ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
الذهاب إلى القناة على Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
إظهار المزيد2 951
المشتركون
+1424 ساعات
+247 أيام
+38330 أيام
أرشيف المشاركات
+6
የነፃነት ጉዞን የማይበግረው የአማራ ፋኖ ፅናት እና የከሃዲያን ውድቀት!
ከትናንት እስከ ዛሬ፦ የውስጥ ባንዳዎችና "የሚዲያ ዳይፐሮች" ሴራ! ትናንት መቀመጫቸውን በአረብና በግብፅ አድርገው፣ ለአይን የሚያሳሱትን የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ እንቁዎችን ከጀሌ እስከ ከፍተኛ አመራር ሲያጠለሹ የነበሩ ድኩማን ዛሬም ከታሪክ አልተማሩም።
ከጠላት ወገን አይሏቸው ወይ ከወገን፣ በስም ብቻ አማራ መስለው፣ በርገር በበሉ አፋቸው ጀግኖችን በአደባባይ ስም ሲያጠፉና በፎክ (Fake) አካውንት በስተጀርባ ተሸሽገው ስድብ ሲያዘንቡ የነበሩት ፣ ዛሬም ሌላ የክህደት ድራማ ይዘው ብቅ ብለዋል።
አሁን ደግሞ በጀግኖቹ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ምዕራብ አማራ ቴዎድሮስ ዕዝ መካከል የመከፋፈል መርዝ ለመርጨት አፋቸውን ይከፍታሉ። ይባስ ብሎም፣ የአፋብን አንበሳ፣ እሳታማውንና ኮስታራውን የራስ አርበኛ ዘመነ ካሴን ፎቶ በተደጋጋሚ ሲለጥፉ ይታያሉ። ይህ ለአማራ ሕዝብ ተቆርቋሪ ለመምሰል፣ ለመወደድና የራሳቸውን የሐሰት ትርክት ለመገንባት የሚጠቀሙበት የፖለቲካ ቁማር መሆኑ አያጠራጥርም!
እናንተ የሚዲያ ቅጥረኞች ሳይቀድሙን አውቀንባችኋል፣ የምታሴሩትንም ጠንቅቀን እናውቃለን!" አማራን በመከፋፈልና በመበተን የጀመራችሁት ትግል አሁን ዝግ ነው ምክንያቱም የተጀመረውን የአማራ ልጅ የመኖርና የነፃነት ትግል አንድ እርምጃ እንኳ ወደ ኋላ ማስቀረት ከቶ አትችሉም።
በቅርቡ የከፈታችሁትን የሐሰት ሚዲያ ይዛችሁ በቁጭትና በዋይታ የምታለቅሱበት ቀን ይመጣል።
ምክንያቱም... በአማራ ጀግኖች ክንድ፣ በቅርቡ መላውን ዓለም ጉድ የሚያሰኙ ታላላቅና ታሪካዊ ድሎች በአደባባይ ይበሰራሉ!
የአማራ ሕዝብ ትግል በድል ይጠናቀቃል!
+6
የነፃነት ጉዞን የማይበግረው የአማራ ፋኖ ፅናት እና የከሃዲያን ውድቀት!
ከትናንት እስከ ዛሬ፦ የውስጥ ባንዳዎችና "የሚዲያ ዳይፐሮች" ሴራ!
ትናንት መቀመጫቸውን በአረብና በግብፅ አድርገው፣ ለአይን የሚያሳሱትን የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ እንቁዎችን—ከጀሌ እስከ ከፍተኛ አመራር—ሲያጠለሹ የነበሩ ድኩማን ዛሬም ከታሪክ አልተማሩም። ከጠላት ወገን ሳይመደቡ፣ በስም ብቻ አማራ መስለው፣ በርገር በበሉ አፋቸው ጀግኖችን በአደባባይ ስም ሲያጠፉና በፎክ (Fake) አካውንት በስተጀርባ ተሸሽገው ስድብ ሲያዘንቡ የነበሩት እነዚህ የቁም ስደተኞች፣ ዛሬም ሌላ የክህደት ድራማ ይዘው ብቅ ብለዋል።
አሁን ደግሞ በጀግኖቹ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ምዕራብ አማራ ቴዎድሮስ ዕዝ መካከል የመከፋፈል መርዝ ለመርጨት አፋቸውን ይከፍታሉ። ይባስ ብሎም፣ ያንን የአፋፉን አንበሳ፣ እሳታማውንና ኮስታራውን የራስ አርበኛ ዘመነ ካሴን ፎቶ በተደጋጋሚ ሲለጥፉ ይታያሉ። ይህ ለአማራ ሕዝብ ተቆርቋሪ ለመምሰል፣ ለመወደድና የራሳቸውን የሐሰት ትርክት ለመገንባት የሚጠቀሙበት የፖለቲካ ቁማር መሆኑ አያጠራጥርም!
📌 ለእነዚህ የሚዲያ ቅጥረኞች የተሰጠ ጥብቅ ማስጠንቀቂያ፦
"ሳይቀድሙን አውቀንባችኋል፣ የምታሴሩትንም ጠንቅቀን እናውቃለን!" አማራን በመከፋፈልና በመበተን የተጀመረውን የአማራ ልጅ የመኖርና የነፃነት ትግል አንድ እርምጃ እንኳ ወደ ኋላ ማስቀረት ከቶ አትችሉም። በቅርቡ የከፈታችሁትን የሐሰት ሚዲያ ይዛችሁ በቁጭትና በዋይታ የምታለቅሱበት ቀን ይመጣል።
ምክንያቱም... በአማራ ጀግኖች ክንድ፣ በቅርቡ መላውን ዓለም ጉድ የሚያሰኙ ታላላቅና ታሪካዊ ድሎች በአደባባይ ይበሰራሉ!
የአማራ ሕዝብ ትግል በድል ይጠናቀቃል!
የ206ኛ ከፍያለው ደሴ ኮር ነጻ በወጡ ቀጠናዎች የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ፈተናዎችን በስኬት ለማስፈተን የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን በልዩ ትኩረት እያከናወነ ይገኛል።
ከህልውና ትግላችን ጎን ለጎን የትምህርት ስራ እንዲከወን በርካታ ቅድመ ዝግጅት ስራ መስራታችን የሚታወስ ነው።በመሆኑም ከ 2018 ዓ.ም በጀት ዓመት ጀምሮ ዓመቱን የትምህርት ዘመን ነጻ በወጡ ቀጠናዎች ሁሉ በሰላማዊ መንገድ እንዲከወኑ እንደተቋም ከድርጅት እስከ ታችኛው ወታደራዊ መዋቅር ድረስ በመተማመን አያሌ ስራዎችን ሰርተናል።
ስለሆነም ሰኔ 8 /2018 ዓ.ም በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀሰው የፈተና ጥያቄ ኮረጆዎችን በሰላምና በጥንቃቄ የመረከብ ስራ ሲሆን፣ ይህ አቀባበል በተቀናጀ መልኩ ሰላማዊ በሆነ መልኩ በመከወን ላይ ነን ። በአራቱም የክፍለ ጦር ቀጠናዎች የፈተና ቁሳቁሶችን ሙሉ በሙሉ የማድረስና የማደራጀት ስራዎች የተጠናቀቁ ሲሆን፣ ተማሪዎች ያለምንም ስጋት ፈተናቸውን መውሰድ እንዲችሉ ከክፍለ ጦር አዛዦች፣የፖለቲካ መምሪያዎችና የህዝብ ግንኙነቶች በጋራ ጥምረት ምቹ ሁኔታዎች ተፈጥረዋል።
በዚህም መሰረት:-
🎤 በጉና በጌምድር ወረዳ 6ኛ ክፍል 48 ትምህርት ቤቶች ፣ 8ኛ ክፍል 28 ትምህርት ቤቶች፤
🎤ስማዳ ወረዳ በበኩሉ የ6ኛ ክፍል 49 ትምህርት ቤቶች ፣ የ8ኛ ክፍል 47 ትምህርት ቤቶች ፤
🎤ታች ጋይንት ወረዳ 6ኛ 10 ትምህርት ቤቶች ፣ 8ኛ ክፍል 46 ትምህርት ቤቶች፤
🎤ላይ ጋይንት ወረዳ 6ኛ ክፍል 51 ትምህርት ቤቶች 8ኛ ክፍል 42 ትምህርት ቤቶች ላይ ፈተናውን ለመጀመር በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ።
የፈተናው ሂደት መጀመርያም ሆነ ፍጻሜው ሙሉ በሙሉ አስተማማኝ እንዲሆን የጸጥታው ስራው ለሁሉም ክፍለ ጦሮች በልዩ ትኩረት እየተመራ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት በሁሉም ቀጠናዎች ሰላማዊ ድባብ የሰፈነ ሲሆን፣ 206ኛ ኮርም የጸጥታ ስራውን እስከ መጨረሻው በሰላማዊ መልኩ በስኬት እንዲጠናቀቅ አበክሮ እየሰራ መሆኑን ያረጋግጣል።
ድል ለአማራ ህዝብ !!!
ድል ለአማራ ፋኖ !!!
የ206ኛ ከፍያለው ደሴ ኮር ቃል አቀባይ ክፍል!!!
የብልፅግናዉ ስርዓትን የተፀየፉ የሰራዊት አባላት አንድ ጥቁር እስናይፐር እና አንድ ጥቁር ክላሽ በመያዝ ፋኖን ተቀላቀሉ!!
የሰራዊት አባሎቹም የአገዛዙ 11ኛ እዝ 104ኛ ኮር 84ኛ ክፍለ ጦር የወጡ ሲሆኑ አገዛዙ እያደረገ ያለዉን ዘር ተኮር ጭፍጨፋ እና ግድያ በመፀየፍ አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር 33ኛ ክፍለ ጦርን ተቀላቅለዋል።
የሰራዊት አባሎቹ ወደ ፋኖ ሲመጡ በ105ኛ ኮር እና በ33 ኛ ክፍለ ጦር አመራሮች ደማቅ አቀባበል የተደረገላቸዉ ሲሆን አባሎቹም በተደረገላቸዉ ደማቅ አቀባበል እና እንክብካቤ መደሰታቸዉን ገልፀዋል ሲል የ105ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃዉን አድርሷል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!!
ግንቦት 7/2018ዓ.ም
በአለም ላይ በባዶ እጁ ጦርነት ገጥሞ፣የጠላትን ትጥቅ ማርኮ፣ በገዛ ትጥቁ እየገረፈ ያሽነፈ ፍጡር አማራ በቻ ነው።።።ፋኖ ያሸንፋል ድል ለአማራ ህዝብ!!!!ያሬድ ወንድሙ
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ምንጃርና ከረዩ አውራጃ ነበልባል ክፍለ ጦር ድል ተቀዳጀች
ሰኔ 07/2018 ዓ.ም
የአፋብን ሸዋ/ጠ/ግ/አሳምነው ዕዝ ከሠም ፪ኛ ኮር ነበልባል ክፍለ ጦር የብልፅግናውን ጥምር ጦር እንደ ቅጠል አረገፉት።
ሁለት የነበልባል ክፍለ ጦር ሻለቆች የተሳተፉበት ውጊያ ማለትም መብረቅ ሻለቃ እና መቶ አለቃ አበባው ሻለቃ ፋኖዎች በጥምረት ባደረጉት ገድል የብልፅግናውን ግብስብስ ሠራዊት በ06/10/2018 ከቀኑ 6:00 እስከ ማታ 9:45 ሰዓት በነበረው ፍልሚያ ፋኖዎቹ መብረቃዊ ክንዳቸውን በመሰንዘር እንደ እሳት ሲለበልቡት አምሽተዋል።
መነሻውን ከባልጪ አድርጎ ወደ ኢራንቡቲ ቀበሌ ያቀናውን የሪፐፕሊካን ጥበቃ 5ኛ ክፍለጦር እና በስሩ በጥቅማጥቅም የሰበሰባቸውን ሆድ አደር ሚሊሾች እንዲሁም አዲስ ተጨማሪ ሰራዊት በመያዝ ኢራንቡቲ ቀበሌን እቆጣጠራለሁ ብሎ በመንጋ ቢመጣም በአይበገሬዎቹ ነበልባል ክፍለ ጦር ሠራዊታችን ወደ መጣበት እዲመለስ አድርገውታል።
የሀይል ብልጫ የተወሰደበት የጠላት ሀይል ከ15 በላይ እንደተገደለበት እና ቁጥሩ በውል ያልታወቀ ቁስለኛ በአንቡላንስ ከአራት ጊዜ በላይ ጭኖ እንዳመላለሰ እና የሞተበትን ሀይል በአካባቢው ማህበረሰብ በማስገደድ ለህክምና የምታመላልሰው አንቡላንስ ደርሳ እስክትደርስ 15ቱን እሬሳ እዲያቀብሉት ማስገደዱን የውስጥ መረጃችን አሳውቆናል።
ይህ በእንዲሕ እንዳለ የአፋብን ሸ/ጠ/ግ/አ/ዕዝ ዓፄ አምደ ጽዮን ኮር 7/70 ክፍለጦር አንድ(1) የአገዛዙ ወታደር
=> አንድ(1) ዘመናዊ ስናይፐር መሳሪያ
=> አንድ(1) የደረት ትጥቅ
=> አራት(4) ካዝና በመያዝ ወደ ፋኖ ተቀላቅሏል።
በሌላ የአውደ ውጊያ ቀጠና
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ይፋት አውራጃ አስገራሚ ጀብዶች ተሠርተዋል
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው እዝ የዓፄ ዘርዓ ያዕቆብ ፩ኛ ኮር 7/ለ70 ክፍለ ጦር ዛሬም እንደ ትላንቱ በጠላት ይዞታዎች ውስጥ ሰርገው በመግባት አስገራሚ ድሎችን ማስመዝገባቸውን ቀጥለውበታል።
የክፍለ ጦሩ ልዩ የኦፕሬሽን ቃኝዎች የፋሺስት አብይ አህመድ ግብስብስ ሰራዊትን ወደ ሚንቀሳቀስበት ቦታ ሰርገው በመግባት የጠላትን እቅድ በማክሸፍ መብረቃዊ ጥቃቶችን ፈፅመዋል።
የሰርጎ ገብ ውጊያ ስምሪቱ በቀን 05/10/2018 ዓ.ም ከለሊቱ 5:00 ሰዓት ላይ ከአጣዬ ተነስቶ ወደ በርግቢ አቅጣጫ እየገሰገሰ በነበረው የጠላት መከላከያ ሰራዊት ላይ የ7ለ70 ክፍለ ጦር ጀግኖች በ06/10/2018 በበርግቢ ቀበሌ እና በይምልዎ መካከል ላይ አድፍጠው በመጠበቅ ከባድ ድንገተኛ ጥቃት ፈፅመዋል። በዚህ እልህ አስጨራሽ የለሊት ውጊያ የጠላት ኃይል ድባቅ በመመታቱ ወደ መጣበት ተገዶ ለማፈግፈግ ተገዷል። በዚሕም ከጠላት ሀይል አራት(4) የተገደሉ ሲሆን የተቀሩት ደግሞ በጽኑ ቆስለው በሕክምና ላይ እንደሚገኙ የውስጥ መረጃዎቻችን ገልፀዋል።
ይህ የድል ጉዞ ሳይቋረጥ በማግስቱ በ07/09/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 12:00 ሰዓት ላይ ከአጣዬ ከተማ ተነስቶ ወደ አላላ በመጓዝ ላይ በነበረው የሆድ አደር ሚሊሻ ኃይል ላይ ሌላ ስልታዊ ጥቃት ተፈጽሟል። የክፍለ ጦሩ የቁርጥ ቀን ልጆች አራዳ በር ላይ ቀድመው ሰርገው በመግባትና ምሽግ በመያዝ፣ በሚሊሻው ላይ የጀግንነት ክንዳቸውን አሳርፈዋል።በዚህ እልህ አስጨራሽ ውጊያ እንድሪስ የተባለው የጠላት ሚሊሻ መሪ እስከ ግብረ አበሮቹ ሙሉ በሙሉ የተደመሰሰ ሲሆን፣ ካጋጠማቸው ከባድ ሽንፈት የተረፉት 3ቱ (ሦስቱ) ደግሞ በከባድ የመቁሰል አደጋ ምክንያት ሪፈር ተጽፎላቸው በሕይወትና በሞት መካከል ይገኛሉ ሲል መረጃዎቻችን ተናግረዋል።
" ክብር ለጀግኖች ሰማዕታት"
"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን"
የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
+3
በአሜሪካን ሀገር የፔንሴሌቪያ ምክር ቤት ለአድዋ ድል በሰጠው ታሪካዊ እውቅና ላይ የተሰጠ ምስጋና እና የአቋም መግለጫ!
መርዛማ መሪነት፦ የተንኮለኛ መሪዎች መገለጫዎች"
ብቃት የሌለው እና ተንኮለኛ (ክፉ አሳቢ) መሪዎች የሚፈጽሟቸው ተግባራት የአንድን ተቋም፣ ቡድን ወይም ሀገር ህልውና አደጋ ላይ የሚጥሉ ናቸው። እነዚህ መሪዎች በአብዛኛው በግል ጥቅምና በስልጣን ጥም ስለሚመሩ የሚከተሉትን ዋና ዋና ጎጂ ተግባራትን ይፈጽማሉ፦
1. በሴራ እና በመከፋፈል ማስተዳደር (Divide and Rule)
• ሰዎችን ማጋጨት፦ ተንኮለኛ መሪ በበታቾቹ መካከል እርስ በእርስ ጥርጣሬና አለመተማመን እንዲፈጠር ያደርጋል። ሰዎች አንድ ላይ ከሆኑ እሱን ሊቃወሙት እንደሚችሉ ስለሚሰጋ፣ ወሬ በማውራት እና ወገንተኝነትን በመፍጠር አንድነታቸውን ያጠፋል።
• በቡድን መክፈል፦ ሰራተኞችን ወይም ተከታዮችን "የእኔ መስመር ተከታይ" እና "ተቃዋሚ" በማለት ፈርጆ በመካከላቸው የጥላቻ መንፈስ ይዘራል።
2. ብቃት ያላቸውን ሰዎች ማራቅና ማሳደድ
• የበታችነት ስሜት፦ ተንኮለኛ መሪ እውቀትና ክህሎት ያላቸውን ሰዎች እንደ ስጋት ያያቸዋል። የራሱን ድክመት እንዳያጋልጡበት በመፍራት የተማሩ እና ጠንካራ ሰራተኞችን ወደ ጎን ያገላል።
• አሽቃባጮችን መሰብሰብ፦ በዙሪያው የሚያሰባስበው እውነትን የሚናገሩ ሰዎችን ሳይሆን፣ ስህተቱንም ጭምር "ልክ ነህ" እያሉ የሚያጨበጭቡለትን ደካማና አድርባይ ሰዎችን ነው።
3. ተቋማዊ አሰራርንና ህግን ማፍረስ
• የግል ውሳኔ ማብሰል፦ ተንኮለኛ መሪ ህግና መመሪያን አይከተልም። ተቋማዊ አሰራርን በመጣስ ውሳኔዎችን በግል ፍላጎቱና በስሜቱ ላይ ተመስርቶ ያስተላልፋል።
• ድብቅ አጀንዳ መያዝ፦ ውሳኔዎቹ ግልጽነት የሌላቸው፣ ሚስጥራዊ እና ለግል ወይም ለተወሰኑ ቡድኖች ጥቅም ብቻ ያደሉ ይሆናሉ።
4. ስልጣንን ለበቀል እና ለማስፈራሪያነት መጠቀም
• ማስፈራራትና ጫና መፍጠር፦ ተከታዮቹ ወይም ሰራተኞቹ በሃሳብ ሲለዩት በስልጣኑ ተጠቅሞ ያስፈራራቸዋል፣ ጥቅማ ጥቅማቸውን ይከለክላል፣ ወይም ከስራ ያባርራል።
• በቀልኝነት፦ ትናንሽ ስህተቶችን እንኳን ይቅር ከመስራትና ከመማር ይልቅ፣ ሰዎችን ለመጉዳትና ለመበቀል እንደ ትልቅ አጋጣሚ ይጠቀምባቸዋል።
5. ሃላፊነት አለመውሰድ (ጥፋትን ወደ ሌላ ማዛወር)
• የአውራ ጣት ስልት (Scapegoating)፦ ተንኮለኛ መሪ ስራ ሲበላሽ ወይም ውድቀት ሲያጋጥም መሪነቱን ወስዶ አያስተካክልም። ይልቁንም ጥፋቱን በሙሉ ወደ በታችኞቹ በማላከክ ራሱን ንጹህ ለማድረግ ይሞክራል።
• የሌሎችን ስኬት መስረቅ፦ ቡድኑ ጥሩ ስራ ሲሰራ ግን ውጤቱን የራሱ ብቻ አድርጎ ያቀርባል።
6. አርቆ አሳቢነት ማጣትና በአጭር እይታ መመራት
• ጊዜያዊ ጥቅም ማሳደድ፦ ለረጅም ጊዜ የሚዘልቅ እቅድና ራዕይ የለውም። ዛሬን በሴራና በውሸት ማለፍ ላይ ብቻ ያተኩራል።
• ለልማትና ለለውጥ ዝግ መሆን፦ አዳዲስ ሃሳቦችን እና ተቋማዊ ለውጦችን አይቀበልም። ለውጥ ከመጣ ጥቅሜ ይነካል ብሎ ስለሚሰጋ የቆየውንና ያልሰራውን አሰራር ሙጥኝ ብሎ ይኖራል።
ባጭሩ፦ ተንኮለኛ መሪ የቆመበትን ተቋም የሚያፈርስ፣ የሰዎችን ተነሳሽነት የሚገድል እና በሰላም አብሮ የመስራት ባህልን የሚያጠፋ "መርዛማ መሪ" (Toxic Leader) ነው።
📌📌እርስዎስ ይህ አይነት መሪ ገጥሞዎት ይሆን?? ይለናል አርበኛው ዝመተኛው ገዳይ የምኒልክ ግልገል አርበኛ ኤፍሬም ባዬ
በሸበል በረንታ የሚገኘው የአገዛዙ ቅጥረኛ የሚሊሻ መዋቅር መፈራረሱ እንደቀጠለ ነው!!
64ኛ ክ/ጦር ሰኔ 06/2018 ዓ.ም
መንገሻ ጎቻው ፖራ ኮማንዶ ወይንየ ቀበሌ ተወላጅ ሲሆን አንድ ኮሪያ ክላሽ ከ40 ጥይት እና የደረት ትጥቅ በመያዝ በሸበል በረንታ የዕድውሃ ከተማ ከሚገኘው የአገዛዙ አረመ* ኔዊ ኃይል በአካባቢው የሚገኝ ማህበረሰብ ላይ እያካሄደ ያለውን ዝርፊያ እና ጭቆና በመቃወም አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ከእነ ሙሉ ትጥቁ ተቀላቅሏል።
በሌላ መረጃ በእነማይ ወረዳ ማህበረብረሃን ቀበሌ የሚገኘው የአገዛዙ ኃይል ከፋኖ ሐይሎችን ጋር መፋለም ሲያቅተው በስር-እየሱስ ቀበሌ የጤና ተቋምን እና የአካባቢው ማህበረሰብ የቤት በር በመስበር የቤት እቃቸውን በመዝረፋ እና በማውደም የቀረውን የቤት ዕቃ በመጫን አረመኔዊ ተግባሩን ዛሬም አሳይቷል።
የአብይ አህመድ አገዛዝ በቢቸና እና የዕድውሃ ከተማ የሚኖሩ ነጋዴዎች እና የመንግስት ሰራተኞች ላይ ከፍተኛ ዝርፊ እየፈፀመ ይገኛል። በአገዛዙ ከፍተኛ ዝርፊ ከተፈፀመባቸው ነጋዴዎች እና የመንግስት ተቋማት ውስጥ:-
✍️ከግል ክሊኒኮች 50.000 ብር
✍️ከሆቴል 25.000 ብር
✍️ከሱቅ 2,000 ብር
✍️የጭነት ሲኖ ተሽከረካሪዎች 10.000 ብር
✍️የህዝብ ማመላለሻ 5,000 ብር
✍️የመንግስት ሰራተኛ ከ10.000.ብር እስከ 20,000 ብር ከ10.000 ብር በታች ደሞዝ የሚበሉ ከሆነ 2,000 ብር ከደሞዛቸው እንዲነሳ ተወስኖል።
✍️የጤና ባለሙያዎች የአዳር ብር (ዱቲ) የ7 ወር ደሞዝ እንዳልተከፈለ እና በአስገዳጅ ሁኔታ እያሰሩ እንደሆነ ተረጋግጦል።
✍️ከባጃጅ ሹፊሮች 1,000 ብር እንዲከፍል ትዛዝ ከተሰጠ በሆላ ካልከፈለ ከ2,000 ብር እስከ 3,000 ብር በአስገዳጅ ሁኔታ እንዲከፍሉ ይደረጋሉ። በዚህም የተነሳ በሁለቱም ወረዳ የሚገኙ የከተማ ኖሪዎች አገዛዙ እየፈፀመባቸው ባለውን ዝርፊያ መማረራቸውን ከውስጥ መረጃ ምንጮቻችን አረጋግጠናል።
አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!!
ሰኔ 06/2018 ዓ.ም
አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት
ማፍረስ፣ መናድ እንደቀጠለ ነው!!!
አፋብን ላስታ ጄ/ል አሳምነው ፅጌ የጠላትን ሰራዊት ከውጊያ ባሻገር ለምን ዋጋ እንደሚከፍሉ ቆም ብለው በማሰብ ከራሳቸው ጋር የታረቁ ከህዝብ የህዝብ የሆኑ ወንድሞቻችንን አረፈዳችሁ ብለን ሳንቆጣ፣ ሳናገራግር ስቀን በክብር ተቀብለናቸዋል።
አባቶቻችን ከምዓራብ እቅጣጫ ነአኩተለአብ በር፣ በስተምስራቅ አቦ መሳለሚያ፣ በስተደቡብ መካነ-ልዕልት፣ በስተሰሜን መዳጌ ሲደርሱ ከበቅሎአቸው ወርደው፣ ጫማቸውን አውልቀው ስለቦታው ቅድስና እና ክብር ሲሉ የማይሆኑለት አልነበረም።
የአቢይ አህመድ አገዛዝ አምርሮ የሚጠላውን ህዝብ እና እምነት ለማርከስ አቢይ አህመድ የግራኝ አህመድ የግብር ልጅ ነውና ከአባቱ በላይ ጨክኖ የቅዱስ ላሊበላ ውብ እና ብርቅዬ ቤተመቅደሶችን በከባድ መሳሪያ ተኩሶ መታቸው፣ ታንክ ነዳባቸው። ይህንን ግፉን እያደር የተረዱ ከድሃ ልጆች ተውጣጥተው ለዚህ እርኩስ ሰው መንበር ሲባል የውሻ ሞት ይብቃ ብለው የነቁ ሙሉ ትጥቃቸውን በመያዝ ወደ እናት የአማራ ህዝብ እቅፍ በሰላም መጥተዋል።
#ፋኖነት ግፍን ተቃውመህ ፍትህና ርትዕት የምትገዛበት ከወርቅ የከበረ የማዕዘን ድንጋይ ነው!!!
#ድል ለፋኖ!!!
አፋብን ሸ/ጠ/ግ/አ/ዕዝ አፄ አምደ ፅዮን ኮር በስሩ ላሉ የክፍለጦርና የሻለቃ PR መሰረታዊ የICT ክህሎት ስልጠና ለተከታታይ ቀናት ሰጥቶ አጠናቀቀ።
፻ አለቃ ክብርት ገረመው የ 6ኛ ዕዝ 602ኛ ኮር 32ኛ ክ/ጦር ሀለተኛ ሬጅመንት የሻምበል ሁለት አዛዥ 206ኛ ኮር14ኛ ክ/ጦር ንጉስ ተክለሃይማኖት ሻለቃ ተቀላቀለ።
( 206ኛ ኮር) ሰኔ 6/2018 ዓ.ም
================================
የአረመኔው ሰርዊት ምንም አይነት የመዋጋት ብቃትና ፍላጎት ባለመኖሩ ከምመራት ሻምበል 23 አባላት ከድተዋል ያለ ሲሆን ከ206ኛ ኮር 14ኛ ክ/ጦር የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ጋር ቆይታ አድርጓል።
ሰራዊቱ ሴቶችን አስገድዶ እንዲደፍር ካድሬዎች በአካል ተገኝተው ያበረታታሉ ያለ ሲሆን የአረመኔው ሰራዊት በንፁሐን ላይ በተለይም በሴቶችና ህፃናት ላይ የሚደርሰውን የአስገድዶ መድፈር ፆታዊ ጥቃት የስናን ወረዳ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ባወቀ በሰራዊቱ መካከል ተግኝቶ ሲያበረታታ እንደነበር ለአብነት ገልጿል።
የወንበዴዎችን ምር*ጫ ተከትሎ ማብራሪ የሰጠው ፻ አለቃ ክብረት ገረመው የመከላከያ ሰራዊት አባላት ከ3 በላይ ምር*ጫ ካርድ በመውሰድ ግንቦት 22 እና 23 በተደረገው ማጭበርበር ተሳታፊ ይሁኑ እንጂ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ከደብረ ማርቆስ ከተማ ጀምሮ በሁሉም ቀጠናዎች ከፍተኛ ውጊያ በመደረጉ ምንም አይነት ምር*ጫ አለመደረጉን አስታውቋል ።
አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ! አዲስ ተስፋ
የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
