ar
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

الذهاب إلى القناة على Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

إظهار المزيد
2 938
المشتركون
+1424 ساعات
+3877 أيام
+38530 أيام
أرشيف المشاركات
ጋንታ መሪውን ጨምሮ የአገዛዙ ወታደሮች ከነ ሙሉ ትጥቃቸው ምኒልክ ዕዝን ተቀላቀሉ!! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ አሳምነው ኮር በሚንቀሳቀስባቸው ቀጠናዎች ከውጊያ ጎንለጎን የጠላትን ሃይል ስቦ ማስከዳቱን አጠናክሮ ቀጥሏል ። መነሻቸውን ሰሜን ወሎ ዞን ላስታ ወረዳ ሹምሽሃ/ ላሊበላ አየር ማረፊያ/ከተከማቸው  የአፓርታይዱ አብይ አህመድ እና የምርኮኛው ብርሃኑ ጁላ ስብስብ ተስፋ ቆራጩ ወታደር በመነሳት 3 መሰረታዊ ወታደሮች አምስት ጥቁር ክላሽ ፣6 ኤፍዋን የእጅ ቦንብ፣ 3 የደረት ትጥቅ እና 840 የክላሽ ተተኳሽ በመያዝ 303ኛ  አሳምነው ኮር 19ኛ(እሸት )ክፍለጦርን ተቀላቅለዋል። ጋንታ መሪው የራሱን አንድ ጥቁር ክላሽ እና ዋርድያ ላይ የነበሩትን የሁለት ጓዶቹን ጥቁር ክላሽ ጨምሮ አጠቃላይ በድምሩ 3 ጥቁር ክላሽ በመያዝ ወደ ፋኖ በመግባት ትልቅ አርአያነትን ለሌሎች ቀሪ የአገዛዙ ወታደሮች አሳይቷል ሲል የ303ኛ  አሳምነው ኮር  ህዝብ ግንኙነት መረጃውን አድርሷል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!! አፋብን ወሎ ቤተ- አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ!   ሐምሌ17/11/2018ዓ'ም

አዲስና ወቅታዊ መረጃዎችን ያገኙበታል ይህንን ፊስቡክ ይወዳጁት!! https://www.facebook.com/share/19X1Yenzkf/

አማራ ሆኖ መወለድ የፈጣሪ ትልቅ ስጦታ ነበር... ዛሬ ግን ያ ክብር በገዛ ደማችን ሲረክስ ማየት ነፍስን በቁም የሚያቃጥል ገሃነም ሆኗል። ​ወዮልን! ትናንት የትኛውም አስፈሪ የውጭ ጠላት ያላንበረከ
+4
አማራ ሆኖ መወለድ የፈጣሪ ትልቅ ስጦታ ነበር... ዛሬ ግን ያ ክብር በገዛ ደማችን ሲረክስ ማየት ነፍስን በቁም የሚያቃጥል ገሃነም ሆኗል። ​ወዮልን! ትናንት የትኛውም አስፈሪ የውጭ ጠላት ያላንበረከከውን፣ በነፃነት አየር ላይ በአንበሳነት የተራመደውን ጀግና... ዛሬ በገዛ ሰፈሩ፣ በጎጥና በበረት አጥር በተከለሉ የጅል ወንድሞቹ ጥቁር ሴራ ተሸጦ ሲታረድ ማየት እንዴት ያለ ድቅድቅ ጨለማ ነው? ​አብሮት እንጀራ ተካፍሎ የበላ፣ ወንድሜ ብሎ ህይወቱን ያመነው ሰው... መረጃ እየሸጠ ጀግናውን ለሞት አሳልፎ ሲሰጥ ማየት የህሊና መቃብር ነው! የጀግኖቻችን ደም በከንቱ ፈሶ ምድር ስትጠጣ፣ ገዳይም በአንድ ደም ሆነው ሲያልቁ... ሰማዩም ቢሆን የሀዘን ካባ ለብሶ እያለቀሰ ነው። ​እህ... ገብርዬ! ምነው ዛሬ ከሞት ጉድጓድ ብቅ ብለህ ባየንኸ? አይንህ ያያት የነበረችው የጀግኖች ምድር በከሃዲዎች ተወርሳ፣ ያንተ የታማኝነት አጥንት ተረግጦ፣ ወንድም የጎጥ አጋንንት ተሳፍሮበት ወንድሙን ሲያስታርድ ባላየኸው ነበር! . የአንተን ደም የማይመልስ አማራ አይወለድም!! ወንድሜ ነፍስህ በሰላም ትርፍ!!

#ሰበር_ዜና‼️ የጀብደኛዉ ምኒልክ ዕዝ የአገዛዙን ድሮን በማውደም አንፀባራቂ ድል ተቀዳጀ‼️ የምኒልክ ዕዝ #የድሮን_ኢንተርሰፕተር_ምድብተኛ አርበኞች በወገን ኃይል ላይ ጥቃት የመፈፀም ተልዕኮ ይዞ ሲንቀሳቀስ የነበረ የጠላት ተዋጊ ድሮንን አየር ላይ እንዳለ ከመቆጣጠሪያ ማዕከሉ ጋር የሚያገናኘውን ሲግናል በመጥለፍ ድሮኑ እንዲከሰከስ በማድረግ የሕልውና ትግሉን ወደ አዲስ ምዕራፍ ያሸጋገረ አኩሪ ድል ተቀዳጅተዋል። በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ የቴክኖሎጂ ምህንድስና ክፍል አቋቁሞ በሙከራ ደረጃ ወደ ስራ በማስገባት የአማራን የህልውና ትግል ወደ አዲስና የላቀ የቴክኖሎጂ ምዕራፍ ለማሸጋገር አበክሮ እየሰራ ይገኛል። የጦር ጠበብቶችንና ስትራቴጂስቶችን፣ ከፍተኛ የምህንድስና ተመራማሪዎችን አቅፎ በያዘው የቴክኖሎጂ ምህንድስና ክፍሉ፡ የጠላት ድሮን እንቅስቃሴዎችን በማጥናትና ኢንተርሰፕት በማድረግ ከማውደም ጀምሮ አቅጣጫ በማሳት ኦፕሬሽኖችን እስከማምከን የደረሰ እርምጃዎችን በመውሰድ የጠላትን የአየር የበላይነት መገዳደር የሚያስችሉ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል። ትናንት ሐምሌ 15/2018 ዓ/ም በወሎ ቤተ አማራ ቀጠና ምዕራብ ወረዳዎች በሕዝብ ላይ ጥቃት የመፈፀም ተልዕኮ ይዞ በእንቅስቃሴ የነበረን የጠላት ተዋጊ ድሮንን የዕዙ የቴክኖሎጂ ምህንድስና ክፍል የኢንተርሰፕተር ምድብተኛ አርበኞች፡ ተዋጊ ድሮኑን ከመቆጣጠሪያ ማዕከሉ የሚያገናኘውን የሎንግ ሬንጅ ሲግናል በመጥለፍና የሲግናል ማስተላለፊያ የኤሌክትሮኒክስ ሰሌዳዎችን ከቁጥጥር ውጭ በማድረግ ድሮኑ እንዲከሰከስ ማድረግ ችለዋል። የዕዙ ኢንተርሰፕተር ምድብተኛ አርበኞች ተዋጊ ድሮኑን አየር ላይ እንዳለ ነው ከማዕከሉ ጋር ያለውን ግንኙነት ያቋረጡበት። በዚህም ድሮኑ በአንድ ቦታ ላይ ለደቂቃዎች ከተሽከረከረ በኋላ የሚቆጣጠረውና የሚያዘው አካል በማጣቱ ሊከሰከስ ችሏል። ድሮኑ ከተከሰከሰበት አከባቢ በቅርብ ርቀት የነበረው የጠላት ጦር ድሮኑ በተከሰከሰበት ቅፅበት በቦታው በመድረስ ዋና ዋና ቅሪተ አካሉን በባለሦስት እግር ባጃጅ ተሽከርካሪ እና በባለ ሁለት እግር ሞተር ተሽከርካሪ ጭኖ የወሰደ ሲሆን በምስሉ የምትመለከቱን የጠላት ወታደሮች ጭነው ከወሰዱት የተረፈ የድሮኑ ፍርስራሽ አካል ነው። እነዚኸው የዕዙ ምህንድስና ክፍል የኢንተርሰፕተር ምድብተኛ አርበኞች፡ ከሳምንታት በፊት በራያ ግንባር በወገን ጦር ላይ ጥቃት የመፈፀም ተልዕኮ ይዞ በእንቅስቃሴ የነበረን የጠላት አጥፍቶ ጠፊ ድሮንን ከማዕከሉ ጋር ያለውን ግንኙነት እንዲቋረጥ በማድረግና የዕዝ ሰንሰለቱን በመበጠስ ከተራራ ጋር ተጋጭቶ እንዲከሰከስ አድርገው ድል መቀዳጀት ችለዋል። የጠላትን የትኩረት አቅጣጫ ለማሳትና የወገን ጦርን ተገማችነት ለማራቅ ሲባል ጥቃቱ በተፈፀመበት እለት መረጃው እንዳይወጣ ተደርጎ በሰነበተው በዚህ ኦፕሬሽን፡ ዋና ማዕከሉን  በራያ ቆቦ ወረዳ ቆቦ ከተማ ሆርማት ካምፕ አድርጎ ጎለሻና አከባቢው ላይ ጥቃት ለመፈፀም በእንቅስቃሴ ላይ የነበረውን የጠላት ካሚካዚ ድሮን፡ አየር ላይ እንዳለ ሲግናሉን በመጥለፍ ከማዕከል ጋር የነበረውን ግንኙነት ካቋረጡ በኋላ ነው እንዲከሰከስ ያደረጉት የምህንድስና ክፍሉ አርበኞች። በዚህ ስፍራ ተመትቶ የወደቀው የድሮኑ ቅሪተ-አካል ወደ ምህንድስና ክፍሉ የላብራቶሪ ስቶር ተወስዶ ምርመራ እየተካሄደበት ሲሆን፡ ለተለያዩ የቁጥጥር አገልግሎቶች የሚውሉ የኤሌክትሪክ መቀያየሪያ መሣሪያዎች በምርኮነት ተይዘዋል። በቅርቡ ተቋቁሞ በሙከራ ደረጃ ወደ ስራ የገባው የዕዙ ምህንድስና ክፍል በታጠቃቸው አዳዲስ የቴክኖሎጂ ግኝቶች የጠላትን ድሮን አቅጣጫ ከማሳትና ኢንተርሰፕት ከማድረግ ጀምሮ ከፍተኛ ጥቃት በመፈፀም የሕልውና ትግሉን ወደ ላቀ የቴክኖሎጂ ምዕራፍ ከማሸጋገሩ ባለፈ፡ የጠላትን የአየር ላይ እንቅስቃሴ በመገደብ ፋኖ #በምድር_ጦር እየተቀዳጀ የሚገኘውን ድል #በአየር_ኃይል ዘርፉም ለመድገም የሚደረገውን ጥረት በእጅጉ እንደሚያግዝ ታምኖበታል። 16/11/2018 ዓ.ም

ከአፋብን ወሎ ቤተአማራ ምኒልክ ዕዝ የተሰጠ የሀዘን መግለጫ የብልፅግናው አገዛዝ ሕዝብን፣ ታሪክን እና ሃይማኖትን መሠረት ያደረገ አደገኛና ፀረ-ሕዝብ አካሄዱን አጠናክሮ ቀጥሏል። ላለፉት ሶስት ዓመታት በአማራው ሕዝብ ላይ በከፈተው አጥፊ ጦርነትና ከውጭ በሚያስገባቸው ጅምላ ጨራሽ መሣሪያዎች አማካኝነት በንጹሐን ላይ እያደረሰ ያለው እልቂት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል። በዚህ ወቅት አለማቀፉ ማህበረሰብን ለማደናገር "የምክክር ጉባኤ" በሚል አዲስ አበባ ላይ ፖለቲካዊ ድራማ እየሰራ ያለው አረመኔው የብልፅግና አገዛዝ  ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓ.ም በደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት በሚገኘው የዓባይ ቅድስት አርሴማ ገዳም መነኮሳት ላይ በፈጸመዉ አሰቃቂና ጭካኔ የተሞላበት የድሮን ጥቃት በርካታ የገዳሙ መነኮሳት ሕይወት አልፏል፣ በርካታ መነኮሳት በከባድ ሁኔታ ቆስለዋል። ገዳሙም በድሮን ጥቃቱ ከፍተኛ ዉድመት ደርሶበታል። "ዓለም በቃኝ" ብለው በጸሎት ላይ ያሉ ገዳማውያንን ሳይቀር ማጥቃት፣ በሕዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለው ስልታዊ የዘር ማጥፋት ወንጀል ማሳያ ነው። ቅዱሳን መካናትንና መናንያንን ኢላማ ያደረገውን ይህንን ዘግናኝና አረመኔያዊ ድርጊት በጽኑ እናወግዛለን። በጥቃቱ ሕይወታቸውን ላጡ ገዳማውያን የተሰማንን ጥልቅ ሐዘን እየገለጽን፣ ለቆሰሉት ፈጣን ምሕረትን እንመኛለን። ንጹሐን ዜጎችንና የሃይማኖት ተቋማትን ከዚህ ጥፋት መታደግና አገዛዙን መታገል የሰው ልጆች ሁሉ ሰብአዊ ግዴታ ነው። ስለሆነም ይህንን ዘር አጥፊ እና አገር አፍራሽ ሥርዓት ለመገርሰስ መላው የአማራ እና የኢትዮጵያ ሕዝብ ከትግሉ ጎን እንዲቆም፣ የሃይማኖት አባቶች ሥርዓቱንና ድርጊቱን በግልጽ እንዲያወግዙ ታሪካዊ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። በመጨረሻም ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተቋማት በአገዛዙ እየተፈጸመ ያለውን የዘር ማጥፋት ወንጀል በጽኑ እንዲያወግዙ፣ የአለማቀፉ ማህበረሰብ የብልጽግናዉ አገዛዝ በአማራ ላይ እየደረሰ ያለዉን ሰብአዊ ጭፍጨፋና የዘር ማጥፋት ድርጊት ትኩረት እንዲሰጠዉ እና ገለልተኛ ምርመራ በማድረግ አስፈላጊው ዓለም አቀፋዊ እርምጃ እንዲወሰድ በጥብቅ እንጠይቃለን።                   ህልዉናችን በተባበረ ክንዳችን!          ሀምሌ 16 ቀን 2018 ዓ.ም           ወሎ ቤተአማራ፣ አማራ፣ ኢትዮጵያ

ሶስተኛ ቀኑን የያዘው አውደ ውጊያ  እስከ ዛሬ ሐምሌ 16ቀን2018ዓ.ም ባደረጉት ከባድ ተጋድሎ በጥላት ጥምር ጦር ላይ አንፀባራቂ ድል ተቀዳጀ። ላለፉት ሁለት ቀን ሽንፈቱን የተከናነበውና ለወራቶች መሽጎባቸው የነበሩትን ቦታዎች ሙትና ቁስለኛውን አዝረክርኮ መሔዱና የፈሪ ዱላውን ንፁኋን መንደሮች ላይ መደብደቡን መግለፃቺን የሚታወስ ነው። የደረሰበትን ሽፈትና ምት መቋቋም አቅቶት የነበረዉ የአገዛዙ ጥምር ጦር ዘሬ ላይ ከየቦታው ኃይል በማሰባሰብ ማለትም ከነቀምት፣ከኡኬ፣ከአንገር ጉትንና፣ከትሉጋና ከተሞች በመሰብሰብ ጥቃት ለመሰንዘር የመጣ ኃይል ላይ እደተለመደው የአንሻ ሰይድ ዕዝ የአምሃራ የቁርጥ ቀን ልጆቺ በመጣበት ቋንቋ እያናገሩት ይገኛሉ። ሐምሌ 16/2018ዓ.ም ዛሬ ከጠዋቱ 12:00ሰዓት መነሻውን በምስራቅ ወለጋ ዞን የዞኑ መቀመጫ በሆነቺው ነቀምት ከተማና በጉቶ ጊዳ ወረዳ ከኡኬ ከተማ በመነሳት ወደ ለጎና መርካቶ የተንቀሳቀሰ ሲሆን እድሁም በተጨማሪም በመስራቅ ወለጋ ዞን ጊዳ አያና ወረዳ ከአንገር ጉትን ከተማና በሆሩ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አቤ ደንጎሮ ወረዳ በቱሉጋና እና በመንደር 18 በተለያዩ ቦታዎች ላይ በመግባት በታንክ፣በመድፍ፣በዙ23 እና በሞርተር ቢደበድብም የአንሻ ሰይድ አናብስቶች ጌጤ ግርማ መብረቅ ክ/ጦር፣አንገር ጉትን ክ/ጦር፣ታፈረ አለሙ ሳተናው ክ/ጦርና አበጀ ጥበቡ ነበልባል ክ/ጦር በጥላት ምሺግና አስክሬን ላይ እየተረማመዱ የጥይት ነዶ ሲያወርዱበት ውለዋል።በመጨረሻም ያሰበውን ሳያሳካ ባለበትእዲቆም ተገዷል። ግፍ የወለደን: ግፈኞቺን የምቀጣ የአንሻ ሰይድ ወድሞች ነን!!! አፋብን ወለጋ/ቢዛሞ አንሻ ሰይድ ዕዝ ህ/ግንኙነት መምሪያ

በምዕራብ ጎንደርና በመተማ ወረዳዎች የአገዛዙ የሚሊሻና የፀረ-ሽምቅ መዋቅር መፍረሱና በልዩ ኦፕሬሽን የአገዛዙ አዛዦች መደመሰሳቸው ተገለጸ! (ሐምሌ 16 ቀን 2018 ዓ.ም በአፋብን በላይ ዘለቀ ዕዝ፣ መይሣው ካሳ (2ኛ) ኮር፣ ፊታውራሪ ገበየሁ ክፍለጦር በምዕራብ ጎንደር አዳኝ አገር ጫቆ ወረዳ ነጋዴ ባህር እና በመተማ ወረዳ ኩመር አውላላ ባካሄደው ልዩ ወታደራዊና የማኅበረሰብ ውይይት የአገዛዙ የሚሊሻና የፀረ-ሽምቅ መዋቅር ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ መፍረሱ ታወቀ። የኮሩ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ይፋ ባደረገው መረጃ መሠረት፣ አገዛዙ በአካባቢው የሚገኙ የሕዝብ ክፍሎችን "አማራና ቅማንት" በማለት ለዘመናት ሲያጋጭና ለጥፋት ዓላማው ሲጠቀምበት የቆየውን ሴራ ፊታውራሪ ገበየሁ ክፍለጦር ባካሄደው የማኅበረሰብ ውይይትና ከታጠቁ ኃይሎች ጋር ባደረገው ስምምነት ማክሸፍ ተችሏል። በዚህም ሳቢያ አገዛዙ መዋቅሩን ለሌላ ግጭት ለማዘጋጀት ያደርገው የነበረው ጥረት ከንቱ ሆኖ የቀረ ሲሆን፣ ከ50 በላይ የሚሊሻና የፀረ-ሽምቅ አባላት ከነሙሉ ትጥቃቸው በልዩ አቀባበል መይሣው ካሳ ኮርን የተቀላቀሉ ሲሆን፣ በርካቶች ደግሞ መሣሪያቸውን አስቀምጠው በሰላም ወደየቤታቸው ተመልሰው ከማኅበረሰቡ ጋር ተቀላቅለዋል። በሌላ በኩል ትናንት ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓ.ም በመተማ ወረዳ ኩመር አውላላ አካባቢ የፊታውራሪ ገበየሁ ክፍለጦር 1ኛ ሬጅመንት በተሳካ ሁኔታ ባከናወነው ልዩ ኦፕሬሽን የአገዛዙን ሰራዊት ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል። በዚህም መሠረት አንድ የአገዛዙ ሰራዊት የሻምበል መሪ እና አንድ የሐምሳ አለቃ ማዕረግ ያለው የአድማ ብተና አባል የተደመሰሱ ሲሆን፣ ሁለት የአድማ ብተና አባላት ደግሞ ከነሙሉ ትጥቃቸው በቁጥጥር ሥር ውለው ከቦታው መወሰዳቸውን የመይሣው ካሳ (2ኛ) ኮር ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ አረጋግጧል።

ጠላት ደጋ ዳሞትን መቆጣጠር የጎጃምን ቀጠና የፉኖ ትጥቅ ትግል ቅስም መስበር ነው ብሎ ያምናል። ጁላና ሙሀመድ ፍላጎታቸው ቢሳካ እንደ ጮቄ ያሉ 09ወረዳ የሚያዋስኑ የጎጃምን ከፍታማ ቦታዎች ተቆጣጥሬ ከላይ ወደታች መልሶ ማጥቃት መክፈት፣ በፉኖ በኩል ወደከተማ የማጥቃት እንቅስቃሴ እንዳይኖር ቀድሞ ውጊያ መክፈት፣ በቀጣይም ቆላማ ቦታዎችን መውረር እቅዱ አድርጎ እየተንቀሳቀሰ ነው። ግን ይሆናል ወይ?! ፤ ከዕለታት በአንድ ቀን ከገጠመኞቼ መሀከል👇🏿 አንድ የዳሞት ገበሬ በውጊያ መሀል ከኋላ ዘግይቶ ኑሮ ከፊት የቀደሙ ጓደኞቹ አምስትም ስድስትም ክላሽ ማርከው ሲመለሱ ይመለከታል። ከኋላው ዞር ብሎ ሲመለከት ደግሞ ዝናቡ ልንገረው ከኋላ ተቀምጦ የተማረኩ የቡድን መሳሪያዎችን ሲቀበል ይመለከታል። ንግግር ተጀመረ፦ ገበሬው፦ እኔ የምለው አለቃ ዝናቡ… ዝናቡ፦ አቤት ገበሬው፦ ሁሉም ጠላት ተገድሏል፣ ተማርኳል። አብይ መቼ ነው ሌላ መከላከያ ወደ ፈረስ ቤት የሚልክ?! ዝናቡ፦ ለምን? ደጋ ዳሞት እንዲያዝ ትፈልጋለህ ማለት ነው? ገበሬው፦ ኤዲያ ሀብታምና ደሀ አድርገውን ሄዱ ብየ ነው እንጅ፤ እነ አዋ እከሌ ይሄንን ያክል ክላሽ ማርከው መሄዳቸው ሲሰማ ምሽቴስ ከአልጋው ላይ አብራኝ አደረች ብለህ ነው?!። ፤ ጦርነትን የሚፈሩ ህዝቦች የራሳቸው የነፃነት ታሪክ የላቸውም እንዲሉ ሀገር ወዳድ ፀሀፊያን አብይ ይሄንን ስነልቦና እሰብራለሁ ብሎ ሲኳትን አራተኛ ክረምት ላይ ደርሰናል። ግን የት ላይ ደረስን?! ፤ በመሀመድ ተሰማ ቀጥታ ትዕዛዝ ቢኤም፣ ጀኔራል መድፍ፣ ጄት፣ ድሮን፣ ሞርተር የታጠቁ የጠላት ሜካናይዝድ ሀይል በየዓይነቱ የርቀት ሰሌዳቸውን ወድረው በመጥመድ የፋኖ ሀይል ይዞታ ናቸው ወደሚሉት ቀጠና ዛሬም ድረስ ተኩስን እያዘነቡ ነው። የጠላት እግረኛ ሀይል ከገባው ውስጥ የረገፈው ይበልጣል። የተማረከበትን ሀይል ለማስለቀቅ ጫና እፈጥራለሁ የሚለው የጁላ ጦር ሀይሉ ለከፉ እልቂት ተዳርጓል። በደጋ ዳሞት ብቻ በአራት ክረምት ውስጥ ከ13 ጊዜ በላይ ሙሉ የድምሰሳ ታሪክን የተከናነበው የጠላት ሀይል ፈረስ ቤት መግባት ያስፈነጠዘው ይመስላል። ፤ ይህን ወራሪ ሀይል አዛብተን በመበተን፣ ደምስሰን በመማረክ ተግፎ የመጣ ዓላማ-አልባ መሆኑን እናሳየዋለን። እናደርገዋለንም። ፤ በሌላ ጎኑ ደግሞ ይህ የጠላት ሀይል ፈንጠዝያ፣ የዘነቡብን ሮኬቶች፣ የተወነጨፉ ቅንቡላዎች ሁሉ “ፉኖ አሁን ለደረሰበት አስተማማኝ ቁመና ከበቂ በላይ ማሳያ” ናቸው። እየለቃቀምነው የተባለው ስውሩ ጦር፣ እጅ ሰጡን ተብሎ የደነቆርነበት መንፈስ የሆነ ጦር “በምን ዓይነት ቁመና ላይ ለመገኘቱ” ሰሞንኛ የጠላት ዘመቻ ምስክር ናቸው። በክላሽ ያልተበተነው ኢመደበኛ ሀይል በቢኤም የማይፈርስ፣ በመድፍ የማይበረግግ፣ በድሮን የማይደናበር አቅምን ገንብቷል። የሚጠመዱበትን ርቀት፣ የፍንዳታ ወሰንና ድምፃቸውን የተረዳው ሀይላችን በቅርብ እነዚህን ከባባድ መሳሪያዎች ማርኮ ይታጠቃቸዋል። Mark My Words. ፤ የ insurgence ላይ በርካታ ፅናትን ያደረጉ የዘርፉ ምሁራን ለፋሽሽታዊ መሪዎች አንድ ጠንካራ ሀሳብን ይመክራሉ፦ “ከተመሰረተበት ጀምሮ የቆይታ ጊዜው ስድስት ወር ያለፈን የታጠቀን ድርጅት በሀይል አማራጭ ማጥፋት ስለማይቻል ፖለቲካዊ መፍትሄ እንዲመርጡ”ይመክራሉ። በዚህ ረገድ አብይ አህመድና አገዛዙ በወታደራዊ ሀይል የሚያንበረክኩት የአማራ ህዝብና ትግል እንደማይኖር ተዘግቶ ያደረ መራር ሀቅን የያዘ ማኅደር ነው። ፤ አፉብን የተበተነውን የአማራ ትጥቅ ትግል ሽክፍ አድርጎ በመጠርነፍ አንድነቱን አስጠብቆ እየተጓዘ ነው። ይህ አካሄድ ያስፈራቸው የጠላት ክንፍ ሁሉ አንድነቱ ያልጠበቀ ወይም የላላ ድርጅታዊ መስተጋብር እንዲኖር መስራታቸው የሚጠበቅ ነው። በተጨባጭ የጠላት አሰላለፍ አካል የሆኑ ግን ደግሞ ከአማራ ግዛት ውስጥ የአንዱ ክፍለ ሀገር ተቆርቋሪ በመምሰል መርዝ የሚረጩት ቢችሉ ትግሉን በአንድ ቀን አዳር የመበተን ፍላጎት ነበራቸው። ይህም ደግሞ የማይሳካው የዚህ ትግል ድል ያስገኘው ሌላኛው መራር ሀቅ ነው። ትግሉ በድል ብስራት እስኪጠናቀቅ ድረስ እኚህ መሰል አካላት ማወናበዳቸው ይቀጥላል። ፤ ባልተያያዘ ርዕስ አሲምባ በሚኖራቸው ቤዝ ጉዳይ ላይ ከአልጀሪያም ይሁን አዲስአበባ ከምትገኝ አንዲት ጋራጅ ጀርባ በሚደረግ ክርክር መስማማት ያቃተው ኢህአፓ አሁን መሬት ላይ ካለው የፉኖ ትግል ጋር ምንም ዓይነት የመስመር አንድነት የለውም። ከአሁን በፊት እንደተናገርኩት የምንጓዝበት ፎርሙላ ለጠላት ፍቺ ትርጓሜ የራቀ ፍፁማዊ መስመር የተከተለ ነው። በ “ሸ” እና “ቸ” የተፋጀው ትውልድና አስተምህሮው ከዚህ የለም። ዱር ቤቱን ለማድረግ ያወላወለ ሀይልም ከዚህ የለም። በኛ ትውልድና በያ ትውልድ መካከል የአስተሳሰብ፣ ሰው ሀይል፣ መሳሪያና ርዕዮት በጣም ሩቅ የሆነ ልዩነት አለ። ከምንም በላይ ደግሞ “ሞቱ ሲጠበቅ ከመቃብር ፈንቅሎ የወጣው የአማራ ብሄርተኝነት አራማጆች” ነን። ፤ እኛ ያልፈቀድንለት ስርዓት እንዳይፀና አድርገን ተቅበዝባዥ እንዳደረግነው ሁሉ “የክብርና ኩራት ታሪክን እየፃፍን፣ ከሙሉ ክብርና ማንነታችን ጋር የተዋሀደ ሀገርና የራስ የሆነ ሀገረ መንግስት” እንገነባለን። ማንችሎት የዝናቡ ወንድም መከታዉ✌️

የራንቦ ክፍለ ጦር ልዩ የወታደራዊና ፖለቲካዊ አቅም ግንባታ ተሃድሶ መርሃ ግብር አካሔደ!! ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም የአፋበን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የአፄ አምደ ፅዮን ኮር አካል የሆነው የራንቦ ክፍለ ጦር የተሳካ ልዩ የፖለቲካና ወታደራዊ አቅም ግንባታ ስልጠና (ተሃድሶ) ማድረጉን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል አስታወቀ። ከሐምሌ 01-16/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት የድርጅትና የዕዝ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ስልጠናው ሲጠናቀቅ በተጋባዥነት የተገኙት የአፋብን ተ/ምክትል ሊቀመንበር አርበኛ መከታው ማሞ በተገኙበት ተጠናቋል። የዚህ ልዩ የተሃድሶ መርሃ ግብር ዋና ዓላማዎች፦ ➧ የዓላማ አንድነት መፍጠር፦ ስለ ትግሉ አሁናዊ ሁኔታ፣ ስለ ማህበረሰብ አያያዝ እና ስለ ውስጣዊ አንድነት ➧ ስለ ጠላት አሰላለፍና ቁመና ➧ በወታደራዊ ታክቲኮች ➧በፖለቲካ ግንባታ በነዚሕ አንኳር ነጥቦች ላይ ስልጠናውን አጠናቋል። በስልጠናው በማጠቃለያ መርሀግብር ላይ የተጋበዙት የአፋብን ተ/ምክትል ሊቀመንበር አርበኛ መከታው ማሞ " ከግል ቤታችን ወጥተን የጋራ ቤታችን በሆነው ድርጅት መሠባሠባችን ለአማራ ታሪካዊ" ያሠኘዋል ሲሉ ገልፀዋል። የመድረኩ ተሳታፊ የሆኑት የኮርና የክፍለ ጦሩ አመራሮችና አባላት በሰጡት አስተያየት፤ መድረኩ ቀደም ሲል የነበሩ በርካታ ብዥታዎችን ያጠራና የተናጠል ትግሉን ወደ ህብረትና ብቃት አረጋጋጭ ሊሆን እደሚችል ገልጸዋል። ለህልውና ትግሉ የሚከፈለውን መስዋዕትነት በሙሉ ልብ ለመወጣትና ድርጅቱ ካስቀመጠው ግብ ላይ ለመድረስ ቁርጠኛ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። "ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

16/11/2018 ዓ.ም ከሲያደብርና ዋዩ ወረዳ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዘርያዕቆብ ኮር በነጎድጓድ ክ/ጦር ግንቦት ወር ላይ በልዩ ኦፕሬሽን የተያዙት የኦሮሞ ብሔር ተወላጅ የሆነው የሚሊሻ አመራር አቶ ነጋሽ ተስፋዬ የሰጡት ቃለ-ምልልስ :- =================== -የፋኖ አያያዝ በጎና፣ለተቋምሕግ እና ሰብአዊነት የተገዛ ነው። -ፋኖ አላማ ያለው ሀይል እንጂ ከዬትኛውም ሕዝብ ጋር ጥል የለውም። -ጠላቱ የብልፅግና አገዛዝ ብቻ መሆኑን አይቻለሁ። የሚሉና ለአድማ ብተና እና ሚሊሻ ያቀረቡት ጥሪ :-

አራት የአገዛዙ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ከነ ሙሉ ትጥቃቸው የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦርን ተቀላቀሉ! ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም የብልፅግናው ስርዓት ግብዓተ-መሬቱ መቃረቡን ተከትሎ ከመቸውም ጊዜ በላይ ጦ
+4
አራት የአገዛዙ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ከነ ሙሉ ትጥቃቸው የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦርን ተቀላቀሉ! ሐምሌ 16/2018 ዓ.ም የብልፅግናው ስርዓት ግብዓተ-መሬቱ መቃረቡን ተከትሎ ከመቸውም ጊዜ በላይ ጦረኛው አገዛዝ የሚመካበት ወታደሮች አነ ሙሉ ትጥቃቸው ንቅናቄውን እየተቀላቀሉ ሲሆን ትላንት ረብዕ አራት የመከላከያ ሰራዊት አባላት ከነ ሙሉ ትጥቃቸው የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዓምደ ጽዮን ኮር የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦርን ከነ ሙሉ ትጥቃቸው መቀላቀላቸውን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል በምስል አስደግፎ ለዕዙ የዜና ክፍል በላከው የግንባር መረጃ አስታውቋል። ወደ ፋኖ ከተቀላቀሉት ውስጥ 3ቱ የ15ኛ ክፍለ ጦር አባላት ሲሆኑ አንዱ የ101ኛ አየር ወለድ ክፍለ ጦር አባል መሆኑን ኮሩ አክሎ ገልጿል። "ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

🎯 ፍትሐዊው ባለ ሚዛን! ​(አዲሱ ደረበ) ​የአማራ ሕዝብ ሁሌም ቢሆን ፍትሐዊ፣ ባለሚዛንና ሥርዓት አዋቂ ሕዝብ ነው። ለመንግሥት፣ ለሕግና ለመንግሥታዊ አሠራር ያለው ቀናኢነትና አክብሮት ለዘመናት የጸና ቢሆንም፣ ይህ በጎ እሴቱ ግን ግፍና ጭቆና በእርሱና በወገኖቹ ላይ ሲጫኑ እጁን አጣጥፎ እንዲቀመጥ አድርጎት አያውቅም። ዛሬማ ይልቁን በአማራዊ ማንነቱ ላይ የህልውና አደጋና የዘር ማጥፋት ጥቃት ተደቅኖበት እንዴት ዝም ይላል? ወትሮም ቢሆን ኢ-ፍትሐዊነትንና ጥቃትን እምቢ ለማለትና ለመፋለም ቦዝኖ የሚያውቅ ሕዝብ አይደለም! ​እውነቱ አሁን እንደሚታየው ነው፤ እንኳን አሁን መላው አማራ በየአቅጣጫው አለሁ ብሎ በአንድነት ተሰልፎ ይቅርና፣ ወትሮም ቢሆን በየትኛውም አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ በአጥቢያው ተደራጅቶ ግፈኞችንና ወራሪዎችን ለመታገል አንዲት ሰከንድ የማያመነታ ብርቱና ኩሩ ሕዝብ ነው። የታሪክ መዝገብ ለዚህ ሕያው ምስክር ነው፤ የፋሽስት ጣሊያንን እብሪትና ወረራ፤ ዘመናዊ የጦር መሣሪያና የመርዝ ጋዝ ሳይበግረው ዱር ቤቴ ብሎ ተፋልሟቸዋል። በቀደሙት ስርአቶች ሁሉ የመሬት ግብር ጭቆና በበረታበት ወቅትም፣ የማይከሰሱና የማይጠየቁ የሚመስሉትን መሳፍንቶች አልገብርም ብሎ በመሬት ግብር እምቢተኝነት አንቀጥቅጧቸዋል። በአህጉር ደረጃ ገናና ስምና ግዙፍ የጦር ግንባር የነበረውን የደርግን መራር ግፍና ቀይ ሽብር የመታገልና የመቋቋም ታሪካዊ ውርስ ያለው ነው፤ ለዚህም የጀግኖች ምድር አቸፈር፣ በለሳና ሰቆጣ ሕያው ምስክሮች ናቸው። እንዲሁም የወያኔ ኢሕአዴግን ዘረኛ አገዛዝ ከዘረኝነት፣ ከጠባብነትና ከመድሎ እንዲወጣ ያለ ምንም ፍርሃትና ተሸማቃቂነት በአደባባይ የተጋፈጠውና የታገለው ይኸው ሕዝብ ነው። ​ዛሬማ መደራጀት፣ መቀራረብና በጋራ የአማራነት ጉዳይ ላይ በጋራ መሰለፍን ዘመኑም፣ የታሪክ አጋጣሚውም ፈቅዶለታል! ትናንት የፋሽስት ጣሊያን የመርዝ ጋዝ ያልበተነውና ያላበረከከው ሕዝብ፣ ዛሬ በፋሽስቱ አብይ አሕመድ ድሮን በፍጹም አይንበረከክም። የደርግን አሰቃቂ ቀይ ሽብር በጽናት የተሻገረው አቅሙ፣ በዛሬው ገዢ ቡድን የዘር ማጥ*ፋት ዘመቻ አይፈታም። የወያኔ የትጥቅ ማስፈታት አዋጅና በሐውልት ማቆም አንገት አስደፊነት ተግባር ያልተሰበረው ወኔ፣ በዛሬው የብአዴንና የአገዛዙ ሱሪ የማስፈታት ዘመቻ ከቶ ድል አይደረግም። ​ጥቅሙን፣ ጉዳቱንና ክብሩን አሳምሮ የሚያውቅ፣ ፍትሐዊ ባለሚዛን የሆነው የአማራ ሕዝብ—ትናንት ጅራፍ እያጮኸ ያልተሰማውን አጠቃላይ ብሶቱን፣ ዛሬ በእውነተኛው የፋኖ ክንድና በጥይት አረር እየታገለ፣ መብቱንና ሕልውናውን እያስከበረ ይገኛል። ከትናንት እስከ ዛሬ ባልተለወጠው የገዢዎች ክፋት፣ ሴራና የወገናችን መራር አኗኗር ውስጥ አንድ ቋሚና የማይናወጥ ትልቅ እሴት አለ፤ እርሱም የአማራ ሕዝብ እምቢ ባይነትና የማይበገር ወኔ ነው! ​ድል ለአማራ የህልውና ትግል! 🎯