ar
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

الذهاب إلى القناة على Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

إظهار المزيد
2 940
المشتركون
-1524 ساعات
+287 أيام
+37030 أيام
أرشيف المشاركات
ሰበር ዜና!!! 🔥🔥    ሰኔ 13/2018 የአገዛዙ የጭንቀት የሌሊት እንቅስቃሴ ከሽፏል እንዲሁም ከፍተኛ ሽንፈትን ተከናንቧል!!! በዛሬው እለትም በዳስጉንዶ አገዛዙ ተደምስሷል ምርኮ በምርኮም ሆኗል!!! በዛሬው እለት ሰኔ 13/2018 አይበገሬዎቹ አፋብን በላይ ዕዝ መይሳው ካሳ (፪ኛ) ኮር ካራማራ ክ/ር 2ኛ ሬጅመንት በአርበኛ አጠቃ ሞገስ እየተመራ በመተማ ወረዳ ዳስጉንዶ የሰፈረውን የአማራን ደም መጣጭ የአገዛዙ ጥምር ሰራዊት ተደምስሶ ከተማዋን መቆጣጠር ተችሏል። እንዲሁም በርካታ የነብስ ወከፍ መሳሪያና የቡድን መሳሪያን ብሬንን ጨምሮ ፋኖ ገቢ አድርጓል። ሰኔ10/2018 በተደረገው እልህ አስጨራሽ አውደውጊያ የተሰው ጓዶችን አስመልክቶ ዘመቻ አርበኛ ፈንታሁን ገበየሁ በቁርጠኝነት ጠላትን በመደምሰስና በመማረክ ተጀምሯል። አሁን ለጊዜው የደረሰን መረዳ ከ45 በላይ የነብስ ወከፍ መሳሪያ እና 5 ብሬኖች ተማርኳል። አውደውጊያው እንደተቋጨ ሙሉ የድል ዜናውን እናቀርባለን ሲል የክ/ሩ የህ/ግ መረጃውን አድርሶናል። በኔትወርክ ችግር ያልተዘገበ ዜና: የአገዛዙ ሰራዊት እንደ አማራጭ ኔትወርክ በማጥፋት ጨለማን ተገን በማድረግ ፋኖ ወዳለበት ቀጠና እየተንቀሳቀሰ ባለበት ስአት አፋብን በላይ ዕዝ መይሳው ካሳ (፪ኛ) ኮር ቋራኦሜድላ ክ/ር ነብሮ ብርጌድ ቀድሞ መረጃ በማፈንፈን ሰኔ 10/2018 ከደለጎና ከበሙር መነሻውን አድርጎ ወደ ማህዲድ ቢያደርግም ነበልባሉ የነብሮ ብርጌድ ፋኖ ገዥ ቦታዎችን በመቆጣጠር ከጧቱ 1:00 ስአት ጀምሮ እስከ 6:00 ስአት በቆየው እልህ አስጨራሽ የትንቅንቅ አውደ ውጊያ የጠላትን ሀይል ግራራ ከተባለ ተራራ በመስቀል ቁም ስቅል አሳይተውታል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የቋራኦሜድላ ክ/ር አመራሮች ከነብሮ ብርጌድ የሻለቃ አመራሮች ጋር ባደረጉት ልዩ ጥምረት ከፍተኛ ጀብድ ከመፈፀም ባሻገር የጠላትን እቅድ መቶ ፐርሰንት ማክሸፍ ተችሏል ሲል የክፍለጦሩ የህ/ግ አርበኛ አስቻለው አለባቸው ገልፆታል። በዚህ የአውደውጊያ ፍልሚያ ከፊት መርቶ በመግባት የዚህ ድል ታላቅ ጀብዱን ፈፅሞ አርበኛ ሶሎሞን መስዋትነትን ከፍሏል። ስለ አማራ መከራ ስለኢትዮጲያ ውርደት ምክንያት የሆነውን የብልፅግናን ፋሽስታዊ ስርአት አጥብቆ በመታገል ረገድ ጫካ ቤቴ ብሎ በመግባት ቋራኦሜድላ ባስመዘገበው ትልልቅ ጀብዶች ቀዳሚው ይህ አርበኛ ለወገኑ ሲል እስከ ደም ጠብታ ድረስ በፅናት ሲታገልና ሲያታግል የነበረ የአማራ የቁርጥ ልጅ እንደነበረ ይታዎቃል። በዚህ አውደውጊያ የተገኘ ድል መታሰቢያነቱ ለአርበኛ ሶሎሞን ሆኖ የተመዘገበ ሲሆን ከ30 በላይ አስክሬንና አንድ አይሱዙ ቁስለኛ ይዞ ገለጎ ሆስፒታል ገብቷል። ሌላው አገዛዙ ከሽንፈት የማያድነውን የኔት ወርክ ማጥፋት አማራጭ ቢያደርግም ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ስአት ድረስ የጠላት አስክሬን በየአርሶአደሩ ማሳ እንደወደቀ የአይን እማኞች ነግረውናል እንዲሁም ቀጠናው ላይ ውጥረቱ እንደቀጠለ ይገኛል ሲል የክ/ሩ የህ/ግ ተጨማሪ መረጃዎችን አድርሶናል። ሁለተኛው አውደውጊያ በመተማ ወረዳ ከሽንፋ ከተማ ከቅርብ እርቀት የተደረገ ሲሆን የአገዛዙ ጥምር ሰራዊት በአራት አቅጣጫ ማለትም በደለጎ፣ በሽንፋ፣ በቱመትና በሰልፈረዲ እንቅስቃሴ ቢያደርግም በሰልፈረዲ በኩል የመጣውን ግብስብስ ሀይል አፋብን በላይ ዕዝ መይሳው ካሳ (፪ኛ) ኮር ካራማራ ክ/ር አንደኛ ሬጅመንት ጠላት ባላሰበው መንገድ ሰኔ 10/2018 አነጋግ ላይ የደፈጣ መብረቃዊ ጥቃት ማድረስ የተቻለ ሲሆን ምቱን መቋቋም ያቃተው የጠላት ሀይል ከፍተኛ ሙትና ቁስለኛውን እያዝረከረከ ወደ ኋላ ተመልሷል። ......

በወለጋ በጦርነት የተማረኩ ምርኮኞች በድሮን ጥቃት ተገደሉ አሻራ ሚዲያ ​ዋሽንግተን ዲሲ - ሰኔ 13 ቀን 2018 ዓ.ም ​ከአካባቢው የደረሰን መረጃ  እንደሚያመለክተው፣ በትናንትናው ዕለት በወለጋ በተካሄደው ውጊያ ተማርከው የነበሩ የጦር ምርኮኞች የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች በፈጸሙት የድሮን ጥቃት ህይወታቸው አልፏል። ​የመረጃ ምንጮች እንደገለጹት፣ አገዛዙ የጥቃቱን አሰቃቂ ሁኔታ እና ምርኮኞቹ በምስል ተቀድተው ለማህበራዊ ሚዲያ እንዳይደርሱ ለመከላከል፣ በስፍራው የነበረውን የኢንተርኔት አገልግሎት እና የስልክ ግንኙነት ሙሉ በሙሉ አቋርጧል። ​የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እና የአካባቢው ነዋሪዎች ይህ ድርጊት አለም አቀፍ የጦር ህግጋትን የሚጥስ እና በምርኮኞች ላይ የተፈጸመ ግፍ መሆኑን በመግለጽ ላይ ናቸው። ​ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ጥረታችንን የቀጠልን ሲሆን፣ ሁኔታው ሲጣራ የምናደርስ ይሆናል። ©አሻራ ሚዲያ

የ19ኛ ክፍለ ጦርን ምት መቋቋም ያቃተው የብልፅግና ሰራዊት እስከሬኑን በአግባቡ ሳይቀብር ፈርጥጦ ተመለሰ! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ ግዙፉ አሳምነው
+1
የ19ኛ ክፍለ ጦርን ምት መቋቋም ያቃተው የብልፅግና ሰራዊት እስከሬኑን በአግባቡ ሳይቀብር ፈርጥጦ ተመለሰ! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር አካል የሆነው 19ኛ(እሸት) ክፍለ ጦር እየተግተለተለ በመጣው በብልፅግና ሰራዊት ላይ ብርቱ ክንዳቸውን በማሳረፍ ጠላትን አንገት አስደፍተው መልሰውታል። ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ/ም ከንጋቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ አገዛዙ ውጊያ የከፈተ ቢሆንም ክንደ ብርቱዎቹ ፋኖዎች በገለሶት ምድር ቃሪያ ወንዝ ዙሪያ ዳገትና ሸንተረሩ ሳይበግራቸው ሲፈልጉ በደፈጣ ሲያሻቸው በቆረጣ በመግባት የጁላን ሰራዊት ሲያራግፉት ውለዋል። በተካሔደው አውደ ውጊያ 12 የጠላት ኃይል ሲደመሰስ ጠላት ገለሶት ቃሪያ ወንዝ ዳር አራቱን እስከሬን በአንድ ጉድጓድ አድርጎ በአግባቡ አፈር ሳያለብሳቸው ከ18 በላይ ቁስለኛውን ይዞ ወደ መጣበት ፈርጥጦ ተመልሷል ሲል የ303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃውን አድርሷል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!! አፋብን ወሎ ቤተ- አማራ ምኒልክ ዕዝ  ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!!     ሰኔ:- 13/ 2018 ዓ/ም

የ64ኛ ክ/ጦር ቃኝ እና መሃንዲስ በሰሩት የደፈጣ ኦፕሬሽን 6 የአገዛዙ ሰራዊት አባላት ሲወገዱ 2ቱ ቁስለኛ ሆነዋል!! 64ኛ ክ/ጦር ሰኔ 10/2018 ዓ.ም የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ቃኝ እና መሃንዲስ ሰኔ 09/2018 ዓ.ም በእነማይ ወረዳ ሁለት አንባ ዲቢሳ ቀበሌ በተጣለ ደፈጣ ስድስት የአገዛዙ ሰራዊት አባላት እስከ ወዳኛው ሲወገዱ ሁለቱ ቁሰለኛ ሆነዋል ከእነዚህም ውስጥ #ተክለ አብ አባቡ አይተን የተባሉ የአገዛዙ ሰራዊት አባል ቢቸና የመጀመሪያ ደረጃ ሆስቢታል የገባ ቢሆንም ወዲያውኑ መሞቱ ተረጋግጦል። ከዚህ ጋር በተየያዘ ሰኔ 10/2018 ዓ.ም በማህበረ ብርሃን ቅዱስ ገብሬኤል ቤተክርስትያን በጅምላ ተቀብረዋል። በሁለት አንባ ዲቢሳ ቀበሌ በተጣለ ደፈጣ ከፍተኛ ኪሳራ ያስተናገደው የአገዛዙ ሰራዊት አባላት የንፁሃንን ሀብት ንብረት ዘረፎል አውድሟል። ከእነዚህም ውስጥ:- 1ኛ.መ/ር ሰው ዓለም የኔሰው ሙሉ የቤት ዕቃ 2ኛ.የሽዋስ መግስቱ የልብስ መስፊያ መኪና እና የኤሌክትሮኒክስ ሱቅ ሙሉ በሙሉ ሲዘረፍ 3ኛ.ሞጋ ስታየሁ እና 4ኛ.ሐብቴ አያሌዉ በዱላ ከጥቅም ውጭ የሆኑ 6ኛ.ዳቆን ባን ታምላክ ዉዱ በአፈሙዝ የተመታ 7ኛ.የቻለዉ ሞሴ የቀንድ ከብት በአገዛዙ ጥይት የተገደሉ ሲሆን አገዛዙ በፋኖ ከፍተኛ ብትር ሲገጥመው ንፁሃንን በመረሸን እና በመዝረፍ ለአማራ ህዝብ አረመኔ መሆኑን አረጋግጦል። አዲስ ትውልድ! አዲስተሳሰብ! አዲስ ተስፋ!!               ሰኔ 10/2018 ዓ.ም አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት

የእነማይ ወረዳ ጊ/መንግስት በሁለት ቀበሌዎች ላይ ሰፊ የህዝብ ውይይት መድርክ በማመቻቸት አካሂዶል። 64ኛ ክ/ጦር ሰኔ 13/2018 ዓ.ም ሰኔ 12/2018 ዓ.ም የእነማይ ወረዳ ጊ/መንግስት በእነማይ ወረዳ ደብረገነት መሌ እና ወንዳሳ ቁስቋም ቀበሌ ህዝባዊ ውይይቶች አካሂዶል። በእነማይ ወረዳ ደብረገነት መሌ እና ወንዳሳ ቁስቋም ቀበሌ የተገኘው የማህበረሰብ ክፍል በአማራ ህዝብ የህልውና ትግል ወቅታዊ ሁኔታዎች እና በህዝብ አስተዳደር ስራዎች ላይ ሰፊ ውይይት ተካሂዶል። የእነማይ ወረዳ ጊ/መንግስት አመራሮች በመሩት የስብሰባ መድርክ ስለ አማራ ህዝብ የህልውና ትግል ያለበት ወቅታዊ ሁኔታ ሰፊ ግንዛቤ በመስጠት በቀበሌ ያሉ ጊ/መንግስት አመራሮች:- ✍️የፍትህ አሰጣጥ ✍️የቀበሌ መልካም አስተዳደር ፀጥታ ✍️ ህገወጥ የኦል መሬት ማስከበር ✍️የፋይናስ እና ሎጀስቲክ አሰባሰብ በተመለከተ በሰፊው በመወያየት ለቀበሌ ጊ/መንግስት አመራሮች አቅጣጫ ተሰጥቷል። በውይይት መድረኩ የተገኙት ማህበረሰብ ክፍል እንደተናገሩት የአብይ አህመድ አምባ ገነን አገዛዝ በአማራ ህዝብ ላይ ከፍተኛ የሆነ በደል እና ጭቆና እያደረሰ ቢገኝም ይህንን አምባ ገነን ስረዓት ለመገርሰስ መስዋትነት እየከፈለ የሚገኘው የአማራ ፋኖ ጎን እንደሆኑ በሰፊው አስረድተዋል። አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!! ሰኔ 13/2018 ዓ.ም አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት

በእናርጅ እናውጋ የሗላ ደጀኑ ጦር በ5 ቀበሌ የተውጣጣ የመች ሀይሎችን በመለየት ቀጠናውን የማስከበር ስራ ወደ ተግባር ገብተዋል። ========================== ሰኔ 12 / 2018 ዓ.ም
+3
በእናርጅ እናውጋ የሗላ ደጀኑ ጦር በ5 ቀበሌ የተውጣጣ የመች ሀይሎችን በመለየት ቀጠናውን የማስከበር ስራ ወደ ተግባር ገብተዋል። ========================== ሰኔ 12 / 2018 ዓ.ም የእናርጅ እናውጋ ወረዳ ጊዜአዊ መንግስት ከ5ቱ ቀበሌዎች የተመረጡ መች ሀይሎችን በማደራጀት በመጠያ ከተማ ውይይት በማድረግ ቀጠናው ለማስከበር ቆርጦ የተነሳ ሲሆን በተለያዩ አጀንዳዋች ላይም ውይይት ተካሂዷል። 1: የቀበሌዎችን የፀጥታ ሁኔታ 2 : የህዝብ ፍትህ አገልግሎት አሰጣጥ 3 : የሀብት እና ፋይናንስ አሰባሰብ አፈጻጸም ምን እንደሚመስል ውይይት ተደርጓል ።በዚህ ስብሰባ የተሻለ ስራ ለመስራት በቂ መነሳሳት የተፈጠረ ሲሆን ውይይቱን የመሩት የ74ኛ ክ/ጦር አመራሮች እና ጊዜያዊ መንግስት በማስተባበር የእናርጅ እናውጋ ወረዳ ጊዜያዊ መንግስት የህዝብ ንቅናቄ ተጠሪው አሳውቀዋል። ^^ የራሳችን ችግሮች በራሳችን አመራሮች እየፈታን ወደ ተሻለ ለውጥ እንገሰግሳለን^^ አዲስ ትውልድ፣አዲስ አስተሳሰብ፣አዲስ ተስፋ አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት

በ2እጅ እነሴ ወረዳ ቦዳ በረድ ቀበሌ ላይ በወቅታዊ ጉዳዮች ከህዝቡ ጋር የክ/ጦር አመራሮች በመገኘት ውይይት ተካሄደ። ============================= ሰኔ12/2018ዓ.ም የአፋብን ቴ
+3
በ2እጅ እነሴ ወረዳ ቦዳ በረድ ቀበሌ ላይ በወቅታዊ ጉዳዮች ከህዝቡ ጋር የክ/ጦር አመራሮች በመገኘት ውይይት ተካሄደ። ============================= ሰኔ12/2018ዓ.ም የአፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 54ኛ ክ/ጦር በ2እጁ እነሴ ወረዳ ቦዳ በረድ ቀበሌ የቀጠናውን ጀብደኝነት በወትሮው ግለት ለማስቀጠል ብሎም ማሻሻል ከቦዳ በረድ ቀበሌ ህዝብ ጋር የጋራ ውይይት ተደርጓል። በቀጠናው የቀበሌ መዋቅርና በፍትህ አሰጣጥ እና የመልካም አስ/ር ችግሮችን በመለየት ህዝባዊ አስተዳደርን ጨምሮ የተገመገመና የወደፊት አቅጣጫ የተቀመጠበት ሲሆን ትግላችን አሁን ላይ የደረሰበትን ሁኔታ አጭር ማብራሪያ በኮሩ እና በክፍለ ጦር አመራሮች የማስረዳት ስራ ተሰርቷል። እናደራጃለን ! እንመክራለን! እንፈፅማለን!! አዲስ ትውለድ፣አዲስ አስተሳሰብ፣አዲስ ተስፋ!! አፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት

የፋኖ ጥሪ ለጀግናው የደራ ህዝብ! የደራ ወጣቶች፣ የታጠቁ ሚሊሻዎች፣ በየሀገሩ የምትገኙ ፋኖዎች እና በተለያዩ አካባቢዎች የተሰደዳችሁ የደራ ተወላጆች በሙሉ፦ ዛሬ ታሪክ እና ትውልድ ይቅር የማይለው ወሳኝ ምዕራፍ ላይ እንገኛለን። ጠላት የሸኔ ቡድን አንተን ከምድረ-ገፅ ለማጥፋት፣ ማንነትህን ለመደምሰስ እና መሬትህን ለመውረስ ቆርጦ ተነስቷል። ዛሬ ዝም ብለን የምንተኛበት፣ እጃችንን አጣጥፈን የምንቀመጥበት ሰዓት አይደለም። አባት፣ እናት፣ ሚስት፣ ልጅ፣ ወንድም፣ እህት፣ አጎት እና አክስቶችህ በግፍ በሞት እየተቀሙህ፣ አንገትህ እስከሚቆረጥ ድረስ ዝም ብለህ የምትጠብቅበት ምንም ምክንያት የለም! ጠላት ብትወደውም ብትጠላውም ሊያጠፋህ ተዘጋጅቷል። ራስህን፣ ቤተሰብህን እና ታሪክህን ማዳን የሚቻለው ግንባር ላይ ተነስቶ በመመከት ብቻ ነው። ስለዚህ ይህ የህልውና ጥሪ ለሁላችሁም ይድረስ፦ 1ኛ. የደራ ወጣቶች ሆይ፦ የአባቶቻችሁን ጀግንነት የምታሳዩበት ወቅት አሁን ነው። ጉልበታችሁን፣ እውቀታችሁን እና ወኔያችሁን ተጠቅማችሁ አካባቢያችሁን ከጥፋት እንድትታደጉ እና ክንድ እንድትሆኑ ጥሪያችን ይደርሳችኋል። 2ኛ. የታጠቁ ሚሊሻ አባላት በሙሉ፦ በየትኛውም ቦታ የምትገኙ፣ የአገርና የወገን አለኝታ የሆናችሁ የታጠቁ ሚሊሻዎች፤ በአስቸኳይ በየግንባሩ በቱቲ፣ በሜታ እና በኮሉ ግንባር በመገኘት መስመር በመያዝ ጠላትን እንድትመክቱ እና ግንባሩን እንድትቀላቀሉ ጥሪ ቀርቦላችኋል። 3ኛ. በየቦታው የተሰደዳችሁ የደራ ልጆች፦ ከዚህ በፊት በመንደራችሁ መቃጠልና መውደም ምክንያት በመርሓቤቴ፣ በሬማ እንዲሁም በሌሎች የተለያዩ አካባቢዎች ተሰዳችሁ የምትገኙ ወገኖቻችን፤ የትውልድ ቀያችሁን ከወራሪ በማጽዳት ወደ ቀደመው ህይወታችሁ ለመመለስ በጋራ የምንነሳበት ጊዜ አሁን ነው። 4ኛ. በስደት የምትገኙ የፋኖ አባላት፦ በአንድም በሌላ ምክንያት ወደ ጅቡቲ፣ ሳውዲ አረቢያ፣ ዱባይ እንዲሁም ወደተለያዩ የዓለም ሀገራት የተሰደዳችሁ ፋኖዎች በሙሉ፤ ወገናችሁ በግፍ እየታረደ ባለበት በዚህ ፈታኝ ወቅት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ወደ ነበራችሁበት ህዝብን የማዳን የፋኖ ትግል እንድትመለሱ እና እንድትቀላቀሉ ታሪካዊ ጥሪ ቀርቦላችኋል። የደራ ህዝብ ሆይ፦ ከመሞት መሰንበት፣ ከመቀመጥ መነሳት ይሻላል! ተኛህ ማለት ጠላትህ ይምርሃል ማለት አይደለም፤ ይልቁኑ አንገትህን እስክትቀላ ይጠብቅሃል። ስለዚህ ቆርጠህ ተነሳ! ማረፊያህ ግንባር፣ መከላከያህ ክንድህ ይሁን! ክብር ለጀግናው ህዝባችን! ደራ በልጆቿ አንድነት ታሸንፋለች! ይህንን ታሪካዊ ጥሪ ያስተላለፉት፦ አርበኛ ሽመልስ ንጉሴ የቀድሞ የደራ አመራር እና የማንነት አስመላሽ ኮሚቴ፣ በአሁኑ የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳም ዕዝ ህግ መምሪያ ኃላፊ።

ክብረ በዓሉ በሰላም መጠናቀቁን ክፍለጦሩ አስታወቀ! ሰኔ 12/2018 ዓ.ም በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ተጉለትና ቡልጋ አውራጃ በሳሲት ክላስተር ስር የሚገኘው የአጃና ቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ በዓል ዛሬ ሰኔ
+3
ክብረ በዓሉ በሰላም መጠናቀቁን ክፍለጦሩ አስታወቀ! ሰኔ 12/2018 ዓ.ም በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ተጉለትና ቡልጋ አውራጃ በሳሲት ክላስተር ስር የሚገኘው የአጃና ቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ በዓል ዛሬ ሰኔ 12 ቀን 2018ዓ.ም ጀግናው ሰራዊታችን ባለበት በደማቅ ሁኔታ ተከብሮ ሲውል፣ የንጉስ ሳህለ ሥላሴ ክፍለ ጦር አባላትና አመራሮች በቦታው ላይ በመገኘት አጠቃላይ የፀጥታና ደህንነት ስራውን ማስከበራቸውን ክፍለጦሩ በህዝብ ግንኙነት ክፍሉ በኩል በላከው መረጃ ገልጿል። በዓሉን ለመሳተፍ ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል ከዋዜማው ጀምረው የመጡ እንግዶች በዓሉን አክብረው በሰላም ወደየመጡበት መመለሳቸውን ክፍለጦሩ አስታውቋል።      ''ክብር ለትግሉ ሰማዕታት''    ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ አምደ ፅዮን ኮር ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል

​የአገዛዙ ሀይል ከዕለት ወደ ዕለት መቀጠሉን ተከትሎ አድማ ብተና አመራሩ ሙሉ ትጥቅ ይዞ ፋኖን ተቀላቀለ!! ​ሰኔ 12/2018 ዓ.ም ​ከደብረብርሃን ከተማ የተነሳውና ቀደም ሲል ብልፅግናን ሲያገለግል የነበረው የአድማ ብተና አመራር አሥር አለቃ ብሩክ ሸዋንግዛው፣ ፋኖን መቀላቀሉ ታውቋል። ​የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ አምደ ጽዮን ኮር ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ክፍል እንደገለጸው የአገዛዙን ፀረ -አማራነት የተረዳው አድማ ብተና አሁን ላይ ሙሉ ትጥቁን በመያዝ የዕዙ አካል የሆነውን የአፄ አምደ ፅዮን ኮር አፄ ምኒልክ ክፍለጦርን ተቀላቅሏል ሲል ከምስል ጋር አያይዞ ገልጿል። ክብር ለትግሉ ሰማዕታት ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

የጠላት ኃይል እየፈረሰ የወገንን ኃይል መቀላቀሉን ቀጥሏል! በዛሬው እለት ስድስት የአብይ ዙፋን አስጠባቂ ሰራዊት አፋብን ጎ/ጠ/ግ በላይ ዕዝ 206ኛ ሜ/ጄ ከፍያለው ደሴ የጠላት ኃይል በመፍረስ ላይ ነው። እየፈረሰ ያለው የአገዛዙ ሰራዊት አባላት አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ 206ኛ ከፍያለው ደሴ ኮር ተራራው ራስ ጉና ክፍለ ጦር ዶክተር አምባቸው መኮንን ብርጌድን በሰላም ተቀላቅለዋል። 06 የአገዛዙ መከላከያ አባላቱ የ 59ኛ ክፍለ ጦር አባላት የነበሩ ሲሆን በቆይታቸው ስርዓቱ እያደረገ ያለው አንድን ማህበረሰብ በመለየት የመጨፍጨፍ፣ ማህበረሰባዊ እሴትና ባህልን እንዲሁም የሀገሪቱን አብሮት እሚንድ በመሆኑ ከነ ሙሉ ትጥቃችን ወደ ፋኖ ለመቀላቀል አስገድዶናል ብለዋል ። ​የዶክተር አምባቸው መኮንን ብርጌድ ዋና ወታደራዊ አዛዥ ሻለቃ ቄሴ ተስፋ (የጉናው መብረቅ) እንደገለጸው፣ ጠላትን በወታደራዊ ዘመቻ ብቻ ሳይሆን በሰላማዊ ንግግርና በወንድማማችነት መንፈስ እንዲፈርስ ማድረግ መቻሉ ታላቅ ስኬት ነው ብሏል። አዛዡ አክሎም ቀደም ሲል እጃቸውን የሰጡ የሰራዊት አባላትን በአግባቡ ተቀብለን  ወደመጡበት አካባቢና ትውልድ ቀያቸው በሰላም ማሸኘታችን እሚታወቅ በመሆኑ ይህ ተግባር ለሀገርና ህዝባዊ  አብሮነት ትልቅ ፋይዳ ስላለው  ፤ትክክለኛ የሕዝብ እውነተኛ ልጅና አስተማማኝ ጋሻ መሆናችንን በተግባር ያረጋገጠበት መሆኑን ሊታወቅ ይገባል ብሏል። ድል ለአማራ ህዝብ !!! ድል ለአማራ ፋኖ !!! አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ 206ኛ ከፍያለው ደሴ ኮር ቃል አቀባይ ክፍል!!!

የፋሽስቱ ብልፅግና የ58ኛ ፣የ48ኛ ክፍለጦርና የ42ኛ ክፍለጦር የሰራዊት አባላት ከየአቅጣጫው በመፍረስ የ102ኛ ኮር አካል የቀድሞው ካላኮርማ ክፍለጦር የአሁኑ 49ኛ ክፍለጦርን ተቀላቀሉ። በሰሜን ወሎ ዞን በራያ ቆቦ ወረዳ የአፋብን ወሎ ቤተ አማራ ጀብደኛው ምኒልክ ዕዝ የ102ኛ ኮር የጥንካሬ ምልክት የሆነው 49ኛ ክፍለጦርን የጠላት 58ኛና 48ኛ ክፍለጦር 3 የሰራዊት አባላት ከሮቢት ከተማና አንድ የሚሊሻ አባል ሳንቃ ከተማ መነሻቸውን በማድረግ ከስምሪት ቀጠና በመጥፋት ሙሉ ትጥቃቸውን ከተተኳሽ ጋር በመያዝ ዛሬ ሰኔ 12/2018ዓ/ም ተቀላቀሉ።  ከተቀላቀሉት የሰራዊት አባላት መካከል አንዱ የአገዛዙ ወታደር ሁለት ጥቁር ክላሾችን በመያዝ የመጣ በመሆኑ የ49ኛ ክ/ጦር አመራሮች የጀግና አቀባበል አድርውለታል። የተቀላቀሉት የሰራዊት አባላት በስም ዝርዝርና የስራ ሀላፊነት 1ኛ.በአምላኩ አዳነ አለም 42ኛ ክፍለጦር 4ኛ ሬጂመንት ጓድ መሪ 2ኛ.መለሰ በላይ ዘውዱ 58ኛ ክፍለጦር 6ኛ ሬጅመንት የሎጅስቲክ መምሪያ ሀላፊ 3ኛ.ይበልጣል ውብ አለም የ48ኛ ክፍለጦር 6ኛ ሬጅመንት ጓድ መሪ ናቸው። 4ኛ. ገለታው ሞላልኝ --------- አጠቃላይ ገቢ የተደረገ 5 ክላሽን ኮፍ መሳሪያና 780 የክላሽ ጥይት ተተኳሽ አንድሁም 12 ኤፍዋን ቦንብ  መሆኑን የክፍለ ጦሩ እርድናንስ ገልጿል። ከዚህ በፊት እንደተገለፀው የጨፍጫፊውና የእብሪተኛው አገዛዝ ወታደሮች እንደተናገሩት ከሆነ በአሁኑ ሰዓት በሰራዊቱ መካከል የእርስ በእርስ አለመተማመንና ከፍተኛ የሆነ መጠራጠር ፣ ዘር ተኮር ግድያ እንዲሁም አድሏዊ አሰራር  የውጊያ ሞራልና ወትሮ ዝግጁነት አለመኖሩን ገልፀዋል። በኢትዮጵያ የአገር መከላከያ ሰራዊት መስሪያ ቤት በፊት ያልነበረና ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየተለመደ የመጣው ሰዎች ብቃት ሳይኖራቸው በኮታ ምደባ የስርዓቱ ሰዎች በመሆናቸው ብቻ ማለትም የኦህዴድ የበላይነት በግልፅ የሚታይበትና ሌላው የሰራዊት አባላት የሀገር ባለቤት የማይሆንበት መንገድ እየሰፋ በመምጣቱ ደስተኛ አለመሆናቸውን ተናግረዋል። በመጨረሻም የአገዛዙ የ58ኛ፣የ48ኛና የ42ኛ ክፍለጦር  የሰራዊት አባላቱ አያይዘው በገለፁት መሰረት በሀገሪቱ ተከታታይ የእርስ በእርስ ጦርነትና የአማራ ህዝብ የሚያሳየን ጥላቻና መሰላቸት እንዲሁም ህዝቡ የፖለቲካ፣ የህገ መንግስት፣የዴሞክራሲ፣ የእኩልነትና ነፃነት ግልፅ የሆነ ጥያቄ እንዳለውና ጦርነቱ ህዝባዊ ድጋፍ እንዳለው  በማወቃችን  የሚከፈለው ህይወት  ከንቱ  መሰዋትነት መሆኑን በመረዳት የበደልነውን የአማራ ህዝብ ይቅርታ በመጠየቅ ወደ ሀገራችን መግባት እንፈልጋለን ሲሉ ሀሳባቸውን ገልፀዋል ሲል የ102ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃዉን አድርሷል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!! አፋብን ወሎ ቤተ- አማራ ምኒልክ ዕዝ  ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!! ሰኔ 12/2018ዓ.ም