ch
Feedback
የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት-Ethiopian Archives and Library Service

የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት-Ethiopian Archives and Library Service

前往频道在 Telegram

.ይህ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ይፋዊ የቴሌግራም ቻናል ነው፡፡

显示更多
未指定国家未指定类别
514
订阅者
无数据24 小时
无数据7
无数据30
帖子存档
ኀዳር 22/2018 ዓ.ም ልዩ የእውቀት ድግስ ለአንባብያን በሙሉ። በአዲስ አበባ "lgnite   Your Love For Words!" በሚል መሪ ቃል የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን 75 ዓመት በዓል ምክንያት በማድረግ አዲስ ሊትሬቸር ፌስቲቫል ከነገ ኀዳር 23/2018 ዓ.ም እስከ ታህሣሥ 5/2018 ዓ.ም የንባብ ሳምንት ፌስቲቫል አዘጋጅቷል። በዝግጅቱም የሥነ ጽሑፍ መድረክ፣የመጻሕፍት አውደ ርዕይ፣የደራስያን ተሞክሮ፣የደራሲያን የዝክር መድረክ ወዘተ መዘጋጀቱን በተላከልን ፕሮግራም አሳውቆናል በዝግጅቱ መሳተፍ ለምትፈልጉ በወጣው ፕሮግራም መሠረት መታደም የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።

የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን የሀገራችን ሕዝቦች የማንነት መገለጫ ነው፡፡ (ክብርት ወ/ሮ ነፊሳ አልማህዲ) ኀዳር 20/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ 20ኛው የብሔሮች፣ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በፓናል ውይይት ተከበረ፡፡ ዘንድሮ ለ20ኛ ጊዜ ሕዳር 29 የሚከበረውን የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት፣ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እና ከሌሎች የተጠሪ ተቋማት አመራርና ሠራተኞች ጋር በፓናል ውይይትና በሌሎች ዝግጅቶች በብሔራዊ ቲያትር አዳራሽ በድምቀት አክብረዋል። የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ ነፊሳ አልማህዲ የጋራ ስምምነት የፀደቀበት ኀዳር 29 ቀን የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በሚል ስያሜ በየዓመቱ በተለያዩ ዝግጅቶች እንዲከበር ውሳኔ እንደተላለፈና የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን የሚከበርበት ዋነኛ ምክንያትም ለዘመናት የቆየው የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች የእኩልነት፣የዴሞክራሲና የፍትህ ጥያቄ ለመመለስ፣የሀገሪቱን የፌዴራል አስተዳደር ሥርዓት ለማጽናት እና ብዝሃነትን ማክበርና እኩልነትን ማረጋገጥ ያስቻለ መሆኑና ለዚህም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የብሔር፣ብሔረሰቦች ባህልና ቋንቋ ተጠብቀውና ለምተው ለትውልድ እንዲተላለፉ በኃላፊነት እየሰራ እንደሚገኝ ተናረዋል፡፡ በዓሉ የሀገራችን ሕዝቦች የማንነት መገለጫ በመሆኑ በየዓመቱ በድምቀት የምናከብረው ታላቅ በዓላችንም ነው ብለዋል፡፡ “ ዲሞክራሲያዊ መግባባት ለኀብረ ብሔራዊ አንድነት!” በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው 20ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ብሔረሰቦች ሕዝቦች ቀን በዓልን ምክንያት በማድረግ ”ዲሞክራሲያዊ መግባባት እና ሕብረ ብሔራዊ አንድነት“ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ መነሻ ሰነድ በባህልና ስፖርት ሚኒስቴር የሚኒስትር አማካሪ በአቶ አለማየሁ አርጋው ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል። ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!! ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr Twitter:https//@wemezekr

ኀዳር /2018 ዓ.ም አዲስ አበባ የሀገሪቷ አጠቃላይ የመረጃ ሀብቶች የሚገኝበትን ታላቅ ተቋም በማስጎብኘት ልጆች ኢትዮጵያዊ ባህላቸውን ማወቅ የሚያስችል ጉብኝት ተካሔደ፡፡ ሙሉ ለሙሉ በብሪቲሽ የትም
+6
ኀዳር /2018 ዓ.ም አዲስ አበባ የሀገሪቷ አጠቃላይ የመረጃ ሀብቶች የሚገኝበትን ታላቅ ተቋም በማስጎብኘት ልጆች ኢትዮጵያዊ ባህላቸውን ማወቅ የሚያስችል ጉብኝት ተካሔደ፡፡ ሙሉ ለሙሉ በብሪቲሽ የትምህርት ስርዓት የሚማሩ የብሪቲሽ ኢንተርናሽናል ትምህርት ቤት በቁጥር 19 ተማሪዎች የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎትን ጎብኝተዋል፡፡ ተማሪዎቹ በጎብኝታቸው በዩኒስኮ በዓለም ቅርስነት የተመዘገቡ፣ለመመዝገብ በሒደት ላይ ያሉትንና ተጠብቀው የሚገኙትን የጽሑፍ ቅርሶች የሚገኙበትንና የማይክሮ ፊልም ክፍል፣ የህጻናት ቤተ መጻህፍት በጥልቀት ሲጎበኙ ሌሎች የተቋሙን አገልግሎት መስጫ ክፍሎችን ተመልክተዋል፡፡ በጎብኝቱ የተገኙት ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ በብሪቲሽ የትምህርት ስርዓት የሚማሩ እንደሆኑም ተጠቁሟል፡፡ትምህርት ቤቱ ከእነርሱ በተጨማሪ በኢትዮጵያ ስርዓተ ትምህርት መሰረት ትምህርት እንደሚሰጥና ተማሪዎችም እንዳሉት በጉብኝቱ ላይ ነግረውናል፡፡ የጉብኝቱ ዓላማም ልጆቹ ከኢትዮጵዊ ቤተሰብ የተገኙና ኢትዮያዊ ስለሆኑ የሀገራቸውን ባህልና ታሪክ እንዲያውቁ ለማስቻል እንደሆነም ተጠቁሟል፡፡ ተማሪዎቹም በየስራ ክፍሎቹ ባለሙያዎች በተደረገላቸው ገለጻ ባዩት ነገር መገረማቸውንና መደሰታቸውን፤ ሀገራችን ኢትዮጵያ የበርካታ ባህል፣ቱውፊት ባለቤት መሆኗንና የሀገር በቀል ጥበብ እውቀት ባለቤት ታላቅ ሀገር መሆኗንም የተገነዘቡበት እንደሆነም ነግረውናል፡፡

ኀዳር 2018ዓ.ም አዲስ አበባ ከኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የምህንድስና ክፍል መዛግብት በተዛወሩ ሰነዶች ላይ የምዘናና መረጣ ሂደት ተጠናቀቀ፡፡ የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት በአዋጅ ቁጥር 179/91 በተሰጠው ስልጣን መሰረት በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የምህንድስና ክፍል መዛግብት ታሪካዊ መዛግብትን እንዲመረጡና ወደ ተቋሙ እንዲዛወሩ፤የአገልግሎት ዘመናቸውን የጨረሱና ዘላቂ ፋይዳ የሌላቸውን ሰነዶች ደግሞ ሕጋዊ አሰራርን ተከትሎ እንዲወገዱ የማድረግ ስራ አከናውኗል፡፡ በሰነድ ውገዳው ከኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት የጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አባተ ካሳው እና የሚመለከታቸው ኃላፊዎችና ባለሙያች እንዲሁም ከኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ተቋሙን በመወከል የሰራተኛ ግንኙነትና ማህከላዊ ዶክመንቴሽን ቡድን መሪ አቶ አሰግድ አድነውና የሚመለከታቸው የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡ በውደገዳ ስነ ስርዓቱ ላይ የተቋሙ የጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አባተ ካሳው ተቋማችን በተሰጠው ስልጣን ሰነዶችን በመለየትና የማስወገድ ስራዎችን ከበርካታ ተቋማት ጋር በጥንቃቄ እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረው አደራ የምንላችሁ ተቋማችሁ ብዙ ስራችን እንደሚሰራ ይታወቃል በርካታ ሰነዶች አሏችሁ የማያስፈልጉትን በጥንቃቄ እንዲወገዱ ለእናንተም ለሀገርም ታሪክ የሚጠቅሙትን ተሰንደው እንዲያዙ ከዛሬ ጀምሩ በተቋማችሁ የቀሩ ሰነዶች እንዲሰነዱ ለማድረግ የድርሻችሁን እንድትወጡ በማለት ጥሪቸውን አስተላልፈዋል፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ተቋሙን በመወከል የተገኙት የሰራተኛ ግንኙነትና ማህከላዊ ዶክመንቴሽን ቡድን መሪ አቶ አሰግድ አድነውም ተቋሙ እየሰራ ያለውን ለሀገር የሚጠቅም ተግባር አድንቀው ይሄ ተግባር በአዋጅ የሚመለከተው ተቋም የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት መሆኑ እየታወቀ ግንዛቤ ከማጣት በርካታ ተቋማት ወደ ተቋማቸው በመምጣት ይመለከተናል እያሉ ሰነዶችን ለመውሰድ እንደሞከሩ ጠቁመው የቀረውን ለመስራት ለበላይ አመራሩና ለሚመለከታቸው አካላት መድረክ በማዘጋጀት የግንዛቤ ማስጨበጫ የሚሰጥበት ሁኔታ እንዲመቻች ጠቁመዋል፡፡ ከኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር 9225 (ዘጠኝ ሺህ ሁለት መቶ ሃያ አምስት) ጥራዞች 458 ሊ.ሜ የምህንድስና ክፍል ያመነጫቸው የውገዳ ጥያቄ የቀረበባቸው ሲሆን ከነዚህም ውስጥ 231 ጥራዞች ተለይተው ወደ መዛግብት ክምችት ተደራጅተው እንደሚጠበቁ የብሔራዊ የሰነድ አስወጋጅ ኮሚቴ ሰብሳቢ እና የተቋሙ የአብያተ መዛግብትና የአብያተ መጻሕፍት ስልጠናና ምክር ስራ አስፈጻሚ አቶ መኮንን ከፋለ ገልጸዋል፡፡ ማንኛውም ሰነድ አመንጪ ተቋማት ሰነዶችን ማስወገድ እንደማይችልና ሰነዶችን ለማስወገድ ሊታለፉ የሚገባቸውን ህጋዊና ሙያዊ ደረጃዎች አልፎ የተከናወነ በመሆኑ ለሌሎች ተቋማትም ግንዛቤን የሚያሰፋ እንደሆነም ሰብሳቢው በአጥንኦት ገልጸዋል፡፡ በመጨረሻም ሁለቱም ተቋማት ውሉን ተፈራርመው የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ያዘጋጀውን የሰነድ ውገዳ ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት የጽ/ቤት ኃላፊው አቶ አባተ ካሳው አበርክተው ዝግጅቱ ተጠናቋል፡፡ ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!! ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr

የታዳጊ ልጆችን የንባብ ባህል ለማነቃቃት የሚረዳ የንባብ ቀን ተካሔደ ። ኀዳር 9 / 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ በኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ከሜጀር ጀነራል ሐየሎም አርዓያ አ
+2
የታዳጊ ልጆችን የንባብ ባህል ለማነቃቃት የሚረዳ የንባብ ቀን ተካሔደ ። ኀዳር 9 / 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ በኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት ከሜጀር ጀነራል ሐየሎም አርዓያ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት የመጡ ተማሪዎች በተገኙበት የታዳጊ ልጆች የንባብ ባህልን ለማሳደግ የሚረዳ የንባብ ቀን ተካሔደ ። የንባብ ቀኑ ማራኪ ትረካዎች፣ በተለያዩ ዘርፎች የቀረቡ የጥያቄና መልስ ውድድር ፣ የጉብኝት መርሐግብር እንደዚሁም ለመምህራን፣ ጥያቄና መልስ ላሸነፉ ተማሪዎችና የሕጻናት ቤተ-መጻሕፍትን አዘውትረው ለሚገለገሉ ተማሪዎች የሽልማት መርሐ ግብርን አካቷል፡፡ ለተማሪዎች መልዕክት ያስተላለፉት የአገልግሎቱ የጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አባተ ካሳው ከትምህርት ቤት ከሚገኝ እውቀት በተጨማሪ ከንባብ የሚገኝ እውቀት ሰፊ እንደሆነ ገልጸው ተቋሙ ብዙ ታሪኮቻችሁን የምታውቁበትና በእውቀት የምታድጉበት በመሆኑ መጥታችሁ ተገልገሉ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል። ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችንን ይከታተሉ!! ቴሌግራም: https://t.me/wamezeker ድረገጽ: https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ: https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr

ከሱሰኝነት የነፃ ትውልድ በመፍጠር በአዎንታዊ አመለካከት የተገነባና ለጋራ ሀገራዊ እድገት የሚተጋ ትውልድን ለማነሳሳት የሚረዳ ስልጠና ተሰጠ ። ጥቅምት 28/ 2018 አዲስ አበባ በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት "የተደመረ የወጣቶች አቅም ለዘላቂ ልማት ግቦች ስኬት" በሚል መሪ ቃል አለም አቀፍ የወጣቶች ቀን በዓል ወጣቶችን በተመለከተ የተዘጋጀ የአእምሮ ውቅር (Mind Set) ስልጠና ለተቋሙ ሰራተኞች በመስጠት ተከበረ ። መርሐግብሩን በንግግር የከፈቱት የተቋሙ የጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አባተ ካሳው ለወጣቶች፣ ለወላጆች እንዲሁም ወጣቶችን ለሚያገለግሉ የስራ ክፍሎች እውቀትና ልምድ ለማጋራት ታልሞ የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮ ከሱስ የነፃ ትውልድ በጎ አድራጎት ድርጅት መስራችና ሰብሳቢ እንደዚሁም የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አባል ዶ/ር ጃራ ሰማ ሱስና ሱሰኝነት፣ መጤ አሉታዊ ልማዳዊ ድርጊቶች የሚፀየፍ እና በስነ-ምግባር የታነፀ ትውልድ ማፍራት በሚል ርዕስ ለተቋሙ ሰራተኞች ስልጠና ሰጥተዋል። ስልጠናው ከሱሰኝነት የነፃ ትውልድ በመፍጠር በአዎንታዊ አመለካከት የተገነባና ለጋራ ሀገራዊ እድገት የሚተጋ ትውልድን ማነሳሳት ዓላማ እንዳደረገ ዶ/ር ጃራ ገልፀዋል። በስልጠናው ከተለመዱት አይነት ሱሶች በተጨማሪ የነገር፣ የተንኮል ፣ የሌብነትና የመሳሰሉ ሱሶች ፣ አዲስ እየተለመዱ ያሉ አሉታዊ መጤ ልማዶች፣ ባህልን የሚጻረሩ ድርጊቶች፣ ለስነ ምግባር ጉድለት የሚያደርሱ መሰረታዊ ምክንያቶች እንዲሁም የመፍትሔ እርምጃዎችን እንዴት እናቀናጅ የሚሉ ሀሳቦች በስፍት ተዳሰውብታል ። በመጨረሻም የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች አካቶ ትግበራ ስራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ሀገሬ መኮንን ሱስና መፍትሔዎቻቸውን በተመለከተ ዶ/ር ጃራ ሰማ የጻፏቸውን 10 መጻሕፍት በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አንባብያን እንዲያገኟቸውና ለትውልድ እንዲቀመጡ እንዲሁም ለተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች ተደራሽ ለማድረግ እንደሚሰሩ ገልጸው አክለውም በተለያዩ የሱስ ማገገሚያ ማዕከላት የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን ከጎጂ ሱሶች ወጥተው የንባብ ባህልን ማዳበር የሚያስችላቸውን የንባብ ቀን ለማካሔድ እንደሚሰሩ ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት 10ኛውን የወር ወንበር በድምቀት አከናወነ። በአስረኛው የወር ወንበር "ስለ አደባባይ ሐውልቶቻችን ሥነ ጥበባዊ ወግ" የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) ማህበራዊ፣ፍልስፍናዊ፣ታሪካዊ፣ጥበባ ዊና ሀገራዊ ጉዳዮችን በማንሳት ጥልቅ ውይይት እና የሀሳብ ልውውጥ የሚደረግበት የወር ወንበር አስረኛ መርሐግብሩን ጥቅምት 22 ቀን 2018 ዓ.ም በተቋሙ ብላታ መርስዔ ኃዘን ወልደ ቂርቆስ አዳራሽ አከናውኗል። የወሩ ወንበር "ስለ አደባባይ ሐውልቶቻችን ሥነ ጥበብ ወግ" በሚል ርዕስ ሲሆን የውውይት መነሻ ሀሳብ ያቀረቡት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአለ ፈለገ ሰላም የሥነ ጥበብ ትምህርት ቤት ዲን ሰዓሊ አገኘሁ አዳነ ናቸው። የአደባባይ ሐውልቶቻችን አሠራራቸው፣በታሪክ ውስጥ ያለፉበት መንገድ፣የታለመላቸውን ሀሳብ ዓላማ የማስተላለፍ አቅማቸው፣ የተሰሩበት ዓላማ፣የፈረሱ ሐውልቶች፣በአደባባይ በቆሙ ሐውልቶቻችን ላይ የተነሱ ጉዳዮች እና ስለሐውልቶቹ ምን ተባለ የሚሉትን ሰዓሊ አገኘሁ አዳነ በገለጻቸው ከዳሰሷቸው ነጥቦች የሚጠቀሱ ናቸው። የዕለቱ ታዳሚያን ንቁ ተሳትፎ ጎልቶ በወጣበት የወር ወንበር፤የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሠርፀ ፍሬስብሐት መርሐግብሩን ከዚህ በላቀ መልኩም ለማስቀጠል ተቋሙ እንደሚሰራ እና የወር ወንበር ሁሌም በወሩ የመጨረሻ ሳምንት ቅዳሜ ላይ የሚዘጋጅ በመሆኑ ታዳሚያን ይገኙ ዘንድ የክብር ጥሪን አስተላልፈዋል።

የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ነገ ጥቅምት 22/2018 ዓ.ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ጀምሮ የማይቀርበት የሥነ ጥበብ ድግስ አዘጋጅቷል፡፡ በዝግጅቱ ጥሪ የተደረገላችሁ እንግዶች፣የጥ
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ነገ ጥቅምት 22/2018 ዓ.ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ጀምሮ የማይቀርበት የሥነ ጥበብ ድግስ አዘጋጅቷል፡፡ በዝግጅቱ ጥሪ የተደረገላችሁ እንግዶች፣የጥበብ ባለሙያዎች እንዲሁም የሚድያ አካላት በቦታው በመገኘት ዝግጅቱን በመዘገብ ለሕዝቡ እንድታደርሱ ከወዲሁ በአክብሮት እንጋብዛለን፡፡

ቅዳሜ ጥቅምት 22/2018 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአለ ሥነ ጥበብ እና ዲዛይን ትምህርት ቤት ዲን ሠዓሊ አገኘሁ አዳነ "ስለ ዐደባባይ ሐውልቶቻችን ሥነ ጥበብ ወ
ቅዳሜ ጥቅምት 22/2018 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአለ ሥነ ጥበብ እና ዲዛይን ትምህርት ቤት ዲን ሠዓሊ አገኘሁ አዳነ "ስለ ዐደባባይ ሐውልቶቻችን ሥነ ጥበብ ወግ" የሚነግረን አለ። ይህንኑ መርሐ ግብር ለመታደም ጥሪ ለተደረገላቸው እንግዶች፣ ዘርፉን መቀላቀል ለሚሹ እና ለጀመሩ እንዲሁም አድናቂዎቹን ከሠዓሊው ጋር ለማገናኘት የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብት እና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት 10ኛውን የወር ወንበር አሰናድቷል። ዝግጅቱ በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) ብላታ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ አዳራሽ (ከዋናው ቤተ መጻሕፍት አጠገብ) ይካሔዳል። በአክብሮት ተጋብዛችኃል! ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችን!! የቴሌግራም https://t.me/wamezeker ድረገጽ፡ https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ፡ https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr

ጥቅምት 18/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ በ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጥልቀት ምላሽ ከተሰጠባቸው፡፡ ተጨማሪ የመረጃ አ
ጥቅምት 18/2018 ዓ.ም አዲስ አበባ በ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጥልቀት ምላሽ ከተሰጠባቸው፡፡ ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችን!! ቴሌግራም https://t.me/wamezeker ድረገጽ፡ https://www.nala.gov.et/ ዩቲዩብ፡ https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572 ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr