የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት-Ethiopian Archives and Library Service
前往频道在 Telegram
.ይህ የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ይፋዊ የቴሌግራም ቻናል ነው፡፡
显示更多未指定国家未指定类别
514
订阅者
无数据24 小时
无数据7 天
无数据30 天
帖子存档
የዓለም የኦዲዮ ቪዥዋል ቅርሶች መታሰቢያ ዕለት በታሪካዊ ሁነት ታጀበ
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) የዓለም የኦዲዮ ቪዥዋል ቅርሶች መታሰቢያ ዕለትን ጥቅምት 17/2018 ዓ.ም ከዩኔስኮ ጋር በመተባበር በተቋሙ አክብሯል።
ተቋሙ ይህን ልዩ ዕለት በተለየ መልኩ የሚያጎላውን የኢትዮጵያ የጽሑፍ ቅርሶች አስመዝጋቢ ብሔራዊ ኮሚቴ መቋቋሙን ይፋ ያደረገበትም ሆኗል።
በዚህ መርሐግብር የተከበሩ ሙሐዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት የክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር የማህበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር፣ክቡር ረዳት ፕሮፌሰር ነብዩ ባዬ የባህልና ስፓርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ እና የኢትዮጵያ የጽሑፍ ቅርሶች አስመዝጋቢ ብሔራዊ ኮሚቴ የክብር አባል፣ዶ/ር ሪታ ቢሶኖት የዩኔስኮ በአዲስአበባ ዳይሬክተር፣ፕሮፌሰር አሉላ ፓንክረስት፣ ኤምሬትስ ፕሮፌሰር ባህሩ ዘውዴ ፣ የኃይማኖት እና የማህበረሰብ ጥናትና ምርምር ተቋማት እንዲሁም ታላላቅ የታሪክና የምርምር አጥኚዎች በተገኙበት የኢትዮጵያ የጽሑፍ ቅርሶች አስመዝጋቢ ብሔራዊ ኮሚቴ መቋቋም ይፋተደርጓል።
ኮሚቴው በህዳር ወር 2025 ሁለት ጥንታዊያን የሀገራችንን ታላላቅ የጽሑፍ ቅርሶች በዓለም የትዝታ (የትውስታ) ማኅደር ለማስመዝገብ አስፈላጊውን ሰነድ የማሟላት ስራ ሲሰራ መቆየቱንና ከዚህ በኋላም በየሁለት አመቱ በተመሳሳይ የኢትዮጵያ ጥንታዊያን የጽሑፍ ቅርሶችን የማስመዝገብ ስራን እንደሚያከናውን የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰርፀ ፍሬ ስብሐት አሳውቀዋል።
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ከዛሬ 20 አመት በፊት 12 ያህል የጽሑፍ ቅርሶችን በዓለም አቀፍ የሰው ልጆች የአእምሮ ሀብትነት የማስመዝገብ ስራ መስራቱ ይታወሳል።
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችን!!
ቴሌግራም https://t.me/wamezeker
ድረገጽ፡ https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ፡ https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብት እና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት 10ኛውን የወር ወንበር ለማካሔድ ዝግጅቱን አጠናቋል።
የፊታችን ቅዳሜ ጥቅምት 22/2018 ዓ.ም "ስለ ዐደባባይ ሐውልቶቻችን ሥነ ጥበባዊ ወግ" በሚል ርእስ ሠዓሊ አገኘሁ አዳነ (የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአለ ሥነ ጥበብ እና ዲዛይን ትምህርት ቤት ዲን ) የሚቀርበውን 10ኛውን የወር ወንበር በወመዘክር ዝግጅት አሰናድተን እንጠብቃችኃለን።
በአክብሮት ተጋብዛችኃል!
የሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ መልዕክት፤ በ15ኛው መቶ ክ.ዘ የተጻፈ
ወደ 15ኛው መቶ ክ.ዘ ተመልሰን ጥልቅ የሆነውን የኢትዮጵያውያን ስነ-ጽሑፍ ዱካ ስንከተል የሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ መልዕክቶችን በብራና ተሰንደው እናገኛቸዋለን፡፡ በኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት በጥንታውያን ስነ-ጽሑፍ ቅርሶች ክፍል ውስጥ ተጠብቆ የሚገኘው ይህ የከበረ ብራና እንደ ሀገር በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስ እና የባህል ድርጅት (UNESCO) ከተመዘገቡ 12 የጽሑፍ ቅርሶች መካከል አንዱ ነው፡፡
ከሮሜ እስከ ዕብራውያን ያለው እያንዳንዱ መልዕክት ለእምነት፣ ለጽናትና ለዘለቄታው የወንጌል ሰበካ ተሰንዷል፡፡
ይህ ብራና 35ሴ.ሜ*25ሴ.ሜ ስፋት ያለው ሲሆን 282 ቅጠል (564 ገፅ) ብዛት አለው፡፡ በግእዝ ቋንቋ ተጽፏል፤ በወቅቱ ለነበረው አስገራሚ የስነ-ጥበብ ስራ ሀረጋቱ እና ሥዕላቱ ምስክር ናቸው፡፡ ከንጉሠ ነገሥት ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሤ ለተቋሙ በስጦታ እንደተበረከተም ከክፍሉ መረጃ አግኝተናል፡፡
ይህ የ15ኛው መቶ ክ.ዘ የእጅ ጽሑፍ እንዲህ እንዳሁኑ ሕትመቶች በስፋት በማይሠራጩበት በዚያ ዘመን ኢትዮጵያ ያላትን የቅዱሳት መጻሕፍት ጠባቂነት ሚና አጉልቶ የሚያሳይ ነው፡፡
ለሥነ-መለኮታዊ ትርጓሜዎች ተቀዳሚ ግብዓት የሆኑት እንዲህ ያሉ ጥንታውያን ጽሑፎች ለታሪክ፣ ለሥነ-መለኮት፣ ለቋንቋ ጥናትና ለሌሎችም ሙያዎች ዝንባሌ ላላቸው ሰዎች ጠቀሜታቸው የጎላ ነው፡፡
+5
18ኛው ብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን በድምቀት ተከበረ፡፡
ጥቅምት 03/ 2018 ዓ.ም
በሀገር ደረጃ ለ18ኛ ጊዜ እየተከበረ የሚገኘው ብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን “ሰንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ!” በሚል መሪ ቃል የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት ከባሕልና ስፖርት ሚኒስቴርና ከኢፌድሪ ወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ አባላት ጋር በጋራ አከበረ፡፡
በብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ በዓሉ ላይ ንግግር ያደረጉት የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ተወካይ አቶ ናስር ለገሰ ሰንደቅ አላማችን የሉዓላዊነታችን ምልክት፣ አድዋንና ታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጨምሮ ላሉን በርካታ ብሔራዊ ኩራታችን ምንጭ እንደሆነም ተናግረዋል፡፡
ተወካዩ አክለውም የዘንድሮው የሠንደቅ ዓላማ በዓል የሕዳሴ ግድባችን በድል ከተጠናቀቀ በኃላ መከበሩ ልዩ እንደሚያደርገውም ተናግረዋል፡፡
ተጨማሪ የመረጃ አማራጮቻችን;-
የቴሌግራም https://t.me/wamezeker
ድረገጽ፡ https://www.nala.gov.et/
ዩቲዩብ፡ https://www.youtube.com/@nationalarchivesandlibrary7572
ፌስቡክ: https://web.facebook.com/Wemezekr
በየም ዞን ሣጃ ከተማ በተካሔደው የንባብ ሳምንት በኢትዮጵያ ቤተመዛግትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት የመረጃ ሀብቶች አስተዳደር መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ስለሺ ሽፈራው ተቋሙ ያስለማውን የተቀናጀ የቤተ መጻሕፍት መዛግብት እና ሰነድ አስተዳደር ስርዓት ILARMS /Integrated Library Archive and Record Management System/ አስመልክቶ የተናገሩት ከሀገሬ ቲቪ የተወሰደ……..
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት በየም ዞን ሣጃ ከተማ ባካሔደው የንባብ ሳምንት በሀገሬ ቲቪ ከተላለፈው የተወሰደ………….
መስከረም 20/ 2018 ዓ.ም
ሣጃ ማረሚያ ተቋም
ንባብ ላይ መስራት ትውልድ ላይ መስራት እንደሆነ ተገለጸ::
የኢትዮጵያ ቤተ- መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት፤ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባህል ቱሪዝም ቢሮ፣ከየም ዞን ትምህርት መምሪያ እና ከየም ዞን ባህል ቱሪዝም መምሪያ ጋር በመተባበር “የንባብ ሳምንት ለትምህርት ጥራት!” በሚል መሪ ቃል የየም ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ “ሄቦ” በዓልን ምክንያት በማድረግ በሣጃ ማረሚያ ተቋም የንባብ ሳምንት በድምቀት አካሒዷል።
የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር የየም ዞን ሣጃ ማረሚያ ተቋም ኃላፊ ኮማንደር አሰፋ ገርዲ ሲደረግ መርሐ ግብሩን በማስመልከት መልዕክት ያስተላለፉት የዞኑ ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ አማኑኤል ሳምቢ የተደረገውን የመጽሐፍት ድጋፍ አስመልክተው “እኛ የምንከፍለው ነገር የለም ነገር ግን ትውልድ ራሱ ይከፍላል::” ሲሉ ንባብ ላይ በመስራታችን በአሁንና በመጪው ትውልድ የምንቀበለው መልካም ፍሬ እንደሚኖር ገልጸዋል፡፡
በአገልግሎቱ የስትራቴጂክ ጉዳዮች ስራ አስፈጻሚ ተወካይ አቶ አህመድ እስማኤል የዝግጅቱን ዓላማ ተቋሙ ዛሬ በሣጃ ማረሚያ ተቋም እያከናወነ ያለውን ተግባር በበርካታ የሀገሪቱ ክፍሎች እየተዘዋወረ እየሰራ እንደሚገኝና ስልጣንና ተግባሩንም ከማከናወን አንጻር እንዲህ ያሉ ለትውልዱ የሚጠቅሙ፣ ትውልዱን የሚያንጹ ተግባራትን በአትኩሮት እየሰራ እንደሚገኝ እና ለወደፊትም የንባብ ባህልን ከማሳደግ አንጻር በዘርፉ አጠናክሮ እንደሚሰራም ተናግረው የዛሬውም በሣጃ ማረሚያ ተቋም እየተከናወነ የሚገኘው የንባብ ሳምንት ለሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የንባብ ባህል እንዲዳብር ታልሞ የተዘጋጀ ዝግጅት እንደሆነም ተናግረዋል፡፡
ንባብን በማስመልከት የደራሲ ተሞክሮ በደራሲ ገዛኸኝ ሀብቴ ለታራሚው ሲቀርብ፤ማረሚያ ቤት እና ንባብ በሚል ርዕስ ገለጻ ያደረጉት ደራሲ ይታገሱ ጌትነት ማረሚያ ቤት ሰዎች መጽሐፍት አንብበው የራሳቸውን ጽፈው ራሳቸውንና አለምን የቀየሩ ትልልቅ ታዋቂ ሰዎች የፈሩበት ቦታ እንደሆነ ገልጸዋል፡
በማረሚያ ቤት ቆይታችሁ መጽሐፍት አንብባችሁ ወደ ህብረተሰቡ ስትቀላቀሉ ሀሳባችሁን የምትገልፁ ትሆናላችሁ፤በእርምት ጊዜያችሁም ትታነጹበታላችሁ ብለዋል፡፡
እንዲሁም አነቃቂ ንግግር በአካባቢው ተወላጅ በአቶ ከማል ሞጋ የመታመምንና የመታሰርን ጉዳይ ፈልገን ባናመጣውም ወደምንለወጥበት፣ራሳችንን ፈልገን ወደ ምናገኝበትና ወደ ምናደምጥበት መንገድ ሊመራን ስለሚችል እዚህ ቦታ በመገኘታችን የምንጸጸትበትን ነገር ትተን ራሳችንን አጎልብተን ወደ ተሻለ ደረጃ የምንሻገርበት ሊሆን ይገባል ብለዋል፡፡
በመርሐ ግብሩ ሥነ-ጽሑፍ ላቀረቡ ታራሚዎች የመጽሐፍት ሽልማት ሲበረከት ተቋሙ ለሣጃ ማረሚያ ተቋም ከ145 ሺ ብር በላይ የፈጁ 410 መጻሕፍት የአገልግሎቱ የአብያተ መጻሕፍት መረጃ ሀብቶች አስተዳደር መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ስለሺ ሽፈራው ለሣጃ ማረሚያ ተቋም ኃላፊ ኮማንደር አሰፋ ገርዲ አስረክበዋል፡
መስከረም 20/12018.ዓ.ም
ሣጃ ከተማ
የኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት በየም ዞን ሣጃ ከተማ ባዘጋጀው የንባብ ሳምንት ከ900ሺህ ብር በላይ የፈጀ የመጽሐፍት ስጦታ አበረከተ።
"የንባብ ሳምንት ለትምህርት ጥራት!" በሚል መሪ ቃል የየም ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ "ሄቦ"በዓልን ምክንያት በማድረግ የኢትዮጵያ ቤተ- መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት፤ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ባህል ቱሪዝም ቢሮ፣ከየም ዞን ትምህርት መምሪያ እና ከየም ዞን ባህል ቱሪዝም መምሪያ ጋር በመተባበር በሣጃ ከተማ የንባብ ሳምንት በድምቀት አካሒዷል።
በንባብ ሳምንቱ ከአገልግሎቱ የሚመለከታቸው የስራ ክፍል ኃላፊዎች፣ የየም ዞን ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ ሽመልስ እጅጉ፣የየም ዞን የትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ አማኑኤል ሳንቢ፣የየም ዞን የመንግስት ዋና ተጠሪ የተከበሩ አቶ አብርሃም ዝናብ፣ደራሲ ይታገሱ ጌትነት እና ደራሲ ገዛኸኝ ሀብቴ፣የብሔረሰቡ ተወላጅ ንባብን በማስመልከት አነቃቂ ንግግር ያቀረቡት አቶ ከማል ሞጋ እና የሚድያ አካላት ተገኝተውበታል።
የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር በአቶ አማኑኤል ሳንቢ ሲደረግ የመክፈቻ ንግግር በየም ዞን ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ ሽመልስ እጅጉ ሲደረግ እንደ ሀገር ያለው የትምህርት ስብራት መሰረቱ የንባብ ባህል አለመደበር አንደሆነ ገልጸው የሚታየውን ስብራት ለመጠገን የሚታዩ የግብዓት ችግርን ለመፍታት ተቋሙ ችግሩ አለባቸው ብሎ በሚያስብባቸው ቦታዎች ሁሉ በአካል ባለሙያዎቹን ይዞ በመግባት እየሰራ ያለውን ተግባር አመስግነዋል።
የዝግጅቱን ዓላማም ሰፋ ያሉ ሃሳቦችን በማንሳት ለታዳሚው መልዕክት ያስተላለፉት የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ስልጠና ምክር መሪ ሥራ አስፈፅሚ አቶ መኮንን ከፋለም ለተማሪዎች የውጤት መቀነስ ሁሉም ሊመለከተው ሲገባ በመገፋፋት አንዱ ወደ አንዱ ለማሳበብ የምንጠቀመው ሰበብ ትተን መንግስት ስብራቱን ለመጠገን አብያተ መጻሕፍትን ገንብቶ አንባቢ ትውልድ ለመፍጠር እየሰራ ያለውን ተግባር እኛም በአካባቢያችን አብያተ መጻሕፍትን በመገንባት ማንበቢያ ቦታዎችን ማሟላት ካልሆነ ግን የሚያመጣው ችግር ሰፊ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
በአንዳንድ አካባቢዎች ለወጣቱ መጠቀሚያ የሚያገለግሉ ቤተመጻሕፍት አለመኖር በተማሪው ላይ የሚያሳድረው ተጽዕኖ እንደ ዋና ተግዳሮት ተደርጎ የሚወሰድ እንደሆነና ለንባብ ባህል አለመዳበር የሚኖረው ሚና ጉልህ እንደሆነም ተናግረዋል::
የሚያነብ ትውልድ ሀገር የሚሰራና ሀገርን የሚያሻግር ነው::
እውነቱን ከውሽቱ የሚለዩ ትውልድ የሚፈጥር በመሆኑ የማንበብ ባህልን በየደረጃው ማዳበር ላይ መስራት የግድ እንደሚልም ተናግረዋል።
የራሲ ተሞክሮ በንባብ አንጻር በደራሲ ገዛኸኝ ሀብቴ ሲቀርብ የንባብ ባህል ለትምህርት ጥራት ያለውን ፋይዳ በደራሲ ይታገሱ ጌትነት ሲቀርብ የንባብ ባህል አለማዳበር ተማሪዎች በቂ እውቀት አንዳይጨብጡ ብሎም ከክፍል ክፍል አንዳይሻገሩ አደርጓል ከአለፉት ጊዜያት አንጻር ሲታይ በብዙ መልኩ ውጤታማ ተማሪዎችን ማግኘት ያልተቻለው በእውቀት ማንበብ መዘጋጀት ባለመቻሉ ነው::
ሁሉም በየደረጃው መስራት እንደሚገባውም ተናግረው በተለይ ቤተሰብ የመምህራንና በትምህርት ዘርፉ ላይ ያሉ ኃላፊዎች መስራት አንደሚጠበቅባቸው ተናግረዋል::
በኢትዮጵያ ቤተመዛግትና ቤተ መጻሕፍትንና አገልግሎት የመረጃ ሀብቶች አስተዳደር መሪ ሥራ አስፈጻሚነት አቶ ስለሺ ሽፈራው የንባብ ባህል አንዲዳብር የንባብ ሳምንት ከማዘጋጅት ባሻገር ለትምህርት ጥራት ወሳኝ የሆነ የማጣቀሽ መጽሐፍትና በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት የተዘጋጁ ለስድስት ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት እና ለሁለት አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በአጠቃላይ ለስምንት ትምህርት ቤቶች ከ900 ሺህ ብር ላይ ወጪ የተደረገባቸው በቁጥር 2500 መጽሐፍት አገልግሎታቸው ከተማሪዎች ባሻገር ለሁሉም ማህበረሰብ የሚሆን መጽሐፍት መበርከቱን ተናግረዋል።
በዝግጅቱ የተማሪዎች ጥያቄና መልስ ውድደር እና የሥነ ጽሑፍ ስራ ላቀረቡ አሸናፊዎች በአገልግሎቱ የአብያተ መጻሕፍት አገልግሎት መሪ ስራ አስፈጻሚ (ተወካይ) በወ/ሮ ዓለም ጌታቸው የመጽሐፍት ስጦታ ሲበረከት በየም ዞን ለሚገኙ ለዘጠኝ ትምህርት ቤቶች ከተቋሙ የተበረከቱ መጽሐፍት አቶ ስለሺ ሽፈራው ለየም ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ ለአቶ አማኑኤል በማስረከብ የዕለቱ ዝግጅት ተጠናቋል።
+1
የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት "የንባብ ባህል ለትምህርት ጥራት!" በሚል መሪ ቃል ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት ባህልና ቱሪዝም ቢሮ፣ከየም ዞን ትምህርት መምሪያ እንዲሁም ከየም ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ጋር በመተባበር ከመስከረም 19/2018 ዓ.ም ጀምሮ የየም ብሔረሰብ ዘመን መለወጫ “ሄቦ” በዓልን ምክንያት በማድረግ የንባብ ሳምንት፣ስልጠና እና የፓናል ውይይት መድረክ በሣጃ ከተማ እና በሣጃ ማረሚያ ተቋም ለማካሔድ ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡
የኢትዮጵያ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ አደረሳቹ እያለ በዓሉ የሠላም፣ የፍቅር፣ የአንድነት፣ የመከባበር፣የመረዳዳት እንዲሆንላችሁ እየተመኘ በዓሉን ስናከብር የኢትዮጵያውያን ባህል በሆነው ያለው ለሌለው በማካፈል የምናከብረው በዓል እንዲሆንም በመመኘት ነው፡፡
መልካም በዓል!!🌿🌿❤️🌿
