

频道 ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ  (@computer_android_tricks) 是活跃参与者。目前社区聚集了 11 983 名订阅者,在 教育 类别中位列第 17 269,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 838 位。

📊 受众指标与增长动态

自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 11 983 名订阅者。

根据 04 三月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -107,过去 24 小时变化为 0,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 0%。内容发布后 24 小时内通常能获得 N/A% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 0 次浏览,首日通常累积 0 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 0。

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“ስለቴክኖሎጂ አዳዲስ መረጃዎች እና ሶፍትዌር የሚያገኙበት ቻናል፡፡ 🕳Professional Hack Tips and tricks 💡Cracked Softwares 🌎 ዘመኑ የቴክኖሎጂ ነው ከዘመኑ ጋር አብረው ይዘምኑ YouTube channel https://youtube.com/c/MkTechZoneETH”

凭借高频更新(最新数据采集于 05 三月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 教育 类别中的关键影响点。

11 983
订阅者
无数据24 小时
-337 夊
-10730 夊
帖子存档
የዲቪ 2021 ውጤት ዛሬ ይፋ ይሆናል -- የ2020 ዲቪ ሎተሪ ውጤት ዛሬ ከምሽቱ አንድ ሰአት ጀምሮ ይፋ እንደሚሆን አዲስአበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ አስታወቀ። ዲቪ የሞሉ አመልካቾች በተከታዩ ሊንክ https:// dvprogram.state.gov/ በመግባት ቅፅ በሚሞሉበት ወቅት የተሰጣቸውን የማረጋገጫ ቁጥር በማስገባት አሸናፊ መሆን አለመሆናቸውን ማወቅ ይችላሉ። ኤምባሲው በኢሜይል አሸናፊነት እንደማይገልፅ በመጠቆም አመልካቾች ከእንዲህ አይነት መጭበርበሮች እንዲጠነቀቁ መክሯል። The 2021 Diversity Visa (DV) lottery winners will be announced today, Saturday, June 6. Starting at 7:00 PM local time, DV-2021 entrants will be able to visit https://dvprogram.state.gov/ to enter their confirmation information and check their status. The link will remain active until September 30, 2021. Entrants who find they have not won are encouraged to check their status several times during this period as the website may be updated with new information. Entrants who were selected for the 2021 DV lottery will be able to attend an interview upon confirmation. However, please be aware that routine visa services, including the processing of Diversity Visa applications, are currently suspended due to precautions against COVID-19. Though we will resume visa services as soon as it is safe to do so, we are unable to provide a specific date at this time. If you were selected, here are a few tips to be aware of: - BE CAREFUL of fake emails. DV lottery results are never revealed in email. Applicants can only check their status at https://dvlottery.state.gov/ . - DO NOT share any personal details publicly on social media. - SPEAK truthfully and confidently during your interview. - AVOID short answers during your interview. Make sure to elaborate on the questions. - DO NOT submit fraudulent documents including work experience and school certificates. If possible, please submit original school documents (even if old.) - DO NOT claim children if they are not your own (unless legally adopted). - DO NOT engage in a fraudulent marriage. # DV2021 ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

Reset adjprog, waste ink pad repair, epson, repair error 5B00 canon, chipless, virtual chip. Www.camosystemsreset.com WhatsAp
+1
Reset adjprog, waste ink pad repair, epson, repair error 5B00 canon, chipless, virtual chip. Www.camosystemsreset.com WhatsApp +573133675937 L3060 3050 3150 3110 3100 4160 4150 5190 XP2101 241 243 245 8620 ET2500 all models you need

⚠️⚠️⚠️⚠️⚠️⚠️⚠️⚠️⚠️⚠️ ኢትዮ ቴሌኮም አንድ ወደፊት ሁለት ወደኋላ! Ethio-telecom አሁንም የኢትዮጵያን ህዝብ ማታለልና ማጭበርበሩን ቀጥሎበታል! ❌❌❌❌❌❌❌❌❌❌❌ ሰላም የቻናላችን ቤተሰቦች ለዛሬ አንድ የታዘብኩትን ነገር ላካፍላችሁ ብዙዎቻችን ኢትዮ ቴሌኮም በአዲስ መልኩ የBrodband/Wifi በየቤታችን እያስገባን እንገኛለን! ኢትዮ ቴሌኮም በተለያዩ ፍጥነቶች እና የገንዘብ መጠኖች አማራጭ በመስጠት ከ69% በላይ ቅናሽ በሚል ድለላ ብዙዎች Wifi አስገብተዋል! ጀርባው ሲጠና ግን ሀይለኛ ብዝበዛ (ዝርፊያ) ብንለው ይቀላል! እየፈፀመ  ይገኛል! በመጀመሪያ ቀነስኩ ያለው ዝርዝር ይህንን ይመስላል ለግለሰብና ለድርጅት በሚል ለ2 ከፍሎታል እኛ Review የምናደርገው ለግለሰብ የሚለውን ነው 1mb/s = 499 ብር 2mb/s = 699 ብር 3mb/s = 899 ብር 4mb/s = 1,099 ብር...እያለ ይቀጥላል ለምሳሌ : 2mb/s ፍጥነት ያለው  wifi አስገባሁ እንበል ማለትም በወር 699 ብር እየከፈልኩ ማለት ነው! በሚገርም ሁኔታ ፍጥነቱ ግን በሁለት እጥፍ የቀነሰ ነው የተገጠመው 1mb/ ተብሎ ቢሆንም የሚደርሰው 200kb/s ነው። የተገጠመው 2mb/s ተብሎ ቢሆንም የሚደርሰው 600-700kb/s ነው። የተገጠመው 3mb/s ተብሎ ቢሆንም የሚደርሰው 1mb/s ነው። ⚠️የዚህን ነገር እውነተኛነት ለማረጋገጥ speedtest.net ላይ በመሄድ ወይንም Speed checker የሚል የAndroid APK በመጠቀም ማረጋገጥ ትችላላችሁ! Mega byte እና Megabit በጣም ልዩነት አላቸው! ለምሳሌ 1 ሜጋ ባይትን ወደ 3 የተለያዩ ዩኒቶች ስንመድበው 1 Megabyte = 8 Megabit ነው 1 Megabyte = 125 Kilobyte ነው 1 Megabyte = 8000 Kilobit ነው በጥንቃቄ እዩት☝ ቴሌ በMegabyte ሳይሆን በMegabit ነው ኢንተርኔትን የሚያቀርበው እኛም Review ያደረግነው በMegabit ነው! 1megabit = 1000 kilobits 2megabits = 2000 kilobits 3megabits = 3000 kilobits 1megabits ስንለካው 100-200kilobits ሆነ ይህ ግን መሆን አልነበረበትም! 800 kilobits የት ገባ? ትክክለኛ ከሆነ 1megabits 1000 kilobits  (Not Kilobyte) ወይም 125 kilobyte መሆን ነበረበት! ኢትዮ ቴሌኮም ብዝበዛውን እንዲያቆምና Fair የሆነ ሾል እንዲሰራ ሁላችንም ቅሬታችንን እናሰማ! ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

📌ውድ የቻናላችን ተከታታዮች መረጃዎችን በ "video" መከታተል ለምትፈልጉ የ youtube ቻናላችንን ከታች ባለው ሊንክ ገብታችው Subscribe በማድረግ መከታተል ትችላላችሁ። TECH ZONE TUBE - YouTube https://www.youtube.com/channel/UC41VxoyfSBqLHZn2rYaaucg

በኢትዮጵያ በአንድ ቀን 61 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋገጠ! ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 3,757 የላብራቶሪ ምርመራ ስልሳ አንድ (61) ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል። በአ
በኢትዮጵያ በአንድ ቀን 61 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋገጠ! ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 3,757 የላብራቶሪ ምርመራ ስልሳ አንድ (61) ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል። በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 494 ደርሷል፡፡ ቫይረሱ የተገኘባቸው 43 ወንድ እና 18 ሴት ናቸው። በዜግነት ሁሉም ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ ከ15 እስከ 70 ዓመት የእድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ናቸው። ቫይረሱ የተገኘባቸው 48 ሰዎች ከአዲስ አበባ (5 ሰዎች በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት ያላቸው እና 43 ሰዎች የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ እና በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት #የሌላቸው) ፣ 3 ሰዎች ከአፋር ክልል (በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት ያላቸው እና በዱብቲ ለይቶ ማቆያ ያሉ) ፣ 1 ሰው ከአማራ ክልል (የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ ያለውና በደሴ ለይቶ ማቆያ ያሉ)፣ 7 ሰዎች ከሶማሌ ክልል (የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ ያላቸውና በጅግጅጋ ለይቶ ማቆያ ያሉ) እንዲሁም 2 ሰዎች ሰዎች ከኦሮሚያ ክልል (የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክና በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት #የሌላቸው ሲሆኑ የቡራዩና የሰበታ ከተማ ነዋሪዎች) ናቸው። የዕለቱ ታማሚዎች የጉዞ ታሪክና በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ያላቸው ግንኙነት ፦ • የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ ያላቸው - 11 • በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት ያላቸው - 5 • የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ እና በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት የሌላቸው - 45 ተጨማሪ መረጃ ፦ በትላትናው ዕለት 23 ሰዎች (14 ከአዲስ አበባና 9 ሰዎች ከአፋር ክልል) ከበሽታው ያገገሙ ሲሆን አጠቃላይ በሀገራችን ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር አንድ መቶ ሃምሳ አንድ (151) ደርሷል። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_

COVID-19 UPDATES 🇪🇹 🇪🇹 #DrLiaTadesse, minister of Health በኢትዮጵያ ተጨማሪ 9 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል!! በአጠቃላይ በሀገራችን በቫይረሱ የ
COVID-19 UPDATES 🇪🇹 🇪🇹 #DrLiaTadesse, minister of Health በኢትዮጵያ ተጨማሪ 9 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል!! በአጠቃላይ በሀገራችን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 398 ደርሷል:: "በመጠንቀቅ ያተረፈ እንጂ የተጎዳ የለም" ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ! በመላው ዓለም በኮቪድ-19 መያዛቸው የተረጋገጠ ሰዎች ከ5 ሚሊዮን በላይ ሆኗል። ከነዚህ ውስጥ ከ327,000 በላይ ሰዎች ሞተዋል፤ 1.9 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ሰዎች አገግ
የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ! በመላው ዓለም በኮቪድ-19 መያዛቸው የተረጋገጠ ሰዎች ከ5 ሚሊዮን በላይ ሆኗል። ከነዚህ ውስጥ ከ327,000 በላይ ሰዎች ሞተዋል፤ 1.9 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ሰዎች አገግመዋል። በአፍሪካ የቫይረሱ ስርጭት እጅግ በፍጥነት እየተስፋፋ ሲሆን እስካሁን ከ96,000 በላይ ሰዎች በቫይረሱ ሲያዙ ከ2,900 በላይ ሰዎች ሞተዋል ፤ ከ39,000 በላይ ሰዎች አገግመዋል። 3 ከፍተኛ ኬዝ የተመዘገበባቸው የአፍሪካ ሀገራት ፦ - ደቡብ አፍሪካ በቫይረሱ የተያዙ 18,003 ፣ ሞት 339 ፣ ያገገሙ 8,950 - ግብፅ በቫይረሱ የተያዙ 14,229 ፣ ሞት 680 ፣ ያገገሙ 3,994 - አልጄሪያ በቫይረሱ የተያዙ 7,542 ፣ ሞት 568 ፣ ያገገሙ 3,968 ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

ሰበር ዜና ‼️ #Coronavirus የደቡብ ሱዳን ምክትል ፕሬዘዳንት ዶክተር ሬክ ማቻር እና ባለቤታቸው አንጀሊና ቴኒ (የመከላከያ ሚኒስትር) በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። በተጨማሪ የፕሬዘዳ
ሰበር ዜና ‼️ #Coronavirus የደቡብ ሱዳን ምክትል ፕሬዘዳንት ዶክተር ሬክ ማቻር እና ባለቤታቸው አንጀሊና ቴኒ (የመከላከያ ሚኒስትር) በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። በተጨማሪ የፕሬዘዳንቱ የቢሮ ሰራተኞች እና ጠባቂዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተገልጿል።

✞✞✞ ይህ “ የትናንቱን ለነገ ” የተሰኘ የቴሌግራም ስብስባችን ነው:: • በእርጅናና በተለያየ ምክንያት ጤናቸው የተጓደሉና በየመቃብር ቤቱ የወደቁ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያንን ለመንከባከብ :: • የአብነት ትምህርት መምህራንን: ተማሪዎችን በሚያስፈልጋቸው ሁሉ ለመርዳት እንዲሁም የትናንቱን ለነገ ለማስቀጠል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ልጆች የሚመክሩበት ገፅ ነው:: እንኳን በደህና መጡ !!! ✟✟✟ ----------------------- ቻናላችን ደግሞ ይህ ነው:- (https://t.me/yetenantun_lenege ይግቡና ቤተሰባችን ይሁኑ:: እናመሰግናለን! "የትናንቱን_ለነገ"

🔸አሰላ እና አከባቢዋ ለምትኖሩ 📌Channel LINK 👇👇 https://t.me/joinchat/AAAAAFWoH0Ht89osWMfsPg

የአለም የጤና ድርጅት 7 ወይንም 8 የኮሮና ቫይረስ የክትባት መድሃኒት እዉን ለማድረግ በፍጥነት እየተሰራ መሆኑን አስታወቀ #Coronavirus የአለም የጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ቴድሮስ አድሃኖም
የአለም የጤና ድርጅት 7 ወይንም 8 የኮሮና ቫይረስ የክትባት መድሃኒት እዉን ለማድረግ በፍጥነት እየተሰራ መሆኑን አስታወቀ #Coronavirus የአለም የጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ቴድሮስ አድሃኖም ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኢኮኖሚና የማህበራዊ ምክር ቤት ጋር በቪዲዮ በነበራቸዉ ዉይይት እዳስታወቁት 7 ወይንም 8 የሚሆኑ የቫይረሱ የክትባት መድሃኒት በእጩነት በመምረጥ የምርምር ስራዉ ተጠናክሮ መቀጠሉን አስታዉቀዋል፡፡ በትላንትናዉ የቪዲዮ ኮንፍረንስ ላይ እንደተገለጸዉ ባሳለፍነዉ ሳምንት ከ40 የአለም ሀገራት፣ተቋማትና ባንኮች ለክትባቱ፣ለምርምር ስራ በተለገሰዉ 8 ቢሊየን የአሜሪካ ዶላር ስራዉ የሚከናወን ሲሆን ተጨማሪ ፈንድ እንደሚያስ ፈልግ ዋና ዳይሬክተሩ ዶ/ር ቴድሮስ ተናግረዋል፡፡ ለኮሮና ቫይረስ ክትባት በሚል ከ100 በላይ እጩ የምርምር ስራዎች የቀረቡ ሲሆን ከነዚህ መካከል እጅግ የተሸሉ የተባሉ 7 ወይንም 8 መለየታቸዉን የአለም የጤና ደርጅት አስታዉቋል፡፡ተለዩ ስለተባሉት የክትባት መድሃኒት ግን ዝርዝር መረጃ አልተሰጠም፡፡ ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

ቻይና የኮሮና ቫይረስ ቀውስ እዳን ክፈይ ከተባልኩ አሜሪካም ኤች አይ ቪ ኤድስ በዓለማችን ላደረሰው ቀውስ መክፈል አለባት አለች። ✒️ፒፕልስ ዴይሊ ቻይና የተሰኘው የአገሪቱ ተነባቢ ጋዜጣ እንደዘገበው አሜሪካ ለኤች አይ ቪ ኤድስ ወረርሽኝ ተጠያቂ ነች በሚል በሀገሪቱ ዙሪያ ዓለም አቀፋዊ የፍርድ ሂደት ጥሰቶችን በማሰራጨት ላይ ናቸው፡፡ ✒️አሜሪካ በአውሮፓውያኑ 2008 በቫይረሱ ምክንያት ለተከሰተው የገንዘብ ቀውስም ተጠያቂ መሆን አለባት ያሉት የቻይና ሚዲያዎች በ1918 የተከሰተውን የስፓኒሽ ፍሉ (የህዳር በሽታ) ወረርሽኝንም በዝርዝሩ ውስጥ አካተዋል፡፡ በቻይንኛ እና እንግሊዘኛ ቋንቋ የሚታተሙት እጅግ ተነባቢዎቹ ዘ ግሎባል ታይምስ እና ፒፕልስ ዴይሊ የተሰኙት የቻይና ጋዜጦች ቻይና ለኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ በሰጠችው ምላሸ ላይ በተለይ ከአሜሪካ ለሚነሱባት ተደጋጋሚ ዓለም አቀፋዊ ክሶች ተደጋጋሚ ምላሽ በመስጠት ላይ መሆናቸውን ዘገባው ጠቅሷል፡፡ ✒️በአሜሪካ የሚገኙ ሁለት ግዛቶችም ለመጀመረያ ጊዜ በቻይና ውሀን ግዛት የኮሮና ቫይረስ ሲከሰት መረጃውን ሸሽጋለች በጊዜውም ለዓለም አላሳወቀችም በሚል ለአሜሪካ ፍርድ ቤት ክስ መመስረታቸውም ተነግሯል፡፡ ለማሳያም ቻይና ለመጀመሪያ ጊዜ የኮሮና ቫይረስ መከሰቱን ይፋ ያረገውን ዶክተሯን ማሰሯን ፣ ቫይረሱ ከሰው ወደ ሰው የማይተላፍ ነው በሚል የተሳሳቱ መረጃዎች ሲያሰራጩ እና ሀገራት እንቅስቃሴንም ሆነ ማኛውንም ጉዞ እንዳያግዱ ሲያደርጉ ነበር የሚሉ ማስረጃዎችን አያይዘው ማቅረባቸውም ተጠቅሷል፡፡ ✒️እነዚህ ክሶች ቻይና ላይ ሊነሱ አይገባም የሚሉት የቻይና ሚዲያዎችም እንደውም አሜሪካም ሆነ ሌሎች ሀገራት እንደ ስፓኒሽ ፍሉ ፣ ኤች አይ ቪ ኤድስ እና ሌሎችም ከዚህ ቀደም የተከሰቱ ወረርሽኞች ላደረሱት ኢኮኖሚያዊ ቀውስም ሆነ በዓለም ላይ በጦርነት ምክንያት ለተከሰቱ ውድመቶችና ለሰዎች ህይወት ማለፍ አሜሪካ ብሎም የዓለም ህብረተሰብ ተጠያቂ ናቸው ሲሉ ክርክር መግጠማቸውም ተሰምቷል፡፡ ✒️የቻይና ጋዜጣዎች በአሜሪካ ቻይና ላይ የተከፈቱት ክሶች በሰው ልጅ ሥልጣኔ ከተከሰቱ ድርጊቶች መካከል አሳፋሪው እና ከአለም አቀፍ ህግ እና ከፍትህ ፅንሰ ሀሳብ የወጣ ነው ሲሉ ተችተዋል፡፡ Via:- Ethio FM ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

ሰበርዜና❗️: በኢትዮጵያ ተጨማሪ 11 ሰዎች በኮሮና መያዛቸው ተረጋገጠ:: በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰአታት በተደረገ 1764 የላብራቶሪ ምርመራ 11 በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች መገኘታቸውን ተከትሎ
ሰበርዜና❗️: በኢትዮጵያ ተጨማሪ 11 ሰዎች በኮሮና መያዛቸው ተረጋገጠ:: በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰአታት በተደረገ 1764 የላብራቶሪ ምርመራ 11 በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች መገኘታቸውን ተከትሎ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 250 መድረሱን ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል። የታማሚዎች ሁኔታ 1. ከበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት ያላቸው - 6 ሰዎች 2.ከውጪ ሀገር ጉዞ ታሪክ ያላቸው - 5 3.ከውጪ ሀገር ጉዞ ታሪክ እና ከበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት የሌላቸው - 0። ሁሉም ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ [እድሜያቸው ከ18-38እድሜ] የታማሚዎች መኖሪያ❗️ 5 ሰዎች- ከአዲስ አበባ 3 ሰዎች - ከአፋር ለይቶ ማቆያ 2 ሰዎች- ከትግራይ ክልል(ለይቶ ማቆያ) 1 ሰው - ከአዳማ ለይቶ መከታተያ ---------------------------------------------- ተጨማሪ 6 ሰዎች ከአዲስአበባ ያገገሙ ሲሆን አጠቃላይ 105 ሰዎች አገግመዋል። #ማስታወሻ በዚህ ሪፖርት ከትግራይ ክልል የተካተቱት ሁለት ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች በትላንትናው ዕለት በክልሉ ሪፖርት የተደረጉ ናቸው። ጤና ሚኒስተር

🖍በትግራይ ክልል ተጨማሪ 2 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 86 የላብራቶሪ ምርመራ ሁለት ሰዎች የኮሮና ቫይረስ መያዛቸውን ትግራይ ቲቪ ዘግቧል። ቫ
🖍በትግራይ ክልል ተጨማሪ 2 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 86 የላብራቶሪ ምርመራ ሁለት ሰዎች የኮሮና ቫይረስ መያዛቸውን ትግራይ ቲቪ ዘግቧል። ቫይረሱ የተገኘባቸው ግለሰቦች ከጅቡቲ መተው በለይቶ ማቆያ ያሉ የመኪና ረዳቶች መሆናቸው ተገልጿል። በትግራይ ክልል አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 6 የደረሰ ሲሆን በኢትዮጵያ ዛሬ በኮሮና መያዛቸው በምርመራ የተረጋገጠ ሰዎች ቁጥር 31 ደርሷል። በኢትዮጵያ አጠቃላይ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎችን ቁጥር ወደ 241 ደርሷል። tigrai mass media

ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 2171 የላብራቶሪ ምርመራ 29 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል፡፡ በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 239 ደርሷል፡፡ በተጨማሪም 2 ሰዎች ከቫይረሱ ያገገሙ ሲሆን አጠቃላይ ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 99 ደርሷል፡፡ 133 ሰዎች በቫይረሱ ተይዘው በህክምና ላይ ይገኛሉ፡፡ አጠቃላይ የተመረመሩት ሰዎች ቁጥር 34,860 ደርሷል፡፡

በኮሮና ቫይረስ (COVID-19) ተይዘው ያሳለፉትን ስቃይና ከሞት ጋር ያደረጉትን ግብግብ አጫውተውናል፡፡ እኛም በሚከተለው መልኩ አቅርበንላችኋል :: ይከታተሉት! ሌሎች ያጋሩት! [Ministry of Health,Ethiopia]

❗️የሟቾች ቁጥር 5 ደርሷል።❗️ በኢትዮጵያ የሟቾች ቁጥር 5 ደርሷል! በዛሬው ዕለት በፅኑ ህክምና ላይ የነበሩ የ65 ዓመት የአዲስ አበባ ነዋሪ የሆኑ ወንድ ኢትዮጵያዊ ህይወታቸው አልፏል ፤ ይህም
❗️የሟቾች ቁጥር 5 ደርሷል።❗️ በኢትዮጵያ የሟቾች ቁጥር 5 ደርሷል! በዛሬው ዕለት በፅኑ ህክምና ላይ የነበሩ የ65 ዓመት የአዲስ አበባ ነዋሪ የሆኑ ወንድ ኢትዮጵያዊ ህይወታቸው አልፏል ፤ ይህም አጠቃላይ በሀገራችን በቫይረሱ ምክንያት ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥር 5 አድርሶታል። ያገገሙ ሰዎች በኢትዮጵያ ተጨማሪ 2 ሰዎች (ከአዲስአበባ) ከኮሮና ቫይረስ ያገገሙ ሲሆን፣ እስከ አሁን በአገሪቱ ከቫይረሱ ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 97 ደርሷል፡፡ ዝርዝር መረጃ -አጠቃላይ የተከናወነ ምርመራ: 32,689 -በ24 ሰዓት ተከናወነ ምርመራ : 2383 -በዛሬው ዕለት የተገኙ ተጠቂዎች : 16 -በአጠቃላይ በለይቶ ከህክምና ያሉ :106 -በፅኑ ህክምና ላይ ያሉ : 0 -አዲስ ያገገሙ : 2 -በአጠቃላይ ያገገሙ : 97 -በበሽታው ሕይወታቸው ያለፈ : 5 -ወደ ሀገራቸው የተመለሱ : 2 -አጠቃላይ በበሽታው የተያዙ : 210 #SHARE ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

በጉራጌ ዞን የመጀመሪያው የኮሮና ቫይረስ ተጠቂ ተገኘ በቡታጅራ አጠቃላይ ሆስፒታል አንድ ሰው ላይ የኮሮና ቫይረስ ተገኘ ግለሠቡ ላሌላ በሽታ ሕክምና የደም ናሙናው ሲወሰድ የኮሮና ቫይረስ እናዳለበት
በጉራጌ ዞን የመጀመሪያው የኮሮና ቫይረስ ተጠቂ ተገኘ በቡታጅራ አጠቃላይ ሆስፒታል አንድ ሰው ላይ የኮሮና ቫይረስ ተገኘ ግለሠቡ ላሌላ በሽታ ሕክምና የደም ናሙናው ሲወሰድ የኮሮና ቫይረስ እናዳለበት ታውቋል። የከተማዉ ማህበረሰብ ምንም አይነት መረበሽና መደናገጥ ሳያሳይ ከዚህ ቀደም ከህክምና ባለሙያዎችና ከመንግስት የሚሰጡት ምክርና መመርያ በመተግበር እራሱንና ቤተሰቡን ከወረርሽኙ ይጠብቅ። #የቡታጅራ ከተማ ጤና ቢሮ ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

#ሰበር_ዜና #Telegram ስለኮሮና ቫይረስ ወቅታዊ መረጃ ለማግኘት ከስር ያለውን ማስፈንጠራያ (Link) ተጫኑ 🙏👇👇👇👇👇👇 https://t.me/joinchat/AAAAAEzq2mPY0Cuo4LJpow