ch
Feedback
ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ

ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ 

前往频道在 Telegram

ስለቴክኖሎጂ አዳዲስ መረጃዎች እና ሶፍትዌር የሚያገኙበት ቻናል፡፡ 🕳Professional Hack Tips and tricks 💡Cracked Softwares 🌎 ዘመኑ የቴክኖሎጂ ነው ከዘመኑ ጋር አብረው ይዘምኑ YouTube channel https://youtube.com/c/MkTechZoneETH

显示更多

📈 Telegram 频道 ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ  的分析概览

频道 ᴛᴇᴄʜ🌍ᴢᴏɴᴇᴱᵗʰ  (@computer_android_tricks) 是活跃参与者。目前社区聚集了 11 983 名订阅者,在 教育 类别中位列第 17 269,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 838 位。

📊 受众指标与增长动态

自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 11 983 名订阅者。

根据 04 三月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -107,过去 24 小时变化为 0,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 0%。内容发布后 24 小时内通常能获得 N/A% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 0 次浏览,首日通常累积 0 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 0。

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“ስለቴክኖሎጂ አዳዲስ መረጃዎች እና ሶፍትዌር የሚያገኙበት ቻናል፡፡ 🕳Professional Hack Tips and tricks 💡Cracked Softwares 🌎 ዘመኑ የቴክኖሎጂ ነው ከዘመኑ ጋር አብረው ይዘምኑ YouTube channel https://youtube.com/c/MkTechZoneETH”

凭借高频更新(最新数据采集于 05 三月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 教育 类别中的关键影响点。

11 983
订阅者
无数据24 小时
-337 夊
-10730 夊
帖子存档
#BREAKING የኢትዮጵያ ሠራዊት ሶማሊያ ውስጥ የኬንያን የጭነት አውሮፕላን መትቶ መጣሉን በሶማሊያ የአፍሪካ ሕብረት ሰላም አስከባሪ ኃይል - አሚሶም አስታውቋል፡፡ አውሮፕላኑ ተመቶ የወደቀበት ቦታ
#BREAKING የኢትዮጵያ ሠራዊት ሶማሊያ ውስጥ የኬንያን የጭነት አውሮፕላን መትቶ መጣሉን በሶማሊያ የአፍሪካ ሕብረት ሰላም አስከባሪ ኃይል - አሚሶም አስታውቋል፡፡ አውሮፕላኑ ተመቶ የወደቀበት ቦታን ተቆጣጥሮ የሚገኘው የአሚሶም ሴክተር ሦስት ኃይል አዛዥ የሆኑት ኮማንደር አለሙ አየነ እንዳሉት በአካባቢው ያለው ጦር ሠራዊት ስለ በረራው የሚያውቁት እንደሌለ እና አውሮፕላኑነ ለማረፍ የሄደበት አቅጣጫ አጠራጣሪ ነበር ብለዋል። የአፍሪካ ሕብረት የሶማሊያ ሰላም አስከባሪ-አሚሶም እንዳለው አውሮፕላኑ ምንም እንኳ አየር ላይ ሳለ በኢትዮጵያ ሠራዊት ቢመታም፤ ለማረፍ በሚያደርገው ጥረት በጣም ወደ ምድር ተጠግቶ ስለነበረ ጎማዎቹን መዘርጋት ባለመቻሉ ያለችግር የማረፍ እድል አልነበረው ብሏል። አሚሶም በመግለጫው በጉዳዩ ላይ ዝርዝር እውነታውን ለማወቅ የኢትዮጵያ፣ ኬንያ እና ሶማሊያ መንግሥታት በጣምራ በአደጋው ዙሪያ ምርመራ እንዲያደርጉ ጠይቋል። More https://telegra.ph/BBC-05-09-3 #BBC ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

#Breaking በአለም በኮሮና ቫይረስ በሽታ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 4ሚሊዮን አለፈ። #በአለም - 🔹አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ-4,015,107 ▪️አጠቃላይ በቫይረሱ የሞቱት - 276,268 🔸አጠቃላ
#Breaking በአለም በኮሮና ቫይረስ በሽታ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 4ሚሊዮን አለፈ። #በአለም - 🔹አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ-4,015,107 ▪️አጠቃላይ በቫይረሱ የሞቱት - 276,268 🔸አጠቃላይ ከቫይረሱ ያገገሙ - 1,387,478 ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

አስራ ዘጠኙ (19) የኮቪድ-19 ታማሚዎች እንዴት በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋገጠ ? #Ethiopia : በትላንትናው ዕለት በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ከተረጋገጠ አዳዲስ ሰዎች መካከል አስራ ዘጠኙ (19)
አስራ ዘጠኙ (19) የኮቪድ-19 ታማሚዎች እንዴት በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋገጠ ? #Ethiopia : በትላንትናው ዕለት በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ከተረጋገጠ አዳዲስ ሰዎች መካከል አስራ ዘጠኙ (19) በአዲስ አበባ ከተማ ቤት ለቤት በተደረገ አሰሳ የተገኙ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ገልጿል። ይህ ሁኔታ ኮቪድ-19 በህብረተሰቡ ውስጥ ተሰራጭቶ እንደሚገኝ የሚጠቁም በመሆኑ ከመቼውም ጊዜ በላይ ጥንቃቄ እንዲደረግ መልዕክት ተላልፏል። በኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የኮቪድ-19 ቅድመ ዝግጅት እና ምላሽ አስተባባሪው አቶ ዘውዱ አሰፋ እነዚህ አስራ ዘጠኙ (19) ሰዎች (የጉዞ ታሪክ የሌላቸው እና በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ንክኪ የሌላቸው) በቤት ለቤት አሰሳና ተጋላጭ ናቸው ተብለው የተለዩ ወገኖችን በመመርመር በሽታው እንደተገኘባቸው መረጋገጡን ለሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ተናግረዋል። አቶ ዘውዱ ከዚህ ቀደምም ከአዲስ አበባ ውጭ በአፋር ፣ በደቡብ እና በኦሮሚያ ክልል የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ የሌላቸውና በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ንክኪ ያልነበራቸው ሰዎች በቫይረሱ ተይዘው እንደተገኙ አስታውሰዋል። በበሽታው ከተያዙት መካከል ሰማንያ በመቶዎቹ (80%) ምልክት እንደማያሳዩ ገልፀው በቫይረሱ መያዛቸውን እራሳቸውም ሳያውቁ ሌላውም ሰው ሳያውቅ ቫይረሱን የሚያስተላልፉ ብዙ ሰዎች ሊኖሩ ስለሚችሉ ህብረተሰቡ ጥንቃቄው ላይ እንዲበረታ አሳስበዋል። በሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

🖍በኢትዮጵያ ተጨማሪ 3 ሰዎች በኮሮና መያዛቸው ተረጋገጠ:: በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰአታት በተደረገ 1861 የላብራቶሪ ምርመራ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ 3 ሰዎች መገኘታቸውን ተከትሎ በቫይረሱ የተያ
🖍በኢትዮጵያ ተጨማሪ 3 ሰዎች በኮሮና መያዛቸው ተረጋገጠ:: በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰአታት በተደረገ 1861 የላብራቶሪ ምርመራ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ 3 ሰዎች መገኘታቸውን ተከትሎ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 194 መድረሱን ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል። ጤና ሚኒስተር ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

44 ሚሊዮን አፍሪካውያን በኮሮና ቫይረስ ሊጠቁ እንደሚችሉ የዓለም የጤና ድርጅት አስታወቀ። በዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቢሮ ከደቂቃዎች በፊት በድረገጹ ባሰራጨው መረጃ ከ29 እስከ 44 ሚሊዮን አፍሪካውያን በኮሮና ቫይረስ ሊጠቁ ይችላሉ ብሏል። ድርጅቱ የኮሮና ቫይረስ ከአፍሪካ አየር ንብረት እና የኑሮ ዘዴ እና ህዝብ ብዛት አንጻር ስርጭቱን ምን ሊመስል እንደሚችል ለመረዳት በ47 የአህጉሪቱ አገራት ያስጠናውን አዲስ ጥናት ይፋ አድርጓል። በዚህ ጥናት መሰረትም አፍሪካውያን መዘናጋታቸውን ከቀጠሉ ከ29 እስከ 44 ሚሊዮን ዜጎች በቫይረሱ የሚያዙ ሲሆን እስከ 190 ሺህ የሚሆኑ ዜጎች ደግሞ ህይወታቸውን ያጣሉ። በቫይረሱ ከሚያዙ ዜጎች ውስጥም ከ5 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የሆስፒታል ህክምና የሚያስፈልጋቸው ሲሆን 107 ሺህ ያህሉ ደግሞ የጽኑ ህክምና ክትትል ያስፈልጋቸዋል ተብሏል። አፍሪካውያን ቫይረሱ ጥቁሮችን አያጠቃም፣አየር ንብረቱ ተስማሚ ነው እና ሌሎች የሚያዘናጉ እርምጃዎችን ከመውሰድ እንዲቆጠቡ ድርጅቱ አሳስቧል። ቫይረሱ ሁሉንም አፍሪካውያንን የሚያጠቃ ቢሆንም በተለይ ግን አልጅሪያ፣ ደቡብ አፍሪካ እና ካሜሩን ላይ የከፋ ጉዳት ሊያደርስ ይችላልም ተብሏል። Via:- Ethio FM ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

#DrLiaTadesse ዛሬ መደበኛ የ24 ሰዓት ዕለታዊ መግለጫ ከተሰጠ በኃላ በደረሰን አዲስ መረጃ መሰረት በትግራይ ክልል ጤና ምርምር ኢንስቲትዩት በተደረገ 85 የላብራቶሪ ምርመራ ተጨማሪ 4 ሰዎች
#DrLiaTadesse ዛሬ መደበኛ የ24 ሰዓት ዕለታዊ መግለጫ ከተሰጠ በኃላ በደረሰን አዲስ መረጃ መሰረት በትግራይ ክልል ጤና ምርምር ኢንስቲትዩት በተደረገ 85 የላብራቶሪ ምርመራ ተጨማሪ 4 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል። በዕለቱ ሃያ ዘጠኝ (29) ሰዎች የኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸው ሲሆን አጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች 191 ደርሷል። በትግራይ ክልል ኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የተረጋገጠው አራቱም ኢትዮጵያውያን ወንዶች ሲሆኑ እድሜያቸው ከ24-33 ዓመት የሆኑ ይገኙበታል። አራቱም ታማሚዎች ከጅቡቱ የተመለሱና በመቐለ አስገዳጅ ለይቶ ማቆያ የሚገኙ ናቸው። በሀገራችን የኮሮና ቫይረስ ሁኔታ መግለጫ ፦ • አጠቃላይ የተከናወነ የላብራቶሪ ምርመራ - 28,445 • በ24 ሰዓት የተከናወነ ላብራቶሪ ምርመራ - 1,928 • ዛሬ በበሽታው መያዛቸው የተረጋገጠ - 29 • በቫይረሱ ተይዘው በለይቶ ህክምና ውስጥ ያሉ - 92 • በፅኑ ህክምና ላይ ያሉ - 1 • አዲስ ያገገሙ - 0 • አጠቃላይ ያገገሙ - 93 • በበሽታው ህይወታቸው ያለፈ - 4 • ወደሀገራቸው የተመለሱ - 2 • እስካሁን በበሽታው የተያዙ - 191 (የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ) ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

❗️ምስራቅ አፍሪካ - ኮቪድ19 ሪፖርት❗️ -በኬንያ ተጨማሪ 47 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተገለፀ። አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 581 ደርሷል። ተጨማሪ 8 ሰዎች ከበሽታው ማገገማቸውን ተገልጿል። አጠቃላይ ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 190 ደርሷል። 2ተጨማሪ ሰዎች የሞቱ ሲሆን የሟቾች ቁጥር 26መድረሱ ተገልጿል። -በሱዳን ተጨማሪ 74 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 852 ደርሰዋል። ተጨማሪ 10 ሰዎች ከበሽታው ማገገማቸው ተገልጿል። አጠቃላይ ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 80 መድረሳቸው ተገልጿል። 4ተጨማሪ ሰዎች የሞቱ ሲሆን የሟቾች ቁጥር 49 መድረሱ ተገልጿል። -በሱማሊያ ተጨማሪ 38 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸዉ ተረጋገጧል! የ4 ሰዎች ህይወት ማለፉንና 12 ሰዎች በተደረገላቸዉ ህክምና ማገገማቸዉን ገልጿል። በአጠቃላይ በሀገሪቱ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 873 የደረሰ ሲሆን ከዚህ ዉስጥ 35 ሰዎች ህይወታቸዉ ሲያልፍ 87 ሰዎች ማገገማቸዉ ተገልጿል። - በጅቡቲ ተጨማሪ 10 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 1,124 ደርሰዋል። ተጨማሪ 10 ሰዎች ከበሽታው ማገገማቸው ተገልጿል። አጠቃላይ ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 755 መድረሳቸው ተገልጿል። ዛሬ ተጨማሪ የ1 ሰው ሞት ተመዝግቧል። -በኢትዮጵያ ተጨማሪ 17 ሰዎች በኮሮና መያዛቸው ተረጋገጧል:: አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 162 መድረሱን ተገልጿል። በኢትዮጵያ ተጨማሪ 2 ሰዎች ከኮሮና ቫይረስ ያገገሙ ሲሆን፣ እስከ አሁን በአገሪቱ ከቫይረሱ ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 93 ደርሷል፡፡ አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር 4 ደርሷል ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

በኮሮናቫይረስ ላይ ምርምር እየሰራ የነበር የህክምና ተመራማሪ ተገድሎ ተገኘ ። አሶሼትድ ፕሬስ አንደዘገበው ቢንግ ሉ የተባለ የ37 አመቱ ሴንጋፖሪዊ ዶክተር በሚኖርበት አሜሪካ ፔንሲልቪኒያ ቤት ውስጥ
በኮሮናቫይረስ ላይ ምርምር እየሰራ የነበር የህክምና ተመራማሪ ተገድሎ ተገኘ ። አሶሼትድ ፕሬስ አንደዘገበው ቢንግ ሉ የተባለ የ37 አመቱ ሴንጋፖሪዊ ዶክተር በሚኖርበት አሜሪካ ፔንሲልቪኒያ ቤት ውስጥ ባለፈው ቅዳሜ ተገሎ የተገኘ ሲሆን ከሱ ብዙም ሳይርቅ በተመሳሳይ ሰአት ሌላ ሰው መንገድ ላይ ትንሽ ራቅ ብሎ ተገድሉ መገኘቱ ጉዳዩን ውስብስብ አድርጎታል። ዶክተሩ በኮሮናቫይረስ ሴል አወቃቀር እና ባህርያት ላይ በፒተርስበርግ የህክምና ት/ቤት ጫፍ ላይ የደረሰ ምርምር እያከናወነ ነበር። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት የሰዎች እንቅስቃሴ በተገደበበት ወቅት በ27 ሴቶች ላይ የአስገድዶ መድፈርን ጨምሮ ሌሎች ጾታዊ ጥቃቶች እንደተፈጸመባቸው የሴት የሕግ ባለሚሙያዎች ማህበር አስታወቀ። ከኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መከሰት ጋር ተያይዞ ስርጭቱን ለመቀነስ እና የዜጎቻቸውን ህይወት ለመታደግ በሚል ሀገራት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅን ከማወጅ ጀምሮ እንቅስቃሴዎችን የሚገድቡ የተለያዩ መመሪያዎችን እያሳለፉ ይገኛሉ፡፡ የሚተላለፉት የእቅስቃሴ ገደቦች በተለይ ሰዎች ከቤት እንዳይወጡ የሚለውን የሚያካትት በመሆኑ ሰዉ ለስራ ፣ለትምህርት እንዲሁም ለሌሎች ተግባራት የሚያውለውን ጊዜ ከቤቱ ሳይወጣ አንድ ቦታ ላይ እንዲያሳልፍ ተገደዋል፡፡ በቤት ውስጥ ረጅም ጊዜ ማሳለፍ ደግሞ ከሚያደርሰው ኢኮኖሚያዊ ጉዳት ባለፈ የተለያዩ ማህበራዊ ቀውሶችን ያስከትላል፡፡ ከነዚያ መካከል ደግሞ ዋነኛው ተጠቃሽ ቀውስ የቤት ውስጥ ጥቃት ነው፡፡ እንደ ተባበሩት መንግስታት ድርጅት የህዝብ ገንዘብ ፈንድ (UNFPA) ከሆነ የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመቀነስ የሰዎች እንቅስቃሴ ሲገደብ የቤት ውስጥ ጥቃት በዓለም አቀፍ ደረጃ በ20 በመቶ ሊጨምር እንደሚችል ያሳያል፡፡ ኢትዮ ኤፍ ኤምም ከኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ መከሰት ጋር ተያይዞ በሀገራችን ያለው የቤት ውስጥ ጥቃት በምን ደረጃ ይገኝ ይሆን የሚለውን ቃኝቷል፡፡ በኢትዮጲያ የህግ ባለሙያ ሴቶች ማህበር ስራ አስፈፃሚ ሌንሳ ቢየና የሰዎች እንቅስቃሴ ሲገደብ የቤት ውስጥ ጥቃት ሊጨምር ይችላል የሚሉ ስጋቶች በመኖራቸው እና ፍርድ ቤትም በከፊል እነዚህን ጉዳዮች ስለሚያስተናግድ የቤት ውስጥ ጥቃት ለደረሰባቸው ሴቶች የህግ ድጋፍ እያደረግን ነው ብለውናል፡፡ በአንድ ሳምንት ውስጥ ብቻ 11 ሴቶችም የቤት ውስጥ ጥቃት ደርሶባቸው ወደ ተቋሙ መሄዳቸውን ነግረውናል፡፡ ማህበሩ ጥቃት የደረሰባቸው ሴቶች የሚያገግሙበት እና የተለየ ድጋፍ የሚያኙበት በሀገር አቀፍ ደረጃ 7 ቅርንጫፎች ያሉት የሴቶች ማረፊያ እና ልማት ማህበር ወይም አውሳድ የተባለ ጊዜአዊ ማዕከል አለው፡፡ የማዕከሉ የሴቶች ልማት ፕሮግራም ሀላፊ ሰናይት ዘውዴ ከኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ጋር ተያይዞ በርካታ የቤት ውስጥ ጥቃት የደረሰባቸው ሴቶች ወደ ተቋሙ ይመጣሉ ለመቀበልም ተቸግረን ነበር ብለውናል፡፡ በክልል ያሉንን ቅርንጫፎቹን በቫይረሱ ምክንያት ለጊዜው የዘጋን ቢሆንም በአዲስ አበባ ጥቃት የደረሰባቸው 50 ሴቶችን ማስተናገድ የሚችል አዲስ ማረፊያ አዘጋጅተናል ብለዋል። ከኮሮና ቫይረስ መከሰት ወዲህም 27 ሴቶች የቤት ውስጥ ጥቃት ደርሶባቸው ወደ ማዕከሉ መግባታቸውን ሀላፊዋ ነግረውናል፡፡ ሰዎች ጊዜአቸውን በቤት ውስጥ ሲያሳልፉ የቤት ውስጥ ጥቃት ይጨምራል የሚል ስጋት አለ፤ ከቫይረሱ መከሰት ወዲህ ምን ያህል የቤት ውስጥ ጥቃቶች ተፈፅመው ፍርድ ቤት ደረሰዋል ስንል የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤትንም ጠይቀናል፡፡ ፍርድ ቤቱ 11 ምድብ ችሎቶች ያሉት ሲሆን በተወሰኑት ምድብ ችሎቶች ላይ 17 የቤት ውስጥ ጥቃትን መሰረት ያደረጉ መዝገቦች ስለመከፈታቸው ሰምተናል፡፡ በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት እና የፌደራል ፍርድ ቤቶች ቃል አቀባይ አቶ ተስፋዬ ነዋይ ከቤት ውስጥ ጥቃት ጋር ተያይዘው ከተከፈቱት 17 መዝገቦች መካከል የአስገድዶ መድፈር እና የአካል ማጉደል ወጀሎች እንደሚገኙበት ነግረውን ሰዎች ረጅም ጊዜን በቤት ውስጥ ስለሚያሳልፉ የቤት ውስጥ ጥቃት ጨምሯል የሚለውን የሚያሳይ መረጃ ግን የለም ብለውናል፡፡ ፍርድ ቤቶች በከፊል በሚሰሩበት በዚህ ጊዜ የቤት ውስጥ ጥቃት ሰለባዎች ወደ ህግ አካላት እንደማያመሩ እና በየሰፈሩ በሽምግልና እና በገንዘብ የሚያልቁ ጉዳዮች አሉ፡፡ ነገር ግን ከኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ጋር በተያያዘ ፍርድ ቤቶች በልዩ ሁኔታ አንዲያስተናግዱ በጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንቷ በኩል ከተወሰኑ ጉዳዮች መካከል የቤት ውስጥ ጥቃት ስለሚገኝበት የጥቃት ሰለባ የሆናችሁ ሁሉ ወደ ህግ ቦታ ብትመጡ ትስተናገዳላችሁ ተብላችኋል። በትግስት ዘላለም ሚያዝያ 27 ቀን 2012 ዓ.ም ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

''መልካም ዜና''❗ በኢትዮጵያ ተጨማሪ 16 ሰዎች (15 ከአዲስአበባ እና 1 ከአማራ ክልል) በትናንትናው እለት ከኮሮና ቫይረስ ያገገሙ ሲሆን፣ እስከ አሁን በአገሪቱ ከቫይረሱ ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 9
''መልካም ዜና''❗ በኢትዮጵያ ተጨማሪ 16 ሰዎች (15 ከአዲስአበባ እና 1 ከአማራ ክልል) በትናንትናው እለት ከኮሮና ቫይረስ ያገገሙ ሲሆን፣ እስከ አሁን በአገሪቱ ከቫይረሱ ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 91 ደርሷል፡፡ ባለፉት 24 ሰዓታት በተደረገው የ1047 ላቦራቶሪ ምርመራ 5 ሰው በኮሮና ቫይረስ መያዙ ተረጋግጧል። #ዝርዝር መረጃ -አጠቃላይ የተከናወነ ምርመራ: 25,135 -በ24 ሰዓት ተከናወነ ምርመራ : 1047 -በዛሬው ዕለት የተገኙ ተጠቂዎች : 5 -በአጠቃላይ በለይቶ ከህክምና ያሉ :48 -በፅኑ ህክምና ላይ ያሉ : 0 -አዲስ ያገገሙ : 16 -በአጠቃላይ ያገገሙ : 91 -በበሽታው ሕይወታቸው ያለፈ : 4 -ወደ ሀገራቸው የተመለሱ : 2 -አጠቃላይ በበሽታው የተያዙ : 145 በመግለጫው ላይ 4ሰዎች እንደሞቱ ይገልፃል። REPORT 53 #DrLiyaTadesse ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

‼️140 ደርሷል። የታማሚዎች ሁኔታ 1ኛ ታማሚ : የ24 ዓመት ኢትዮጵያዊ ፤ ከፑንትላንድ የተመለሰና በጅግጅጋ አስገዳጅ ለይቶ ማቆያ ውስጥ ያለ። 2ኛ ታማሚ :የ23 ዓመት ኢትዮጵያዊ ፤ ከፑንትላንድ የተመለሰና በጅግጅጋ አስገዳጅ ለይቶ ማቆያ ውስጥ ያለ። 3ኛ ታማሚ :የ20 ዓመት ኢትዮጵያዊ ፤ ከፑንትላንድ የተመለሰና በጅግጅጋ አስገዳጅ ለይቶ ማቆያ ውስጥ ያለ። 4ኛ ታማሚ : - የ17 ዓመት ኢትዮጵያዊ የባህር ዳር ነዋሪ፤ በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት ያለው። 5ኛ ታማሚ - የ19 ዓመት ስዊድናዊ (ትውልደ ኢትዮጵያዊ) ፤ ከስዊድን የተመለሰና በአስገዳጅ ለይቶ ማቆያ ውስጥ ያለ። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

🎯 ከዛሬው የምርመራ ውጤት ምን እንማር 👉|| ዛሬ በሁለት ኢትዮጵውያን ላይ የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው ጤና ሚኒስቴር ማሳወቁ ይታወሳል፡፡ ሁለቱም የውጭ ሀገር ጉዞ ታሪክ የሌላቸውና በቫይረሱ ከተያዙ ሰዎች ጋር ንክኪ ስለመኖራቸውም ያልታወቁ ናቸው፡፡ 👉|| እንደ ጤና ሚኒስቴር ገለጻ አንደኛው ግለሰብ በአዲስ አበባ በጤና ተቋም ተኝተው በመታከም ላይ እያሉ ከተወሰደ ናሙና ነው ቫይረሱ የተገኘባቸው፤ መኖሪያቸውም ዝዋይ ነው፡፡ 👉|| ሁለተኛዋ ደግሞ በቤት ለቤት ቅኝት ወቅት በተወሰደ ናሙና ነው የኮሮና ቫይረስ እንዳለባቸው የተረጋገጠው፡፡ መኖሪያቸውም ደቡብ ክልል ስልጤ ወረዳ ነው፡፡ 👉|| አሁን ላይ እየተደረገ ያለው ጥንቃቄም የኮሮና ቫይረስ ወደ ኢትዮጵያ እንደገባ ይደረግ ከነበረው ያነሰ፣ ከፍተኛ መዘናጋት የሚስተዋልበት እንደሆነ እየዘገነዘብን እንገኛለን፡፡ የጤና ባለሙያዎች፣ የጤና ዘርፍ ምሁራን እና መንግሥትም ቸልተኝነቱ አስከፊ እልቂት እንዳያስከትል ሁሉም ሰው ኃላፊነቱን እንዲወጣ እየመከሩም፣ እያሳሰቡም ይገኛሉ፡፡ 👉|| አሁን ላይ በገበያ ቦታዎች፣ በታክሲ እና የባንክ ወረፋዎች፣ በየመጠጥ ግሮሰሪዎች ሰዎች ከወትሮው ባልተለዬ መልኩ ተሰባስበው እንመለከታለን፡፡ እንደ ጫት ቤቶች ባሉ የተከለከሉ አካባቢዎች ተሰባስበው በተገኙት ላይ ፖሊስ ርምጃ እየወሰደ እንደሆነም እየተገለጸ ነው፡፡ 👉|| በሕዝብ መጓጓዣ ተሽከርካሪዎች ላይ የተሳፋሪዎችን ቁጥር በግማሽ ቀንሶ መጫን ላይ፣ ከፍተኛ ንክኪ በሚፈጠርባቸው ባጃጆች እና ሞተር ሳይክሎች ላይም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን በመተግበር ላይ በተለይም የወረዳ እና የገጠር ከተሞች ላይ የተዘነጋ ይመስላል፡፡ 👉|| “ታሞ ከመማቀቅ አስቀድሞ መጠንቀቅ” የሚለውን መልካምና ሕይወት አድን ምክር ችላ ማለቱ ደግሞ ነገ አስከፊ ዋጋ እንዳያስከፍል የሚያሰጋ፣ ሊታሰብበትም የሚገባ ነው፡፡ 👉|| የኮሮና ቫይረስ ከውጭ ሀገራት ከመጡት እና በቫይረሱ ከተያዙት ጋር ንክኪ ካለቸው ሰዎች ባለፈ በዚህ መልኩ መገኘት መጀመሩ አሁን እየታዬ ካለው መዘናጋት አንጻር ሲታይ ሁሉም ኃላፊነቱን ካልተወጣ ሊከሰት የሚችለውን አስከፊ ውጤት መገመት አያዳግትም፡፡ 👉|| እርስዎስ በወረርሽኙ ላለመያዝና ወደ ሌሎችም ላለማዛመት ምን ጥንቃቄ እያደረጉ ነው። መልሱን ለእናንተ እንተው። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

🖍የ2ቱ ታማሚዎች ሁኔታ 1. የ49አመት ኢትዮጵያዊ የባቱ/ዝዋይ ኗሪ እና አዲስ አበባ ህክምና በመከታተል ላይ ያለ የውጪ ሀገር የጉዞ ታሪክ የሌለው እና በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት የለውም። 2. የ45አመት ኢትዮጵያዊ የስልጤ ዞን የስልጢ ወረዳ ኗሪ የሆነች እና የውጪ ሀገር የጉዞ ታሪክ የሌላት እና በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት የላትም። ቤት ለቤት ቅኝት የተገኘች። 🖍መልካም ዜና በኢትዮጵያ ተጨማሪ 6 ሰዎች በትናንትናው እለት #ከድሬዳዋ ከኮሮና ቫይረስ ያገገሙ ሲሆን፣ እስከ አሁን በአገሪቱ ከቫይረሱ ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 75 ደርሷል፡፡ ባለፉት 24 ሰዓታት በተደረገው የ1560 ላቦራቶሪ ምርመራ 2 ሰው በኮሮና ቫይረስ መያዙ ተረጋግጧል። 🖍ዝርዝር መረጃ -አጠቃላይ የተከናወነ ምርመራ: 22330 -በ24 ሰዓት ተከናወነ ምርመራ : 1560 -በዛሬው ዕለት የተገኙ ተጠቂዎች : 2 -በአጠቃላይ በለይቶ ከህክምና ያሉ :55 -በፅኑ ህክምና ላይ ያሉ : 0 -አዲስ ያገገሙ : 6 -በአጠቃላይ ያገገሙ : 75 -በበሽታው ሕይወታቸው ያለፈ : 3 -ወደ ሀገራቸው የተመለሱ : 2 -አጠቃላይ በበሽታው የተያዙ : 135 #SHARE REPORT 51 #DrLiyaTadesse ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

🖍ዛሬ በደቡብ ክልል የተገኘው የኮሮና ተጠቂ ግለሰብ በኢትዮጵያ ጤና ሚኒስተር ዶክተር ሊያ ታደሰ ዛሬ ከተገለፁት 2 የኮሮና ተጠቂዎች መካከል አንዱ ሲሆን ግለሰቡ የ25 ዓመት ኢትዮጵያዊ ከኬንያ የተመለሰና በሞያሌ አስገዳጅ ለይቶ ማቆያ ውስጥ የነበረ ሰው መሆኑ እና የምርመራ ውጤታቸው ሳይታወቅ ወደ ሀዋሳ የተጓዘ ሲሆን ከዛም ወደ ሀላባ የሄደ እና እዛም ሲደርስ በክትትል የተያዘ መሆኑን እና ወደ መኖሪያ ቦታው ከንባታ ጠንባሮ ዞን ሊሄድ የነበረ መሆኑን የደቡብ ክልል ጤና ቢሮ ሀላፊ ገልፀዋል። የደቡብ ክልል ጤና ቢሮ ሀላፊ ከ ደቡብ ቲቪ ጋር ያደረጉት ቆይታ ይመልከቱ። ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

🖍ከሶማሌ ክልል ያመለጠ የኮሮና ቫይረስ ተጠቂ ደቡብ ክልል ሀላባ ከተማ ተያዘ:: በሶማሌ ክልል በለይቶ ማቆያ ክትትል ሲደረግለት የነበረ ግለሰብ የደም ናሙናው ከተወሰደ በኋላ ከለይቶ ማቆያ ማዕከል
🖍ከሶማሌ ክልል ያመለጠ የኮሮና ቫይረስ ተጠቂ ደቡብ ክልል ሀላባ ከተማ ተያዘ:: በሶማሌ ክልል በለይቶ ማቆያ ክትትል ሲደረግለት የነበረ ግለሰብ የደም ናሙናው ከተወሰደ በኋላ ከለይቶ ማቆያ ማዕከል እንዲወጣ በተደረገለት የመጨረሻ ምርመራ የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘበት ይረጋገጣል:: ታዲያ በበሽታው እንደተያዘ ያወቀዉ ግለሰቡ ክትትል ሲደረግለት ከቆየዉ ከሶማሌ ክልል ለይቶ ማገገሚያ ማዕከል ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ አምልጦ በመውጣት በደቡብ ክልል ሀላባ ከተማ መናኸሪያ ውስጥ በክትትል መያዙ ተሰምቷል:: ግለሰቡ በዛሬው እለት ከሀዋሳ ወደ ሀላባ ቁሊቶ የመጣ ሲሆን ወደ ዱራሜ ከመሄዱ በፊት በመናኸሪያዉ ዙሪያ ባሉ ሻይ ቤቶች ቁርሱን እንደተመገበ ታዉቋል:: ስለሆነም የቫይረሱ ታማሚ ግለሰብ የተመገበባቸዉ ሻይ ቤቶቹ እንዲዘጉ መደረጉን የከተማ አስተዳደሩ አስታዉቋል:: ግለሰቡ በአሁን ሰዓት በሀላባ ቁሊቶ ጤና ጣቢያ ለይቶ ማቆያ ያለ ሲሆን ከደቡብ ክልል ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር ሀዋሳ ሄዶ ህክምናውን እንዲከታተል የማድረግ ስራ እየተከናወነ ይገኛል ተብሏል:: የሀላባ ከተማ አስተዳደር ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

🖍 #133 ደርሷል። #በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓታት በተደረገ የላቦራቶሪ ምርመራ 2 ተጨማሪ ሰዎች ኮሮናቫይረስ እንደተገኘባቸው ተረጋገጠ። የኮቪድ-19 ስርጭትን ለመከላከል የተቋቋመው ብሔራዊ የሚኒስትሮች ኮሚቴ የእስካሁን አፈፃፀሙን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በተገኙበት እየገመገመ ነው፡፡ የኮሚቴውን ሪፖርት እያቀረቡ ያሉት የጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር ሊያ ታደሰ እንዳሉት ባለፉት 24 ሰዓታት በተደረገ የላቦራቶሪ ምርመራ 2 ተጨማሪ ሰዎች ኮሮናቫይረስ እንደተገኘባቸው ተረጋግጧል ብለዋል፡፡ ይህም በሀገሪቱ ቫይረሱ የተገኘባቸውን ሰዎች ቁጥር 133 አድርሶታል፡፡ Via : EBC

🖍 ''ዶ/ር ሊያ ታደሰ'' በኢትዮጵያ 9 ተጨማሪ ሰዎች ከኮሮና ቫይረስ አገገሙ። በኢትዮጵያ ተጨማሪ 9 ሰዎች (8 #ከአዲስአበባ እና 1 ከባህርዳር) ከኮሮና ቫይረስ ያገገሙ ሲሆን፣ እስከ አሁን በአ
🖍 ''ዶ/ር ሊያ ታደሰ'' በኢትዮጵያ 9 ተጨማሪ ሰዎች ከኮሮና ቫይረስ አገገሙ። በኢትዮጵያ ተጨማሪ 9 ሰዎች (8 #ከአዲስአበባ እና 1 ከባህርዳር) ከኮሮና ቫይረስ ያገገሙ ሲሆን፣ እስከ አሁን በአገሪቱ ከቫይረሱ ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 50 ደርሷል፡፡ ባለፉት 24 ሰዓታት በተደረገው የ943 ላቦራቶሪ ምርመራ 1 ሰው በኮሮና ቫይረስ መያዙ ተረጋግጧል። 🖍ዝርዝር መረጃ -አጠቃላይ የተከናወነ ምርመራ: 14,588 -በ24 ሰዓት ተከናወነ ምርመራ : 943 -በዛሬው ዕለት የተገኙ ተጠቂዎች : 1 -በአጠቃላይ በለይቶ ከህክምና ያሉ :69 -በፅኑ ህክምና ላይ ያሉ : 0 -አዲስ ያገገሙ : 9 -በአጠቃላይ ያገገሙ : 50 -በበሽታው ሕይወታቸው ያለፈ : 3 -ወደ ሀገራቸው የተመለሱ : 2 -አጠቃላይ በበሽታው የተያዙ : 124 #SHARE REPORT 45 #DrLiyaTadesse ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

በሊባኖስ የ100 ኢትዮጵያውያን አስከሬን በማድረቂያ ውስጥ ሲሆን ከ80 በላይ የሚሆኑት ደግሞ በአእምሮ ህመም እየተሰቃዩ መሆኑ ተገለጸ። በሊባኖስ መዲና ቤሩት ከተማ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ላለፉት ሰባት ወራት ካለ ስራ መቀመጣቸውንና ከባድ ችግር ውስጥ መግባታቸውን ለኢትዮ ኤፍ ኤም ተናግረዋል፡፡ እነሱ እንደሚሉት በሃገሪቷ ስራ የጠፋው የሃገሪቷ ዜጎችም ሰራተኞቻቸውን ማሰናበት የጀመሩት ከሰባት ወራት በፊት ባጋጠማቸው የኢኮኖሚ ችግር ምክንያት ነው፡፡ በወቅቱም በሁኔታው ተስፋ ቆርጠው ወደ ሃገራቸው ለመመለስ በኢትዮጵያ ቆንስላ በኩል የተጠየቁትን 550 ዶላር ከፍለው የተወሰኑት ሃገራቸው መግባታቸውን አጫውተውናል፡፡ ቀሪዎቹ ደግሞ ተራቸውን እየጠበቁ ባለበት ሁኔታ ኮሮና ቫይረስ በመከሰቱ ወደ ኢትዮጲያ የመመለሻቸው ነገር እየራቀባቸው መምጣቱን ይናገራሉ፡፡ ስደተኞቹ ባጋጠማቸው የገንዘብ ችግር ምክንያት በርካቶች ከተከራዩበት ቤት እንዲወጡ እየተደረጉ መሆኑንና በዚህም ራሳቸውን የሚያጠፉ፤እንዲሁም ለአእምሮ ህመም የሚዳረጉ ዜጎቻችን ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን ነግረውናል፡፡ በሊባኖስ የኢትዮጵያ ቆንስላ እንደነገረን ከ80 በላይ ልጆች አእምሮ በሽተኛ ሆነው ኤምባሲው ውስጥ አሉ ወደ 100 የሚጠጉ ልጆች ደግሞ ህይወታቸው አልፎ አስከሬናቸው ማድረቂያ ውስጥ እንዳለም እናውቃለን ብለውናል፡፡ እናም መንግስት የሚችለውን አድርጎ ወደ ሃገራችን ያስገባን ሲሉ ነው ድምጻቸውን ያሰሙት፡፡ በውጪ ጉዳይ ሚኒስትር የቆንስላ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጄኔራል አቶ ዬሃንስ ሾዴ ከስደተኞቹ የተነሳው አቤቱታ ትክክል መሆኑን በማመን፤ይህ በሊባኖስ ብቻ ሳይሆን በሁሉም መካከለኛው ምስራቅና ሌሎችም በርካታ ሃገራት ያሉ ዜቻችን ጥያቄ ነው ብለውናል፡፡ ሆኖም ሃገራት በኮሮና ወረርሽኝ ስጋት ምክንያት አለም አቀፍ በረራዎችን በማገዳቸው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአየር ክልላቸውን ጥሶ መግባት አይችልም ይላሉ፡፡ በመሆኑም ሁኔታዎች ወደ ቦታዎች እስከሚመለሱ ድረስ በሁሉም አቅጣጫ ያሉ ኢትዮጵያዊያን ራሳቸውን እየጠበቁ በትእግስት ይህን ጊዜ እንዲያሳልፉት ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በአባይነሽ ሽባባው ሚያዝያ 19 ቀን 2012 ዓ.ም

አሜሪካ የአለም ጤና ድርጅትን የሚተካ ሌላ የጤና ድርጅት ልታቋቁም እንደምትችል አስጠነቀቀች። የአሜሪካ ውጪ ጉዳይ ሚንስትር ማይክ ፖምፒዮ ለአለም ጤና ድርጅት አሜሪካ የምትሰጠውን ገንዘብ እስከመጨረሻው ልታስቀር እንደምትችል ተናግረዋል። የአለም ጤና ድርጅት አመራር እስካልተቀየረ ድረስ አሜሪካ ያቋረጠችውን የገንዘብ መዋጮ እስከመጨረሻው እንደምታስቀረውም ገለፃለች። የኮቪድ 19 ወረርሽኝ የአለም ጤና ድርጅትን በደንብ መመርመር እንደሚያስፈልገን አስገንዝቦናል ብለዋል ፖምፒዮ፡፡ ዋሽንግተን ለአለም ጤና ድርጅት መስጠት ያቋረጠችውን ፈንድ መቼም ላትመልሰው ትችላለች፤እንደውም አንድ የተመድ አካል የሆነ አማራጭ የጤና ተቋም ለማቋቋም ልትሰራ ትችላለች ሲሉ አስጠንቅቀዋል፡፡ በአሜሪካ የህዝብ ተዋካዮች ምክር ቤት የፕሬዝዳንት ትራምፕ አስተዳደር ወረርሽኙን መቆጣጠር ሲያቅተው የአለም ጤና ድርጅትን ማምለጫ እያረገው ነው ብሎ ከሶ ነበር፡፡ ፖምፒዮ ግን አሁንም በአዲስ መልኩ ተቋሙን ማጥቃታቸወን ቀጥለዋል፡፡ ምክር ቤቱ ለፕሬዝዳንት ትራምፕ በላከው ደብዳቤ በአስቸኳይ ለአለም ጤና ድርጅት ያቋረጠውን ፈንድ መልሶ እንዲጀምር አሳስቦ ነበር፡፡ ትራምፕ የአለም ጤና ድርጅት በቻይና የሚመራ ተቋም ከመሆኑም በላይ ስለ ኮሮና ወረርሽኝ ቻይና የሰጠችውን የተዛባ መረጃ በማሰራጨት ተቋሙን ይከሳሉ፡፡ ፖምፒዮ ከ ፎክስኒውስ ጋር በነበራቸው ቆይታ ተቋማዊና መዋቅራዊ ለውጥ ይፈልጋል ድርጅቱ ብለዋል፡፡ አመራሩ መቀየር ብቻ ሳይሆን ከዚያም በላይ ስር ነቀል ለውጥ ይፈልጋል አለበለዚያ የአሜሪካውያን ግብር ከፋዮች ገንዘብ ወደ አለም ጤና ድርጅት የሚሄድበት ምንም ምክንያት የለም፤ መቼም መልሰን ድርጅቱን ፈንድ ላናደርገው እንችላለን ሲሉ አስጠንቅቀዋል፡፡ ፖምፒዮ ቤጂንግ በወቅቱ ወረርሽኙን ሪፖርት አላደረገችም፤ይሄ የአለም ጤና ድርጅትን መመርያ መጣስ ነው፤ የአለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ቴድሮስ አድሀኖም ደግሞ ስልጣንና ችሎታቸውን ተጠቅመው የድርጅቱ አባል ሀገር መመርያ እንደጣሰች ለህዝብ ይፋ አላደረጉም ሲሉ ወቅሰዋል፡፡ ቻይና ለዚህ ስራዋ ዋጋ ትከፍልበታለች ሲሉም ዝተዋል፡፡ አሜሪካ ትልቋ የአለም ጤና ድርጅት ለጋሽ ነች፤ በ 2019 ከአጠቃላይ የአለም ጤና ድርጅት በጀት 15 በመቶውን ወይንም 400 ሚሊዮን ዶላር አስተዋፅኦ አድርጋለች፡፡ በሔኖክ አስራት ሚያዝያ 16 ቀን 2012 ዓ.ም ━━━━━━━━━━━━━━━ 📢: @Computer_Android_tricks

🖍 ዶክተር ሊያ ታደሰ :- ኢትዮጵያ ውስጥ ከኮሮና ቫይረስ ያገገሙ ሰዎች 25 ደርሰዋል! #በአጠቃላይ በሀገራችን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር አንድ መቶ አስራ ሰባት (117) ደርሷል፡፡ በሌላ መል
🖍 ዶክተር ሊያ ታደሰ :- ኢትዮጵያ ውስጥ ከኮሮና ቫይረስ ያገገሙ ሰዎች 25 ደርሰዋል! #በአጠቃላይ በሀገራችን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር አንድ መቶ አስራ ሰባት (117) ደርሷል፡፡ በሌላ መልኩ በትላንትናው ዕለት አራት (4) ሰዎች (2 ከአዲስ አበባና 2 ከባህርዳር) ከበሽታው ያገገሙ ሲሆን በአጠቃላይ በሀገራችን ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር ሃያ አምስት (25) ነው፡፡ #ዛሬ በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው የተረጋገጠው የ60 ዓመት ኢትዮጵያዊት እንስት ሲሆኑ ከእንግሊዝ የመጡና በአስገዳጅ ለይቶ ማቆያ ውስጥ ያሉ ናቸው። #ዝርዝር_መረጃ -አጠቃላይ የተከናወነ ምርመራ: 11,669 -በ24 ሰዓት ተከናወነ ምርመራ : 933 -በዛሬው ዕለት የተገኙ ተጠቂዎች : 1 -በአጠቃላይ በለይቶ ከህክምና ያሉ :87 -በፅኑ ህክምና ላይ ያሉ : 0 -አዲስ ያገገሙ : 4 -በአጠቃላይ ያነገሙ : 25 -በበሽታው ሕይወታቸው ያለፈ : 3 -ወደ ሀገራቸው የተመለሱ : 2 -አጠቃላይ በበሽታው የተያዙ: 117 #SHARE ምንጭ : ጤና ሚኒስተር 🇪🇹 @ethio_me