ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
الذهاب إلى القناة على Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
إظهار المزيد2 918
المشتركون
-1524 ساعات
+287 أيام
+37030 أيام
أرشيف المشاركات
በምስራቅ ወለጋ መጠነ-ሰፊ ወታደራዊ ጥቃት መከፈቱና በንጹሃን ላይ የጅምላ ፍጅት ስጋት መጋረጡ ተገለጠ
ሰኔ 17 ቀን 2018 ዓ.ም (አዲስ አበባ)፦ በምስራቅ ወለጋ ዞን ጊዳ አያና ወረዳ እና በአካባቢው በሚገኝ ታዳጊ ከተማና ቀበሌዎች ላይ የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች በምድር እግረኛ ጦር፣ በሜካናይዝድ ክፍለ-ጦር እና በአየር ኃይል የታገዘ መጠነ-ሰፊ ወታደራዊ ጥቃት መክፈታቸውን ከአካባቢው የተገኙ መረጃዎች አመለከቱ። በትናንትናው እለት ብቻ በተፈጸሙ ተከታታይ የአየር ላይ ድብደባዎች በርካታ ንጹሃን ዜጎች ህይወታቸውን አጥተዋል።
ጥቃቱ በዋነኝነት ያረፈው አንዶዴ ዲቾ ከተማን ጨምሮ በአሊ፣ በዋጃ እና በጉልማ ቀበሌዎች ላይ ሲሆን፣ በጥቃቱ ሳቢያ በርካታ ቁጥር ያላቸው አርሶ አደሮችና ነጋዴዎች ሰለባ መሆናቸው ተረጋግጧል። በአሊ ቀበሌ በትናንትናው እለት ብቻ በሁለት የጦር ሄሊኮፕተሮች እና በሰው አልባ አውሮፕላኖች (ድሮኖች) የታገዘ የ42 ጊዜ ድብደባ የተፈጸመ ሲሆን፣ በዛሬው እለትም የሄሊኮፕተር የቅኝት በረራዎች ቀጥለው መዋላቸው ታውቋል። በጥቃቱ ማግስት ዛሬ ሰኔ 17 ቀን የማዕከላዊ ዕዝ ጦር የኦሮሚያ ሚሊሻን፣ የአድማ ብተናንና የገዳ ኮማንዶን መንገድ መሪነት በማድረግ፣ በርካታ በቆንጨራና በቢለዋ የታጠቁ ወጣቶችን አስከትሎ ወደ አሊ ቀበሌ መግባቱ የተገለጸ ሲሆን፣ ይህም በአካባቢው በሚኖሩ የአማራ ተወላጆች ላይ የታቀደ የጅምላ ፍጅት ለመፈጸም ነው የሚል ከፍተኛ ስጋት በአካባቢው ላይ ጥሏል።
በተመሳሳይ ሁኔታ በአንዶዴ ዲቾ ከተማ በትናንትናው እለት በረፋዱና በአመሻሹ ላይ የጦር ሄሊኮፕተር በከፈተችው አውቶማቲክ የተኩስ ጥቃት በእለት ተእለት እንቅስቃሴ ላይ የነበሩ በርካታ ነጋዴዎችና አርሶ አደሮች ተገድለዋል። በዋጃ ቀበሌ ደግሞ በአንድ ዙር የጄት ድብደባ፣ በሶስት ዙር የሄሊኮፕተር ጥቃት እና በታንኮች የታገዘ ከባድ ድብደባ የተፈጸመ ሲሆን፣ በጉልማ ቀበሌ በበኩሉ ከ5 ጊዜ በላይ የሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን) ጥቃት ተፈጽሟል።
ከጥቃቱ ሰለባ አካባቢዎች በ30 እና 40 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኘው የነቀምቴ (ኡኬ) አየር ማረፊያ የሲቪል በረራዎች ሙሉ በሙሉ የተቋረጡ ሲሆን፣ አየር ማረፊያው ትናንትና ዛሬ የሙሉ ሰዓት የወታደር ማመላለሻ፣ የሄሊኮፕተር፣ የድሮን እና የጦር ጄቶች ማኮብኮቢያ ሆኖ እያገለገለ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት በአካባቢው መደበኛ የኮሙኒኬሽንና የኔትዎርክ አገልግሎቶች ሙሉ በሙሉ መቋረጣቸው ተረጋግጧል።
በሌላ በኩል፣ መንግስት በምስራቅ እና ምዕራብ ወለጋ ዞኖች አዋሳኝ፣ ከአርጆ ጉደቱ ከተማ በቅርብ ርቀት ላይ የሚገኘውንና በደርግ ዘመን ተገንብቶ ከአገልግሎት ውጭ የነበረውን የደዴሣ አየር ማረፊያ መልሶ በማፅዳትና በማደስ በአዲስ መልኩ ስራ ማስጀመሩ ታውቋል። ይህ ስፍራ በቄለም ወለጋ (ደምቢዶሎ) በኩል በረራ ሲለካ ለሱዳን ድንበር ቅርብ በመሆኑ፣ የጄነራል መሀመድ ሀምዳን ዳጋሎ (ሄሜቲ) የፈጣን ድጋፍ ሰጪ ኃይል (RSF) እንደ ድሮን ጣቢያ ሊጠቀምበት እንደሚችል የደረሱን መረጃዎች ያመለክታሉ።
የደዴሣ ካምፕ አካባቢ ከ1950ዎቹ እና 60ዎቹ ጀምሮ በርካታ ቁጥር ያላቸው የአማራ ተወላጆች የሰፈሩበት ስፍራ ነው። አካባቢው በ2013 እና 2014 ዓ.ም የጅምላ ጭፍጨፋ ከተፈጸመበት የጊምቢ (ቶሌ) አካባቢ በ10 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ብቻ የሚገኝ ሲሆን፣ አሁንም በቶሌ፣ ጊምቢ፣ አርጆ ጉደቱ፣ ጨዋቃ፣ ኤፍሬም እና ዲጋ አካባቢዎች ከፍተኛ ቁጥር ያለው የአማራ ማህበረሰብ ይኖራል። ካምፑ ከቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል በሎ-ጂጋንፎይ ወረዳ ጋር የሚዋሰን ሲሆን፣ የአየር ማረፊያው በአዲስ መልኩ መዋቀር በአካባቢው ባለው ሰፊ ህዝብ ላይ የወደፊት የአየር ጥቃቶችን ለመፈጸም እንደ አመቺ ሁኔታ ሊያገለግል ይችላል የሚል ስጋት ማሳደሩን ከአካባቢው የወጡ መረጃዎች ያመለክታሉ።
ታሪክ የማይረሳው በደል፣ ምድሪቱን ያጨማለቃት የአብይ አህመድ ስርዓት የደም አዙሪት!
ይህ አገዛዝ ወደ ስልጣን ከመጣበት ቀን ጀምሮ በሀገሪቱ ላይ ያልተፈጸመ የግፍ አይነት፣ ያልተዘራ የጥል ዘር የለም። በታሪክ ሰነድ ላይ ጥቁር ጠባሳ ሆኖ የሚቀረውና አማራን ከምድር ገፅ ለማጥፋት ያለመው የመጀመሪያው የጆነሳይድ ስራ፣ ዛሬም ድረስ በንጹሀን ደም ምድሪቱን እያራሳት ይገኛል። ሆኖም ግን... ይህ የጥፋት እሳት በሀገር በቀል ወገኖች ላይ ብቻ አልተገታም። ዛሬ የኦሮሚያ መሬት ለኢንቨስተሮችና ለውጭ ሀገራት ዜጎች ጭምር የፍርሃትና የደም መሬት ሆናለች።
በአደባባይ መዋረድ፣ መደብደብና መዘረፍ የዕለት ተዕለት ክስተት ሆኗል። ሰሞኑን በዚሁ በኦሮሚያ ክልል ውስጥ የተፈጸመው አሰቃቂ ድርጊት ደግሞ የጉዳዩን አሳሳቢነት ይበልጥ ያጎላዋል። በክልሉ ኢንቨስት አድርጎ የሚንቀሳቀሰውን የሆላንድ ዜጋ ባለሀብት በማነጣጠር፣ ንብረቱን ከመዝረፍ ባለፈ በአደባባይ ከፍተኛ ድብደባና ውርደት ተፈፅሞበታል።
የህግ የበላይነት በጠፋበት፣ ስርአተ-አልበኝነት በነገሰበት መድረክ ላይ... ማንም ዋስትና የለውም! ይህ በሆላንዱ ዜጋ ላይ የደረሰው ጥቃት፣ የአገዛዙ ስርአት-አልበኝነት የት ደረጃ ላይ እንደደረሰና ንጹሀን ዜጎችም ሆኑ የውጭ ሀገር ተወላጆች ለዝርፊያና ለደህንነት ስጋት መጋለጣቸውን በግልፅ ያሳየ ክስተት ሆኗል።
የደም መሬቷ ኦሮሚያ ዛሬም በውጭ ዜጎች እንባና ስቃይ እየታመሰች፣ ዝርፊያውና ግፉ ያለማቋረጥ ቀጥሏል።#Dawit #Amhara
የአገዛዙ ወታደሮች ከኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ጋር በመቀናጀት በድሮን ጭምር ታግዘው በደራ አማራዎች ላይ የከፈቱት ጥቃት ተባብሶ ቀጥሏል።
በትናንትናው እለት በተፈፀመ የድሮን ጥቃት 18 ሰዎች ሙትና ቁስለኛ ሆነዋል።
ኦህዴድ መሩ የብልፅግና አገዛዝ ከኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ጋር ቅንጅት በመፍጠር በደራ እና አካባቢው አማራዎች ላይ የዘር ጭፍጨፋ እየፈፀመ ነው።
በጥቃቱ የንፁኋኖች ሕይወት አልፏል።ህፃናትና አረጋውያንን ጨምሮ ከ80 በላይ ንፁኋን ወገኖች ታግተው ተወስደው ደብዛቸው ጠፍቷል። ሃብት ንብረት ወድሟል፣ የቀንድ ከብቶች ጭምር ተዘርፈዋል።
በደራ ወረዳ ትላንት ሰኔ 15/ 2018 ዓ/ም በተፈፀመ የድሮን ጥቃት ሰባት ሰዎች ሲገደሉ፡ 11 ሰዎች ደግሞ የአካል ጉዳት እንደ ደረሰባቸው ነው መረብ ሚዲያ ለማረጋገጥ የቻለው።
ከድሮን ጥቃቱ በተጨማሪ አበጦ ቀበሌን ጨምሮ በሌሎች የደራ ወረዳ አከባቢዎች ትላንት ሰኔ 15/ 2018 ዓ/ም ህፃናትና አረጋውያንን ጨምሮ ከ80 በላይ ንፁኋን ወገኖች በመከላከያ ሠራዊቱና በኦነግ ሸኔ ታጣቂ ጥምር ጦር ታግተው ተወስደው ደብዛቸው መጥፋቱም ታውቋል።
በተጨማሪም 500 የሚደርሱ የቀንድ ከብቶች በጥምር ጦሩ ተዘርፈው የተወሰዱ ሲሆን፡ ቀሪ የነዋሪዎቹ ሃብት ንብረትም በታጣቂዎቱ መውደሙን መረብ ሚዲያ ለማረጋገጥ ችሏል።
ጀምበር ያዘቀዘቀችበት የብልፅግናው አገዛዝ በይልማ መርዳሳ አየር ኃይል አዛዥነት በድሮን ጭምር በመታገዝ በደራ ጉምዶ መስቀልና አከባቢው አማራዎች ላይ የከፈተው የዘር ፍጅት ተባብሶ ቀጥሏል።
የጥንቃቄ መልዕክት!!
ሃገር አፍራሹና ፀረ አማራው የብልፅግና አገዛዝ በተለያዩ ቦታዎቺ የደረሰበትን ምት መቋቋም ሲያቅተው የፈሪ ዱላውን ንፁኋን ማህበረሰብ ላይ እያሳረፈ ይገኛል። በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን ስር በሚገኙ የአማራ ተወላጆች ብቻ በሚኖሩባቸው የተለያዩ ቀበሌዎች ላይ በጦር ሄሊኮፍተርና በጄት እንዲሁም በሰው አልባ አውሮፕላን የታገዘ ጥቃት በመፈፀም የንፁኋኖችን ሕይወት ቀጥፏል።
ጥቃቱ የተፈፀመው ዛሬ ሰኔ 16/2018 ዓ/ም ሲሆን፡ በተለይ በምስራቅ ወለጋ ዞን ጊዳ አያና ወረዳ አንዶዴ ዲቾ ቀበሌ ላይ አድት እናት የጥቃቱ ሰለባ ስትሆን በረካቶቺ ደግሞ ቀስለኛ ሁነዋል። በሌላኛው ልዩ ቦታው ደግሞ አሊ በተባለ መንደር ላይ ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ በርካታ ንፁኋን ወገኖች የጥቃቱ ሰለባ ሆነዋል።
ጥቃቱ ከተፈፀመበት አከባቢ በግምት በ30km ርቀት ላይ በሚገኘው በነቀምቴ አየር ማረፊያ መነሻና መንደርደሪያውን ባደረገው የጦር ጄት፡ በተለይ በአሊ ቀበሌ በተፈፀመው ጥቃት ሕይወታቸው ካለፈ ንፁኋኖች በተጨማሪ የቆሰሉ ወገኖች ወደ አንገር ጉትን ከተማ ተወስደው እንዳይታከሙ መከላከያ ሠራዊቱና የገዳ ኮማንዶ መንገድ በመዝጋት ጭምር አረመኔያዊ ድርጊት ፈፅመዋል።
በተመሣሣይ በዞኑ ዋጃ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ አገዛዙ በንፁኋኖች ላይ በጦር ሄሊኮፍተር ታግዞ ፈንጅ ሲወረውር ውሏል።
በተመሣሣይ፡ ጉልማ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ በጦር ጄትና በሰው አልባ አውሮፕላን የታገዘ ድብደባ ሲፈፀም የዋለ ሲሆን፡ በዚህም በእርሻ ስራ ላይ የነበሩ አርሶ አደሮች ጭምር የጥቃቱ ሰለባ መሆናቸው ታውቋል።
በተያያዘ ዜና፡ ቱሉጋና ከተማን ጨምሮ ለምስራቅ ወለጋ አጎራባች በሆኑ የሆሮጉድሩ ወለጋ ዞን አከባቢዎች ላይ ሰፊ የሆነ የሰው አልባ አውሮፕላን ቅኝት ሲደረግ ውሏል።
ስለሆነም መላ ህዝባቺን ከዚህ ፀረ ፋሺስት አገዛዝ እራሳቸንን በመከላከልና አለስፈለጊ የሆኑ ስብስቦቺን እድናቆም ስንል በጥብቅ እናሳስብለን።
አፋብን ወለጋ(ቢዛሞ) አንሻ ሰይድ ዕዝ ህ/ግንኙነት መምሪያ
አገዛዙ ንፁኋኖችን ኢላማ ያደረገ የጄትና የሄሊኮፍተር ድብደባ ፈፀመ!
ሃገር አፍራሹና ፀረ አማራው የብልፅግና አገዛዝ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን ስር በሚገኙ የአማራ ተወላጆች ብቻ በሚኖሩባቸው የተለያዩ ቀበሌዎች ላይ በጦር ሄሊኮፍተርና በጄት እንዲሁም በሰው አልባ አውሮፕላን የታገዘ ጥቃት በመፈፀም የንፁኋኖችን ሕይወት ቀጥፏል።
ጥቃቱ የተፈፀመው ዛሬ ሰኔ 16/2018 ዓ/ም ሲሆን፡ በተለይ በምስራቅ ወለጋ ዞን ጊዳ አያና ወረዳ አንዶዴ ዲቾ ቀበሌ ልዩ ቦታው አሊ በተባለ መንደር ላይ ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ በርካታ ንፁኋን ወገኖች የጥቃቱ ሰለባ ሆነዋል።
ጥቃቱ ከተፈፀመበት አከባቢ በግምት በ30km ርቀት ላይ በሚገኘው በነቀምቴ አየር ማረፊያ መነሻና መንደርደሪያውን ባደረገው የጦር ጄት፡ በተለይ በአሊ ቀበሌ በተፈፀመው ጥቃት ሕይወታቸው ካለፈ ንፁኋኖች በተጨማሪ የቆሰሉ ወገኖች ወደ አንገር ጉትን ከተማ ተወስደው እንዳይታከሙ መከላከያ ሠራዊቱና የገዳ ኮማንዶ መንገድ በመዝጋት ጭምር አረመኔያዊ ድርጊት ፈፅመዋል።
በተመሣሣይ በዞኑ ዋጃ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ አገዛዙ በንፁኋኖች ላይ በጦር ሄሊኮፍተር ታግዞ ፈንጅ ሲወረውር ውሏል።
በአከባቢው መደበኛው የኔትዎርክ አገልግሎት በመቋረጡ የደረሰውን ሰብአዊ ጉዳት በውል ለማወቅ አልተቻለም።
በተመሣሣይ፡ ጉልማ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ በጦር ጄትና በሰው አልባ አውሮፕላን የታገዘ ድብደባ ሲፈፀም የዋለ ሲሆን፡ በዚህም በእርሻ ስራ ላይ የነበሩ አርሶ አደሮች ጭምር የጥቃቱ ሰለባ መሆናቸው ታውቋል።
በተያያዘ ዜና፡ ቱሉጋና ከተማን ጨምሮ ለምስራቅ ወለጋ አጎራባች በሆኑ የሆሮጉድሩ ወለጋ ዞን አከባቢዎች ላይ ሰፊ የሆነ የሰው አልባ አውሮፕላን ቅኝት ሲደረግ ውሏል።
በሸበል በረንታ ወረዳ 2 የአገዛዙ ሰራዊት አባላት ሲወገዱ 2ቱ ከባድ ቁስለኛ ሆነዋል!!
64ኛ ክ/ጦር ሰኔ 16/2018 ዓ.ም
~~~~~~~
ሰኔ 16/2018 ዓ.ም በሸበል በረንታ ወረዳ የዕዱውሃ ከተማ ሰፍሮ የሚገኘው የአገዛዙ አረ* ናዊ ሰራዊት አባላት ከመንገድ መሪው ቅጥረኛ ሚሊሻ ጋር በመቀናጀት በየዕድውሃ እና አካባቢው የሚገኙ አርሶ አደሮች የግል መሳሪያ ለመዝረፍ እንቅስቃሴ ቢያደርጉም በጀግኖቹ የሽፈራው ገርባው ልጆች የዝረፊያ ዕቅዱን አክሽፈውታል።
አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር በሸበል በረንታ ወረዳ የዕዱውሃ እና አካባቢው ወረጎ ቀበሌ ወይንውሃ ጉጥ በወሰደው ከባድ እርምጃ 2 የአገዛዙ ሰራዊት አባላት ላይ እርምጃ ወስዶል። ከእነዚህም ውስጥ የ10 ዓለቃ ማዕርግ ያለው ሻንበል መሪ ሲወገድ 2 የአገዛዙ ሰራዊት አባላትን ከባድ ቁስለኛ ሆነዋል።
ክ/ጦር በአገዛዙ ሀይል ላይ በወሰደው ከባድ እርምጃ ተስፋ የቆረጠው የአገዛዙ ሰራዊት አባላት የአካባቢው ማህበረሰብን የቤት በር በመስበር አርሶ አደሮችን ለማዳበሪያ መግዥያ ያስቀመጡትን ገንዘብ በመዝረፍ ወደ መጣበት የዕድውሃ ከተማ ተመልሰዋል።
አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!!
ሰኔ 16/2018 ዓ.ም
አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት
በማህበራዊ ሚዲያ የኑግ አገዳ አቅም ያላቸው "ቀበኛ" የሚያሰራጩት መረጃዎች በሆዳቸው ያደሩ የብልፅግናን አጀንዳ በመሸከም የጎበጡ ሐስተኛ መሆናቸውን ስለማሳወቅ፤
♨️♨️♨️♨️♨️♨️♨️♨️♨️♨️
ሰኔ 16/2018
👉የተከበራችሁ ውድ የአማራ የፋኖ መሪዎች፣
👉የተከበራችሁ የአማራ ፋኖዎች፣
👉 የተከበራችሁ ውድ የትግሉ ደጋፋዎች እንዲሁም የፋኖ ድል ናፋቂዎች አማራውያን በሙሉ፤
=======================
📌 በመጀመሪያ ከሁሉም በማስቀደም ሰላምታ ማቅርብ እንወዳለን🙏🙏🙏
ከዚህ በመቀጠል አሁን እስከ አለንበት ሰዓት ድረስ የመከራ ቀንበር ለተሸከመው ለታላቁ አማራ ህዝብ ህልውና ሲሉ አካላቸውን ላጡና አይተኬ ህይወታቸውን ለገበሩ ለትግሉ ሰማዕታት ለከፈሉት የህይወት ዋጋ ያለነን ታላቅ አክብሮት እና ስሜትን መግለፅ እንሻለን።
የአማራ ፋኖ ትግል በጀግኖች መስዕዋትነት ከአለት የተመሰርተ እንደ "ፌሮ"ብርት የጠና መሰረቱ በአማራ ህዝብ ውኃ ልክ የተሰራ ሳይሆን ኖሮ ቢሆን በሚወረወረው የአንባገነኑ ስርዓት የማህበራዊ ሚሊሻ የሚዲያ ጋጋታ ፣ ሽለላ፣ቅርርቶ፣ የፔስታል አቅም የተሸከሙ የውስጥም ተኩላዎች እና ቁራዎች ጨምሮ በሚሰጡት አጀንዳዎች ቢሆን ኖሮ እንፈርስ ነበር።
እውነተው ግን እንዲህ ነው.....!
አባታችን ታላቁ ሰማዕቱ ሜጀር ጀኔራል ውባንተ አባተን ጨምሮ ታሪካቸውን በብዕር ቀለም ሳይሆን በደምና አጥንት አስቀምጠው ያለፉትን የታሪክ ጀግኖች ወንድሞቻችን የእነሱን ፈለግ በመከተል በጀብደኝነት መፋለም በክብር ለወጣንለት ዓላማ እስከ ህይወት መስዕዋትነት በመክፈል የታላቁን አማራ ህዝብ ህልውና ማረጋገጥ ህፀፅ የሌለው የአዕምሮ ማህተማችን ነው።
የጀመርነውን የህልውና ተጋድሎ ከታለመለት ዓላማ ግብ ለማድረስ በመንደር፣ በጎጥ ፣በቀጠና ፣በዘር ሀርግ ፣ጠላቶቻችን በሰጡን አቅጣጫ፣ ፣እርስ በራስ በመጠላለፍ፣ የተለያዩ ታልጋዎችን በመለጠፍ፣የራስን ፍላጎት በማስቀደም፣ በእኔነት አባዜ ሳንባዝዝ በግል ጥቅም ሳንወድቅ በፅኑ ታምነን ትግላችን በተግባር እንደ ወርቅ በእሳቱ ተፈትነን አላማችን እስከ ቀራኒዮ ድረስ ማስቀጠል የዘወትር ግዴታችን ነው።
ስለሆነም የአገዛዙ የሚዲያ ጉድፍቻ በጥቅም የሰከሩ በቀዳሚነት የሆነው "ሙሉጌታ ካሴ"እና ግብር አበሮቹ በማሳተፍ በሜ/ጀኔራል ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር ስር በርካታ ጀብዶችን በመፈፀም የሚታወቀው የጠላት ራስ ምታት ጉና ክፍለ ጦር ሰም የማጠልሸት ከውስጥም ከውጭም የጠላትን ስውር አጀንዳ በማስፈፀም የነፈዙ በማህበራዊ ሚዲያ AIን በመጠቀም የሚያሰራጩት ሃሳብ ፍፁም በሬ ወለድ ሐስትን የተሸከመ እውነትን የቀበር ፀረ አንድነትን በመሆኑ የአማራ ፋኖ የትግላችን ፊታውራሪ መሪዎች፣ ታጋይ ሰራዊታችን እንዲሁም የትግሉ ደጋፊዎች እውነቱን እንዲረዱ እና እንዲያውቅ ስንል መልዕክታችን እናስተላልፋለን።
የጀመርናውን ታሪካዊ የህልውና ተጋድሎ ሳንካዎች ሳይበግሩን ይበልጥ ካስማ ሁነን ተጠናክረን ቀጥለናል።
ዘላለማዊ ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
✍️ የሜጀር ጀኔራል ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር ጉና ክፍለ ጦር ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ይፋትና ጥሙጋ አውራጃ ደጃች ተሰማ እርገጤ ክፍለ ጦር እና የማጀቴ አባት አርበኛኞች ድል ተቀዳጁ!!
ቀን 16/10/2018 ዓ.ም
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ መሀመድ ቢሆነኝ ኮር ደጃች ተሰማ እርገጤ ክፍለጦር ሸዋሮቢት ማረሚያ ቤት አካባቢ ልዩ ስሙ አቦምሳ ከተባለ ስፍራ መሽጎ የነበረውን ጠላት እንደ ቅጠል አርግፈው ምሽጉን ተቆጣጥረው ውለዋል።
በዚሕ አውደ ውጊያ ጠላት ክፉኛ በመመታቱ ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ሙትና ቁስለኛ ሆነዋል። ጠላት የሞቱበትን አባላቱን ከምሽግ አቅራቢያ እንደቀበረ ና ቁስለኞቹን ሸዋሮቢት ሆስፒታልን ማጨናነቁ ተረጋግጧል። በቀን 15/10/2018 ዓ.ም በተካሔደው የሌሊት ሰባት ስአት(7:00) ደጃዝማች ተሰማ እርገጤ የክ/ጦ ቃኘና የሻለቃ ሁለት ውስን አባላት አቦምሳ በተባለ ቦታ ላይ የመሸገውን የጠላት ሃይል በክላሽንኮቪና ቦንብ ብቻ በጨበጣ ውጊያ ምሽጉን ለመደረማመስ ችለዋል።
በሌላ ዜና በዚሁ አውራጃ በማጀቴ ቆላ የቆላ ዘብ አባት አርበኞች አስደናቂ ድል ተጎናፅፈዋል። ከኦሮሞ ብሔረሰብ ዳዋ ጨፋ ወረዳ ጨፋ ሮቢት ከተማ መነሻወን አድርጎ የማጀቴ ቆላ ዘብ ጠባቂ አባት አርበኞችን ለመክበብ የሞከረውን የሽመልስ አብዲሳ ተላላኪ ሚሊሻን አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት ታላቅ ድል ተጎናፅፏል።
በዚሕ አውደ ውጊያ አባት አርበኞቹ እንዳመጣጡ ተቀብለው ያልጠበቀው ሽንፈት የገጠመው ሲሆን የሟቹ ሁሴን ልጅ " አህመድ ሁሴንን" ጨምሮ ተሸኝተዋል።
ይሕ የብልፅግና ግሪሳ የአባት አርበኞችን ክንድ መቋቋም ያቃተው ከኬሚሴ ከተማ አጋዥ ሀይል በመጠየቅ በቦታው ለማሠለፍ ሞክሮ አርበኞቹ ለዳግም ድል እየተጠባበቁት ይገኛሉ።
በዚሕም አርበኞቹ ካገኟቸው ድሎች፦
1. ሰባት(7) ሚሊሻ እስከ ወዲያኛው ተሸኝቷል
2.ስምንት (8) ክላሽኮቭ መሳሪያ
3.ሰባት(7) የወገብና የደረት ትጥቅ
4.አራት(3) የእጅ ስልኮች
"ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን !
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!!
በሸበል በረንታ ወረዳ 2 የአገዛዙ ሰራዊት አባላት ሲወገዱ 2ቱ ከባድ ቁስለኛ ሆነዋል!!
64ኛ ክ/ጦር ሰኔ 16/2018 ዓ.ም
~~~
ሰኔ 16/2018 ዓ.ም በሸበል በረንታ ወረዳ የዕዱውሃ ከተማ ሰፍሮ የሚገኘው የአገዛዙ አረ* ናዊ ሰራዊት አባላት ከመንገድ መሪው ቅጥረኛ ሚሊሻ ጋር በመቀናጀት በየዕድውሃ እና አካባቢው የሚገኙ አርሶ አደሮች የግል መሳሪያ ለመዝረፍ እንቅስቃሴ ቢያደርጉም በጀግኖቹ የሽፈራው ገርባው ልጆች የዝረፊያ ዕቅዱን አክሽፈውታል።
አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር በሸበል በረንታ ወረዳ የዕዱውሃ እና አካባቢው ወረጎ ቀበሌ ወይንውሃ ጉጥ በወሰደው ከባድ እርምጃ 2 የአገዛዙ ሰራዊት አባላት ላይ እርምጃ ወስዶል። ከእነዚህም ውስጥ የ10 ዓለቃ ማዕርግ ያለው ሻንበል መሪ ሲወገድ 2 የአገዛዙ ሰራዊት አባላትን ከባድ ቁስለኛ ሆነዋል።
ክ/ጦር በአገዛዙ ሀይል ላይ በወሰደው ከባድ እርምጃ ተስፋ የቆረጠው የአገዛዙ ሰራዊት አባላት የአካባቢው ማህበረሰብን የቤት በር በመስበር አርሶ አደሮችን ለማዳበሪያ መግዥያ ያስቀመጡትን ገንዘብ በመዝረፍ ወደ መጣበት የዕድውሃ ከተማ ተመልሰዋል።
አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!!
ሰኔ 16/2018 ዓ.ም
አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት
‹‹እናንተ ውጡ፤ እኛ መውጣት አንችልም›› የጀግኖቹ የመጨረሻ ቃል!
ለዓላማ ታምኖ በጀግንነት መውደቅ፤ የአማራ ፋኖ የአባቶቹ ውርስ ነው።
ከአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ እዝ የተሰጠ መግለጫ፦
የአማራ ሕዝብ የተከፈተበትን ሥርዓታዊ የዘር ማጥፋት ጦርነት ለመቀልበስ በጽናት እየተዋጋ ያለው የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ፤ በጠላት ብልጽግና አገዛዝ ላይ ተደጋጋሚ ክንዱን እያሳረፈ፤ የድል ግስጋሴውን አስጠብቆ ይገኛል፡፡
በዚህ መራራ እና ፈተናው ብዙ በሆነው የህልውና ትግል ላይ፤ የአማራ ፋኖ በርካታ ተግዳሮቶችን በጽናት እያለፈ፤ ውድ እና ጀግና ልጆቹም በጀግንነት የህይወት መስዋዕት እየከፈሉ፤ የድል ጉዞውን አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ እዝ፤ ከመቼውም ጊዜ በላይ የአንድነት ሂደቱን እያጠናቀቀ ይገኛል፡፡ ይህ የፋኖ አንድነት ያሳሰበውና የጭቆና አገዛዝነት ዘመኑ ማብቂያ መሆኑን የተረዳው ጠላት ኦህዴድ/ብልጽግና አገዛዝ፤ የዘወትር የአማራ ሕዝብ የስቃይ ምንጭ የሆነውንና ለአገዛዙም የጥቃት ዓላማ ዋና ምርኩዝ የሆነውን የብአዴን መዋቅር እንዲሁም ሰርጎ ገብ ሀይሉን ተጠቅሞ በርካታ ሠራዊት በሜካናይዝድ መሣሪያ አጅቦ ወደ ማዕካለዊ ጎንደር ደንቢያና ማክሰኝት ዙሪያ ዘመቻ ከፍቶ ነበር፡፡
ጠላት በከፍተኛ ዝግጅትና በጀት፤ እንዲሁም በመንገድ መሪ ምርኩዙ ብአዴን እየተመራ የፋኖ መሪዎችን ለመክበብ ባደረገው ውጊያ፤ በርካታ የጠላትን ሠራዊት አንበርክከው የተሰው ውድ የአማራ ልጆች፤ ለወጡለት ዓላማ እና አደራ ለሰጣቸው ሕዝብ ታምነው የክብር መስዋዕት ሆነዋል፡፡
የጠላት ሠራዊት ከፍተኛ ሀይል ይዞ ያደረገውን ከበባ ለመስበር በተደረገው ብርቱ ትንቅንቅ፤ ውድ የአማራ ልጆች የሆኑት መሪዎቻችን፤ አርበኛ አማረ አቸነፍ ታደገ፣ አርበኛ ሳምሶን አማረ፣ አርበኛ መቶ አለቃ አበራ አግማስ፣ አርበኛ ሥጦት ጀምበር እና አርበኛ አትርሳው ገበያውን ጨምሮ፤ ሌሎች ጀግኖች የትግል አጋሮቻችን ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም በክብር ተሰውተዋል፡፡ በጀግኖች መስዋዕት መሆን እዛችን የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለጸ፤ ጀግኖቹ የተሰውለትን ዓላማ ከግብ ለማድረስ፤ መላው የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ እዝ አመራርና ሠራዊት፤ ቃል እነገባለን፡፡
ጀግኖቹ በመጨረሻው የተጋድሏቸው ሰዓት፤ ‹‹እኛ መውጣት አንችልም፤ የአማራን ሕዝብ እኛ ሞተን ልናድነው ስለሆነ ትግላችንን የጀመርነው ለወጣንለት ዓላማ ታምነን እንሰዋለን፡፡ አንድ ጥይት እስኪቀረን ድረስ እንፋለማለን እናንተ ወደኋላ ሁኑና ትግሉን አድኑ፡፡ አንድነቱን በጉጉት ለሚጠብቀው ወገናችን እንድታበስሩት በመጨረሻዋ እስትንፋሳችን ላይ ቆመን አደራ እንላችኋለን›› በማለት ነበር የመጨረሻ ቃላቸውን ለመሪዎቻቸውና ለትግል አጋሮቻቸው በማስተላለፍ የተሰናበቱን፡፡ ጀግኖቹ በቃላቸው መሠረት ህልቆ መሳፍርት የጠላትን ሠራዊት ከአፈር ከቀላቀሉ በኋላ፤ ለአማራ ሕዝብ ህልውና እና ነፃነት ሲሉ በጀግንነትና በክብር ተወስተዋል፡፡
ይህ የጀግኖች ወንድሞቻችን የክብር መስዋዕትነት፤ ሠራዊታችን የወጣለትን ዓላማ ከዳር ለማድረስ የበለጠ የሚያነሳሳን እንጂ፤ ትግላችንን የሚያዳክም፤ በሠራዊታችን ላይም የስነ ልቦና ስብራት እንደማያደርስ ልናረጋግጥላችሁ እንወዳለን፡፡
የጀግና ፍጻሜው በጀግኖች ሜዳ እንጂ፤ ለጠላቱ እጁን በመስጠት የሚጠናቀቅ ታሪክ የለውም፡፡ በጀግኖች ወንድሞቻችን መስዋዕት መክፈል፤ መሪር ሀዘን ቢሰማንም፤ ወንድሞቻችን ለተሰውለት ዓላማ እና የአማራ ፋኖ ለወጣለት የትግል ዓላማ፤ በጽናት በመፋለም፤ የአማራን ሕዝብ ስቃይና መከራ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እናስቆማለን፡፡
ዘላለማዊ ክብር ለጀግኖች ሰማዕታት
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ እዝ
ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም
ጎንደር--- አማራ ---ኢትዮጵያ
ከሠም ፪ኛ ኮር ለተከታታይ ሶስት ቀናት ከጠላት ኃይል ጋር ከፍተኛ ትንቅንቅ አድርጎ ድል ሲቀዳጅ በሌላ በኩል ተስፋ የቆረጠው የአገዛዙ ኃይል በደራ ከፍተኛ ዝርፊያ እና የንፁሃን እገታን ስራዬ ብሎ የዕለተ ከእለት ተግባሩ አድርጎታል::
ሰኔ 16/2018 ዓ.ም
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ከሠም ኮር ነበልባል ክ/ጦር ከነብሮ ሻለቃ እና ከምኒልክ ሻለቃ በተውጣጣ ኃይል ጠላት ላይ ከባድ ኪሳራ ማድረስ ችሏል። በሁለት የፋኖ ሻለቆች ለሁለት ተከታታይ ቀናት ከወራሪው ኃይል ጋር በተደረገ እልህ አስጨራሽ ውጊያ በምስራቅ ሸዋ ዞን አዳማ ወረዳ በሙኩዬ ቀበሌ ዘልቀው የገቡት የፋኖ ኃይሎች ወራሪው ኃይል ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረስ ችለዋል። በተደረገው እልህ አስጨራሽ ውጊያ የጠላት ኃይል ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ኪሳራ ደርሶበታል:: ይኸውም
.አንድ ከአዳማ ወረዳ የመጣ ከፍተኛ አመራር የሞተ
. አንድ የሙኩዬ ቀበሌ ኮማንደር ፖሊስ የሞተ
.አንድ ሚሊሻ የተማረከ
.አምስት የአገዛዙን ኃይል ቁስለኛ ማድረግ የተቻለ ሲሆን በምርኮ የተገኙ ንብረቶች
. ሁለት ክላሽ ኮፍ
.አንድ ኤምዋን መሳሪያ ገቢ ተደርገዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ከሠም ኮር ሀይለማርያም ማሞ ክፍለ ጦር እና ነበልባል ክፍለ ጦር በጥምረት ባደረጉት አውደ ውጊያ ጠላትን ቀጥቅጠው ድል ተቀዳጅተዋል።ከሀገረ ማርያም ከሰም ወረዳና ከምንጃር ሸንኮራ ወረዳ በኩል ለወረራ እና ለዘረፋ የገባውን የጠላት ኃይል በሀይለ ማርያም ማሞ ከፍለ ጦር ክፉኛ ተመትቶ ወደ መጣበት እዲመለስ ተደርጓል። በዚሕ አውደውጊያ ክፉኛ የተመታው ጠላት ለተከታታይ ሶስት ቀናት በተደረገው እልህ አስጨራሽ ውጊያ ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ኪሳራን አስተናግዶ ወደ መጣበት ተመልሷል። አገዛዙ ቁጥራቸው በውል ያልታወቁትን ቁስለኛቹን ወደ ሀገረማርያም የህክምና ማዕከሉ የላከ ሲሆን የሞቱት አባሎቹን የቻለውን ባገኘበት ቀብሮ ያልቻለውን አስከሬናቸውን ሳይዝ ትቶ መፈርጠጡ ተረጋግጧል።
በሌላ ግንባር ነበልባል ክፍለ ጦር ከ14/10/2018 ጀምሮ ከሀገረ ማርያም ተነስቶ በዮላት እና በቅዱሥጌ ቀበሌ የመጣውን ወራሪ ሰራዊት እንደ አንዳ አመጣጡ ተመቶ የተመለሰ ሲሆን ሥቻት ቀበሌ ላይ ሰፍሮ የነበረውን የጠላት ኃይል ለተከታታይ ሶስት ቀን በተደረገ እልህ አስጨራሽ ውጊያ ወራሪው ኃይል ስቻትን ለቆ እንዲወጣ ተደርጕል::
በሌላ አቅጣጫ በምንታምር በኩል ወደ አክርሚት የገባው የጠላት ኃይል በጀግኖቹ የነበልባል ክፍለ ጦር ቃኚዎች እና አንድ ሻለቃ ባደረጉት አውደ ውጊያ ሰቃዋጮ በምትባል ቀበሌ ላይ የጠላት ኃይል ከፍተኛ ጉዳት ያስተናገደ ሲሆን ጠላት ይዞታውን ለቆ እየሸሸ ይገኛል። ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ድረስ ውጊያው በተለያየ ግንባሮች አሁንም እንደቀጠለ ሲሆን ተጨማሪ የአውደ ውጊያ ዘገባዎችን በቀጣይ ይዘን የምንመለስ ይሆናል::
በሌላ ዜና በደራ እና አካባቢው ህዝባችን ላይ በተፈፀመ ዝርፊያ እና ውንብድና ከ400 በላይ የሚሆኑ የቀንድ ከብቶች ሲዘረፉ፣ ከ84 በላይ ንፁሀን ወገኖች ታግተው መወሰዳቸውን ነዋሪዎች ገለፁ።
በውድቀቱ ዋዜማ ላይ የሚገኘው የብልፅግናው አገዛዝ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መርሀቤቴ አውራጃ በደራ ጉንዶ መስቀል ወረዳ ነዋሪዎች ላይ መጠነ ሰፊ ግፍና መከራ ማድረሱን አጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን የኦሆዴድ ብልፅግና መራሹ ቡድን ካሰማራው የጃል ሰኚ የሸኔ ትራፊ ወንበዴዎች ጋር በፈፀሙት የጋራ የዝርፊያ ተግባር በወረዳው ስር የሚገኙ የአባጦ ቀበሌ ነዋሪዎችን ከ400 በላይ የሚሆኑ የቀንድ ከብቶችን የዘረፉ ሲሆን ከ84 በላይ ንፁሀን ሰዎችን በማገት መውሰዳቸውን ነዋሪዎች ገልፀዋል።
ትላንት ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም በተፈፀመው የዝርፊያ እና የአጋችነት ተግባር እጅግ አሳፋሪ የሚያደርገው ንብረታቸውን ከወራሪው ለመከላከል የጦር መሳሪያ ይዘው የወጡ የአካባቢው ነዋሪዎችን በመነጠል እና አንድ ላይ በመሰብሰብ አገዛዙ በፈፀመው የድሮን ጥቃት ንፁሓኖቹ ኢላማ እንደሆኑ ተደርጎ 7ቱ ወዲያውኑ ህይዎታቸው ሲያልፍ 11ዱ ቁስለኛ ሆነው ሀብት ንብረታቸውን እንዳይከላከሉ ከመደረጉም ባሻገር ግፍ ተፈፅሞባቸዋል::
አገዛዙ ባሰማራቸው የሸኔ ቡድን በአባጦ ቀበሌ ነዋሪዎች ላይ መጠነ ሰፊ ዝርፊያ እና ወረራ መደረጉን ተከትሎ ነዋሪዎች ባሰሙት የድረሱልን ጥሪ መሰረት የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ አምደ ፅዮን ኮር የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር አሃዶች በፍጥነት ተወርውረው በቦታው ላይ ደርሰው ለመታደግ ባደረጉት ከፍተኛ ጥረት ውስን የኦሮሞ ብሔር ተወላጆችን ከእገታው ቢያስለቅቁም በሁለት አቅጣጫ በብልፅግናው ሰራዊት በተፈፀመበት ከበባና ጥቃት የፋኖ ኃይሉ ወደመከላከል ውጊያ በመግባቱ በአባጦ ቀበሌ የታገቱ ንፁሃን ነዋሪዎች እና የተዘረፈውን ንበራታቸውን ሙሉ በሙሉ ማትረፍ አለመቻሉን ኮሩ ባደረሰን መረጃ ገልጿል።
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ በተደጋጋሚ ጊዜ ባደረገው የማጣራት ስራ በደራ ጉንዶ መስቀልና አጎራባች ወረዳዎች የሚገኘው የብልፅግና አመራሮች ከሸኔ ቡድን ጋር ጥብቅ ቁርኝት እንዳላቸውና የጦር መሳሪያና የተተኳሽ ድጋፍ ጭምር እንደሚያደርግላቸው ያረጋገጠ ሲሆን በተጨማሪም በንፁሀን ወገኖች ላይ የሚፈፀሙ እገታና ዘረፋዎች በቅንጅት እንደሚሰሩ ማሳያ መሆኑን ለሰፊው ህዝባችን መግለፅ እንወዳለን።
''ክብር ለትግሉ ሰማዕታት''
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
