Abu Hayder Aliy
前往频道在 Telegram
显示更多
未指定国家未指定类别
380
订阅者
+124 小时
+37 天
+1630 天
帖子存档
🚨 ታላቅ የደዕዋና የገራዶ ቢላል መስጅድ ጉብኝት ጥሪ 🚨
ለአላህ ዲን ኻዲም የሆናችሁ ውድ ወንድምና እህቶች!
እነሆ የፊታችን ሐሙስ ከምሽቱ የዒሻእ ሶላት እንደተሰገደ ታላቅ ፕሮግራም ተዘጋጅቶ ይጠብቆታል።
📌 የፕሮግራሙ ርዕስ፦
"ለመስጅዱ የገቢ ማስገኛ በምን አይነት አሰራርና ዘዴ?"
(የገራዶ ቢላል መስጂድ ጉብኝትና የገቢ ማሰባሰቢያ ውይይት)
⏰ የፕሮግራሙ ሰዓት፦
🇪🇹 በኢትዮጵያ፦ ከምሽቱ 2:30 ሰዓት ጀምሮ
🇸🇦 በሳዑዲ፦ ከምሽቱ 8:30 ሰዓት ጀምሮ
🇦🇪 በዱባይ፦ ከምሽቱ 9:30 ሰዓት ጀምሮ
🎤 ተጋባዥ እንግዶች፦
• የተለያዩ እህትና ወንድሞች
• በቴሌግራም እና በዋትስአፕ ግሩፖች ላይ ያላችሁ አባላት በሙሉ
💎 ፕሮግራሙ በተለያዩ ወንድሞች ይመራል (ኢንሻ አላህ)። ይህንን መልዕክት ሼር በማድረግ የኸይር ስራው ተካፋይ ይሁኑ! ቢያንስ ታተርፉበታላችሁ እንጂ አትከስሩበትም።
💳 የባንክ አካውንት ቁጥር (የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ)፦
👉 1000616592673
📍 አድራሻ፦ ገራዶ እንዶድ በር ቢላል መስጅድ
🔗 የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ፦
👉 t.me/geradobilalmesjid
👉 t.me/geradobilalmesjid
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
የዑሥማን እና የሑሰይን ሞት
~
ዑሥማን ብኑ ዐፋን እና ሑሰይን ብኑ ዐሊይ ሁለቱም በጀነት የተመሰከረላቸው ሶሐቦች ናቸው። ሁለቱም በግፍ ነው የተ7ደሉት።
* ዑሥማን ኸሊፋ ነበሩ። አምፀው በወጡባቸው ሰዎች ነው ደማቸው የፈሰሰው። ሑሰይን ኸሊፋ አልነበሩም። እንዲያውም በመሪ ላይ የወጡት። ይሁን እንጂ ወደ መካ ለመመለስ፣ ወይም ከሙስሊሙ ሰራዊት ጋር ለመቀላቀል ወይም ደግሞ ወደ የዚድ ለመሄድ ጠይቀው ነበር። ይሄ ማለት 7ዳዮቻቸው እምቢ ብለዋቸው እንጂ በወጡበት አቋም ላይ አይደለም የሞቱት ማለት ነው።
* ዑሥማን ከነብያችን ﷺ በኋላ የኡማው ሶስተኛው ታላቅ ሰው ናቸው። በደረጃ የሚበልጧቸው አቡበክርና ዑመር ብቻ ናቸው። ከሑሰይን ጋር የሚቀራረቡ አይደሉም።
* በዑሥማን ግdያ ዐሊይን የሚከሱ አሉ። በሑሰይን ግ^ድያ ላይ ደግሞ የዚድን የሚከሱ አሉ። ሁለቱም ለሙግታቸው ትክክለኛ መረጃ ማቅረብ አይችሉም። መረጃ እስካልቀረበ ድረስ ደግሞ ዐሊይም ከዑሥማን ደም ንፁህ ናቸው። የዚድም ከሑሰይን ደም ንፁህ ነው።
* የዚድ በሑሰይን 7ዳዮች ላይ እርምጃ አለመውሰዱን ለክሳቸው ማሳመኛ የሚያደርጉ አሉ። ነገር ግን 0ሊይም በዑሥማን 7ዳዮች ላይ እርምጃ አልወሰዱም። ለምን? የተለያዩ ሀሳቦች ይሰነዘራሉ። ሐቂቃውን አላህ ያውቃል። ነገር ግን "እርምጃ ያልወሰዱት እጃቸው ቢኖርበት ነው"፣ ወይም "የደረሰው ቢያስደስታቸው ነው" የሚል የግምት ሃሳብ ከመሰንዘር ይልቅ ጉዳዩን ለአላህ መተው ነው የሚሻለው።
ከሁለቱ ክስተቶች ጀርባ ያደፈጡ ሁለት ቡድኖች አሉ። የዑሥማንን ግ^ድያ እነ ዐሊይን ለማጣጣል የሚጠቀሙት "ነዋሲብ" የሚባሉ አካላት አሉ። ቁጥራቸው እዚህ ግባ የሚባል ባይሆንም ዛሬም ድረስ አሉ። የሑሰይንን ግድያ በኑ ኡመያን አልፎም ሰፊውን ህዝበ ሙስሊም ለመጥላት የሚጠቀሙት ደግሞ "ረዋፊድ፣ ሺ0ዎች" ናቸው። (የሚገርመው ሑሰይንን ጎትጉተው የጠሩትም ራሳቸው፣ ሲደርስ አብሮ ከመሰለፍ ይልቅ ጥለውት የከዱትም ራሳቸው ኩፋውያን ሆነው ሳለ ኋላ ከሳሽ የሆኑትም ራሳቸው ናቸው።)
ለማንኛውም ዑሥማንም ሑሰይንም በግፍ ነው የሞቱት። ሃዘንን ለፖለቲካ መሸቀጫ ማዋል ቢፈቀድ ኖሮ ዑሥማን ላይ የደረሰው ግፍም፣ የዑሥማን ደረጃም ከሑሰይን የሚበልጥ እንጂ የሚቀርብ አልነበረም።
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
ሞት አላህ በሰው ልጅ ላይ የወሰነው አይቀሬ እጣ ፈንታ ነው። ሁሉም ነፍስ ሞትን ቀማሽ ናት። ከፊሉ በህመም፣ ከፊሉ በአደጋ፣ ከፊሉ በሰው እጅ ይሞታል።
በታሪክ በግፍ ህይወታቸውን ያጡ ታላላቆች አንድና ሁለት አይደሉም። ሑሰይን ብኑ ዐሊይ በዚህ ላይ የመጀመሪያም የመጨረሻም አይደሉም። አሳዛኝ አሟሟታቸው እለቱን በያመቱ እንድናስብ አያደርገንም። ይሄ የሺዐ እንጂ የአህለ ሱና መንገድ አይደለም። በአሳዛኝ ሁኔታ በሰው እጅ የሞቱት ኸሊፋው ዑሥማን ብኑ ዐፋንን የሞቱበትን እለት በያመቱ ጥቁር ለብሰው አካላቸውን እያደሙ፣ ደረታቸውን እየደቁ አያሳልፉም ሙስሊሞች። ይሄ በሑሰይን ሞት ጥላቻ የሚዘሩና ፖለቲካ የሚሸቅጡ ሺ0ዎች መንገድ ነው።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
ኢብኑ_ዑሰይሚን ረሒመሁሏህ እንዲህ ይላሉ : -
«እንስሳቶች እየበሉ፣ እየጠጡና እየተኙ ብቻ እንደሚኖሩት ልንኖር አይደለም ወደ ዱንያ የመጣነው። ይልቁንም ለአኺራህ ስንቅ እንድናዘጋጅ እንጂ!»
📚 ۞ الكــفايــة الشـــافـــيــة【4/279】۞
https://t.me/abu_hayder_aliy
https://t.me/abu_hayder_aliy
ለማስታወስ
ነገ ሰኞ ነው የቻለ ይፁም ያልቻለ ያስታውስ
አሏህ እርሱን በመታዘዝ እና በመገዛት ያግዘን ያረበል አለሚን ሳትቀጣን ማረን ሳትቀጣን ወዳንተ መልሰን ልባችንን አንተን በመፍራት እና በአንተ ፍቅር ሙላልን ኣሚን🤍
Repost from 📚መርከዝ አቡ_ረያን Online የቁርኣን መድረሳ📚
✋የዘንድሮው የዐሹራ ፆም (የሙሐረም 10ኛው) ቀን ሐሙስ ሰኔ 18 ላይ ይውላል። ይህንን ታላቅ ቀን መፆም ያለፈውን የ365 ቀናት (የአንድ ዓመት) ወንጀል ያስምራል።
በላጩና ተመራጩ አፆፃም...ነብዩ (ﷺ) አይሁዶችን ለመለየት ዘጠነኛውንም ቀን አብሮ ለመፆም አስበው ስለነበር፣ በላጩ መንገድ ረቡዕ (ሰኔ 17) እና ሐሙስን (ሰኔ 18) አከታትሎ መፆም ነው።
ሌሎችንም በማስታዎስ የአጅሩ ተጠቃሚ ያድርጓቸው!
~
t.me/Sle_qelbachn1
t.me/Sle_qelbachn1
📚 “የአሊሞች ቃል ልብን ያረጋጋል…”
🌿 ጣፋጭ ፣ ልብን የሚያረጋጉ ፣ ጥበብን የተሞሉ እና ኢማንን የሚጨምሩ
📖 የኡለሞች ውብ ንግግሮችን በየቀኑ ለማግኘት አሁኑኑ " JOIN " በማለት ይቀላቀሉን 👇
+1
~አንድ ወጣት አንድ ሸይኽ ዘንድ ደውሎ አንዲህ ሲል ጠየቃቸው፦
ያ ሸይኽ ጥያቄ ነበረኝ?
ሸይኹ፦ መርሃባ መጠየቅ ትችላለህ።
ወጣቱ፦ሰለፎቻችን ከቁርዐን ጋር የነበራቸው ሁኔታ እንዴት ነበር? አብራሩልኝ
ሸይኹ፦በአሁን ዘመን ወጣቱ ከስልኩ ጋር እንደማይላቀቀው እነሱም ከቁርዐን ጋር አይላቀቁም ነበር።
ኢብኑ_ዑሰይሚን ረሒመሁሏህ እንዲህ ይላሉ : -
«ነፍስ ከፈጣሪዋ ከራቀች ለፍጡራን አታዝንም!!»
📚 ۞ الـشـرح المـمــتـــع【10/223】۞
https://t.me/abu_hayder_aliy
https://t.me/abu_hayder_aliy
