ch
Feedback
Construction Proxy

Construction Proxy

前往频道在 Telegram

#1 construction portal to get: ✅ construction news ✅ construction market ✅construction materials price ✅engineering estimates ✅ Sub contract https://constructionproxy.com Address any comment to admin👨‍💼 @ConproxyBot

显示更多

📈 Telegram 频道 Construction Proxy 的分析概览

频道 Construction Proxy (@constructionproxy) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 19 518 名订阅者,在 商业 类别中位列第 3 477,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 1 726

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 19 518 名订阅者。

根据 19 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -5,过去 24 小时变化为 -2,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 30.91%。内容发布后 24 小时内通常能获得 9.21% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 6 033 次浏览,首日通常累积 1 797 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 30

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
#1 construction portal to get: ✅ construction news ✅ construction market ✅construction materials price ✅engineering estimates ✅ Sub contract https://constructionproxy.com Address any comment to admin👨‍💼 @ConproxyBot

凭借高频更新(最新数据采集于 20 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 商业 类别中的关键影响点。

19 518
订阅者
-224 小时
-17
-530
帖子存档
#EthiopiaCheck Scam Alert አሁንም ራሳችንን ከአታላዮች እንጠብቅ--- ከኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን ኮርፖሬሽኑ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ፋኩልቲ እና የንግድ ሥራ ት/ቤት በታህሳስ ወር 2013 ዓ.ም በየሙያ መስኩ እና በየደረጃው ተመዝግበው መስፈርቱን ላሟሉ አመልካቾች ሰጥቶት በነበረው ፈተና ከማለፊያ ውጤት በታች ያገኙ ማለትም ከ 60% በታች ውጤት ያላቸውን ተወዳዳሪዎችን ስልክ እየደወሉ ገንዘብ ክፈሉና እናስቀጥራችኋለን በማለት የሚያታልሉ እና የኮርፖሬሽኑን መልካም ስም የሚያጎድፉ አጭበርባሪዎች እንዳሉ ወደ መ/ቤታችን በመምጣት ካመለከቱ ተወዳዳሪዎች መረዳት መቻሉን በመግለፅ የሚመለከታቸው አካላት ከመሰል አታላዮች እራሳቸውን እንዲጠብቁ ኮርፖሬሽናችን ቀደም ሲል ማሳሰቢያ መስጠቱ ይታወሳል፡፡ ይሁን እንጂ በአሁኑ ወቅትም ይህ የማታለል ድርጊት በሌለ መልኩ ቀጥሎ ስልክ እየደወለ ገንዘብ ከከፈላችሁኝ ከኮርፖሬሽኑ አንዱ ፕሮጀክት ወደ ሌላው እንድትዛወሩ አደርጋለሁ የሚል ግለሰብ ስለመኖሩ ይኸው የማታለል ሙከራ ደረሰብን ካሉ ግለሰቦች መረጃ ደርሶናል፡፡ በመረጃው መሠረት ይህን የማታለል ሙከራ እያደረገ ያለው ከዚህ ቀደም ኮርፖሬሽኑ በሰጠው ማሳሰቢያ ላይ ረቡኒ ኢሳያስ በሚል ስምና የስልክ ቁጥር 0966459226 በባንክ ሒሳብ ቁጥር 1000338403422 ገንዘብ አስገቡ እና ሥራ አስቀጥራችኋለው እያለ የማታለል ሙከራውን የቀጠለው ይኸው ግለሰብ ገንዘብ ክፈሉና ትዛወሩበታላችሁ በሚል የሚጠቅሰው ፕሮጀክት በአሁኑ ጊዜ ሥራ ላይ የሌለ እና ቀደም ብሎ የተዘጋ ነው፡፡ በመሆኑም የሚመለከታችሁ አካላት ይህንኑ በመገንዘብ ከመሰል የመጭበርበር ጥቃት ራሳችሁን እንድትጠብቁ ኮርፖሬሽኑ በጥብቅ እያሳሰበ ጉዳዩን በሕግ አግባብ እየተከታተለው መሆኑን በድጋሚ ለማስታወስ ይወዳል፡፡

photo content

የታጣቂዎች ጥቃት የ10 ሰዎችን ህይወት ቀጠፈ። • 10 ሰዎች ተገድለዋል። • የሟቾች አስክሬን ዛሬ አርብ ለቤተሰቦቻቸው ይሰጣል። ከቀናት በፊት በደቡብ 'አማሮ ልዩ ወረዳ' አካባቢ ታጣቂዎች የሁለት
የታጣቂዎች ጥቃት የ10 ሰዎችን ህይወት ቀጠፈ። • 10 ሰዎች ተገድለዋል። • የሟቾች አስክሬን ዛሬ አርብ ለቤተሰቦቻቸው ይሰጣል። ከቀናት በፊት በደቡብ 'አማሮ ልዩ ወረዳ' አካባቢ ታጣቂዎች የሁለት ወጣት ኢንጂነሮችን ህይወት በግፍ ማጥፋታቸውን ከሰማን በኃላ ዛሬ ደግሞ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ታጣቂዎች በፈጸሙት ጥቃት በመንገድ ግንባታ ሥራ ላይ ተሰማርተው የነበሩ 10 ሰዎች በአሰቃቂ ሁኔታ መግደላቸውን ሰምተናል። ይህን መረጃ ይፋ ያደረገው ቢቢሲ የአማርኛው ክፍል ነው። ጥቃት ተፈፅም የሰዎች ህይወት መጥፋቱን የምዕራብ ሸዋ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ዲሪርሳ ዋቁማ ያረጋገጡ ሲሆን ጥቃቱ በዞኑ ሜታ ወልቂጤ ወረዳ "ሎያ ጎዳኔ" ቀበሌ ውስጥ ረቡዕ ሰኔ 09/2013 ዓ.ም አመሻሽ 12 ሰዓት አካባቢ መፈፁም ገልፀዋል። በታጣቂዎች የተገደሉት የፌደራል እና የኦሮሚያ መንገዶች ባለስልጣን ባለሙያ የሆኑ 9 ሰዎች እና የቀበሌው ነዋሪ የሆነች አንዲት ሴት ናቸው ብለዋል። ጥቃቱ በተፈጸመበት መኪና ውስጥ ከነበሩ 11 የመንገድ ሥራ ባለሙያዎች በሕይወት የተረፉ መኖራቸውንም አክለዋል። በጥቃቱ የተገደሉት ሰዎች አስከሬን አዲስ አበባ ወደሚገኘው ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል መላኩን እና ለቤተሰቦቻቸው መርዶ መነገሩን ጠቅሰው አስከሬናቸው ዛሬ አርብ እንደሚሰጥ ተናግረዋል። አቶ ዲሪርሳ ፥ ጥቃቱ ከተፈጸመባቸው አስራ አንድ የመንገድ ግንባታ ባለሙያዎች መካከል ከግድያው ያመለጡት ሁለቱ "በአካላቸው ላይ የደረሰ ጉዳት የለም፤ ደህና ናቸው" ብለዋል። በምዕራብ ሸዋ ዞን አስተዳዳሪ ጥቃቱን የፈጸመው "ኦነግ-ሸኔ" የተባለው ቡድን እንደሆነ ገልፀዋል። ያንብቡ : https://telegra.ph/BBC-06-18 @tikvahethiopia

Several cement plants in #Ethiopia will undergo maintenance beginning next month, aggravating fears that shortages in supply will send retail prices through the roof. Via - AddisFortune

የታጣቂዎች ጥቃት የሁለት ወጣት ኢንጂነሮችን ነፍስ ነጠቀ። በኮንስትራክሽን የስራ ላይ ተሰማርተው በሙያቸው ሀገራቸውን እና ህዝባቸውን እያገለገሉ የነበሩ ሁለት ወጣት ኢንጂነሮች በታጣቂዎች ተገደሉ። #
+3
የታጣቂዎች ጥቃት የሁለት ወጣት ኢንጂነሮችን ነፍስ ነጠቀ። በኮንስትራክሽን የስራ ላይ ተሰማርተው በሙያቸው ሀገራቸውን እና ህዝባቸውን እያገለገሉ የነበሩ ሁለት ወጣት ኢንጂነሮች በታጣቂዎች ተገደሉ። #አሥራት_ሺካ እና #ሮቤል_ልደቱ የተባሉት ወጣት ኢንጂነሮች ትላንት ሰኔ 8/2013 ለሥራ ጉዳይ "አማሮ ልዩ ወረዳ" ሲጓዙ "ጀሎ" በምትባል ቀበሌ በታጣቂዎች በተከፈተባቸው ተኩስ ህይወታቸው አልፏል። ሁለቱም ወጣት ኢንጂነሮች ባላቸው እውቀት ህዝባቸውን እና ሀገራቸውን በማገልገል ላይ እያሉ ነው በታጣቂዎች በግፍ የተገደሉት። የወጣቶቹን ግድያ የአማሮ ልዩ ወረዳ ፖሊስ ፅ/ ቤት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ያረጋገጠ ሲሆን ጉዳዩን ለደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አሳውቀናል ብሏል። በሌላ በኩል የደቡብ ክልል ኮንስትራክሽን ባለልስጣን ባወጣው የሀዘን መግለጫ ወጣት ሮቤል ልደቱ የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የመንግስት ፕሮጀክቶች ግንባታ ጥራት ክትትል እና ቁጥጥር ስራ ሂደት ባለሞያ እንደነበር ገልጾ በህልፈቱ የተሰማውን ሀዘን ገልጿል። ባልስልጣኑ 'ድንገተኛ ህልፈተ ህይወት' ብሎ ከመግለፅ በዘለለ ዝርዝር መረጃ አልሰጠም። የደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ስለግድያው ፣ ጥቃት ፈፃሚዎቹ ስለመያዛቸው እና ሌሎች ተያያዥ መረጃ እንዲሰጠን ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም። @tikvahethiopia

photo content

ገምሹ በየነ ኮንስትራክሽን በ4.2 ቢሊዮን ብር መንገድ ሊገነባ ነው ከ4.2 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ ኦሮሚያ እና ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልልን የሚያስተሳስረው 160 ኪ.ሜ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ተጀመረ፡፡ የግንባታ ስራውን የሚያካሂደው ገምሹ በየነ ኮንስትራክሽን ኋ/የተ/የግ/ማ የተባለ አገር በቀል የስራ ተቋራጭ ድርጅት ነው፡፡ የመንገዱን ጥራት ቁጥጥር እና የማማከር ሥራዎችን የሚያከናውነው ደግሞ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ዲዛይን እና ቁጥጥር ስራዎች ድርጅት ነው። የግንባታዉ ወጪው የሚሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ሲሆን፣ ፕሮጀክቱ በሶስት አመታት ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃል። መንገዱ በገጠር ከ8-10 ሜትር ߹ በቀበሌ 12 ሜትር፣ በወረዳ የእግረኛ መንገድን አካቶ ከ19-24 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ይገነባል።

የኮንስትራክሽን ብቃት ማረጋገጫ እና ምዝገባ አዲስ መመሪያ ወጣ ************* የኮስተባ ሕዝብ ግንኑነትና ኮሙኒኬሽን ሰኔ 7 ቀን 2013 ዓ.ም ************* የኮንስትራክሽን ባለሙያ፣ አማካሪ፣ የስራ ተቋራጭ ብቃት ማረጋገጫና ምዝገባ እንዲሁም የኮንስትራክሽን ፕሮጀክት ምዝገባ መመሪያ 648/2013 በአዲስ መልክ ፀድቆ መውጣቱ ተመለከተ፡፡ በዚሁ መሰረትም የቀድሞው የኮንስትራክሽን ባለሙያዎችና ስራ ተቋራጮች የምዝገባ መመሪያ ቁጥር 19/2005፤የኮንስትራክሽን ዲዛይን ባለሙያዎችና አማካሪዎች ምዝገባ መመሪያ ቁጥር 22/2005 ፣ እንዲሁም የቀድሞውን መመሪያ ተከትሎ ወጥተው የነበሩ መስፈርቶችም አዲስ በፀደቀው የኮንስትራክሽን ብቃት ማረጋገጫና ምዝገባ መመሪያ ቁጥር 648/2013መሰረት የተሻሩ መሆናቸው ተመልክቷል:: ይህ የተመለከተው የኮንስትራክሽን ስራዎች ተቆጣጣሪ ባለስልጣን የህግ ዝግጅት ኮድና ስታንዳርድ ዳይሬክቶሬት ለተቋሙ የምዝገባና ሰርተፊኬሽን ስራ ክፍል ሀላፊዎችና ሰራተኞች እንዲሁም በዘርፉ የሚመለከታቸውን የተጠሪ ተቋማት ሃላፊዎችና ባለሙያዎችን አዲስ በፀደቀው የኮንስትራክሽን ብቃት ማረጋገጫና ምዝገባ መመሪያ ቁጥር 648/2013 ላይ በቢሾፍቱ ከተማ ሰሞኑን ባተዘጋጀ የስልጠና መርሃግብር ነው፡፡ በስልጠናው ላይ እንደተመለከተው አዲሱ የኮንስትራክሽን ብቃት ማረጋገጫና ምዝገባ መመሪያ ቁጥር 648/2013 ከረቂቅ ዝግጅቱ አንስቶ አስከ ፀደቀበት ድረስ የተከናወኑ ተግባራት፣ መነሻ መርሆዎቹና አስፈላጊነቱ ተብራርቷል፡፡ በዋናነትም ሀገራዊ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ተሳታፊዎችን በጥራት እና በብዛት ለማሳደግ ብሎም ውድድሩን ለማስፋት ዕድል የሚፈጥር መመሪያ ሆኖ መዘጋጀቱ ነው የተመለከተው፡፡ በተያያዘም የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ሀገርንና ህዝብን ወደ ብልፅግና የሚያሸጋግር መደላድል እንዲሆን የሚስችለውን የአፈፃፀም ሚና ማሳደግ ፣ የምዝገባ አገልግሎት አሰጣጥንና የመረጃ አያያዝን ምቹና ዘመናዊ ማድረግ፣ በኢንዱስትሪው ውስጥ የተንሰራፋውን ብልሹ አሰራር ማስወገድ፣ ዘርፉ ዕውቀት መር እንዲሆን ማስቻል የመመሪያው አበይት መርሆዎች እንደሆኑም ተገብራርቷል፡፡ ኢንዱስትሪው በፕሮጀክቶች አፈፃፀም ማለትም በጊዜ፣ በዋጋ፣ በጥራት እና በደህንነት ረገድ ያሉበትን አሉታዊ ገፅታው እንዲለወጥ የሚያስችል ምቹ የአሰራር ስርዓትን መዘርጋትም ሌላው መርህ ነው፡፡ እንዲሁም ኢትዮጵያን በቀጣይ አስር ዓመታት ውስጥ አፍሪካዊት የብልፅግና ተምሳሌት ለማድረግ የተያዘውን ራዕይ ለማሳካት በሚደረገው ርብርብ ውስጥ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው የላቀ ሚና እንዲጫወት ማስቻልም ትኩረቱ ነው፡፡ አዲሱ የኮንስትራክሽን ብቃት ማረጋገጫና ምዝገባ መመሪያው ከረቂቅ ጀምሮ እስከ ፀደቀበት ድረስ በተለያዩ ባለድርሻ አካላት እየታየ ያለፈባቸውን ሂደቶች፤ በዝግጅት ሂደቱ ውስጥም የተገኙ ግብዓቶች ተካትተው በጠቅላይ አቃቤ ሕግ አማካኝነት ግብዓት ተሰጥቶ የጸደቀ መሆኑም ተብራርቷል፡፡ በመመሪው የሚካተቱ የግንባታ ተዋናዮችና ዘርፎች፣ የመመሪያው ይዘቶች፣ የሚጠበቁ መስፈርቶች፣ የብቃት አረጋጋጭ እና መዝጋቢዎች ኃላፊነቶች የሚሉና ተያያዥ የሆኑ ጉዳዮች ላይ ያጠነጠኑ ሰነዶች ለሰልጣኞች ቀርበዋል፡፡ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ለስራ አፈፃፀም ተግዳሮት ናቸው እንዲሁም መሻሻል ይገባቸዋል ያሏቸውን አስተያየቶች ሰጥተዋል፤፡ በዋናነትም ከፍትሃዊ አሰራር፣ ሚዛናዊነት ከመጠበቅ፣ ከመረጃ ነፃነት፣ ከመመሪው አስገዳጅነት እና ከአሻሚነት አንፃር ይሻሻሉ ሏቸውን ሃሳቦች አካፍለዋል፡፡ በአጠቃላም ሀገራዊ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪውን ከፍ ከማድረግ አኳያ በመመሪው ውስጥ መካተት ያሉባቸው እንዲሁም እርምት ያስፈልጓቸዋል ያሏቸውን አስተያየቶች ሰጥተዋል፡፡ በቀረቡ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ላይ የተለያዩ የስራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ግብረመልስ ሰጥተዋል፡፡ መሰረታዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይም መመሪያው እንደገና እርማት የሚወሰድበት አግባብ በቀጣይ የሚታይ መሆኑም ተመልክቷል፡፡ በዋናነት ግን መመሪው በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ላይ መሰረታዊ ለውጥ እንዲመጣ፣ ተወዳዳሪነቱ እንዲያድግ፣ ሙያ እና ዕውቀት ተኮር እንዲሆን፣ የተሳለጠና አስተማማኝ መረጃ እንዲፈጠር፣ የአሰራር ስርዓቱ እንዲዘምን፣ ከፍተኛ የሆነ የስራ ዕድልን እንዲፈጥር፣ ሙዊ ስነምግባር እና ሕጋዊነት እንዲሰፍን፣ ጥራትና ደህንነቱ የተረጋገጠ የግንባታ ስርኣት እውን እንዲሆን ለማስቻል ወሳኝነቱ ተሰምሮበታል፡፡

% of urban households in Africa who can afford the cheapest newly built house in 2020 According to the research based on inco
% of urban households in Africa who can afford the cheapest newly built house in 2020 According to the research based on income data, 3.52% Ethiopians can afford US $17, 226 for houses. @Businessinfoeth

PROJECT MANAGER WALIIF CONSTRUCTION SHARE COMPANY CIVIL ENGINEERING CONTRACT May 16, 2021 - May 21, 2021 Description Job Requirement Education: BSc in Civil Engineering or Construction Technology & Management Related Experience: 10 years and above Place of Work: Project Sites (out of Addis Ababa) How to Apply Closing Date:5 (five) consecutive days from the first date of announcement Interested applicants who fulfill the above requirements can submit their application with non- returnable copies of the CV’s. Address: Arat Kilo, Infront of Berhanena Selam Printing Press at Dink Sira Building 8th Floor Tel. 0118124767 Email: wcsc1002@gmail.com

photo content

Eid Mubarak

photo content

መንግስት በሲሚንቶ ገበያ ላይ የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት እየሰራ ባለበት ወቅት ነጋዴዎች ኩንታል ሲሚንቶ እስከ 800 ብር በመሸጥ ቀድሞ የተረበሸውን ገበያ ማናጋታቸውን ቀጥለዋል ፡፡ በክፍት ገበያ ውስጥ በሕገወጥ መንገድ እየጨመረ የመጣው የሲሚንቶ ዋጋ በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ላይ ተግዳሮቶችን አስነስቷል ፡፡ መንግስት የአቅርቦት ሰንሰለቱን ለማሻሻል እና ለኮንስትራክሽን ዘርፍ ዋነኛው የሆነውን የሲሚንቶ ዋጋ ለመቆጣጠር በርካታ እርምጃዎችን እየወሰደ ነው ፡፡ ነገር ግን በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች በምሽት ሰዓት ሲሚንቶ ጅምላ ሻጮች በአንድ ኩንታል እስከ 800 ብር ሲሚንቶ እየሸጡ መሆናቸውን ካፒታል ታዝባለች ፡፡ ህገወጥ ደላሎችን ለመቆጣጠር መንግስት ከ 233 ብር እስከ 300 ብር ባሉት ለተዘረዘሩት 12 የሲሚንቶ ፋብሪካዎች የፋብሪካ ማምረቻ ዋጋ አስቀምጧል ፡፡ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከአንድ ወር ጀምሮ በገበያው ውስጥ የሚስተዋለውን የሲሚንቶ እጥረት በዘላቂነት ለመፍታት በመሞከር በፋብሪካዎች ውስጥ የበላይ ተመልካቾችን በመመደብ ሥራቸውን በመቆጣጠር ላይ እና በየከተሞቹ በከንቲባዎች የሚምራ ግብረ ኃይል አደራጅቶ እየሠራ ነው የሚሉት የሚኒስቴሩ ተጠባባቂ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ካሳ አላምረው ሆኖም ችግሩ ጥልቅ በመሆኑንና የአቅርቦት ችግሩ እስካልተፈታ ድረስ በቁጥጥር ስር ለማዋል አስቸጋሪ መሆኑን ይገልፃሉ፡፡ https://www.capitalethiopia.com/featured/cement-price-spike-stiffens-market/

Chinese companies dominated the list of Top Construction contractors in #Africa 1. Sinohydro Corporation 2. China Civil Engineering Construction Corporation (CCECC) 3. China Henan International Cooperation Group Company Limited 4. China Communications Construction Company(CCCC) 5. China Harbour Engineering Company (CHEC) 6. China Road and Bridge Corporation 7. SOGEA-SATOM 8. Mota-Engil China 9. Geo-Engineering Corporation (CGC) (Centum real estate)

List of contractors from grade 1 - 6 ከ ደረጃ 1 - 6 ያሉ ኮንትራክተሮች https://constructionproxy.com/catalog/contractors-in-ethiopia

No dude, you don't get to use this formula , u just have to use ERA manuals.
No dude, you don't get to use this formula , u just have to use ERA manuals.

" The bridge over the Kebenà River built by Germany and Italy near their respective legations "
" The bridge over the Kebenà River built by Germany and Italy near their respective legations "

ማሳሰቢያ ሀሙስ ሚያዚያ 14 ቀን 2013 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ የወጣውን የስራ ማስታወቂያ በተመለከተ የፈተና ቀኑን ወደፊት በባለስልጣኑ የፌስቡክ ገፅ የምናሳውቅ ይሆናል፡፡
+1
ማሳሰቢያ ሀሙስ ሚያዚያ 14 ቀን 2013 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ የወጣውን የስራ ማስታወቂያ በተመለከተ የፈተና ቀኑን ወደፊት በባለስልጣኑ የፌስቡክ ገፅ የምናሳውቅ ይሆናል፡፡