ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
الذهاب إلى القناة على Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
إظهار المزيد2 937
المشتركون
-324 ساعات
+3667 أيام
+38130 أيام
أرشيف المشاركات
በብልፅግና ፈቃድ የሃገርን ሉአላዊነት ጥሰው ወደ ቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል በገቡ የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ታጣቂዎች ላይ የጉምዝ ነፃ አውጭ ኃይሎች እርምጃ መውሰድ መጀመራቸው ታወቀ!
በሱዳን ብሉ ናይል ግዛት በኩል ወደ ኢትዮጵያ ድንበር የተሻገሩት በመሃመድ ሃምዳን ዳጋሎ የሚመራው የፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች፡ በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል የጦር ካምፕ መገንባታቸውን ተከትሎ በክልሉ ነዋሪዎች ከፍተኛ ቁጣ ተቀስቅሷል።
ታጣቂዎቹ በብልፅግናው አገዛዝ ፈቃድ የሃገርን ሉአላዊነት ጥሰው ወደ በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል በመግባት በክልሉ ነዋሪዎች ላይ ከፍተኛ ግፍና በደል እየፈፀሙ ይገኛሉ።
እራሱን የጉምዝ ሕዝብ ነፃ አውጭ ብሎ የሚጠራው ታጣቂ ቡድን፡ በክልሉ ሰፍረው በህዝብ ላይ ግፍ ሲፈፅሙ በነበሩት በእነዚህ የሄሜቲ ታጣቂዎች ላይ እርምጃ መወሰዱን የመረብ ሚዲያ ምንጮች አረጋግጠዋል።
የብልፅግና አገዛዝ እነዚህን የሄሜቲ ታጣቂዎች፡ ቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልልን ለጦር ካምፕነት እንዲጠቀሙ በይፋ መፍቀዱ ሳያንስ፡ ታጣቂዎቹ በሕዝቡ ላይ ለሚፈፅሙት ሰቅጣጭ ድርጊት ምንም አይነት መከላከያ ካለማደጉም በላይ ለታጣቂዎቹ ጋር ወግኖ "ጥቃት ተፈፀመብን" በሚል አቤቱታ በሚያቀርቡ የክልሉ ነዋሪዎች ላይ እርምጃ ሲወስድ መቆየቱን መረብ ሚዲያ ከዚህ ቀደም በሰራቸው ዘገባዎች ለሕዝብ ማድረሱ አይዘነጋም።
ጣቢያችን ያነጋገራቸው የክልሉ ነዋሪዎች እንደገሉፁት፡ ታጣቂዎቹ በክልሉ ሰፍረው ግድያ፣ ዝርፊያ እና አስገድዶ መድፈርን ጨምሮ ሰብአዊ መብት ጥሰቶችን ሲፈፅሙ ቆይተዋል።
ታጣቂዎቹ በየሆቴሉ እና በየሱቁ እየገቡ ለሚመገቡት ምግብና ለሚገዙት ንብረት ክፍያ ሲጠየቁ "ብልፅግና ይክፈላችሁ" በማለት በባለቤቶቹ ላይ ሲሳለቁ እንደነበር ነው መረብ ሚዲያ ያነጋገራቸው የክልሉ ነዋሪዎች አክለው የገለፁት።
የብልፅግና አገዛዝ ካድሬዎች የዜጎችን ደህንነት ከማስጠበቅ ይልቅ፡ ግፉን የሚቃወሙ ነዋሪዎችን እያደኑ በማሰር ለውጭ ታጣቂዎች ከለላ እየሰጡ መሆናቸው ነው የታወቀው።
"ከሱዳን ተነስተው ወደ ኢትዮጵያ የገቡት የሄሜቲ ታጣቂዎች፡ የቤኒሻንጉልን የፀጥታ ሁኔታ አደጋ ላይ ጥለውታል። ይህ ድርጊት አገዛዙ ለሀገር ሉዓላዊነት ያለውን ንቀት የሚያሳይ ነው" ሲሉ ነዋሪዎቹ ቃል በቃል ገልፀዋል።
የሃገርን ሉአላዊነት ጥሰው በመግባት በሕዝብ ላይ ግፍና መከራ በሚያደርሱት በነዚህ የሄሜቲ ታጣቂዎች ላይ ነው እራሱን የጉምዝ ሕዝብ ነፃ አውጭ ብሎ የሚጠራው ታጣቂ ኃይል እርምጃ መውሰድ የጀመረው።
ታጣቂ ቡድኑ የሄሜቲ ጦር የሰፈረበትን ካምፕ ከማውደም ጀምሮ እስከ ጨበጣ ውጊያ የዘለቀ እርምጃ በመውሰድ ወታደሮቹ ክልሉን ለቀው ወደ ሃገራቸው እስኪመለሱ ድረስ እርምጃውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ነው የታወቀው።
ከህዝባችን ጋር እንወያያለን፥እንመክራለን ወደ ፊት እንጓዛለን‼️
መሪያችን አርበኛ ዘመነ ካሴ እንደተናገረው ፦ "የአማራ ህዝብ ህልውና፣ጥቅሙና ምኞቱ ለድርድር አይቀርቡም ፥ቅዱስ ናቸው።"
የትግላችን አልፋና ኦሜጋ ይህ ነው ።ትግሉ የህዝብ ፥ ለህዝብ ነው።
በእያንዳንዷ የትግል ምዕራፍ ላይ ጠንካራም ሆነ ደካማ ጎናችን ህዝባችንን ይዘን እንመክራለን ፥ እንዘክራለን። የትግል ጉዟችንን በመልካም መድላድል እናበጃለን።የተከበረውን ፣ ጀግናውን እና አስተዋዩን የአማራ ህዝብን ይዘን የማንሻገረው ገደል ፣ የማንወጣው አቀበት የለም።
ህዝባችን ፣ ወርቃማ ዓላማችን እና መሪያችን አይነኬ ናቸው ።
'ህዝብ አዬ ፥ እግዜር አዬ አይደል የሚባለው!?
ትላንትም ፥ ዛሬም ፥ ነገም የህዝባችን ፍላጎት ፣ ጥያቄና ጥቅም ምንም ሳናጓድል እንፈፅማለን ፥ እናስፈፅማለን ። ከህዝባችን ከብርና ልዕልና በታች ሆነን ያገባደድነውን የህልውና ትግል በድል እንቋጫለን።
ክፋት ለማንም፣በጎነት ለሁሉም!
አዲስ ትውልድ፣አዲስ አስተሳሰብ ፣አዲስ ተስፋ!
ምስል፦የአቡዬ ገብረመንፈስ ቅዱስ ዕለት (ሐምሌ 05/2018 ዓ.ም) ከጀግናው የሜጫ ህዝብ ጋር ስንመክር ከሚዲያ ክፍል የተገኘ!
ቁራ በጮኸ ቁጥር ንስር ወደ መሬት አይወርድም!
በሐሰተኛ አድራሻዎች (Fake Accounts) ጀርባ ተሸሽጋችሁ፣ በጎጥና በመንደር ጠባብ ቅጥር ውስጥ ሆናችሁ እውነተኛውን አማራነት ለእኔ ልታስተምሩኝ ለምትሞክሩ የዘመኑ አስመሳዮች እናንተ ማን ናችሁ ለእኔ አማራነትን ልታስተምሩ የምትሞክሩ? እኔ የታሪካዊውና ፅኑው የአሳምነው ደም፣ የእውነተኛው የጀግንነት ምሳሌ የራስ አርበኛ የዘመነ ካሴ ፈለግና መርህ ተከታይ ልጅ ነኝ። ማንነቴን ያነጽኩት ለሕዝብና ለሀገር ክብር በቆሙ ታሪካዊ ምሶሶዎች ላይ እንጂ፣ በየሰፈሩ ለይስሙላ በሚጮሁ ጊዜያዊ ስብስቦች ላይ አይደለም። የኔ አማራነት የጥንታውያን ንጉሦቻችንን ሰፊና ታላቅ አገራዊ ራእይ የሚከተል የማይናወጥ የጽናት ማማ ነው።
ዝምታዬ ድክመት ሳይሆን የከፍታዬ መለኪያ ነው! በየማህበራዊ ሚዲያው ከሚሰማው የበታችነት ጩኸት ጋር አፍ ለመካፈት አለመፈለጌ፣ ከእኔ ማንነትና ክብር ጋር የማይመጥኑ የሰፈር ዱከካሞችን መድረክ ማድመቅ ስላልፈለግኩ ብቻ ነው። ንስር ከቁራዎች ጋር አብሮ ለመጮኽ ወደ መሬት አይወርድም፤ እኔም ታሪክንና ስልጣኔን በታላቅነት እንጂ በጎጥ አጥር የማላውቅ በመሆኔ፣ ከማይመጥኑኝ ወገኖች ጋር አፍ መካፈትንና መካሰስን ምርጫዬ አላደረግኩትም።
የእናንተ አማራነት የሰፈር አጥር ነው፤ የኔ ግን የአገር አድማስ! የእናንተ አማራነት ሰውን በመንደርና በጎጥ የሚከፋፍል የጠባብነት ድግስ ነው። በየሰፈሩ ተደራጅታችሁ በሐሰት ስም ማጥፋት እኔን ለማንበርከክ የምታደርጉት ከንቱ ጥረት፣ የእናንተን የሃሳብ ድህነት እንጂ የእኔን ፅኑ ጉዞ ቅንጣት ታክል አያደናቅፈውም።የእኔ ማንነት ከእናንተ የፈጠራ ስም በስተጀርባ ከምትደብቁት ጠባብነት በላይ እጅግ የላቀና ታላቅ ነው። ይህንን ተረድታችሁ ከከንቱ ጩኸታችሁ ብትመለሱ ይበጃችኋል! ዘሜ የአዲሱ ትውልድ ንጉስ ንገርልኝ በሰፈሩ ለተወሸቁ የአብይ አህመድ አጀንዳ ተሸካሚ አስመሳይ አማራዎች #Dave #Amhara
#አሳዛኝ_መረጃ‼️
በቂሊንጦ እስር ቤት ዉስጥ በግፍ ታስረዉ ከሚገኙት መካከል #ብንያም_ሸጋዉ በደረሰበት ድብደባ ህመም ምክንያት ህይወቱ የሞት አደጋ ዉስጥ መግባቱ ተገለፀ።
በአማራነታቸው በማንነታቸው ታስረዉ ከሚገኙት የህሊና እና ፖለቲካ እስረኞች መካከል #ብንያም_ሸጋዉ ከአዲስ አበባ ከሰራ ቦታው በግፍ በአገዛዙ ታፍኖ በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ከታሰር ከ9 ወር በላይ አልፎታል።
በመሆኑም በታፈነበት ወቅት በአዲስአበባ ፖሊስ ማእከላዊ ወንጀል ምርመራ ቢሮ በደረሰበት የሰባዊ መብት ጥሰት ህይወቱ የሞት አደጋ ዉስጥ መግባቱን መረጃ ደርሶናል።በማዕከላዊ ፓሊስ ጣቢያ ምርመራ ወቅት በአገዛዙ የፖሊስ አባላት(በስም የሚታወቁ) በአካል ጉዳት በማድረስ የመንጋጋ ጥረሱን በማዉለቅ፤ የእጅ ክንዱን በመስበር፤የጎን አጥንቱን በመስበር እና እምብርቱን እና እምብርቱ አካባቢ በደረሰበት የጫማ እርግጫ እምብርቱ በመፈንዳቱ ለ9 ወር ያክል ጊዜ ደም በመፈስስ አሁን ላይ ህይወቱ የሞት አደጋ ዉስጥ መገባቱን መረጃ ደርሶናል።
ከዚህ በፊት በነበረው የህክምና ክትትል በፍርድ ቤቱ ትዛዝ በማረሚያ ቤቱ በመሆን በፖሊስ ሆስፒታል ህክምና ክትትል እንዲደረግለት ፍርድቤቱ ቢያዝዝም የፖሊስ ሆስፒታል አልችልም የሚል የህክምና አቅም ማነስ በመስጠቱ ወደ ግል ሆስፒታል ሄዶ እንዲታክም ፍርድቤቱ ለማረሚያ ቤቱ ትዛዝ ሰጥቶ ነበር።ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ይህንን ትዛዝ ለመፈጸም ፍቃደኛ ባለመሆኑ የህክምና አገልግሎት መብቱን ከልክሎታል። በመሆኑም በሚፈሰው ደም ምክንያት ህይወቱ ወደ ሞት ስቃይ እያመራ መሆኑን የደረሰን መረጃ ያመለክታል ስለሆነም ይህ አማራነት ወንጀል ሆኖበት ቂሊንጦ የሚሰቃየው ወንድማችን ቢያንስ ህክምና ያገኝ ዘንድ ድምፅ እንሆን ዘንድ ጥሪ ተላልፏል‼️
#ፍትሕ_ለብንያም‼️
07/11/2018 ዓ.ም
#የድል_ዜና‼️
የበረኸኛው ቀስተ ደመና ሻለቃ በጠላት ላይ ድልን ተቀዳጀ‼️
ሐምሌ 07/11/2018 ዓ.ም
ጀግንነት ቢሉ ወታደራዊ ሥርዓትን መጎናጸፊያ እስከ ጥጉ ተጎናጽፎ፤ መጠሪያ ስሙን በሕብረ ቀለማት በደመቀው የእናት ሀገር አርማ ሰይሞ፤ በአማራ የትጥቅ ትግል ታሪክ ላይ ቀምሶ በማቅመስ የትግልን መሪር ጣዕም በለመለመ የነገ ተስፋ በማጣፈጥ አይተኬና ደማቅ የታሪክ አሻራ አስቀምጦ ያለፈ ቀስተ ደመና ሻለቃ።
ከቀስተ ደመና ጋር #ጥይት_ተወራውሮ አቅሙን ያወቀው ይቅርና #ዜና_ገድላቸውን የሰማ ሁሉ የሚርድላቸው የበረሃ አናብስቶች ነበልባላዊ በሆነ ክንዳቸው የጠላትን አከርካሪ መሰባበራቸውን ከጊዜ ወደ ጊዜ አጠናክረው የቀጠሉት በረኸኞቹ ከሰሞኑ ንጹሐንን ለመዝረፍና ለመጨፍጨፍ የመጣውን ወራሪ የብልጽግና ሠራዊት ሲያንቀጠቅጡት ሰንብተዋል።
በዛሬው ዕለትም #በጎፍጭማ ታዳጊ ከተማ በወሰዱት እርምጃ በርካታ ቁጥር ያለው የጠላት ኃይል የተደመሰሰ ሲሆን ብዙዎች ቆስለዋል፤ ወታደራዊ ቁሳቁሶችና መሳሪያዎችም ተማርከዋል።
ከሌሊቱ 11:30 ሰዓት ላይ በተፈጸመው መብረቃዊ ጥቃት የወገን ጦር የውጊያ የበላይነት የታየበት ስሆን በአንጻሩ በጠላት ላይ ከደረሰው አካላዊና ቁሳዊ ኪሳራ በዘለለ ከፍተኛ የሆነ የስነ ልቡና ውድቀትንም አስተናግዷል።
በውጊያውም በርካታ ቁሳዊ ሰብአዊና ሞራላው ድሎች የተገኙ ሲሆን:-
👉1/ 04 ክላሸ
👉2/ 04 የወገብ ትጥቅ
👉3/ የእጅ ቦምቦች
👉4/ 01 የስናይፐር ካዝና
👉5/ በርካታ የክላሽና የብሬን ተተኳሾች
👉7/ የቆሰለ=02 ፒካፕና 02 አምቡላንስ + 06 ቁስለኛና በርካታ ቁጥር ያለው የጠላት ሠራዊት ተደምስሷል። ለአብነት ያህልም አንድ አካባቢ ብቻ ላይ 08 አስከሬን መነሳቱን የዓይን እማኞች ገልጸውልናል ሲል ፋኖ ዘመን ባሳዝነው ለንስር አማራ ገልፀዋል‼️
07/11/2018 ዓ.ም
+1
የዲፕሎማሲና አለምአቀፍ ግንኙነት ምሁሩ ነፍጥ አንስቶ በርሃ ወረደ‼️
የዲፕሎማሲና አለምአቀፍ ግንኙነት ምሁር ጣሃ ደራሳ አሊ፡ ሃገር አውዳሚ እና ፀረ ሕዝብ የሆነው የብልፅግና አገዛዝን ለመገርሰስ በትጥቅ ትግል ላይ የሚገኘው የአፋር ብሔራዊ አንድነት አብዮታዊ ግንባርን መቀላቀሉን ድርጅቱ በማህበራዊ ትስስር ገፁ አስታውቋል።
07/11/2018 ዓ.ም
+1
የብልፅግና መከላከያ ሰራዊት አባል ሙሉ ትጥቅ ይዞ የፋኖ ምኒልክ ዕዝን ተቀላቀለ
ሐምሌ 07 ቀን 2018 ዓ.ም
(የአፋብን ምኒልክ ዕዝ 303ኛ ኮር )
መነሻውን በላሊበላ ከተማ ከሚገኘው የመንግስት ወታደራዊ ካምፕ ያደረገ አንድ የብልፅግና መከላከያ ሰራዊት አባል፣ ይዞት ከነበረው ሙሉ ትጥቅ ጋር የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄን (አፋብን) መቀላቀሉ ታወቀ።
የምኒልክ ዕዝ ባወጣው መረጃ መሠረት፣ ስሙ ያልተጠቀሰው ይህ የሰራዊቱ አባል ከፍተኛ ወታደራዊ ጠቀሜታ ያላቸውን አንድ ጥቁር ስናይፐር እና አንድ ጥቁር ክላሽንኮቭ መሣሪያ ደርቦ በመያዝ በሰላም እጁን ሰጥቷል።
የመከላከያ ሰራዊት አባሉ የተቀላቀለው በምኒልክ ዕዝ ስር የሚንቀሳቀሰውን ግዙፉን 303ኛ አሳምነው ኮር 16ኛ ነብሮ ተወርዋሪ ኮማንዶ ክፍለ ጦርን መሆኑ ተረጋግጧል። ክፍለ ጦሩ የተቀላቀለውን ወታደር በደማቅ ሁኔታ የተቀበለው ሲሆን፤ ሌሎች በመንግስት ሰራዊት ውስጥ የሚገኙ የአማራ ተወላጆችና የሰራዊት አባላትም የሕዝባቸውን የህልውና ትግል እንዲቀላቀሉ ጥሪ አቅርቧል።
የሰባት ለሰባ (7 ለ 70) ታሪካዊ ጀብዱ፦ ከጋዲሎ ሜዳ ተአምር እስከ ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የሰባት ለሰባ ክፍለ ጦር!
"ኸረ እናንተ ሰዎች ሆዳችሁ አይባባ፣
ይዋጋ የለም ወይ ሰባት እና ሰባ!"
ታሪካዊው ድባብ የተቀረጸው በታላቅ የሀገር ህልውና እና የልብ ትርታ ላይ ነው... ዘመኑ ነሐሴ 17 ቀን 1857 ዓ.ም። የሸዋ ጠቅላይ ግዛት፣ በኤፍራታና ግድም ወረዳ፣ በኤፌሶን ከተማ አቅራቢያ የምትገኘው ጋዲሎ ሜዳ በጸጥታ ተውጣለች። ነገር ግን ያ ጸጥታ ከባድ ማዕበል የተሸከመ ነበር። የወደፊቱ የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት፣ ብልሁና አርቆ አሳቢው እምዬ ምኒልክ ከባድና አስቸጋሪ ከነበረው የመቅደላ የዓፄ ቴዎድሮስ ግዞት አምልጠው፣ የዘር ማንነታቸውና የክብር መሰረታቸው ወደሆነችው ወደ መሀል ሸዋ በመገስገስ ላይ ነበሩ። ንጉሡ ወደ ሀገራቸው ሲመለሱ በታላቅ ተስፋና ናፍቆት ነበር። ነገር ግን በወቅቱ በአፄ ቴዎድሮስ ተሹመው ሸዋን ያስተዳድሩ የነበሩት እንደራሴው አቶ በዛбህ፣ የምኒልክን መምጣት ሲሰሙ ወንበራቸው ተናወጠ፤ ስልጣናቸው በብርቱ ጨለማ ተዋጠ። የምኒልክን ጉዞ በደም ለማደናቀፍና ዳግም ወደ ዙፋን እንዳይመለሱ ለማድረግ ቆረጡ። በመሆኑም በወቅቱ በዘመናዊ መሣሪያ በሚገባ የታጠቀ፣ የሰለጠነና ቁጥሩ ሰባ (70) የሚደርስ ከባድ የጦር ሰራዊት አስከትለው፣ መንገዱን ለመዝጋት ወደ ጋዲሎ ሜዳ አቀኑ።
አቶ በዛብህ ጦራቸውን ይዘው፣ ጋሻና ጦራቸውን እያብረቀረቁ ጋዲሎ ሜዳ ላይ ሲሰፈሩ የተመለከተች አንዲት ስሟ በታሪክ ያልተጠቀሰች የአካባቢው ጀግና እንስት፣ ነገሩ የደም መፋሰስ ሊሆን መሆኑን ተረዳች። መጪው ንጉሥ የእምዬ ምኒልክ ማንነትና የጌታቸው ልጅ መሆን ያሳሰባት ይህች ታሪክ የማይረሳት ሴት፣ ለአቶ በዛብህ ጦርና ለህዝቡ ትልቅ የቅኔ ማስጠንቀቂያና ወቀሳ የምታዘልል ድንቅ ስንኝ እንዲህ ስትል አወረደችው፦
"ማነው ብላችሁ ነው ጋሻው መወልወሉ፣
ማነው ብላችሁ ነው ጦራችሁ መሾሉ፤
ማነው ብላችሁ ነው ካራችሁ መሳሉ፣
የጌታችሁ ልጅ ነው ኧረ በስማም በሉ!"
ይህ ስንኝ በጋዲሎ ሜዳ ላይ አስተጋባ። የመጣው ሌላ ሳይሆን ህጋዊው የሀገር መሪና የጌታቸው ልጅ መሆኑን የምታስታውስ፣ ህሊናን የሚቀሰቅስ ጥሪ ነበረ። ከዛም ከእምዬ ምኒልክ ጋር ከስደት አብረው የመጡት፣ ህይወታቸውን ለንጉሡ የገበሩ ታማኝና ቆራጥ የግል ጠባቂዎች በቁጥር ሰባት (7) ብቻ ነበሩ! አቶ በዛብህ በቁጥር እጅግ መብለጣቸውንና ንጉሡ ምንም መከላከያ የሌላቸው መስሏቸው ታላቅ ንቀት ተሰማቸው። ነጋሪት እየጎሰሙ፣ ፈረስ እየጋለቡና እየፎከሩ በጋዲሎ ሜዳ ላይ ንጉሡን ከበቡ። በታላቅ ትዕቢትም እንዲህ አሉ።
"አንተን አድብኜህ አንተን አጭሼኅ ሥላሴ ያዉቃል፣
አይጥ ከድመት መች ተርፎ ያዉቃል።"
እነ አቶ በዛብህ 7ቱን ጀግኖች እንደ "አይጥ"፣ ራሳቸውን ደግሞ እንደ "ድመት" በመቁጠር ንጉሡን እጅ እንዲሰጡ አስጠነቀቁ። ነገር ግን እነዚያ ሰባት አንበሶች በፍርሃት ፊት አልሰጡም፤ ልባቸው አልደነገጠም! ለአንድ እውነትና ለሀገር ክብር የቆመ ሰው በቁጥር እንደማይበገግር ያውቁ ነበር።
ይህን የሁለቱን ወገን ፍጹም የማይመጣጠን የኃይል አሰላለፍ የተመለከተችው ያቺ የአካባቢው ሴት፣ በሰባቱ ጀግኖች ልባዊ ቆራጥነትና በሰባው ጦር ግርማ መሀል ሊፈጠር ያለውን ተአምር በዓይኗ ስታይ፦
"ኸረ እናንተ ሰዎች ሆዳችሁ አይባባ፣
ይዋጋ የለም ወይ ሰባት እና ሰባ!"
ስትል ታሪካዊውን ስንኝ ለዓለም አበሰረች። የጋዲሎ ሜዳ ተአምር እና የባንዳው ውድቀት ነሐሴ 17 ቀን የጋዲሎ ሜዳ መሬት በፈረሶች ኰቴና በሰይፍ ጩኸት ተናወጠች! ፍልሚያው ተጀመረ። ሰባቱ (7) የምኒልክ የቁርጥ ቀን ልጆች፣ ሰባውን (70) በደንብ የታጠቀ ጦር መሀል ለመሀል ሰንጥቀው በመግባት ማንም አይቶት የማያውቅ አስገራሚ የጦር ስልትና የጀግንነት ጥበብ ማሳየት ጀመሩ። የጦርነቱ ፍጻሜ ግን ታሪክን ለዘላለም የቀየረ ሆነ! በቁጥር አነሱ የተባሉት ሰባቱ ጀግኖች የሰባውን ጦር አምሳያ የሌለው አይቀጡ ቅጣት ቀጥተው፣ በትናንትናው ትዕቢተኛ ላይ ታላቅ ድልን ተቀዳጁ! እምዬ ምኒልክን በታላቅ ክብርና ወኔ አነገሡ። እንደራሴው አቶ በዛብህ የ7ቱን ጀግኖች ክንድ መቋቋም አቅቷቸው፣ በድንጋጤና በሽንፈት ወደ አፍቃራ ቆላ ኰበለሉ።
የበዛብህን ክህደትና አሳፋሪ ሽንፈት የሰሙ የአካባቢው ነዋሪዎችም በትዕቢተኛው መሪ ላይ እንዲህ እያሉ ገጠሙበት፦
"አንተም ጨካኝ ነበርክ ጨካኝ አዘዘብህ፣
እንደ ገና ዳቦ እሳት ነደደብህ!"
የታሪክ ቀጣይነት ዛሬ የአፋብኝ ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ "ሰባት ለሰባ" ክፍለ ጦር! ይህ መረጃ ከኤፍራታና ግድም ወረዳ በተለያዩ ጽሕፈት ቤት በኩራት ተመዝግቦ የሚገኝ የታሪክ አሻራ ነው። ድሉ ከተበሰረ በኋላ እምዬ ምኒልክ በበርግቢ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን አድረው ወደ ታሪካዊቷ መናገሻቸው አንኮበር ተጓዙ። ጋዲሎ ሜዳም ይህንን ታላቅ ተአምር በንጉሷና በ7ቱ አንበሶች ስም አክብራ ትኖራለች።
ታዲያ ይህ ከ160 ዓመታት በፊት በጋዲሎ ሜዳ ላይ የተጻፈው የወርቅ ታሪክ ዛሬም አልሞተም! ያ የ7ቱ ጀግኖች የጽናትና የአንበሳነት መንፈስ፣ ያ ጥቂት ሆኖ የብዙዎችን ግፍና ክንድ የመስበር ተአምራዊ ወኔ፣ ዛሬ በታሪካዊቷ የሸዋ ምድር ላይ በደመቅ ሁኔታ ህያው ሆኗል።የአሁኑ ዘመን የሀገርና የማንነት መከታ የሆኑት የሸዋ ጠቅላይ ግዛት የአሳምነው ዕዝ "ሰባት ለሰባ" ክፍለ ጦር ጀግኖች፣ ስያሜያቸውን ቀጥታ ከዚህ ታሪካዊ የጋዲሎ ሜዳ ድል በመነሳት ኩራታቸውና መለያቸው አድርገውታል።
ያኔ በታሪክ አጋጣሚ 7ቱ ጀግኖች የ70ውን ትዕቢተኛ ክንድ እንደሰበሩት ሁሉ፣ ዛሬም ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሰባት ለሰባ ክፍለ ጦር ያንን የትናንትናውን የጀግንነት አደራ እና የጽናት መንፈስ በመሰነቅ የማንነታቸውንና የሀገራቸውን ክብር ለማስጠበቅ በተጠንቀቅ የቆሙ የቁርጥ ቀን የነጻነት ፋኖዎች ናቸው። ምክንያቱም ታሪክ ይደገማል፤ ድልና ነጻነት ደግሞ የሚገኘው በቁጥር መብዛት ሳይሆን፣ እንደ ትናንቶቹ ሰባቱ ጀግኖች ሁሉ በልብ ቆራጥነትና በጽናት ነውና! በመጨረሻም ለአማራ ህዝብ ብላችሁ መስዋዕትነት የተቀበላችሁ የአማራ የቁርጥ ቀን ልጆች ነፍሳችሁ በአፀደ ገነት እንዲያስቀምጠው መልካምነቴን እየተመኘሁ ዛሬ ላይ ሰባት ለሰባን ክፍለ ጦሩን ብታዩ ብዬ ተመኘሁ #Dawit #Amhara
አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ይፋትና ጥሙጋ አውራጃ አንፆኪያ ገምዛ ወረዳ የኩሬ የጎደል ቀበሌ ህዝብ ጋር ሰፊ ህዝባዊ ውይይት ተደረገ።
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ መሐመድ ቢሆነኝ ኮር አስቴጎማ ተራራ ክፍለጦር ነፃ ካወጣቸው ቀበሌዎች አንዷ የሆነችው በኩሬ የጎደል ቀበሌ አገዛዙ ከሚገኝበት የወረዳ ከተማ በስድስት ኪሎ ሜትርእርቀት ላይ የምትገኝ ቀበሌ ሲሆን በቀን 05/11/2018 ዓ/ም በኩሬ የጎደል ቀበሌ አቧር ከተማ ከቀበሌውህዝብ ጋር ሰፊ ህዝባዊ ውይይት ተደረጓል።
ህዝቡ ሴት ወንድ ሳይል በነቂስ ወጥቶ ስብሰባውን የተሳተፈ ሲሆን መድረኩን የመሩት የአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ አበበ ሙላቱ እና ሌሎችም የዕዝ ፥የኮር እና የክፍለ ጦር አመራሮች ተገኝተዋል።
ለመወያያ የተመረጡ አጀንዳዎች የትግላችን ገፊ ምክንያቶች፥ ትግላችን ያለበት ደረጃ ፥ልማትና ትግል እድሁም ህዝባዊ አደረጃጀትን ማጠናከር የሚሉ ናቸው።
ለማህበረሰባቸን የትግሉ ገፊ ምክንያቶች የተዘነጉ ባይሆንም ብልፅግና በየጊዜዉ ከሚሰራው ደባ አንፃር ለማህበረሰቡ አፅንኦት እየሰጡ ንቃተ ህሊናውን ማሳደግ ተገቢ መሆኑ ታምኖበት ነው በአጀንዳነት የቀረበው በማለት የአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ አርበኛ አበበ ሙላቱ አስረድተዋል።
የትግሉ ገፊ ምክንያቶች እና ትግላችን የደረሰበትን የእድገት ደረጃ ለተሰብሳቢው ማህበረሰብ በስፋት ያብራሩት የአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ አርበኛ አበበ ሙላት በህዝቦች ላይ የተደቀነው የህልውና አደጋ አሳሳቢ ደረጃ ላይ በመድረሱ አማራጭ ወደለለው የትጥቅ ትግል ገብተናል ሲሉ ተናግረዋል።ቃል አቀባዩ አክለውም ይህ አሸባሪ የብልጽግና መንግስት ከስልጣን እስካልተወገደ ድረስ የአማራ ህዝቡ እደ ህዝብ ከምድረ ገፅ መጥፋቱ የማይቀር ነው በማለት የስርዓቱን አስከፊነት ምን ያክል ጨካኝ እደሆነ አስረድተዋል።
አርበኛ አበበ ሙላት እዳሉት የአማራ ህዝቡ በደረሰበት የህልውና አደጋ በተበታተነ መልኩ ትግል ቡንጀምርም የሴርኞችን ሴራ በጣጥሶ ዛሬ ላይ እውነተኛ አታጋይ የሆነውን ድርጀት የአማራን ቤት አፋብንን መመስረት ችለናል ብለዋል።
ይህ ድርጅት ብዙ ሙህራንንና የሰለጠነ ወታደራዊ አዛዦችን የያዘ ስለሆነ በአጭር ጊዜ ውስጥ በቀጠናው ተፅእኖ ፈጣሪ ድርጅት ለመሆን በቅቷል። ያሉት አርበኛ አበበ ሙላት አክለውም የድርጅት አሸባሪውንና ፀረ አማራ የሆነውን የብልፅግና መንግስት ከስልጣኑ እሲኪወገድ ድረስ አምርሮ ይታገላል ደግሞም ያስወግደዋል ብለዋል።
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የፍትህ መምሪያ ሃላፊ አርበኛ ፈለቀ ሙላቱ በትግል ላይ ሆነን ህዝባችን በፍትህ እጦት እዳይቸገር የፍትህ መዋቅሩን አስተካክለን የፍትህ አገልግሎት እየሰጠን እንገኛለን በማለት ገልፀዋል።
ስብሰባ የተሰበሰበውን ህዝብ በማዝናናት እና ስነልቦናውን በመገንባት ከፍ በማድረግ ከፍተኛውን ድርሻ ደግሞ የተወጣው የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ወታደራዊ ባህል ቡድን አባል አርበኛ ንዋይ በቀረርቶና በፉካሮ ስብሰባውን አድምቆታል።
በስብሰባው የታደሙት ሃሳብ ሰጪዎች በቀረበላቸው ሃሳቦች መደሰታቸውን ገልፀው ለቀጣይ ከድርጅታችን ከአፋብን ጎን ሆነው እደሚታገሉ አረጋግጠዋል። ይህ በእንዲህ አንዳለ አንዳንድ አሉብን የሚሏቸውንም ጥያቄዎች ለመድረክ መሪዎች ለማቅረብ ችለዋል።በቀረቡት ጥያቄዎች ላይከመድረክ ተገቢ የሆነ መልስ ከተሰጠ በኋላ የማጠቃለያ ንግግር በአፋብን ወታደራዊ ቃል አቀባይ አበበ ሙላት ተደርጎ የእለቱን ስብሰባ ተጠናቋል።
ክብር ለትግሉ ስማአታት
ህልውናችን በተባባረ ክንዳችን
አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት
ሃምሌ 6/2018 ዓ/ምግብ
