ch
Feedback
ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem

ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem

前往频道在 Telegram

የዘመናችንን ቀለም ያሳያሉ ያልናቸውን የዚህ ትውልድ የስነ ግጥም ውጤቶችን እንጋራ - እናጋራ። ለማካፈል የፈለጋችሁትን በGitem_Sitem ፣ gitemsitem@gmail.com የጸሃፊ ስም እና ርዕስ አክላችሁ ላኩልን። We are all about sharing this generation's poetry. Please email us your pieces gitemsitem@gmail.com

显示更多
1 720
订阅者
-124 小时
-47
-1430
帖子存档
ልወዳት እየጣርኩ ነው ቁንጅናዋን አይኔ አክብዶት ከልቤ ጋር ከመከረ ከጉያዋ የፈለቀ እሳት ውስጤን ካኮማተረ አቅሜን የያዘችው ቢመስላት እንዳሻት የምትዘውረው በቀና ልብ ተንደርድሬ ልወዳት እየጣርኩ ነው ከፍታ ቢሰማው ቀልቧ የወጣ መስሎት ከማማ ወስኜ ነበር ልረሳት ክብሬን እንዳላስቀማ ዛሬ 'ምማትር ዞሬ ገጿን እማይ አጮልቄ ልመራት እንጂ ደፍሬ አይደለም ብርሃን ናፍቄ እዩልኝ ሰዎች ልብ አርጉ ድብቅ መናፍስት ካሉበት በዐይኖቿ ሲበረግጉ ከጠረኗ እጣን ወጥቶ ንቦች ሲውረገረጉ ከአናብርት ቆዳ አብልጠው አዳኞች እሷን ሲወጉ ልብ አርጉ ሰዎች እዩልኝ የወፏ ዜማ ቢያቅታት ንፋስ ስታዜምብኝ ከአሳ ቀድሞ 'ሚበላሽ ፀዳሏን ስትበትንብኝ ከረግረግ ጨፌ በጥሼ በጣቷ 'ምታሾፍብኝ እዩልኝ ልብ አርጉ ሰዎች በየደፍ በአፀድ በጥጉ ስሜን ቆልላዋለች ደሞም በውበት ሰክራ ምኑምኔ ትላለች የልቧን መንፈቅ ከልላ በቀሪው ትጫወታለች ቁማር መሰላት መዋደድ የሆነ ስሜት አስይዞ የሆነ ስሜት ደብቆ ያልሆነ ንዴት መናደድ ይልቅስ አቅሜን እንዳሻት ቢመስላት የምትዘውረው እኔስ በቀና ልቤ ልወዳት እየጣርኩ ነው ሰይፈ ተማም 2010

በጾሙ ልቤ ጠረጠረ ነገር ነገር አለኝ ከተኩሎቹ መሃል ፍየል ቢጤ ባገኝ ስጋዋም ወተቷ መድሃኒት ነው አሉ ዘምዘም እጠጣለሁ ሲያሻኝ ከጠበሉ ወይ እታከማለሁ ደሞ በዶክተሩ ልቤ እንዲጠራልኝ እንዲቀለኝ ቂሙ እላለሁ ተኩሎቹም አብይን በጾሙ አብይን በጾሙ አብይን በጾሙ ሰይፈ ተማም 2010

ከመሬት ነኝ መሬት አይደል መነሻዬ መሬት ያጣሁ መሬት ሁኜ መነሳትን ተጠይፌ የወደቅኩኝ ተንሳፍፌ እኔም ራሴ መሬት ለመብቀያ ያበቀለኝ ከመሬት ነኝ? ከምሬት ነኝ? ከምር የት ነኝ? ቁንጥር አፈር ዘግኖ በእጁ ካበጃጀኝ ቁንጽል አንቀጽ ጠቅሶ በእጁ 'ሚያስፈጀኝ መሆኔ አይደለም ወይ ከመሬትም መሬት ሲረማመዱብኝ እንቁዬን ደብቄ በቀን እኩለ ሌት ሲዘንብ እምቦካ የቋጠርኩኝ አለት ሲያርሱ 'ምበረበር ሲበትኑ 'ምዘር የማያዳብረኝ የሰጡኝ ምርጥ ዘር አለቴን ገድዬ 'ማረገው አፈር ጨረቃን ጋርጄ ፀሃይ የምሰፍር ፀሃይ በዛ ብዬ ደሞ ምንጨረጨር ህዋ ላይ ተጥዬ የማርፍበት የናፈቀኝ አዎ መሬት ያጣሁ መሬት ነኝ ቀማሽ ምላስ ሰጥቶ ጣ'ም 'ሚያስቆጥረኝ ጣፋጭ ስኳር ነስቶ በጨዉ ሲያስመርረኝ መሆኔ አይደለም ወይ ከምሬትም ምሬት ወዳጄ ስሞታ ወዳጄ ጣ'ም ሃሞት የማያጣኝ ከቤት የማያጣኝ ከሬት ብሶት የወለደው ብሶ ያንገሸገሸኝ ጣ'ም ያጣሁ ምሬት ነኝ አገር ማለት መሬት አገር ማለት ምሬት አገር ማለት እኔ ተምታቶብኝ ድንገት መሬት ምሬት ምርየት መሬቱ ሰው አለው አለው የሰው ኩሩ 'ራሱን እማይነጥል ከዱሩ ከአፈሩ ሲጠብቃት ኖሮ ከሷው ነው አዳሩ ይኸም ሰው ጨፍግጓል መረሮታል ጠአሙ መጣፈጥ ጠፍቶታል መልኩም ሆነ ስሙ ለአንድ ቡሃቃ ሊጥ 20 ሺ እያሰሙ ከምር ወደየት ነው ከየት ወየት መንገድ (ከሰከሩም እንኳን) አይቶ ገምቶ ነው ኋላ መንገዳገድ ወይ የሚያቅፉ መስሎ ትከሻ መላመድ ወይ እራስን መብላት ከመሬት መዋደድ የምን ቆሞ መሄድ የምን ሄዶ መቆም በራስ ቤት መታሰር ቂም ይዞ እንደመፆም ለመዋደድ ነቅቶ በፍቅር ነው መሾም እንዳሹት ከምታሽ እንደ ደማከሴ የት እንዳለሁ ሳላውቅ አድር ይሆን ፈውሼ? ያለት ስንጣሪ ከምድር የቀረፀኝ ቅምሻ ፍርፋሪ ኮምጥጦ አገረሸኝ አይኔን አስጨፈነኝ ኸረ ከምር የት ነኝ? ታውሮ ሚመራው መንገዴን ነጠቀኝ እኔጠፋሁ ልበል ካለሁስ ወዴት ነኝ አገር ማለት መሬት አገር ማለት ምሬት አገር ማለት እኔ ተምታቶብኝ ድንገት ... ሆኜ ካለሁበት ሰይፈ ተማም 2010

ለመስራት ለመጨረስስ አልሰራም ለመስራት ልጨርስ እንጂ ተጨርሶ ሲመረቅ እንደሚታደስ መንገድ ስካሩ ጠፋ ሲባል መልሶ 'ሚንገዳገድ እንኳን ተሻለህ ሲሉት እንደሚያቃስት ህመመኛ ለመጨረስስ አንስራ ለመስራት እንጨርስ እኛ ሰይፈ ተማም 2010

እናታችሁንና 1.aac1.53 MB

ሁለት አለሜ መጀመሪያ ሳይሽ ልቤ ምቱ ጠፋው ግጥሜ ተበላሸ ቀለሙ እየሸሸ መጀመሪያ ሳውቅሽ ሰው አለኝ የሚለው ቃልሽ ልቤን ወጋ እንዴት ካንቺ ላውጋ ክንፍ ያለኝ ይመስልጊዜን መራመጃ ነገን ካንቺ ከረምኩ የዛሬዬን እንጃ ጸዳልሽን አየሁ ከጎኔ ሲበራ የቆዘመ ገጼን በሙቀት ሲጣራ ደሞም ደስስ እያለ መልሶ ሲያስፈራ እኔና አንቺ ብቻ ካለንበት ቦታ ከቦን ያለም ሃዘን ከቦን ያለም ሆታ ቅጽበታት ደምረን ስናረገው አፍታ ዱካክ እንዳጠረው እንቅልፍ አልባ ጊዜ ባንኖ መታ ልቤ ባንቺው ስልት አባዜ ሁለት አለም ኖረኝ አንደኛው የንቃት ሌላው የትካዜ ሰይፈ ተማም 2010

ሁለት አለሜ መጀመሪያ ሳይሽ ልቤ ምቱ ጠፋው ግጥሜ ተበላሸ ቀለሙ እየሸሸ መጀመሪያ ሳውቅሽ ሰው አለኝ የሚለው ቃልሽ ልቤን ወጋ እንዴት ካንቺ ላውጋ ክንፍ ያለኝ ይመስልጊዜን መራመጃ ነገን ካንቺ ከረምኩ የዛሬዬን እንጃ ጸዳልሽን አየሁ ከጎኔ ሲበራ የቆዘመ ገጼን በሙቀት ሲጣራ ደሞም ደስስ እያለ መልሶ ሲያስፈራ እኔና አንቺ ብቻ ካለንበት ቦታ ከቦን ያለም ሃዘን ከቦን ያለም ሆታ ቅጽበታት ደምረን ስናረገው አፍታ ዱካክ እንዳጠረው እንቅልፍ አልባ ጊዜ ባንኖ መታ ልቤ ባንቺው ስልት አባዜ ሁለት አለም ኖረኝ አንደኛው የንቃት ሌላው የትካዜ ሰይፈ ተማም 2010

ሰማይ ሆይ - ሰይፈ ተማም.aac7.78 KB

2.74 KB

ግዝት አድምጡኝ እንጂ አትስሙኝ በክፋት ጥላቻ በህይወት ገላችሁ ከነመፈጠሬም በቁሜ ረስታችሁ የአፈሬን ሳጥን በቅርቡ አይታችሁ እንዳታለቅሱልኝ ... ኻላ እንዳላዝንባችሁ አትክልት አይደለሁ እንባችሁ አይረባኝ ከሞት አለምልሞ ህይወት አይዘራብኝ እንዲያው ከንቱ ድካም እንዳይሆንባችሁ መኖሬን ከድታችሁ ሞቴን ካመናችሁ ያኔ... በበድኔ ዙሪያ እንዳላይ ከባችሁ በቁሜ እያለሁ ይኸው ገዘትኳችሁ። እንዳታለቅሱልኝ...!!! ኖታ

እዬዬ ከውዶቹ መሃል አንድ ሰው አነሰኝ ሀዘን ሆዴ ገብቶ እያንሰፈሰፈኝ ጠቆረብኝ ውስጤ ልቤም ጨላለመ ያሸከምኩት ተስፋ በአፈር አከተመ እዬዬ ለራሴ እዬዬ ለሃገሬ ታናሼ ሲቀድመኝ እኔ ተገትሬ እዬዬ ለቋሚ ውዱን ለሸኘ ሰው ከተመረጠማ የአብስራ ድንቅ ነው ሰይፈ

ውዴ ዝምታሽ ቢጨንቀኝ ቴክስትሽ ቢርቀኝ ስልኬ ያለልማዱ ብሬን ቢምርልኝ አፌን አሞጥሙጬ ልነግርሽ ቆረጥኩኝ እቱ የኔ አበባ.... ዝምታሽ ከባድ ነው ሆድን ያሸብራል ቀልብንም አርቆ አንጀት ያላውሣል..... ብዬ እንዳልልሽ.... ብዬ እንዳልልሽ ቃላት አይገዙ በቂ ስንኝ የለኝ እኔም ካንቺ የባስኩ ስንኞች የከዱኝ ብቻ.... ጀማሪ መሆኔ እንዳይነቃብኝ ኝ ኝ ኝ ..... እያልኩኝ መግጠሙ ደብሮኝ የሆዴን ሣልሸና ልተኛ ወሠንኩኝ። (እባክሽ አደራ እንዳትስቂብኝ.ኝ ኝ ኝ..) ኖታ

👆👆👆👆👆 writer...ናትናኤል "አብራራው G12"

40 ልብ አይ እታባ ... እንዴት ቀለድሽ ባክሽ ሆድ ሆዴን ቢበላው ይመጣል ማለትሽ አልታይህ ቢለኝ የያኔው ተረትሽ አልጨበጥ ቢለኝ የፊተኛው ተስፋሽ ይኸው እታባዬ ...... ቧልተኛ ነሽ አልኩሽ ቁጥር እንደው አያፍር ..... ደንደሱን አስፍቶ ደሞ እያጠበበ፤ ይከንፋል... ይበራል ሺዘጠኙን በቅጡ ሳንኖር፤ ፪ሺ ሠፍቶ ያተራምሰናል እሱ ምን አለበት..... እንዳባይ ይነጉዳል... እኔ አለሁ እዚ በሀሳብ የምርድ አርባዬን ቀርጥፌ አፋሽ የሆንኩ አመድ እና እታባዬ..... የታል ታድያ ያ ልብ የነገርሽኝ ቀድሞ በ40 ዘመኔ የማገኘው ቆሞ... (አልያም ተጋድሞ) ከብትንትን ኑሮ የሚገላግለኝ ከ40 ልብ ህይወት የሚያሰናብተኝ የታለ እታባ?? ... የታለ??...

ተወዳዳሪዬ ፍሰሐ ውድድሩን በአንደኝነት አጠናቅቋል ።

ምን_አገባህ_ምን_አገባሽ_ላሽ_ሰይፈ_ተማም.aac1.93 MB

0.88 KB

🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 በዚህ አመት ደግሞ ሌላ ውድድር አዘጋጅቼላችኋለሁ በማንኛውም ርዕስ ላይ የተጻፈ የራሳችሁ ግጥም ። format: ርዕስ ፣ ግጥም ፣ የጸሃፊ ስም መልካም ዕድል!!! ልብ በሉ ተሸላሚ የሚሆነው በብዙ ሰው የተወደደው ብቻ ሳይሆን የ 👎 ምልክት የተሰጠውም ጭምር ነው ። ለመላክ @seifetemam የሚለውን በመጠቀም በቀጥታ አድርሱኝ ። በድጋሚ መልካም በዓል!!! 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼