ch
Feedback
ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem

ግጥም ሲጥም - Gitem Sitem

前往频道在 Telegram

የዘመናችንን ቀለም ያሳያሉ ያልናቸውን የዚህ ትውልድ የስነ ግጥም ውጤቶችን እንጋራ - እናጋራ። ለማካፈል የፈለጋችሁትን በGitem_Sitem ፣ gitemsitem@gmail.com የጸሃፊ ስም እና ርዕስ አክላችሁ ላኩልን። We are all about sharing this generation's poetry. Please email us your pieces gitemsitem@gmail.com

显示更多
1 719
订阅者
-224 小时
-77
-1830
帖子存档
አራተኛው የግጥም ሲጥም ክፍት መድረክ - በሽፍታ! "ሰኔ 30" በቅርቡ መጽሐፍ ያሳተሙ ምርጥ ገጣሚያን የሚገኙበት ለሁሉም ክፍት የሆነ መድረክ ነው። በዚህ ዓመት የወጡ የግጥም መጻሕፍት ለሽያጭ ይቀር
አራተኛው የግጥም ሲጥም ክፍት መድረክ - በሽፍታ! "ሰኔ 30" በቅርቡ መጽሐፍ ያሳተሙ ምርጥ ገጣሚያን የሚገኙበት ለሁሉም ክፍት የሆነ መድረክ ነው። በዚህ ዓመት የወጡ የግጥም መጻሕፍት ለሽያጭ ይቀርባሉ፣ ገጣሚዎቹም እዛው ሊፈርሙላችሁ ይቻላሉ፣ ለበጎ አድራጎት ማሕበራትም መጽሐፍትን የምንለግስ በመሆኑ ወይ ይዛችሁ እንድትመጡ ወይም ከዛው ገዝታችሁ እንድትለግሱ አደራ እንላለን። በተቻለ መጠን ባህላዊ ልብስ ለብሳችሁ ብትመጡ የምናበረታታ ሲሆን ለኮቪድ - 19 የሚደረጉ ጥንቃቄዎች እንዳይዘነጉም ይሁን። ሰኔ 30 እንገናኝ!

Anthony is spoken word poet and a corporate emcee based in Maun, @Botswana. He is the Poetavango vice chairperson and the Coupe D’Afrique De Slam Poésie association, Africa Cup of Slam Poetry, Ambassador to Botswana. His discipline focuses, and speaks to, amongst many, issues of Pan-Africanism, spirituality, social justice and love. In addressing the issue of love, he intentionally writes primarily in Setswana (his indigenous language) as a way of playing a role in language preservation, as he believes that language is the most imperative aspect of culture. He writes with a primary aim of decolonizing himself and his people; to bring about awareness on the importance of Africa' self-determination and will in socio-political, cultural and economic issues. Good luck for Botswana. https://www.facebook.com/1719463041680780/posts/2630974210529654/ #AnthXny #Botswana #AfricanCupofSlamPoetry #CASP #PoeticSaturdays #poetry #poetryslam #poetrylovers #artinaddis #AddisAbeba #JulyNovember2021

So are all passengers comfortably seated? Welcome to Addis Ababa destination for one of the biggest public speaking event in
So are all passengers comfortably seated? Welcome to Addis Ababa destination for one of the biggest public speaking event in the world which will bring together more than 30 national Slam Poetry winners from African countries for the 2nd edition of African Cup of Slam Poetry July-November 2021.

ሐምሌ 5 በ11፡30 ብሔራዊ ቲያትር ተገኘተን ግጥም እንመርቅ! #ኤልያስ_ሽታኹን #ርእስ_የለውም
ሐምሌ 5 በ11፡30 ብሔራዊ ቲያትር ተገኘተን ግጥም እንመርቅ! #ኤልያስ_ሽታኹን #ርእስ_የለውም

ሐምሌ 5 በ11፡30 ብሔራዊ ቲያትር ተገኘተን ግጥም እንመርቅ! #ኤልያስ_ሽታኹን #ርእስ_የለውም

ሐምሌ 5 በ11፡30 ብሔራዊ ቲያትር ተገኘተን ግጥም እንመርቅ! #ኤልያስ_ሽታኹን #ርእስ_የለውም

This is the second edition of the African Cup of Slam Poetry Ethiopia is hosting. I will be sharing each competitors bio everyday expecting your support to the platform, the countries and also your representer, me 😬 ሁለተኛው የአፍሪካ የግጥም ግጥሚያ በኢትዮጵያ አዘጋጅነት ይካሄዳል:: ለዝግጅቱ፣ ለተወዳዳሪ አገራቱ እና ለሚወክላችሁ ሰውዬ (ልጅ😬) ድጋፍና ትብብራችሁን እንደምታሳዩ በማሰብ ስለተወዳዳሪዎቹ የሚገልጹ መረጃዎችን በየቀኑ አእናጋራችኋለን:: https://www.facebook.com/1719463041680780/posts/2630974210529654/

This is the second edition of the African Cup of Slam Poetry Ethiopia is hosting. We will be sharing each competitors bio eve
This is the second edition of the African Cup of Slam Poetry Ethiopia is hosting. We will be sharing each competitors bio everyday expecting your support to the platform, the countries and also your representative ሁለተኛው የአፍሪካ የግጥም ግጥሚያ በኢትዮጵያ አዘጋጅነት ይካሄዳል:: ለዝግጅቱ፣ ለተወዳዳሪ አገራቱ እና ለሚወክላችሁ ሰውዬ (ልጅ😬) ድጋፍና ትብብራችሁን እንደምታሳዩ በማሰብ ስለተወዳዳሪዎቹ የሚገልጹ መረጃዎችን በየቀኑ አእናጋራችኋለን:: https://www.facebook.com/1719463041680780/posts/2630974210529654/

ሰላም ሰላም ግጥማዊ ቅዳሜያውያን! እንዴት ከርማችኋል? ነገ ይውል የነበረው መደበኛው መድረካችንን በተለያዩ ምክንያቶች ማሰናዳት ስላልቻልን ወደሚቀጥለው ሳምንት : ቅዳሜ ሐምሌ ፫ ያዘዋወርነው መኾኑን
ሰላም ሰላም ግጥማዊ ቅዳሜያውያን! እንዴት ከርማችኋል? ነገ ይውል የነበረው መደበኛው መድረካችንን በተለያዩ ምክንያቶች ማሰናዳት ስላልቻልን ወደሚቀጥለው ሳምንት : ቅዳሜ ሐምሌ ፫ ያዘዋወርነው መኾኑን እወቁልን። መልካም ሳምንት! ግጥማዊ ቅዳሜ

‟አትበልጪም ከግጥም” [.... ‟መከዳት ቆሌ ናት ዛር አላት — መረሳት ከድታ የሄደች ሴት ጋርዳ — `ምታነግሣት» አላልኩሽም ነበር ? .....] .... [...ስትሄጂ ያተምሽው እያንዳንዱ — ኮቴ... ነፍስ `ሚዘመዝም ግጥም ነበር — እቴ!!...] .... [...ጥርቅም ያለውን በር ስትሄጂ — ከፍተሽው ነፍስ ነኪ ግጥም መግቢያ — አደረግሽው...] ... [...‟ደስታ ግን ጠበል ናት እምነት ጸሎት — ፍትሃት ሐሴት — ዞሮ መምጣት ቆሌ `ምታባርር ዛር የምትጋፋ ግጥም `ምታስጠፋ» ብዬሽስ አልነበር?...] .... [...ያ ሁሉ እርምጃሽ እያንዳንዱ — ቅርበት ናፍቆት የሚያተንን ተንኮል — ነበረበት...] ... [...ገላዬን ካቀፍሽው ከንፈሬን — ከሳምሽው የተዋረሰኝን ሰይጣን — አስቆጣሽው...] .... [...እዛው በጠበልሽ እዛው — እንዳትመጪ...! ምን ብትወደጂ ከናፍቆት ላትበልጪ...!...] ... [...የና`ት ያባቴ ነው ወል ቤት— ሰንጎ መገል ስንኝ ሳይቋጥሩ ቤት ድቤ ሳይመቱ የለም — መገላገል....] .... [...እዛው እንዳትመጪ ተከዳሁኝ ብዬ ተረሳሁኝ ብዬ ልቁረጥ — የነፍሴን ጥም እወድሻለሁ ግን አትበልጪም — ከግጥም...] ©️HEnock Bekele https://www.facebook.com/henock.bekele.79

My land bleeds from the same hands that once gardened her The soil now spits the blood of fathers and mothers fallen by the children they raised the echo screams the collective silence of the bystanders, us the poets the artists the composers the historians of our generation Too many voices to sound To many troops Too many tales Not enough of those to listen I break my pen For what good is there if my words can’t speak my people’s pain I empty the ink over the soil Where it’s the same as blood without its host I tear my paper apart For what good am I Writing of love amongst war Writing of hope standing over late bodies I am no longer a poet If cries and songs sound the same to my ears If I don’t recognize the faces beyond just news What good are my poems If my vocabulary is limited to the few emotions only my flesh knows What good are my poems If they can’t cross borders and fall with the falling Fight with the fighting Cry with the grieving Die with the dying What good are my poems If they can’t be a daughter to all the mother tongues If they can’t be the moon, the only light the feet can trust What good is my pen What good am I And so, I rest my pen In silence In doubt In question In resent In fear I rest my pen In everything but peace. ©️Everted

ግጥም ሲጥም በሰኔ ፴ በግጥም ሲጥም የክፍት መድረክ ክበብ ረቡዕ, ሰኔ ፴ ከ 12፡30 ጀመሮ ሽፍታ እንገናኝ። ልክ 1 ሰዓት ሲሆን ዝግጅቱ ይጀምራል። ስነ-ግጥም፣ ሙዚቃ፣ መጻሕፍት፣ የቁም ኩምክና፣
ግጥም ሲጥም በሰኔ ፴ በግጥም ሲጥም የክፍት መድረክ ክበብ ረቡዕ, ሰኔ ፴ ከ 12፡30 ጀመሮ ሽፍታ እንገናኝ። ልክ 1 ሰዓት ሲሆን ዝግጅቱ ይጀምራል። ስነ-ግጥም፣ ሙዚቃ፣ መጻሕፍት፣ የቁም ኩምክና፣ ስዕል እና ሌሎችም አዝናኝ የጥበብ ስራዎች ይቀርባሉ። ስራችሁን ለማቅረብ ማስፈንጠሪያውን ተጠቅማችሁ በምታገኙት ቅጽ ተመዝገቡ! https://forms.gle/WveKjAsZ5PBx9MVr9 Gitem Sitem is back with the Sene Selasa Edition. Gitem Sitem at Shifta is an open mic circle of fun and poetry with your hosts Heran and Seife We have very simple rules: 1. Sign up online https://forms.gle/oEbMTixhnKu4HKox7 or by the gate prior to the event 2. 5 minute per performer 3. Be respectful to the performers and all beings around you 4. Be you 5. Make sure you follow all the precaution measures for Covid 19 https://www.facebook.com/gitemsitem https://t.me/GitemSitem

Teraki has launched its Android app on June 30th, 2021 with 30 audiobooks and 100 original podcast episodes available for fre
Teraki has launched its Android app on June 30th, 2021 with 30 audiobooks and 100 original podcast episodes available for free. @ketsenatmagazine

“ይድረስ ወደ ግጥም ሰዎች” ከእሱባለው አበራ ንጉሤ ሥነ ግጥም በባሕርይው መንፈሳዊ ጥበብ ነው። ጥበብነቱም ለሥጋ ሳይሆን ለነፍስ ያደላል። ሲጻፍም በዓላማ ሳይሆን በመነካት ነው። ሲጻፍ በጠበቁት ሳይሆን ባልጠበቁት መወዝወዝ ነው። ሥነ ግጥም “ጻፍ፣ ለዚህ ቀንም አድርስ” ተብለህ እንደምትጽፈው የአምስተኛ ክፍል የአማርኛ ትምህርት የቤት ሥራ አይደለም። ቢያንስ ከዚያ ከፍ ይላል። እግዜርን እስክስታ ሲያስወርድ፤ ሰይጣንን ሱባዔ ያስገባል። አንዳንድ ግጥሞች ከፍጹም መመረር ይወለዳሉ። ያስቆጣሉ፣ ያስተክዛሉ፣ ያስለቅሳሉ፣ ያስደብታሉ፣ አብዮት ያስነሣሉ። ሌሎች ግጥሞች ደግሞ ከፍጹም ሐሴት ይፀነሳሉ። የታወከውን ያረጋጋሉ፣ ያስፈነድቃሉ፣ ያፍነከንካሉ። አንብበን የወደድናቸው ስንኞች በአንድም ሆነ በሌላ መንገድ እንዲህ ካለው መናጥ ውስጥ የተቀዱ ናቸው። ግጥሞቹን አንብበን ስንጨርስ ስሜታቸው ይጫነናል። ድባባቸው ይከተለናል። ሥነ ግጥም የቃላት ድሪቶን በጨበጡት ብዕር በኩል መትፋት አይደለም። የትኛውም ጥበብ ካላከበርከው አያከብርህም። ካልታመንክለት አይታመንልህም። ያለስሜት በቃል ማወቅ ሀኬት ስንኝ ስላማታህ በስምህ ላይ የገጣሚነትን ካባ አትከናነብም። ሲሞቅህ ስካርፍህን ከምታወልቅ “ገጣሚ መሰኘትን ማን ሰጠኝ?” አትልም? አንድ ግጥም አንብበህ “ገጣሚ እገሌ” ስትባል አትደነግጥም? “ሕዝቡ እንዲህ ዓይነት ግጥም ስትገጥም ነው የሚወደው” ስትባል አማትበህ አትሮጥም?? አንዲት ግጥምህን ከቅድመ አስተርእዮ በፊት ሲቀዷት፣ ሲጥፏት “በል እንካ ይህቺ ናት ግጥምህ፤ ወጥተህ የምታቀርባት” ሲሉህ “የፈጠርኳትን ከእነንፍጧ መልሱልኝ” ብለህ አትዋደቅም?? እንደ ገጣሚ አንተ ባልተነካህበት ግጥም ማንም አይነካልህም። ብዕር ከመጨበጥህ በፊት ራስህን መጠየቅ ያለብህ አንድ ጥያቄ አለ። “የእውነት ተነክቼያለሁ ወይ?” ታዲያ ለእንዲህ ዓይነቱ ጥያቄ አዎንታዊ ምላሽ ሳይኖርህ ስለምን ትጽፋለህ? ሳትናፍቅ ለምን እንደ ናፋቂ ትተክዛለህ? ጸጉርህንስ ስለምን ታፍተለትላለህ? ሳታፈቅር እንዳፈቀረ ለምን ትገጥማለህ? የሀገር ፍቅር ሳይገባህ ለምን “ዘራፍ” ትላለህ? ወይስ ተዋናይ ነህ?? እኮ ልብ በማይሞላ “አረ ጎራው” ከጀርባህ ማንን ልታሰልፍ ነው?? ምን መድረክ እንዲህ ቢወርድና ቢረክስ ግጥምን አቅለህ ታቀላለህ? ከእግራቸው ሥር ልትማር ከሚገቡህ ሰዎች እኩል ፎቶህን ነቅሰው ባነር ሲያሠሩል፣ ማይክ ሲያስጨብጡህ “ይህ ሁሉ ሲሆን የት ነበርኩ?” አትልም?የያዝከውን ውኃ ወደ ወይንነት እንድትቀይረው ሲጠይቁህ “እናንተ ሰዎች ከእኔ ምን አላችሁ? ጊዜዬ እንዳልደረሰ አታውቁምን?” አትልም?? የብሔራዊ ቴአትር መድረክ ላይ ውጣ ሲሉህ “በአገሩ ያለው አንጋፋ መድረክ ይሄው ነው። እንግዲህ እኔ ከወጣሁ ማን ሊቀር ነው?” ብለህ አታፈገፍግም?? የኢትዮጵያን ሕዝብ እንዴት ነው የምታስበው? ደደብ ነው የሚመስልህ? የፍረጃ ግጥምን ልክነት የምትለካው በአንድ አዳራሽ ጭብጨባ ነው?? እንዲያው የሥነ ግጥም ድንጋጌ ባይገድህ እንኳን “በማን የቴሌቪዢን (ትዕይንተ) መስኮት ማን ቤት ብቅ እንደምል አላውቅም!” ብለህ ቃላት አትመርጥም? ወዳጅህን ወዳጅነታችን ሳይዝህ እስከ መጨረሻው በግልጽነት ተቸኝ (ሕዝብ በአደባባይ ከሚሰድበኝ አንድ አንተ ወዳጄ በጓዳዬ አጥረግርገኝ!) አትለውም?? መሃል መሥመር ካለ እርሱ “ግጥም” ነው። ግጥም አንድ ያደርጋል። ግጥም መለያየትና መከፋፈል ባሉበት አይርገበገብም። ግጥም የፖለቲካ ፓርቲ የለውም። ግጥም “መድረኬን ስፖንሰር አድርገዋል” ያላቸውን በአይነኬነት አያስቀምጥም። ገጣሚም በዓለማዊ (secular) የግጥም መድብሉ የሃይማኖት ስብከት አያትምም። ይህ ጸያፍም፣ ነውርም ነው። የግጥም መድብልህን የሚገዛህ ሕዝብ አንድ ሃይማኖት፣ አንድ ብሔር የለውም። እና እናውቃለን በቴሌቪዥን መታየት ደስ ይላል። እውነት ነው በራዲዮም መደመጥ ደስ ይላል። ግን ከምንም ከምንም በላይ ለራሱ ያለው ከፍተኛ አመለካከት (egoው) እንቅፋት ያልሆነበት ሰው ደስ ይላል። መጽሐፍ ቅዱስ “ዋናዎቻችሁን አስቡ” እንዲል ዋናዎችህንስ ስለምን አታስብም? እነርሱ “ገጣሚ” በተባሉበት አገር አንተም “ገጣሚ” ትሰኝ ዘንድ የሚጠይቀው ይዘት (Package) እንዳለህና እንደሌለህ ራስህን አትገመግምም? እዚህ ሀገር ተወልደህ (ሀገሩ የእነተዋናይና መልክአብርሃኑ አድማስ ጀምበሬ አይደለ? ቅኔም አለልህ፤ መንዙማስ ሰምተህ ታውቃለህ?? እረኞች እንካ ሰላንቲያን ያውቃሉ፤ ጣቶች በገና ይደረድራሉ፤ አዝማሪዎች በመሰንቆና በክራር የታሸ ግጥም ያንቆረቁራሉ፤ በላ ልበልሃም አለልህ፤ እንቆቅልሽም የሕፃናት የቃላት ፍትፍት ነው፤ በቡሄ በሉ የስንቶቻችን ደጆች ተንጠዋል፣ ተርታ የገጠር ሰዎች በግጥም ያወጋሉ… እዚህ ሀገር ነህ። እዚህ አገርም ነበርህ።) እንዴት ዋና የለህም? ታዲያ መንገድ ሲጠፋህ ዘወር እያልክ እነ ጸጋዬ ገብረ መድኅንን፣ ገብረ ክርስቶስ ደስታን፣ ኃይሉ ገሞራውን፣ ደበበ ሰይፉን፣ ሰሎሞን ደሬሳን፣ ሰይፉ መታፈሪያን፣ መንግሥቱ ለማን፣ ሙሉጌታ ተስፋዬን፣ ፊርማዬ ዓለሙን፣ ከበደ ሚካኤልን፣ አያልነህ ሙላቱን፣ ዮሐንስ አድማሱን፣ ፈቃደ አዘዘን፣ ጌትነት እንየው… ንና መሰል ገጣሚያንን ዞረህ እንዳትቃኛቸው ማን አዚም አደረገብህ?? ጸጋዬ ገብረመድኅን ጼጥሮስ ያቺን ሰዓትን (ሰቆቃው ጴጥሮስን) ለምን ጻፈ?? አንጀቱ እስኪበጠስ ያነደደው ገጠመኝ አልነበረምን? ጻማቸው በእርሳቸው እግር ፈንታ ቆሞ እንደተቀበለ ሁሉ በቃለ ኃይሉ ሲቆስልብን ለምን ተሰማን?? ሙሉጌታ ተስፋዬ “እውነት ከመንበርህ የለህማ”ን ለምን ገጠመ?? በአጉል ፍልስፍና ተወጥሮ? ወይስ ልቡናው በወገኖቹ በደረሰ ርሀብና ቸነፈር ትውስታ ተሰቅዞ ነው?? ገብረክርስቶስ “ይናፍቀኝ ነበር” ሲል ነፍሱ በአገር ፍቅር እቶን እየነደደችበት አልነበረም ወይ?? ፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም “ብቸኝነት”ን ሲጽፉ በባይተዋር ሌሊት ነፍሳቸው ፍጹም አልነቃችባቸውም?? እንቅልፍ “እንቢ” አላላቸውም?? አንድ ግጥም አልቆ ከግርጌ የምታየው ቀን፣ ወርና ዓ.ም ያ ግጥም የተጻፈበትን ጊዜ ብቻ ሳይሆን እርሱን ግጥም ከእውነተኛ መነካት ለመጻፍ የታገሱበትን የጊዜ ሰሌዳም ይወክላል። እናም ኑር፣ እስከሚሰማህም ጠብቅ። ግጥም ያለምጥ አይወለድም። ለሐሳብህ ፅንስ ጊዜ ስጠው። ያለጊዜው የተወለደ ልጅ ጭንግፍ (ሽል) ነው። በጭብጨባ መሃል የማይሰሙ፣ የሚያልፉም ስንኞች ይኖራሉና ታዳሚም ሲያጨበጭብ ለተወለደ እንጂ ለሞተ እንዳይሆን በተናጥል ቀልብ መሰብሰቢያ ጊዜ ቢወስድ መልካም ነው። ግጥም ሆይ የባለቅኔ አባቶቻችን ዕዳ አለብንና እንወድሻለን። የቃለ እሳት ነበልባል ሳለሽ እናውቅሻለንና እሳት አመድ ወለደን አንተርትብሽም። በተወለዱት፣ እየተወለዱ ባሉትም፣ ወደ ፊት በሚወለዱት ልጆችሽም የማያልቅ፣ ዘውትር የሚታደስ ትንሣኤሽን እንናፍቃለን!

ቀን -፩ መገፋት Day 1 Pushed .......... @Ribki @Ribkiphoto
ቀን -፩ መገፋት Day 1 Pushed .......... @Ribki @Ribkiphoto

በይ አፈር እንጫር ምንም ባትናገር የዝምታዋ አድማስ ቃሏን ቢከልለኝ መድረስ እያማራት ሂወት መሮጥ ብቻ ሆነባት መሰለኝ . . . መሬትን ብቻ አምና.... (ነገሩን አልኩ እንጂ እምነት አይባልም ምርጫ ሲያጡ መውደድ በምን ይገለጣል ሰው ከመሬት ሽሸቶ ወደምን ያመልጣል?) ብቻ ለነገሩ... መሬትን ብቻ አምና መሬት ላይ ተቀምጣ እንዳቀረቀረች በሰንጣራ ነገር አፈር እየጫረች ተክዛ አገኘኋት ምነው በቀረብኝ ምነው ባላየኋት ''ተይ አታቀርቅሪ መኖር ግፈኛ ነው ከግፈኞች ቀድሞ ለግፍ ይመረጣ ጎንበስ ያለለትን ደጋግሞ ይረግጣል'' ልላት እየዳዳኝ ጉልበት እያገኘሁ ጉልበት እየከዳኝ ቀና አድርጌ ፊቷን ድርቀት ያሻከረው ከንፈሯን አልፌ ትኩስ እምባ ቀመስኩ ካይኗ ስር ጨልፌ ያኔ ቁስሏ ገባኝ ያኔ ሆዴን ባባኝ ''ተይ'' ልላት ያልኩትን ለራሴው ''ተው'' ብዬ ከጎኗ ተክዤ አብሪያት ተቀመጥኩ እኔም ስንጥር ይዤ ©️አማረ ዘውዱ