ch
Feedback
الزواج في الإسلام /ትዳር በኢስላም

الزواج في الإسلام /ትዳር በኢስላም

前往频道在 Telegram

﴿وَمِنْ آيَاتِهِ أَنْ خَلَقَ لَكُم مِّنْ أَنفُسِكُمْ أَزْوَاجًا لِّتَسْكُنُوا إِلَيْهَا وَجَعَلَ بَيْنَكُم مَّوَدَّةً وَرَحْمَةً﴾ ለማንኛዉም አስተያየት☞☞ @Tidarbaislam_bot ለይ ያድርሱን ለጥያቄ ☞☞ t.me/Hayatbintkedir

显示更多

📈 Telegram 频道 الزواج في الإسلام /ትዳር በኢስላም 的分析概览

频道 الزواج في الإسلام /ትዳር በኢስላም (@tidar_be_islam) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 18 340 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 4 498,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 1 831

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 18 340 名订阅者。

根据 24 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -369,过去 24 小时变化为 -11,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 9.66%。内容发布后 24 小时内通常能获得 2.19% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 1 773 次浏览,首日通常累积 401 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 16

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
﴿وَمِنْ آيَاتِهِ أَنْ خَلَقَ لَكُم مِّنْ أَنفُسِكُمْ أَزْوَاجًا لِّتَسْكُنُوا إِلَيْهَا وَجَعَلَ بَيْنَكُم مَّوَدَّةً وَرَحْمَةً﴾ ለማንኛዉም አስተያየት☞☞ @Tidarbaislam_bot ለይ ያድርሱን ለጥያቄ ☞☞ t.me/Hayatbintkedir

凭借高频更新(最新数据采集于 25 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。

18 340
订阅者
-1124 小时
-617
-36930
帖子存档
የዐሹራእን ፆም የሚመለከቱ ጥቂት ነጥቦች ~ ያለንበት ወር የሙሐረም ወር ነው፡፡ ሙሐረም በሂጅራው አቆጣጠር የአመቱ መጀመሪያ ወር ነው፡፡ በዚህ ወር ውስጥ የሚገኘውን የዓሹራእን ቀን የሚመለከቱ ኢስላማዊ ስርኣቶች አሉና ጥቂት እንተዋወስ 1. በመጀመሪያ ወሩ ታላቅና የተከበረ ወር ነው ነው፡፡ [ተውባህ፡ 36] ነብዩም ﷺ እንዲህ ብለዋል፡ “አንድ አመት 12 ወር ነው፡፡ ከነዚህ ውስጥ አራቱ የተከበሩ ናቸው፡፡ (ከተከበሩት ውስጥ) ሶስቱ ተከታታይ ናቸው፡፡ ዙልቀዕዳህ፣ ዙልሒጃህ፣ ሙሐረም እና በጁማዳ እና በሸዕባን መካከል ያለው የሙደር ረጀብ ነው፡፡" [ቡኻሪ፡ 2958] 2. ሙሐረም ወርን መፆም እጅግ የላቀ ዋጋ አለው፡፡ ነብዩ ﷺ እንዲህ ይላሉ፡ “ከረመዳን ቀጥሎ ከሁሉም በላጩ ፆም የአላህ ወር የሆነው ሙሐረም ነው፡፡” [ሙስሊም፡ 1163] ልብ በሉ! ሁሉም ወሮች የአላህ ሆነው ሳለ ነብዩ ﷺ ሙሐረምን “የአላህ ወር” ሲሉ መጥራታቸው ወሩ ያለውን ልዩ ደረጃ ያመላክታል፡፡ ልክ ሁሉም መስጂዶች የአላህ ቤቶች ሆነው ሳለ ከዕባ ለየት ባለ መልኩ “የአላህ ቤት” እንደሚባለው ማለት ነው፡፡ 3. በዚህ ወር ውስጥ ታላቅ ቀን አለ፡፡ እሱም ሙሐረም 10 ነው፡፡ “ዓሹራእ” በመባል ይታወቃል፡፡ የአላህ መልእክተኛ ﷺ ከመካ ወደ መዲና ሲገቡ  የሁዶች ዓሹራእን ይፆሙ ነበርና “ምንድን ነው ይሄ የምትፆሙት ቀን?” ሲሉ ጠየቋቸው፡፡ እነሱም “ይሄ አላህ ሙሳንና ህዝቦቹን አትርፎ ፊርዐውንና ህዝቦቹን ያሰመጠበት ታላቅ ቀን ነው፡፡ ሙሳ አላህን ለማመስገን ሲሉ ፆመውታል፡፡ እና እኛም እንፆመዋለን” አሉ፡፡ ነብያችን ﷺ ይህን ጊዜ “ከናንተ ይልቅ እኛ ለሙሳ የተገባን ነን” በማለት ፆሙት፡፡ እንዲፆምም አዘዙ፡፡ [ቡኻሪ፡ 2004] [ሙስሊም፡ 1130] 4. ይህን ቀን፣ ማለትም ሙሐረም አስርን መፆም እጅግ የላቀ ዋጋ አለው፡፡ ያለፈውን አንድ አመት ወንጀል እንደሚያሚያሳብስ ነብያችን ﷺ ተናግረዋል፡፡ [ሙስሊም] 5. ይህን ቀን (ሙሐረም አስርን) ለመፆም ከወሰንን ዘጠነኛውንም ጨምረን ብንፆም የተወደደ ነው፡፡ ምክንያቱም ነብዩ ﷺ “ለቀጣይ (አመት) ከቆየሁ በርግጥም ዘጠነኛውንም እፆማለሁ” ብለዋልና።  [ሙስሊም፡ 1134] 6. በነገራችን ላይ ዓሹራእን የመካ ሙሽሪኮችም ይፆሙት ነበር፡፡ ነብያችንም ﷺ ገና ወደ መዲና ሳይሰደዱ በፊት መካ እያሉ ይፆሙት ነበር፡፡ የረመዳን ፆም ከመደንገጉ በፊት ዓሹራእን መፆም በሙስሊሞች ላይ ግዴታ ነበር፡፡ እነኚህን እውነታዎች የሚያመላክተው እናታችን ዓኢሻህ ረዲየላሁ ዐንሃ እንዲህ ስትል የተናገረችው ነው፡- “ዓሹራእ ቁረይሾች በዘመነ ጃሂሊያ (በጨለማው ዘመን) ይፆሙት የነበረ ቀን ነው፡፡ ነብዩም ﷺ ይፆሙት ነበር፡፡ መዲና በመጡ ጊዜ እሳቸውም ፆሙት ሰዎችም እንዲፆሙት አዘዙ፡፡ የወርሃ ረመዳን ግዴታ በወረደ ጊዜ ግን ረመዳንን ሆነ (በግዴታነት) የሚፆሙት፡፡ ዓሹራእን እንዲፆም (ማዘዙን) ተውት፡፡ እናም የፈለገ ይፆመዋል የፈለገ ደግሞ ይቶወዋል፡፡ [ቡኻሪና ሙስሊም] 7. ዓሹራእን እለቱን መፆም እንጂ በምንም መልኩ በዓል አድርጎ ማክበር አይፈቀድም፡፡ አቡ ሙሳ ረዲየላሁ ዐንሁ እንዳስተላለፉት ዓሹራእን የሁዶች ይፆሙት ነበር፡፡ እንደ ዒድ ይቆጥሩት ነበር፡፡ ሴቶቻቸውንም ጌጦቻቸውንና ጥሩ ጥሩ ልብሶቻቸውን ያለብሷቸውም ነበር፡፡ ነብዩ ﷺ ግን “እናንተ ፁሙት” በማለት መፆም እንጂ እንደ ዒድ እንዳይታሰብ ጥቆማ ሰጥተዋል፡፡ [ቡኻሪና ሙስሊም] ማሳሰቢያ፦ ሙሐረም 9 እና 10 ነገ ረቡዕ እና ሃሙስ መሆኑን አውቀን ብንፆም እና ሰዎች እንዲፆሙት ብናስታውስ መልካም ነው። @Darul_Islam_channal @Darul_Islam_channal

‏المبادرة إلى التوبة من الذنب فرضٌ على الفور ، ولا يجوز تأخيرها ، فمتى أخّرها عصى بالتأخير ☞ወንጀል ሰርቶ ተውበት ማድረግ ግዜ የማይሰጠው ፈጣን
‏المبادرة إلى التوبة من الذنب فرضٌ على الفور ، ولا يجوز تأخيرها ، فمتى أخّرها عصى بالتأخير ☞ወንጀል ሰርቶ ተውበት ማድረግ ግዜ የማይሰጠው ፈጣን የሆነ ግዴታ ነው። ማዘግየት አይፈቀድም። ከተውበት የዘገየ ሰው በመዘግየቱ ወንጀለኛ ነው።" ‏📚 ابن القيم | مدارج السالكين ١/٢٠٥

👉 ነብያችን ላይ ሰላትና ሰለዋት ማውረድ በጅሙአ ቀን ብቻ የተገደበ አይደለም 👉 በጅሙአ ቀን ይበልጥ የተወደደ ቢሆንም በሌሎችም ቀናቶች እንድንፈፅመው የተደነገገ ኢባዳ ነው اللهم صلِّ وسلم على نبينا محمد وعلى آله وصحبه وسلم

🚫 የጥንቃቄ መልእክት❗️ እባኳትን በWhatsAppበ,telegram በimo ላይ ከማታውቁት ሰው ቪዲዮ ኮል ቢደውልላችሁ አታንሱ የማታውቋቸው ሊንኮች አትንኩ ፓስዋርዳችሁ አሳልፋችሁ አትስጡ ፕሊስ።             ✅ቴሌግራማችን ╰➤ ❝@Tidar_Be_Islam ╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ- ╰➤ ❝@Tidar_Be_Islam

《 ማንኛዋም ሴት ባሏ ከሷ የወደደላት ሆኖ ከሞተች ጀነት ገባች 》 قال رسول الله ﷺ: « إذا صلت المرأة خمسها وصامت شهرها وحفظت فرجها وأطاعت زوجها قيل لها ادخلي الجنة من أي أبواب الجنة شئت» ورواه ابن حبان في صحيحه عن أبي هريرة رضي الله عنه، والحديث صححه الألباني في الجامع الصغير. "ሴት ልጅ አምስት ወቅቷን ከሰገደች፣ የረመዷን ወሯንም ከፆመች፣ ብልቷንም ከጠበቀች ባሏን በመልካም ከታዘዘች በፈለግሽው የጀነት በር ግቢ ትባላለች"። قال شيخ الإسلام ابن تيمية رحمه الله: "ليس علي المرأة بعد حق الله ورسوله أوجب من حق الزوج." (مجموع الفتاوى: 32/260) "በአንድ ሴት ላይ ከአሏህና ከመልክተኛው ሃቅ በመቀጠል የባልዋ ሐቅ ያህል ግዴታ የለባትም" سألت امرأة الشيخ الالباني رحمه الله አንድት ሴት ሸይኽ አልባኒን እንድህ ብላ ጠየቀች فقالت :يا شيخ قبل زواجي كنتُ فتاةً صوّامة قوّامة أجدُ لذةً للقرآن عجيبة والآن فقدتُ حلاوة الطاعات .. "አንተ ሸይኽ ከማግባቴ በፊት በጣም ፃሚ፣ በጣም ቋሚ በሚገርም ሁኔታ የቁርአንን ጥፍጥና አገኝ ነበር ፣ አሁን  (ካገባሁ በሃላ) ግን የመታዘዝን ጣዕም አጣሁት። قال : ما هي أخبارُ اهتمامك بزوجك  !؟ (ሸይኹም ) አሉ: ስለባልሽ ያለሽ ሀሳብ (እንክብካቤ) ወሬ (የምትይኝ) ምንድን ነው? قالت : يا شيخ أنا أسألك عن القرآن والصوم والصلاة وحلاوة الطاعة ..وأنت تسألني عن زوجي ! ؟ (እርሷም) አለች:- አንተ ሸይኽ እኔ ስለ ቁርአን ስለፆም ስለ ሶላት ስለመታዘዝ ጣዕም እየጠየቅኩህ አንተ ስለ ባሌ ትጠይቀኛለህ? አለች قال : نعم يا أختي .. لماذا لا تَجدُ بعض النساء حلاوة الإيمان ولذَّة الطاعة وأثر العبادة ؟ قال ﷺ : (ولا تَجدُ المرأة حلاوة الإيمان حتَّى تؤدِّي حقَّ زوجها) . (ሸይኹም) አሉ:- አዎን እህቴ ከፊል ሴት የኢማንን ጥፍጥና የመታዘዝን ጣዕም የዒባዳን ፋናን ለምን ይሆን የማታገኘው? የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንድህ አሉ: ("ሴት የኢማንን ጥፍጥና አታገኝም ፣የባሏን ሀቅ እስካላደረሰች ድረስ" ) 📚صحيح الترغيب والترهيب( 1939)             ✅ቴሌግራማችን ╰➤ ❝@Tidar_Be_Islam ╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ- ╰➤ ❝@Tidar_Be_Islam

✍ሁለት ዓይነት ሰዎች .. አጅግ ያሳዝናሉ! ①ኛ:ጀናዛው ካልሆነ እድሜ ልኩን መስጂድ ገብቶ የማያውቅ ወንድ። ②ኛ:ገላዋን ከፈን ካልሆነ በህይወት ዘመኗ በሂጃብ ያልተሸፈነች ሴት። አላህ ይጠብቀን አሚ
✍ሁለት ዓይነት ሰዎች .. አጅግ ያሳዝናሉ! ①ኛ:ጀናዛው ካልሆነ እድሜ ልኩን መስጂድ ገብቶ የማያውቅ ወንድ። ②ኛ:ገላዋን ከፈን ካልሆነ በህይወት ዘመኗ በሂጃብ ያልተሸፈነች ሴት። አላህ ይጠብቀን አሚን 🤲             ✅ቴሌግራማችን ╰➤ ❝@Tidar_Be_Islam ╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ- ╰➤ ❝@Tidar_Be_Islam

ኢብኑ ዑሰይሚን እንዲህ አሉ ፡   ≠በሁለት ጥንዶች መካከል ደስተኛ የትዳር ህይወት የሚገኘው ባል በሚስት ላይ ፅንፈኝነትና የበላይነትን በማንፀባረቅ አይደለም ❗ ይህ ትልቅ ስህተት ነው ❗   ~~ነገር ግን ባል ለሚስቱ ሊኖረው የሚገባው እይታ ፡ √√እርሷ የህይወት አጋሩ ፣ √√የልጆቹ እናት ፣ √√እና እንዲሁም የቤተሰቡ ተንከባካቢ አደርጎ ሊመለከታትና ይሄን ሊያውቅ ይገባል!!   እንዲሁም እርሷ እንድታከብረው እንደሚፈልግ ሁሉ እርሱም ሊያከብራት ይገባል✅             ✅ቴሌግራማችን ╰➤ ❝@Tidar_Be_Islam ╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ- ╰➤ ❝@Tidar_Be_Islam

💢የጁመዓ ቀን ሱናዎች 〰〰〰〰〰〰〰 ①) ሲዋክ መጠቀም ②) ገላን መታጠብ ③) ሽቶ መቀባት ④) ሱረቱ ከህፍን መቅራት ⑤) ጥሩ ልብስ መልበስ ⑥) በጧት ለጁመዓ ሶላት መሄድ ⑦) ዱአ ተቀባይነት ያለበትን ሰአት ስላለ መጠባበቅ ⑧) በነብዩ ﷺ ላይ ሰላትና ሰለዋት ማብዛት

ለመፈቀር ራስህን ብቁ አድርገክ ፍቅር ተነፍገክ ይሆን? ወይስ ፍቅርን ሳትሰጥ ፍቅርን መቀበል ከጅለክ ይሆን? የሆነው ይሁንና ይነበብልኝ እኔ መልዕክት አለኝ ወንድም ጋሼ ብዬ ልጥራህ እንዴ ዛሬ? ጫወታዬ ከባለ ትዳሮች ጋር ብቻ ነው ሌሎች ወደኋላ በሉልኝ! ይቅርታ ወንድም ጋሼ! ሌሎችን ሳባርር ነው። በትዳር ውስጥ ፍቅር አላቸው የሚባሉት ጥንዶች የፍቅር ተግባራት የሆኑትን እነዚህን ነገሮች አሟልተው ሲገኙ ነው። እነሱም፦በቃላትም ሆነ በተግባር መደጋገፍ፣ስለደህንነት መጠያየቅ፣በችግር ጊዜ መደራረስ፣በደስታ ጊዜ ደስታን መካፈል፣ከእኔ ይበልጥ ላንቺ፣ክኔ ይበልጥ ላንተ እየተባባሉ የቃላት እና የተግባር ልዩ ፈገግታ የተሞላበት ህይወት ሲኖሩ ነው። ይህንን ተግባር ለመፈፀም ከምንም በላይ ቅን ልብን ይሻል በመጀመሪያ ከጌታዋ ከአላህ ጋር መልካም ግንኙነት ያላት ልብ ስትሆን ለዚህች ልብ ይሄ ተግባረ ለመተግበረ በጣም ቀላል ይሆንላታል። ወንድም ጋሼ፦እሷ ላንተ ሁና መገኘት የምትፈልጋቸውን ነገራቶች በጠቅላላ እነተ ሆነክ ተገኝ እንድትከባከብህ ተንከባከባት፣ሃሳብክ እንድትጋራ ተጋራት፣ጭንቀትህ እንዲያሰጨንቃት ተጨነቅላት፣ደህንነትክ እንዲያሳስበት አስብላት፣በመልካም እንድታስቀድም አሰቀድማት እንድትዋብልክም ተዋብላት ፍቅር ሰጥቶ በመቀበል የተመሰረተ ነው አንዳንድ ሴቶች በመጀመሪያ የትዳር ህይወት ጊዜያቸው ዓይን አፍርነታቸው ቶሎ አይለቃቸውም በዚህን ጊዜ አደፍፍራት እንጂ እቺ ፋራ እያልክ አትውቀሳት በእርግጥ ብልጥ ነበርች እወድሻለሁ ስትላት እሷም እንድትልህ ጋብዛት፣ከሳምካት እንድትስምህ ጋብዛት፣እንድትዋብልክ በምትፈልገው አልባሳት በስጦታ መልክ አበረክትላት የትዳር አለም ሃሳቢነትን መልካም ተግባራትን እጅግ በጣም ደግሞ ቅን ልብን ይሻል እናንተ ባለትዳር ያልሆናችሁ ጥፉ ከዚይ ዋ! በቃ ተቀመጡ እንድተቀኑና ለማግባት ጥረት እንድታደርጉ ወንድም ጋሼ! እንግዲህ እንደተመካከር ነው አደራ ሴት ልጅ አያያዝ ትፈልጋለች የሙጥኝ የሚልባትንም አትወድም ችላ ብሎ የሚያጎሳቅላትንም አትወድም መካከለኛ ደረጃ ላይ አድርግ ራስክን መቆጣት ባለብክ ቦታ ምከራት ትዳርን ለመሰረታችሁ አላህ እሰከጀነት ያዝልቃችሁ ለምትናፍቁ አላህ በእዝነቱ ይረዝቃችሁ! አሚን።🤲🤲             ✅ቴሌግራማችን ╰➤ ❝@Tidar_Be_Islam ╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ- ╰➤ ❝@Tidar_Be_Islam

ትዳር በአንድ ጊዜ የሚገነባ ሸቀጥ ሳይሆን፣ ቀስ በቀስ የሚገነባ የሂደት ጥበብ ነው። ስኬታማ ትዳር ለመገንባት እርግጠኛ እና ይቅርታ ማለት እጅግ አስፈላጊ ነው። ☞ ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያ ረሒ
ትዳር በአንድ ጊዜ የሚገነባ ሸቀጥ ሳይሆን፣ ቀስ በቀስ የሚገነባ የሂደት ጥበብ ነው። ስኬታማ ትዳር ለመገንባት እርግጠኛ እና ይቅርታ  ማለት እጅግ አስፈላጊ ነው። ☞ ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያ ረሒመሁላህ እንዲህ ይላሉ፦ √√አንዲት ሴት ከባሏ ጋር መኗኗርን ካሳመረች ይሄ ☞አላህ እንዲወዳትና እንዲያከብራት ያደርጋታል።"√√ አልፈታዋ: 32/275             ✅ቴሌግራማችን ╰➤ ❝@Tidar_Be_Islam ╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ- ╰➤ ❝@Tidar_Be_Islam   

አሰላሙዓለይኩም ወረህማቱለሂ ወበረካትሁ ውድ እና የተከበራችሁ እህት ወንድሞቼ አንዴት ናችሁ ስለጠፋዉኝ ይቅርታ እጠይቃለሁ። አፉ በሉኝ በቻልኩት ሀቅም የምችለዉን ሁሉ ሼር አደርግላችኃለሁ  እናም ቻናለችንን ሼር በማድረግ ተባበሩን። አብረን ወደ እዉቀት።✍✍             ✅ቴሌግራማችን ╰➤ ❝@Tidar_Be_Islam ╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ- ╰➤ ❝@Tidar_Be_Islam

*هكذا الفرق بين المرأة المحتشمة والمرأة المتبرجة... لا يستطيع الذباب الدخول إلا إذا تبرجت...!* ✅ቴሌግራማችን ╰➤ ❝@Tidar_Be_Islam ╭
*هكذا الفرق بين المرأة المحتشمة والمرأة المتبرجة... لا يستطيع الذباب الدخول إلا إذا تبرجت...!*             ✅ቴሌግራማችን ╰➤ ❝@Tidar_Be_Islam ╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ- ╰➤ ❝@Tidar_Be_Islam

☹️☹️☹️🤩😜🥳😖☹️ የመጀመሪያው ፕሮግራም 📣  🥳🥳😣☹️☹️😭😏🤩 ​•┈┈•┈┈•⊰✿◇✿⊱•┈┈•┈┈• 🎤       ተ⭐️              ጀ⭐️                   መ⭐️                           ረ⭐️ ገባ ገባ በሉ ባረከሏሁ ፊኩም! ሊንኩን ለሌሎችም ሼር አድርጉት‼  ➘  ➘ ➘ ➘➘ ➘ ➘ ➘  ➘ ➘ ➘ https://t.me/tdarna_islam?livestream https://t.me/tdarna_islam?livestream

◾️የዙልሂጃ ቀናቶች መፃም 〰〰〰〰〰〰〰〰〰 «ኢማሙ ነወውይ አላህ ይዘንላቸውና እንዲህ አሉ።» «ዘጠኙ የዙል ሂጃ ቀናቶች መፃም በጣም የተወደደ ተግባር ነው። በተለይ ከነዚህ ቀናቶች ውስጥ የዘጠነኛውን
◾️የዙልሂጃ ቀናቶች መፃም 〰〰〰〰〰〰〰〰〰 «ኢማሙ ነወውይ አላህ ይዘንላቸውና እንዲህ አሉ።» «ዘጠኙ የዙል ሂጃ ቀናቶች መፃም በጣም የተወደደ ተግባር ነው። በተለይ ከነዚህ ቀናቶች ውስጥ የዘጠነኛውን የአረፋ ቀን መፃም ከሌሎቹ ቀናት በላጭ ነው።» 📚  (شرح مسلم 71/8) ↪️ ማሳሰቢያ‼️ ➖➖➖➖➖ ♦️👉መፃም የፈለገ ከነገ ሰኞ ጀምሮ መፃም ይችላል። ♦️👉አስረኛው የዙልሂጃ ቀን የኢድ ቀን ስለሆነ መፃም ስለማይቻል የሚፃመው ዘጠኙ ቀናቶች ብቻ ነው። ♦️👉እነዚህን ዘጠኝ ቀናቶች መፃም የተወደደ ተግባር እንጂ ግዴታ አይደለምና የፈለገ መፃም ያልፈለገ ማፍጠር ይችላል። ♦️👉እነዚህን ዘጠኝ ቀናቶች በተከታታይ መፃም መስፈርት አይደለም። አንድ ቀን እያፈጠረ ሌላውን ቀን መፃም ይችላል። ♦️👉በበሽታ፣ ሀይድም ሆነ በሌላ ምክንያት የተወሰኑ ቀናቶች ቢያመልጠው ከገራለት ጊዜ ጀምሮ የቀሩትን ቀናቶች መፃም ይችላል። ♦️👉መፃም የፈለገ ሰው ነገ እንደሚፃም በቀልቡ ማሰብ ብቻ በቂ ነው። ሌላ የሚባል የንያ ዚክር የለም።             ✅ቴሌግራማችን ╰➤ ❝@Tidar_Be_Islam ╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ- ╰➤ ❝@Tidar_Be_Islam

🔖 የአላህ መልእክተኛ ﷺ በነዚህ በአስሩ የዙልሂጃ ቀናቶች ውስጥ ዱአ ያበዙ ነበር። በተጨማሪም ተክቢር (الله أكبر) ተህሊል (لا إله إلا الله) እና ተህሚድ (الحمد لله) ማለትን
🔖 የአላህ መልእክተኛ ﷺ በነዚህ በአስሩ የዙልሂጃ ቀናቶች ውስጥ ዱአ ያበዙ ነበር። በተጨማሪም ተክቢር (الله أكبر) ተህሊል (لا إله إلا الله) እና ተህሚድ (الحمد لله) ማለትን በማብዛት ላይ ሰዎችን ያዙ ነበር። 📚[ #زاد_المعاد ٣٦٠/٢ ]             ✅ቴሌግራማችን ╰➤ ❝@Tidar_Be_Islam ╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ- ╰➤ ❝@Tidar_Be_Islam

መልካም ሚስት ልክ እንደጥቁር አዝሙድ ለእያዳዱ በሽታ መድሐኒት ነች ከሞት በስተቀር !! ወንድሞቼ አላህ ሷሊህ ሚስት ይወፋቃችሁ ✅ቴሌግራማችን ╰➤ ❝@Tidar_Be_Islam ╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊ
መልካም ሚስት ልክ እንደጥቁር አዝሙድ ለእያዳዱ በሽታ መድሐኒት ነች ከሞት በስተቀር !! ወንድሞቼ አላህ ሷሊህ ሚስት ይወፋቃችሁ       ✅ቴሌግራማችን ╰➤ ❝@Tidar_Be_Islam ╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ- ╰➤ ❝@Tidar_Be_Islam

🔖ባል ሚስቱን ኒቃብ ልበሺ ብሎ ማስገደድ ይችላል? ❗️የሚያሳዝነው ግን ብዙ ባሎች ኒቃብ ካላወለቅሽ ብለው ማስገደዳቸው ነው።             ✅ቴሌግራማችን ╰➤ ❝@Tidar_Be_Islam ╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ- ╰➤ ❝@Tidar_Be_Islam

❗️መህር ማስወደድ ብልጠት ሳይሆን ሞኝነት ነው።❗️ 👉ወርቅ ካልተገዛልኝ፣ ሻንጣ ልብስ ካልመጣልኝ፣ ከፍተኛ መህር ካልተከፈለኝ አላገባም አትበይ። በሀላል መሰተርሽ ላንቺ ትልቅ ክብር ነው። 👉መህር የተገደበ ባይሆንም ቀለል ማድረግ ግን የተወደደና ሱና ነው። መህርን ማስወደድ የሱናው ተቃራኒ ነው። ⇡☞መህርን ዝቅ ማድረግ የነብዩን ሱና መግጠም አለበት። በውስጡ ብዙ መስለሀና እርስ በርስ መተዛዘንም አለበት። ኒካህ እንዲበዛ በቀላሉ ለመጋባት መንገድ ይከፍታል። የዝሙትና የሀራም በር በእጅጉ ይዘጋል። በዚህ ላይ የነብዩን ሀዲስ እንመልከት፡ قال النبي صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ : (خير النكاح أيسره) رواه ابن حبان . وصححه الألباني في صحيح الجامع (3300) . وقال صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ : (خير الصداق أيسره ) رواه الحاكم والبيهقي . وصححه الألباني في صحيح الجامع (3279) . ☞መህር ማስወደድ መልካም ቢሆን ኖሮ የጀነት ሴቶች አለቃ የሆነችው የውዱ ነብይ ልጅ ፋጢማ መህር አንድ ልብስ ብቻ ባልሆነ ነበር። روى أبو داود (2125) والنسائي (3375) – واللفظ له - عَنْ ابْنِ عَبَّاسٍ أَنَّ عَلِيًّا قَالَ : تَزَوَّجْتُ فَاطِمَةَ رَضِيَ اللَّهُ عَنْهَا ، فَقُلْتُ : يَا رَسُولَ اللَّهِ ، ابْنِ بِي – وهو الدخول بالزوجة - . قَالَ : أَعْطِهَا شَيْئًا . قُلْتُ : مَا عِنْدِي مِنْ شَيْءٍ . قَالَ : فَأَيْنَ دِرْعُكَ الْحُطَمِيَّةُ ؟ قُلْتُ : هِيَ عِنْدِي . قَالَ : فَأَعْطِهَا إِيَّاهُ . صححه الألباني في صحيح النسائي (3160) . ✍የታላቁ ሶሀብይ የኡመር ምክር ይህንን ይጠቁማል። መህርን አታስወድዱ ልጆቻችሁ ከነብዩ ልጆች አይበልጡም። እሳቸው እንዳቀለሉት ቀለል አድርጉ እያለ ነው። وروى ابن ماجه (1887) أن عُمَرَ بْنُ الْخَطَّابِ قال : لا تُغَالُوا صَدَاقَ النِّسَاءِ فَإِنَّهَا لَوْ كَانَتْ مَكْرُمَةً فِي الدُّنْيَا أَوْ تَقْوًى عِنْدَ اللَّهِ كَانَ أَوْلاكُمْ وَأَحَقَّكُمْ بِهَا مُحَمَّدٌ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ مَا أَصْدَقَ امْرَأَةً مِنْ نِسَائِهِ وَلا أُصْدِقَتْ امْرَأَةٌ مِنْ بَنَاتِهِ أَكْثَرَ مِنْ اثْنَتَيْ عَشْرَةَ أُوقِيَّةً وَإِنَّ الرَّجُلَ لَيُثَقِّلُ صَدَقَةَ امْرَأَتِهِ حَتَّى يَكُونَ لَهَا عَدَاوَةٌ فِي نَفْسِهِ وَيَقُولُ قَدْ كَلِفْتُ إِلَيْكِ عَلَقَ الْقِرْبَةِ. صححه الألباني في "صحيح ابن ماجه" (1532) . ✍የምንጊዜም ውዱ የኢስላም መህር ብዙ ገንዘብ የተከፈለበት ወላ ሌላ ሳይሆን የእሙ ሱለይም መህር ነው። ነገሩ ወዲህ ነው፦ አቡ ጠልሀ እሙ ሱለይምን ለትዳር አጨ። አቡ ጦልሀ ሆይ! ያንተ አምሳያ ጥሩ ሰው ለትዳር መቶ አይመለስም። ነገር ግን አንተ ካፊር ነህ እኔ ደግሞ ሙስሊም ሴት ነኝ። ስለዚህ ላገባህ አልችልም። ከሰለምክ ግን "አገባሀለሁ" እሱ ነው መህሬ ሌላ አልጠይቅህም አለችው። ወዲያው ሰለመ መህሯም መስለሙ ሆነ። በኢስላም እጅግ ውዱ መህር ይህ ሆነ።             ✅ቴሌግራማችን ╰➤ ❝@Tidar_Be_Islam ╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ- ╰➤ ❝@Tidar_Be_Islam

✍ወደ ትዳር ስንገባ መሠረቱ ሀሳብ ነዉና ሀሳባችን ይስተካክል፡፡ በጥርጣሬና በግማሽ ልብ የሚገቡበት ቤት ከቶዉኑ ቤት ሆኖ ሊቆም አይችልም፡፡ ዕድሜም፣ ደስታም፣ በረከትም አይኖረዉም፡፡ ምንጊዜም ቢሆን
✍ወደ ትዳር ስንገባ መሠረቱ ሀሳብ ነዉና ሀሳባችን ይስተካክል፡፡ በጥርጣሬና በግማሽ ልብ የሚገቡበት ቤት ከቶዉኑ ቤት ሆኖ ሊቆም አይችልም፡፡ ዕድሜም፣ ደስታም፣ በረከትም አይኖረዉም፡፡ ምንጊዜም ቢሆን ጋብቻ ታላቅ እና የተከበረ ተቋም መሆኑን አንርሳ። ⇛ትዳር አላህን በመፍራት ከሐራም ለመሰተር ብለን የምንገባበት ማዕከል እንጂ ዱንያዊ ጥቅም ልናፍስበት፣ ብዙ የገንዘብ ትርፍ ልናጋብስበት የምንመሠርተው ሼር አይደለም፡፡ አላህ መልካሙን ትዳር ይወፋቃችሁ አሚን 🤲             ✅ቴሌግራማችን ╰➤ ❝@Tidar_Be_Islam ╭┈─────── ೄྀ࿐ ˊˎ- ╰➤ ❝@Tidar_Be_Islam