ወራቤ[ ደርሶች እና ፈዋኢዶች ]
前往频道在 Telegram
በሰለፊይ ኡስታዞች በሀገራችኝ በተለያዩ አከባቢዎች በሚገኙ መስጂዶች፣መርከዞች የሚሰጡ ደርሶች፣ኮርሶች፣ሙሓዳራዎች፣ እና የቁርዓን ተፍሲሮች እና ሙስሊሞችን የሚመለከት ልዩ ልዩ ወቅታዊ ጉዳዮች የሚለቀቁበት ቻናል ነው ። { وَقُل رَّبِّ زِدْنِى عِلْمًا } سورة طه : ١١٤ [ " ጌታዬ ሆይ! እውቀትንም ጨምርልኝ" በል። ] ሱረቱ-ጧሃ: 114
显示更多2 812
订阅者
-124 小时
无数据7 天
-1630 天
帖子存档
2 812
بسم الله الرحمن الرحيم
الحمد لله بنعمته تتم الصالحات، والحمد لله الذي وفقنا لإتمام هذا العمل، والصلاة والسلام على نبينا محمد ﷺ.
የወራቤ ሙስሊም ሴቶች ጀምዓ ያዘጋጀው የሴቶች በሴቶች የሸርዓዊ ኮርስ በስኬት ተጠናቀቀ
"አላህ ለአንድ ሰው ኸይርን ሲሻለት በዲኑ ያስገነዝበዋል።" የሚለውን የነቢያችን ﷺ ሐዲስ መሠረት በማድረግ፣ የወራቤ ሙስሊም ሴቶች ጀምዓ ለሙስሊም እህቶች ብቻ ያዘጋጀው የሶስት ቀን የሸርዓዊ እውቀት ኮርስ እሑድ 14/10/2018 ዓ.ም. በአላህ ፈቃድ በተሳካና በተዋበ ሁኔታ ተጠናቋል።
ከሁሉ በፊት ይህንን መልካም ሥራ ለማስጀመር፣ ለማስኬድና በውብ ፍጻሜ ለማድረስ ለወፈቀን አላህ ﷻ ወደር የሌለውን ምስጋና እናቀርባለን። ከዚያም ለዚህ ኮርስ መሳካት በዱዓ፣ በጊዜ፣ በገንዘብ፣ በጉልበትና በሃሳብ ድጋፍ ያደረጋችሁ ወንድሞችና እህቶች በሙሉ جزاكم الله خيرًا። አላህ ከሁላችሁም ይቀበል፣ ያደረጋችሁትንም በሚዛናችሁ ላይ የሚመዘን ሰደቃ ጃሪያ ያድርግላችሁ።
በኮርሱ የተዳሰሱ ዋና ዋና ርዕሶች
📖 1. አርካኑል ኢማን
የመጀመሪያው ቀን በእምነት መሠረቶች ላይ ያተኮረ ነበር። በተለይም በአላህ ማመን፣ በተውሒድ፣ በአላህ ስሞችና ባህሪያት፣ እንዲሁም በቀደር ማመን ላይ በሰፊው ተብራርቷል። ትምህርቱ አንድ ሙስሊም ሁሉንም ሥራውን በትክክለኛ አቂዳ ላይ መመሥረት እንዳለበት አሳስቧል።
👩👧 2. ተምሳሌታዊ እናትነት
ሁለተኛው ቀን መልካም እናት የመልካም ትውልድ መሠረት መሆኗ ተብራርቷል። ልጆችን በተውሒድ፣ በሶላት፣ በቁርኣንና በመልካም አኽላቅ ማሳደግ፣ ለእነርሱ መልካም አርአያ መሆንና በዱዓ አለመለየት የእያንዳንዷ ሙስሊም እናት ታላቅ ኃላፊነት መሆኑ ተወስቷል።
💰 3. آداب مع المال (ከገንዘብ ጋር ያሉ ኢስላማዊ ሥነ-ምግባሮች)
በመጨረሻው ቀን እስልምና በግብይትና በገንዘብ አያያዝ ያስቀመጠው ታላቅ ሥርዓት ተብራርቷል። የግብይት አርካኖችና ሸርጦች፣ የተፈቀዱና የተከለከሉ የግብይት አይነቶች፣ እንዲሁም ወለድ (ሪባ) እና ጉዳቱ በሰፊው ተዳስሰዋል። ከትምህርቱ የተገኘው ትልቁ መልእክት፣ "የሚያስፈልገን ብዙ ገንዘብ ሳይሆን ሐላልና በረካ ያለው ገቢ ነው" የሚል ነበር። ስለዚህ ሙስሊም በግብይቱ ውስጥ እውነተኛ፣ አማኝ እና ፍትሐዊ መሆን ይገባዋል።
መደምደሚያ
ይህ ኮርስ በአቂዳ፣ በቤተሰብ ግንባታ እና በኢስላማዊ ግብይት ዙሪያ ጠቃሚ እውቀቶችን ያካተተ የኸይር መድረክ ነበር። እውቀት የሚጠቅመው ግን ሲማር ብቻ ሳይሆን ወደ ተግባር ሲቀየር ነው። ስለዚህ አላህ የተማርነውን በሕይወታችን የምንተገብር ያድርገን፣ የተሳተፉትን እህቶች በእውቀታቸው ይባርክ፣ ያልተሳተፉትንም በሚቀጥሉት መሰል የእውቀት መድረኮች ለመሳተፍ ይወፍቃቸው።
በመጨረሻም ይህ ኮርስ እንዲሳካ ከጎናችን ለቆማችሁ፣ በማንኛውም መልኩ ላገዛችሁን ወንድሞችና እህቶች፣ ለኡስታዛችን፣ ለተሳታፊ እህቶች እና ለሁሉም ባለድርሻዎች ከልብ ምስጋናችንን እናቀርባለን። አላህ ከሁላችሁም ይቀበል፣ በዱንያም በአኺራም በኸይር ይመንዳችሁ።
وصلى الله وسلم على نبينا محمد، وعلى آله وصحبه أجمعين. وآخر دعوانا أن الحمد لله رب العالمين.
2 812
﷽
السلام عليكم ورحمة الله وبركاته
🌹 ውድ እህቶቻችን!
አልሐምዱ ሊላህ! በአላህ ፈቃድ የ"ሴቶች በሴቶች" የሦስት ቀን የእውቀት መርሃ ግብራችን ሁለተኛ ቀን በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።
📖 በመጀመሪያው ቀን በ"አርካኑል ኢማን" ርዕስ የእምነታችንን መሠረቶች ተምረናል። ኢማናችን እንዴት እንደሚጠና፣ በአምልኮአችን፣ በሥነ ምግባራችን እና በዕለት ተዕለት ሕይወታችን እንዴት ሊንጸባረቅ እንደሚገባ ተገንዝበናል።
🌷 በሁለተኛው ቀን ደግሞ "ተምሳሌታዊ እናትነት" በሚለው ርዕስ፣ እናት የቤተሰብ ልብ፣ የትውልድ አንፃሪ እና የማኅበረሰብ ግንባታ መሠረት መሆኗን በሰፊው ተምረናል። መልካም እናት መልካም ትውልድን ታንጻለች፤ መልካም ትውልድ ደግሞ መልካም ኡማን ይገነባል።
✨ እነሆ! ነገ የመጨረሻው ቀን ነው።
የመጨረሻው ቀን ብዙ ጊዜ ከሁሉም የበለጠ ልዩ ይሆናል፤ የቀደሙትን ትምህርቶች የሚያጠቃልል፣ የሚያነቃቃ እና በአላህ ፈቃድ በሕይወታችን ውስጥ የሚቆይ መልእክት የምንቋደስበት ቀን ነው።
🍃 ስለዚህ ውድ እህቶች! ይህን የበረከት ዕድል አታምልጡ። ነገ ቀድማችሁ ተገኙ፤ እህታችሁን፣ ጓደኛችሁን፣ ጎረቤታችሁንም ይዛችሁ ኑ። አንዲት ሰው ወደ ኸይር እንድትመጣ ምክንያት መሆን፣ በአላህ ዘንድ ታላቅ ምንዳ ያለው ተግባር ነው።
قال رسول الله ﷺ: «مَنْ دَلَّ عَلَى خَيْرٍ فَلَهُ مِثْلُ أَجْرِ فَاعِلِهِ» "ወደ ኸይር የመራ ሰው፣ ያንን ኸይር እንደሠራው ሰው ምንዳ ያገኛል።" (ሙስሊም)
🌹 ነገ ኢንሻአላህ በፈገግታ፣ በጉጉት እና በእውቀት ፍቅር እንገናኝ።
"የሚቀረው አንድ ቀን ብቻ ነው፤ ነገን አትናፍቁ!"
بارك الله فيكن، ونفع بكن الإسلام والمسلمين
✍ የወራቤ ሙስሊም ሴቶች ጀምዓ
2 812
﷽
አልሐምዱ ሊላህ ረቢል ዓለሚን
የሶስት ቀን ተከታታይ የእስላማዊ ትምህርት ኮርሳችን የመጀመሪያ ቀን "አርካኑል ኢማን" በሚል ርዕስ በአላህ ፈቃድ በእጅጉ የተሳካና የተዋበ በሆነ ሁኔታ ተጠናቋል።
በፕሮግራሙ በመገኘት ዕውቀትን ለመፈለግ የተጉ እህቶቻችንን፣ እንዲሁም ለፕሮግራሙ ስኬት የተባበራችሁን ሁላችሁን አላህ (ሱ.ወ.) በብዙ ኸይር ይክፈላችሁ፣ የተማራችሁትንም ለዱንያና ለአኼራ ጠቃሚ ያድርግላችሁ።
ኢንሻአላህ የነገው ሁለተኛ ቀን ፕሮግራም ከዛሬው የበለጠ በበረካ፣ በተሳካ ሁኔታ እንዲካሄድ ከአላህ (ሱ.ወ.) እንለምናለን።ዛሬ
ለመሳተፍ ያልቻላችሁም ነገ በሰዓታችሁ በመገኘት ከዚህ የእውቀት መድረክ እንድትጠቀሙ በአክብሮት እንጋብዛለን።
አላህ ሁሉንም ሥራችንን ለፊቱ ብቻ የተጣራ ያድርግልን፣ በእውቀት ያሳድገን፣ በሂዳያም ያፅናን። አሚን።
2 812
የጥያቄ እና መልስ ፕሮግራም ውጤት
1ኛ ,ረያን ካሚል ከአቡበክር መድረሳ
2ኛ ,ሀምዛ ጃቢር ከዛዱል ቁሉብ መድረሳ
3ኛ ,ኑህ ሱለይማን ከሰአድ መድረሳ
2 812
የተወዳዳሪዎች ስም እና የመጡበት መድረሳ
1,ረያን ካሚል ከአቡበክር መድረሳ
2,አ/ናስር ሙሳ ከቢላል ቀርሾ መድረሳ
3,ፈውዛን አክመል ከአልከሶ ኑበላ መድረሳ
4,ኑህ ሱለይማን ከሰአድ መድረሳ
5,ሀምዛ ጃቢር ከዛዱል ቁሉብ መድረሳ
6,ሱደይስ ሙህዪዲን ከ ኢብኑ አባስ መድረሳ
2 812
ቀጥታ ስርጭት | LIVE
ታላቅ የዳዕዋ ፕሮግራም
በሚከተለው ሊንክ ይከታተሉ 👇
https://t.me/fewaidworabe?livestream
🕌በወራቤ ከተማ ኡመር መስጂድ
2 812
Repost from N/a
የሰላተል ኢስቲስቃእ ጥሪ!🗓ሀሙስ:ሰኔ 4/2018 ⏰ከጠዋቱ 3:00 📍ቦታ፦ወራቤ እስታዲየም ✅ ዑመር መስጅድ እና መድረሳ(ወራቤ)
2 812
📚 شرح الحديث 📚
ما ترَكَ النبيُّ صلَّى اللهُ عليه وسلَّمَ خَيرًا فيه صَلاحُ الدِّينِ أو الدُّنيا، إلَّا ووَجَّه إليه وحَثَّه عليه، وما تَرَكَ شَرًّا يَضُرُّ بالمؤمِنِ في دِينِه أو دُنياهُ، إلَّا وحَذَّرَه منه.
وفي هذا الحَديثِ يَذكُرُ صلَّى اللهُ عليه وسلَّمَ أنَّ السَّفرَ إلى بلَدٍ أُخرَى غيرِ بلدِ الإقامةِ جُزءٌ مِنَ العَذابِ، والمرادُ بذلك العَذابُ الدُّنَيويُّ، ثُمَّ علَّل ذلك بِقولِه: «يَمنعُ أحدَكم طَعامَه وشَرابَه ونومَه»، أي: كَمالَ ذلك ولَذَّتَه؛ لِما فيه مِن مُعاناةِ الحَرِّ والبرْدِ، والخَوفِ، ومُفارَقةِ الأهْلِ والأصحابِ، وخُشونةِ العَيشِ، فيُؤخِّرُ المسافرُ أكْلَه ونَومَه عن وَقْتِه المألوفِ، ولا يَحصُلُ له منْه القدْرُ الكافي أو اللَّذَّةُ المُعتادةُ.
ثُمَّ أوصَى صلَّى اللهُ عليه وسلَّمَ المسافِرَ بِأنَّه إذا قضَى حاجتَه الَّتي سافَرَ مِن أجْلِها، وانتهى مِنها؛ فعليه أنْ يُعجِّلَ بِالرُّجوعِ إلى وَطَنِه وأهلِه؛ لِيقْطَعَ هذا العَذابَ الَّذي سَيَستمِرُّ بِسَفرِه، ولكى يَتعوَّضَ مِن ألَمِ ما نالَهُ مِن ذلك، فيَنالَ الراحةَ والدَّعةَ في أهْلِه. وعُبِّرَ بالنَّهْمةِ التي هي بُلوغُ الهِمَّةِ؛ إشعارًا بأنَّ الكلامَ في سَفَرٍ لأربٍ دُنيويٍّ، كتِجارةٍ، دونَ السَّفرِ الواجبِ، كحجٍّ، وغزْوٍ.
وليس كَونُ السَّفرِ قِطعةً مِن العَذابِ بمانعٍ أنْ يكونَ فيه مَنفعةٌ ومَصحَّةٌ لكَثيرٍ مِن الناسِ؛ لأنَّ في الحَرَكةِ والرِّياضةِ مَنفعةٌ، ولا سيَّما لأهْلِ الدعةِ والرَّفاهيةِ، كالدَّواءِ المُرِّ المُعْقِبِ للصِّحَّةِ وإنْ كان في تَناوُلِه كَراهيةٌ.
وفي الحديثِ: كَراهةُ التَّغرُّبِ عن الأهلِ لغيرِ حاجةٍ.
وفيه: حثُّ المسافرِ على استِعجالِ الرُّجوعِ مِن السَّفرِ إلى أهْلِه، ولا سيَّما مَن يُخشَى عليهم الضَّيعةِ بالغَيبةِ.
وفيه: أنَّ في الإقامةِ في الأهلِ راحةً مُعِينةً على صَلاحِ الدِّينِ والدُّنيا.
وفيه: التَّرغيبُ في الإقامةِ؛ لئلَّا تَفوتَه الجُمعاتُ والجَماعاتُ، والحقوقُ الواجبةُ للأهلِ والقَراباتِ.
@الجميع
مصدر الشرح الدرر السنية 📚
#شرح_الحديث
اللهم صلِ وسلم وبارك على محمد وعلى آله وأصحابه أجمعين
2 812
🔈 የጁሙዓህ ኹጥባህ
📖ርዕስ፦እግር ኳስ እና ችግሮቹ!
📍ቦታ፦ ወራቤ ከተማ
🌇መስጅድ፦ ዑመር መስጅድ
🎙 በሸይኽ ኑረዲን ኸሊል
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
