ar
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

الذهاب إلى القناة على Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

إظهار المزيد
2 904
المشتركون
+10524 ساعات
+3357 أيام
+33630 أيام
أرشيف المشاركات
#እንደወረደ አንድ #የባንክ ሰራተኛ #ጓደኛዬ ከአዲስ አበባ የላከልኝን ላካፍላችሁ ህዝቡ #ሞቱን የሚመኝለት ገዢ ያላት ብቸኛዋ አገር ኢትዮጵያ! ስማ Dave Amhara ጥንትማ... በአባቶቻችን ዘመን
#እንደወረደ አንድ #የባንክ ሰራተኛ #ጓደኛዬ ከአዲስ አበባ የላከልኝን ላካፍላችሁ ህዝቡ #ሞቱን የሚመኝለት ገዢ ያላት ብቸኛዋ አገር ኢትዮጵያ! ስማ Dave Amhara ጥንትማ... በአባቶቻችን ዘመን እጅ ወደ ሰማይ ተዘርግቶ፣ በደስታና በፍቅር፣ "ሺህ ዓመት ንገስልን" ብሎ ይጸልይ ነበር አገር። ​ዛሬ ግን... #Dave የእናቶች እምባ አልቆ፣ ጉንጫቸው ሲደርቅ፣ ህፃናት በራብ፣ ወጣቶች በግፍ ሲወድቁ፣ የቤት እህል አልቆ፣ ሰላም ህልም ሲሆን፣ የተራቆተው ማዕድ፣ የጨለመው ዘመን... ​ልባቸው በፍቅር ሳይሆን፣ በቁስል ተሞላ፣ ተስፋቸው ተነጥቆ፣ አጣን የሚከላ። ሆኖን አዲስ አበባ ​አሁንስ ጸሎታቸው... ሺህ ዓመት ንገስ" አይደለም... የደም እና የእምባ ጩኸት እንጂ፣ "ቃጦሏችን ይጥፋ፣ ለመቃብሩ ይድረስና ይገላግለን" የሚል... የመጨረሻ የብሶት እጅ! ​የተሰደደው፣ የተቀጨው እና ተስፋው የተነጠቀው ህዝብ የሚኖርበትን ጥልቅ የልብ ስቃይ እና የምሬቱን ጥግ አጎልቶ የሚያሳይ ሆኖል አዲስ አበባ ዛሬ #Dave

ህልውናን ለማስጠበቅ በሚደረገው ተጋድሎ የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ጦር አስደናቂ ድል ተቀናጀ!! ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም በአንኮበር ቀጠና የህዝብን ደህንነት ለማስከበርና የወገን ህልውናን ለማረጋገጥ በሚደረገው ተጋድሎ፣ የአፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ መሐመድ ቢሆነኝ ኮር እቴጌ ጣይቱ ክፍለጦር አስደናቂ ጀብድ መፈጸሙን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ኃላፊ አስታወቀ። መነሻውን ከአልዩ አምባ ከተማ በማድረግ በመኪና ተጭኖ ወደ ደብረ ብርሃን ያመራው የአድማ ብተና ኃይል ጎረቤላ ቀበሌ ሲደርስ፣ የእቴጌ ጣይቱ ክፍለጦር 2ኛ ሻለቃ አባላት ከጠምቄ በሚገኘው ስትራቴጂካዊ ስፍራ ላይ አስቀድመው በያዙት ደፈጣ በመያዝ ጠላትን በጨበጣ ውጊያ ጭምር ተዋግተው ከባድ ሰብአዊና ቁሳዊ ኪሳራ አድርሰውበታል ሲል ገለፀ። በተመሳሳይ ሰዓት ከአንኮበር የተነሳውን ተጨማሪ የጠላት ኃይል በዚሁ ጎረቤላ ቀበሌ ስበው በማስገባት፡ ልዩ ስሙ ቁንዲ በተባለ ቦታ፣ የክፍለጦሩ 3ኛ ሻለቃ አስደናቂ ጀብድ መፈፀማቸውን አክሎ ገልጿል። በዚህ በተቀናጀና ከፍተኛ ወታደራዊ ብቃት የተንጸባረቀበት አውደ ውጊያ ከጠላት በኩል የደረሰ ኪሳራ፦ 👉 10 አባላቱ የተደመሰሱ ፣ 👉 ከ8 በላይ ቁስለኞች ወታደራዊ የበላይነትን በመቆጣጠር፤ ጠላት እዳይወጣ በመቆጣጠር በጠላት ላይ ከፍተኛ ሰብዓዊ ኪሳራ ማድረሳቸውን አረጋግጧል። ከቦታው በደረሰው የውስጥ መረጃ፣ ጠላት በደረሰበት የበላይነት አሰላለፉን ለመቀየርና ለመጨመር እየተዘጋጀ መሆኑንም አክሎ አረጋግጧል። " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

26/12/2018 ዓ.ም የአማራ ህዝብ ጨፍጫፊ ግሪሳ ሰራዊት እስከ መኪናዉ በድንጋጤ ገደል ገባ አፋብን 305ኛ ጎቤ ኮር የኮሩ ልዩ ተወርዋሪ የብልፅግና ሰራዊት ላይ በደፈጣ ከፋተኛ ኪሳራ እንዲደርስበት አደረገ። በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ከጠገዴ ወረዳ ቅራቅር ከተማ ሰፍሮ የሚገኘዉ የሰሜን ምዕራብ ዕዝ 502ኛ ኮር 60ኛ ክፍለ ጦር 7ኛ ሬጅመንት በ5 ተሳቢ ተጭኖ ወደ ወፍ አርግፍ ሲንቀሳቀስ የነበረዉ የግለሰብ ወንበር አስጠባቂ አራዊት ሰራዊት ላይ በኮሩ ልዩ ተወርዋሪ ካዛ ቀበሌ ኮኪያ ከሚባል ቦታ ላይ በዓልሞ ተኳሾች በተወሰደበት እርምጃ አንድ አስር ጎማ የጫነ መኪና በድንጋጤ ዘሎ ወደ ገደል በመግባቱ የጫናቸዉ ሙሉ በሙሉ ሙትና ቁስል ሁኗል። ነሐሴ 26/12/2018 ዓ.ም ከጧቱ 11 ሰዓት ላይ በፍኖዎች ሰርጎ በመግባትና በመመሳሰል በ10ጎማ መኪና የተጫኑ ገዳይ ቡድን 110 የሚሆኑ ቁጥራቸዉ በተወሰደ እርምጃ # ወዲያወኑ እስከዉዲያኛዉ የተሸኙ 65 # ከባድና ቀላል ቁስለኛ 50 የሚሆኑ ማክሰኞ ገቢያ ሆስፒታል እና ቅራቅር ሆስፒታል የገቡ ሲሆን አሁን በደረሰዉ መረጃ የ7ኛ ሬጅመንት አዛዥን መቶ አለቃ እንድሪስን ጨምሮ 40 የሚሆኑት ከሆስፒታሉ ዉስጥ እገዛ ቢደረግላቸዉም ሳይተርፉ ቀርተዋል በብልፅግና መንደር ዉስጥም የፋኖዎች ያልተጠበቀ ምት ድንጋጤ ፈጥሯል። በአጠቃላይ 305ኛ ጎቤ ኮር እንዲህ አይነት እርምጃዎችን ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ለሰራዊቱ አቅጣጫ አስቀምጠዋል። ህልዉናችን በተባበረ ክንዳችን አርበኛ ባንዴራዉ ግርማይ የ305ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ነሐሴ 26/12/2018 ዓ.ም ከትግል ሜዳ

አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ 208ኛ ራስ አሞራው ውብነህ ኮር  ድብ ጠለምት ተከዜ ክፍለ ጦር በጠላት ኃይል ላይ ከፍተኛ ጀብድ ተቀዳጅቷል። ነሐሴ 26 / 2018 ዓ.ም የጠላት ኃይል ለተከታታይ 4 ቀናት መነሻውን ከደባርቅ እና ከማይጠብሪ  በማድረግ ወደ ዛሪማ ስትራቴጂካዊ አቅጣጫ እንቅስቃሴ ያደረገ ሲሆን፣ የክፍለ ጦሩ 1ኛ እና 2ኛ ሬጅመንቶች በቅንጅት በወሰዱት የደፈጣ እና  ማጥቃት እርምጃ ልዩ ስሟ «ፍድቃ» በተባለች ቦታ ላይ ጠላትን በጽኑ በመደምሰስ ከፍተኛ የሰው እና የቁሳቁስ ኪሳራ አድርሰውበታል።​ በዚሁ የአውደ ውጊያ ቀጣና ላይ የነበረውን ወታደራዊ የበላይነት ለማረጋገጥ የአመራሩ እና የውጊያ ውህደቱ ቁልፍ ሚና ተጫውቷል። እድሜ ጠገቡ አርበኛ ሻለቃ ሰፈር መለሰ በተሳተፈበት በዚህ አውደ ውጊያ ፣አርበኛ ይርጋ ክቡሬ እና አርበኛ ጉርባ ይበይን ግንባር ቀደም በመሆን ከፍተኛ ጀብድ ፈጽመዋል። በተመሳሳይ መልኩ አርበኛ አይቸው መብራቱ (ሸሪፎ) እና አርበኛ አራገው ዳኘው የሰራዊቱን የማዋጋትና የውጊያ ስልት የመምራት አቅማቸውን በተግባር በማሳየት፣ ከሁለት አቅጣጫ የተንቀሳቀሰውን የጠላት ኃይል አሰላለፍ በመበተን እና ከፍተኛ ወታደራዊ ጠቀሜታ ያላቸውን ስትራቴጂካዊ ቦታዎች በመቆጣጠር የጠላትን ሰራዊት ሙሉ በሙሉ ከጥቅም ውጭ አድርገውታል። በጠላት ወታደራዊ መዋቅር ላይ የደረሰው ኪሳራ ሰባዊ ቁሳዊ ኪሳራ:- ➛15 ክላሽኮቭ ጠመንጃዎች ተማርከዋል፤ ➛1150 የብሬን እና የክላሽኮቭ ተተኳሾች ተማርከዋል፤​➛4 የመከላከያ (መትረጊስ) እና የአድማ ብተና አባላት  ተማርከዋል፤​ ➛ከ60 በላይ ከከባድ እስከ ቀላል ቁስለኛ፤ ➛20 የጠላት አባላት ሙሉ በሙሉ የተደመሰሰ( ከነዚህም ሁለቱ ቀደም ሲል በፋኖ ስም በቀጣናው ላይ ዘረፋ እና ግድያ ሲፈጽሙ ቆይተው እርምጃ ሊወሰድባቸው ሲባል ወደ ጠላት ሰፈር በመቀላቀል የመንገድ መሪነት ሚና ሲጫወቱ የነበሩ ናቸው።) ➛7 የጠላት አባላት ወደ ዛሪማ ወንዝ ገብተው በስመጥ ህይወታቸው ያለፈ፤ ➛1 ብሬን (መትረጊስ) እና 8 AK-47 ክላሽኮቭ ጠመንጃዎች ይዘው የጠላት አባላት ከዕዝ ሰንሰለት ተበታትነው ጠፍተዋል፤ ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!​ አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

የ16ኛ ኮር የሠራዊት ማዋሃድ፣ ግምገማና ተሃድሶ ስልጠና በስኬት ተጠናቀቀ! የአፋብን የምኒልክ 1ኛ ዕዝ (የቀድሞው ደጋው መብረቅ የአሁኑ 16ኛ ኮር፣ ከሻለቃ እስከ ኮር ለሚገኙ አመራሮች ሲሰጥ የቆየውን ተከታታይ ቀናት የፈጀ የተሃድሶ፣ የግምገማና የስልጠና መርሃ-ግብር በስኬት አጠናቋል። በተመሳሳይ ከድርጅቱ በወረደው ወታደራዊ መመሪያ መሰረት የሠራዊት ማዋሃድ እና የመልሶ ማደራጀት ስራዎች በትክክል ተከናውነዋል። በዚሁ የመርሃ-ግብሩ ማጠቃለያ ላይ የዕዙ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተው፣ አሁናዊና መጻኢ የትግል አቅጣጫዎችን አስመልከተው ሰፊ ማብራሪያና መመሪያ ሰጥተዋል። በስልጠናው ወቅት የአማራ ህዝብ የተደቀነበትን የመጥፋት አደጋ መክቶ፣ የማድረግ አቅምን በማጎልበት ወደ ማጥቃት የተሸጋገረበት የሶስት ዓመታት የትግል ጉዞ፣ አሁናዊ ቁመና እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶች በጥልቀት ተገምግመዋል። ይሄው የመሪዎች ስልጠና የትግሉን ጉዞ ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋገረ ጉልህ እምርታ የፈጠረ ሲሆን፣ ለቀጣዩ እርምጃ መሰራትና መታረም በሚገባቸው ጉዳዮች ላይ እውቀታዊና ጥበባዊ የመፍትሔ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል። ከዚህ በተጨማሪ ባሳለፍናቸው የትግል ዓመታት ትግሉ የደረሰበት የከፍታ ደረጃ፦ በዲፕሎማሲው መስክ የፈጠረው እምቅ አቅም፣ በፖለቲካው ረገድ ያሳየው ተራማጅና ተሻጋሪ እይታ፣ እንዲሁም በወታደራዊ ክንፉ የተጎናጸፈው አይደፈሬነትና ከፍተኛ የማድረግ አቅም በስፋት ተዳስሷል። በትግሉ ሂደት አመራሩ በላቀና ቀና በሆነ ሙሉ ወንድማማችነት የሚመራና የሚተሳሰር በመሆኑ፣ ፈተናዎችንና ተግዳሮቶችን በማሸነፍ አዎንታዊ ውጤቶችን ማብዛት እንደሚገባ ግንዛቤ ተወስዷል። ሁሉም አመራር ለላቀ መሪነት እራሱን እንዲያዘጋጅና ሀገር ለመረከብ ዝግጁ እንዲሆን ማሳሰቢያ የተሰጠ ሲሆን፤ ለዚህ ከፍታ ደግሞ ከወንዜነት በተሻገረ አስተሳሰብ በመራመድ፣ የጊዜውንና የዘመኑን ጥያቄ የሚዋጅ ሆኖ መገኘት የአሸናፊነት መንገድ መሆኑ ተገልጿል ሲል የ16ኛ ኮር ቃል አቀባይ መረጃዉን አድርሷል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ 1ኛ ዕዝ የህዝብ ግንኙነት መምሪያ! ነሐሴ 26 ቀን 2018 ዓ.ም

የዓላማ ጽናትና የጀግንነት ተምሳሌቶች ፦ አርበኛ አማረ ታዘዘ አርበኛ ሰይድ ደምስ እንዲሁም አርበኛ ሃብታሙ እና ጓዶቿቸው በግዳጅ ቀጠና በሔዱበት ውብና ማራኪው የአማራ መሬት የተፈጥሮ ፀጋ ጋር!! ​
+7
የዓላማ ጽናትና የጀግንነት ተምሳሌቶች ፦ አርበኛ አማረ ታዘዘ አርበኛ ሰይድ ደምስ እንዲሁም አርበኛ ሃብታሙ እና ጓዶቿቸው በግዳጅ ቀጠና በሔዱበት ውብና ማራኪው የአማራ መሬት የተፈጥሮ ፀጋ ጋር!! ​ ​ጽናት፦ ለማንኛውም ፈተናና ማስፈራሪያ የማይበገሩ፣ ለህዝቡ ነፃነት ቅድሚያ የሰጡ የጽኑ አቋም ባለቤት የሆኑ። ​ታሪካዊቷ የሸዋ ምድር እንዲህ ያሉ ለዓላማቸው የታመኑ ጀግኖችን በማፍራት የጸናች ናት። በዚህም ፈጣሪ አርበኛቹን ይጠብቅልን! ​የሸዋ መሬት ፍሬ፣ የጀግኖች ተካፋይ፣ አማረ ታዘዘ — የትግሉ ፊት አውራሪና መሪ! በዕውቀት የታነጸ፣ በስልት የበሰለ፣ሴራን አክሻፊ ነው፣ አቋሙ ያልላላ። ​የህዝብና ሰራዊት አስተሳሳሪ አምድ፣ በጽናት ይጓዛል በነፃነቱ መንገድ። የአማራ ህዝብ አለኝታና ጋሻ፣ ለህዝቡ መቆሙ ነው የዓላማው መድረሻ! ​ፈጣሪ ይጠብቅህ አርበኛው በርታ፣ አንተና ጓዶቹህ ናቸው የአማራ የህዝብ አለኝታ! ፈጣሪ ይጠብቃችሁ ወንድሞቼ #Dave #Amhara

ሰበር የምሽት ዜና‼️ ባንዳ ተዋበ ጌትነት በቅፅል ስሙ የኔውበት የአማራን ህዝብ በመክዳት ከአገዛዙ ተልዕኮ ተቀብሎ ከ64ኛ ክ/ጦር በማፈንገጥ የፋኖን ስም ለማጥፋት በዝረፊያ፣ በእገታ በመሳሰሉት ወን
+1
ሰበር የምሽት ዜና‼️ ባንዳ ተዋበ ጌትነት በቅፅል ስሙ የኔውበት የአማራን ህዝብ በመክዳት ከአገዛዙ ተልዕኮ ተቀብሎ ከ64ኛ ክ/ጦር በማፈንገጥ የፋኖን ስም ለማጥፋት በዝረፊያ፣ በእገታ በመሳሰሉት ወንጀሎች ተሰማርቶ የነበረ ቢሆንም ባንዳው ከአንዴ ሁለቴ በሰራቸው ወንጀሎች ታስሮ በ64ኛ ክ/ጦር  የእርምት እርምጃ እንዲወስድ ተደርጓል። በመሆኑም ባንዳ ተዋበ መጀመርያ ከሰራቸው ወንጀሎች ባለመማር ከክ/ጦር በድጋሜ በማፈንገጥ በእነማይ ወረዳና ቢቸና ከተማ የሚገኙ ነዋሪዎች ላይ ከፍተኛ ዝርፊያና እገታ በመፈፀም ቢቸና ከተማ የሚገኘው የብልፅግና አገዛዝ ግንቦት 23/2018 ዓ.ም እጅ የሰጠ ቢሆንም ነሀሴ 25/2018 ዓ.ም በቢቸና ከተማ 03 ቀበሌ ከምሽቱ 3:00 ሰዓት በመኗሪያ ቤቱ ላይ የአፋብን ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ 201ኛ ኮር አይበገሬው 64ኛ ክ/ጦር አስርጎ በአስገባቸው እስከ ወዳኘው ተሸኝቷል። ከፋኖ በመክዳት ወደ ዘር ፈጁ የብልፅግና አገዛዝ የገባ የትኛው ባንዳ ከፋኖ እንደማያመልጥ እናሳውቃለን። አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!!              ነሀሴ 25/2018 ዓ.ም አፋብን ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት

የጉባኤ ማጠቃለያ እና የአቋም መግለጫ፡ "የልሂቃን ሚና በአማራ ህልውና" August 29 እና 30, 2026 በዙም (Zoom) ሲካሄድ የቆየውና በአማራ ህዝብ የህልውና ትግል ላይ በጥልቀት የመከረው ታላቁ የውይይት ጉባኤ በስኬት ተጠናቋል። የአማራ ህዝብ ዛሬ ላይ እጅግ ፈታኝ፣ ውስብስብ እና አደገኛ በሆነ የታሪክ ምዕራፍ ላይ ይገኛል። ህዝባችን በየአቅጣጫው የተከፈተበትን የህልውና አደጋ ለመመከት ወደር የለሽ ተጋድሎ እያደረገ ቢሆንም፤ መጠነ ሰፊ ማፈናቀል፣ ግድያ፣ የኢኮኖሚ ውድመት፣ እና ሁለንተናዊ የመዋቅር ማግለል የዕለት ተዕለት እውነታው ሆኗል። ይህ የተደራጀና ዘርፈ ብዙ ጥቃት ህዝባችንን በከፍተኛ የህልውና ስጋት ውስጥ የከተተው ሲሆን፣ የተቀናጀና አገር አቀፍ መፍትሄ ባለመገኘቱ ምክንያት ውድ የሆነ የሰው ህይወትና የንብረት ዋጋ እየከፈለ ይገኛል። ከዚህ መሪርና አሳሳቢ ነባራዊ ሁኔታ አኳያ፣ እኛ የአማራ ምሁራን እና ልሂቃን ቆም ብለን ራሳችንን ስንገመግም፣ ለህዝባችን የሚመጥንና በታሪክም የሚጠበቅብንን ያህል የበኩላችንን የአመራርና የተግባር ሚና እንዳልተወጣን በግልጽ እናምናለን። በህዝባችን ላይ እየደረሰ ያለውን መከራ ለማስቀረትም ሆነ የህልውና ትግሉን በአስተማማኝ መሰረት ላይ ለማቆም፤ በዕውቀት፣ በስትራቴጂ፣ በዲፕሎማሲ፣ እና ህዝብን በማስተባበር ረገድ የነበረን ተሳትፎ ውስን፣ የተበታተነ እና ወቅቱ የሚጠይቀውን ልክ ያላሟላ እንደነበር ጉባኤው በጽኑ ገምግሟል። ሆኖም ይህ ጉባኤ የታሪክ ማዕዘን መታጠፊያ ነው። ከእንግዲህ ወዲህ የአማራ ምሁራን ከዳር ቆሞ የመመልከትም ሆነ ተበታትኖ የመጓዝ ምዕራፍ በይፋ አብቅቷል። የህዝባችንን ህልውና ለማስጠበቅ፣ ትግሉን በዕውቀት ለመምራት፣ ጠንካራ አንድነት ለመፍጠር፣ እና ለችግሮቹ ሳይንሳዊና ተግባራዊ መፍትሄዎችን ለማምጣት ከመቼውም ጊዜ በላይ በቁርጠኝነት ተነስተናል። አቅማችንን፣ እውቀታችንን እና ጊዜያችንን አሟጦ በመጠቀም ከህዝባችን ጎን በጽናት ቆመን ኃላፊነታችንን ለመወጣት ቃል ገብተናል። በዚህ የምስረታ ጉባኤና በቅድመ ጉባኤ በአጠቃላይ ለአንድ ወር የአማራ ልሂቃን ባደረግነው ጥልቅ ውይይት መሰረት ትግሉን ወደ ሚገባው የድል ምዕራፍ ለማሸጋገር ወስነናል፣ ይህንን ቁርጠኝነት ወደ ተግባር ለመቀየር አበይት ኃላፊነቶች የተከፋፈሉ ሲሆን በሚከተሉት ስትራቴጂካዊ ዘርፎች ዙሪያ ጠንካራ ስራዎች እንደሚሰሩ ተገልጿል፦ ♦️የህዝባዊ ዲፕሎማሲና አለም አቀፍ ግንኙነት፡ ትግሉን ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ በግልጽ የማስረዳት ስራ። የአለም አቀፍ ህግና የሰብአዊ መብት፡ በህዝባችን ላይ የሚደርሱ ግፎችን በህግ ማዕቀፍ የመከታተልና ፍትህ የመፈለግ ዘርፍ። ♦️የሽግግር ወቅት እቅድና የፍትህ ስርዓት፡ ለቀጣይ የፖለቲካና የፍትህ መዋቅር አስቀድሞ መዘጋጀት። የታሪክ፣ ባህልና ማንነት ጥበቃ፡ የህዝባችንን እሴቶች የመንከባከብና የማስቀጠል ስራ። ♦️የኮሙኒኬሽን፣ ሚዲያና የትርክት ግንባታ፡ የተበታተኑ ድምጾችን በማሰባሰብ ጠንካራ ትርክት የመገንባት ዘርፍ። የትብብር፣ ጥምረትና አጋርነት፡ ከሌሎች ሀይሎች ጋር የሚኖረውን ጤናማ ግንኙነት ማስተዳደር። ♦️የህልውና አቅም ግንባታና መረጃ ትንተና ዘርፍ፡ የህዝቡን የመቋቋም አቅም ማጎልበትና ትክክለኛ የመረጃ ፍሰትን ማረጋገጥ። ♦️የፖሊሲ ጥናትና ምርምር ዘርፍ፡ ዘላቂ የፖለቲካና ኢኮኖሚ ፖሊሲዎችን መንደፍ። ♦️የቴክኖሎጂ እና የሳይበር ደህንነት፡ የመረጃ ደህንነትን መጠበቅና በቴክኖሎጂ መታገዝ። ♦️ የዓለም አቀፍ ህግና የሰብአዊ መብቶች ተሟጋችነት ዘርፍ ♦️ የኢኮኖሚ፣ ፋይናንስና የሃብት ማሰባሰብ ዘርፍ በሚል ተቋቁሟል። "አስተዋይና ብሩህ ህዝብ የማይጠፋ ታሪክ አለው፤ የወደፊት ዕጣ ፈንታውንም እራሱ ይገነባል።" ይህን ታላቅ እውነት ሰንቀን ለጋራ ህልውናችን በአንድነት የምንቆምበት ወሳኝ ሰዓት አሁን ነው። የተጋረጡብንን የህልውና ስጋቶች በተቀናጀ መንገድ ለመመከትና ለህዝባችን የተሻለ ነገን ለመፍጠር፣ መላው ህዝባችን በነዚህ በተዋቀሩት ዘርፎች ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የድርሻውን አዎንታዊ አሻራ እንዲያሳርፍ በአክብሮት ጥሪያችንን እናቀርባለን። እንተባበር! እንወያይ! እንገንባ! የዓለም አቀፍ የአማራ ሊህቃን መማክርት ምስረታ ጉባኤ! ነሐሴ 24 ቀን 2018 ዓ.ም

ከአፋብን ሊቀ መንበር አርበኛ ዘመነ ካሴ የተላለፈ የዕለቱ መልዕክት❗️🦅 ይድረስ ለመላው ኢትዮዺያዊያን።

ቀን ፦24/12/2018 ዓም ለአማራ ህልውና በድጋሜ የወጣ የስልጠና ጥሪ ማስታወቂያ የአማራ ህዝብ እየደረሰበት ያለውን የህልውና አደጋ ለመቀልበስ የአማራ ፋኖ ወደ ትጥቅ ትግል ከገባ 37 ወራትን ያስቆጠረ መሆኑ ይታወቃል። ======================= ስለሆነም በሶስት አመት በነበረን የትግል ቆይታችን የአብይ አህመድን መንግስት ፍርስርሱን በማውጣት ከነፍስ ወከፍ መሳሪያ እስከ ቡድን መሳሪያ እስከ አፍጫችን መታጠቃችመታጠቃችኔን የአደባባይ ሀቅ መሆኑ ወገን ቀርቶ ጥላት ይመሰክራል :: በመሆኑም ይህንን የፈራረሰ ስርዓት ግብዓተ መሬት በመፈፀም ህዝባዊ መንግስት በማቋቋም ሀገራችንን ኢትዮጵያን የቀደመ ክብሯን እና ገናነቷን አስጠብቆ ለማስቀጠል ከትግላችን ጎንለጎን ማሰልጠቅንና ማስቲጠቅ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ምክንያት የአፋብን፤ ቴዎድሮስ 2ኛዕዝ ፤206ኛ ኮር 14ኛ ክፍለ ጦር ፤ አዲስ ምልምል ሰልጣኞችን ተቀብሎ ለማሰልጠን ዝግጁቱን አጠናቆ እናንተን በመጠበቅ ላይ ይገኛል። የመመልመያ መሰፈርት፦ 👉 በአማራ ብሔርተኛነት የሚያምን 👉🏼የታደሰ የቀበሌ መታወቂያ ማቅረብ የሚችል: 👉 ዕድሜ ፦ ከ 18 ዓመት - 28 ዓመት 👉 የትምህርት ደረጃ ፦ ከ 5ኛ ክፍል በላይ 👉 ፆታ :- አይለይም 👉 ምንም አይነት የጤና ችግር የሌለበት ፤ 👉 ምንም አይነት ወንጀል የሌለበት በማህበረሰቡ ዘንድ በስነምግባሩ የተመሰከረለት፤ 👉 ከማንኛውም ደባል ሱስ ነፃ የሆነ 👉 ስልጠና ካጠናቀቀ በኋላ ለድርጅቱ ታማኝ የሚሆን በሚመደብበት የትኛውም ቦታ ተንቀሳቅሶ ግዳጅ ለመወጣት ዝግጁ የሆነ፤ 👉 ከጠላት ጋር ምንም አይነት ግንኙነት የሌለው : ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ መስከረም05/01/ 2019 ዓ.ም ድረስ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት ደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር /ንጉስ ተክለሃይማኖት ) ጊዜያዊ መንግስት አሰተዳደር ጎዛምን ወረዳ ጎዛምን ህ/መንግስት አስተዳድር ዘወትር በስራ ስዓት በአካል በመቅረብ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን ##ለበለጠ መረጃ:-በ14ኛ ክ/ጦር በ24ኛ ክ/ጦርበ34ኛ ክ/ጦር እንዲሁም በ206ኛ ኮር የህዝብ ግንኙነት መምሪያ የማህበራዊ ሚዲያ ድህረገጾች በመከታተል በውስጥ መስመር መረጃወችን ማግኘት ትችላላችሁ:: #ማሳሰቢያ :- ያለን ቦታ ውስን ስለሆነ በፍጥነት በመመዝገብ ህልውናችሁን አረጋግጡ:: 👉🏼ከላይ የተዘረዘሩት መስፈርቶች ማሟላት የማይችል የማናስተናግደው መሆኑንን በድጋሜ እናሳስባለን! አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳስብ!! አዲስ ተስፋ!!! 👉ህልውናችንን በተባበረኸሾ ክንዳችን💪💪💪 የአፋብን:ቴዎድሮስ ዕዝ/206ኛ ኮር/የ14ኛ/ክፍለጦር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

የንድፈ-ሐሳብና የተግባር ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ 322 የምልምል ኮማንዶ አባላት በድምቀት ተመረቁ ▬▬▬▬▬▬▬❁✿❁▬▬▬▬▬▬ ነሐሴ  25/2018 ዓ.ም ለተከታታይ አራት ወራት ያህል ሲከታተሉት የቆዩትን ጠንካራ የኮማንዶ ሥልጠና በስኬት ያጠናቀቁ ምልምል ሠልጣኞች ዛሬ በተካሄደ ደማቅ ሥነ-ሥርዓት ተመረቁ። በቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ 102ኛ ኮር 33ኛ ክፍለ-ጦር አዘጋጅነት ሲሰጥ የቆየውንና "አንድነት ኮርስ" የተሰኘውን የኮማንዶ ሥልጠና በስኬት ያጠናቀቁት እነዚህ 322 አዳዲስ ተመራቂዎች፣ በቆይታቸው በሁለት ዋና ዋና ዘርፎች የተቃኙ ሥልጠናዎችን ወስደዋል። #የንድፈ-ሐሳብ ሥልጠና፦ በውጊያ ስልት፣ በውጊያ መሪነት፣ በወታደራዊ ሳይንስ፣ በግብረ-ገብነት፣ በስነ-ልቦና ዝግጅትና በታማኝነት መርኆዎች ላይ ያተኮሩ ትምህርቶች፤ #የተግባር (Practical) ሥልጠና፦ የአካል ብቃት ማጎልበት፣ የነፍስ ወከፍና የቡድን መሣሪያዎች አጠቃቀም፣ ድንገተኛ አደጋዎችን የመቋቋም፣ የደፈጣና የፀረ-ደፈጣ ውጊያዎች እንዲሁም አስቸጋሪ የመሬት አቀማመጦችን የማሸነፍ ተግባራዊ ክህሎቶች። በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ላይ የተገኙ የዕዙ፣ የኮሩ እና የክፍለ-ጦሩ ከፍተኛ አመራሮች እንደገለጹት፤ የ"አንድነት ኮርስ" ተመራቂዎች በዐማራ የሕልውና ትግል ግቡን ያሳካ ዘንድ ከፍተኛ ድርሻ ይኖራቸዋል። ሠልጣኞቹ በስልጠና ወቅት ያሳዩትን ከፍተኛ ጽናት፣ ዲሲፕሊንና የወንድማማችነት መንፈስ በግዳጅ ቀጠናዎች ላይም በተግባር ማሳየት እንዳለባቸው በቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ ወታደራዊ አዛዥ ሻለቃ የኔዓለም ዘለቀ ታዟል። በዕለቱ በተካሄደው የምረቃ ፕሮግራም ላይ ተመራቂዎቹ በወታደራዊ የሰውነት ብቃት፣ በሰው ሠራሽና በተፈጥሮ እንቅፋቶች አሻግሮ የመዋጋት፣ እንዲሁም የጠበበ ውጊያ ማሳያዎችን ለታዳሚው አቅርበዋል። በሥልጠና ቆይታቸው ከፍተኛ ለውጥ ላሳዩ ተመራቂዎች፣ ለአሠልጣኞች እና ለሥልጠናው መጠናቀቅ አስተዋጽኦ ለነበራቸው አካላት የገንዘብና የዕውቅና የምሥክር ወረቀት  ተበርክቶላቸዋል። እነዚህ 322 አዳዲስ የኮማንዶ አባላት የተሰጣቸውን የሕዝብ ግዳጅ ለማከናወን ሙሉ ዝግጁነታቸውን በማረጋገጥ ወደተለያዩ የግዳጅ ቀጠናዎች ይሰማራሉ ሲል ክፍለ-ጦሩ አሳውቋል። የዐፋብን ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ ወታደራዊ አዛዥ ሻለቃ የኔዓለም ዘለቀ፣ ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ ሥልጠና መምሪያ ሓላፊ ሻምበል ጌትነት ንጉሤ፣ የቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ ልዩ ዘመቻ ሓላፊ ፻ አለቃ ማርቆስ አሞኘ፣ የቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ ትምህርት እና ሥልጠና ምክትል ሓላፊ አርበኛ ዘውዳለም አዱኛ፣ በየደረጃው የሚገኙ የኮር እና የክፍለ-ጦር አመራሮች፣ እንዲሁም የተመራቂ ኮማንዶ ቤተሰቦችና የትግሉ ደጋፊዎች የዚህ ታላቅ በዓል ተሳታፊዎች ነበሩ።