ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
الذهاب إلى القناة على Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
إظهار المزيد2 941
المشتركون
+224 ساعات
+3727 أيام
+36730 أيام
أرشيف المشاركات
ነሐሴ 02/2018 ዓ/ሞ
ከአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ 208ኛ ራስ አሞራው ውብነህ ኮር የተሰጠ የአቋም መግለጫ!
የአማራ ሕዝብ የሕልውና፣ የፖለቲካዊ መር የትጥቅ ትግል ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ከፍተኛ መስዋዕትነት እየከፈልን የምንገኝ እኛ የ208ኛ ራስ አሞራው ውብነህ ኮር የሠራዊት አባላት፤ ከአፅናፍ እስከ አፅናፍ በሐሳብ የበላይነት በማመን ከማንኛውም ወገን በመርህና በሐሳብ ለመሞገት ዝግጁ መሆናችንን እናረጋግጣለን።
ነገር ግን የጎንደርን ክብር ፣ የታጋያችንን እና የህዝባችን ፍላጎትና ጥቅም በማያረጋግጥ መልኩ በእታገልልሀለው ሽፋን የግል ወይም ቡድናዊ አመለካከትን ለማስረፅ የሚንቀሳቀስን ማንኛውንም ግለሰብ ይሁን አካል አጥብቀን የምንቃወም ሲሆን፣ ተቋማችን ለጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ልክ እንደሌሎቹ ኮሮች ያለንን ሙሉ ደጋፊነት፣ ታማኝነት እና በመርህ ላይ የተመሠረተ የትግል ቁርጠኝነት ያለን መሆኑን በሙሉ ልብ እናረጋግጣለን።
ከዚህ በተጨማሪም በ208ኛ ራስ አሞራው ውብነህ ኮር ሥር የሚገኙ ሁሉም ክፍለ ጦሮች ''የሰማዕታት አደራ አንድነት ጉባኤ በድርኳዜ'' የተበሰረው የጎንደር አንድነት በታጋይ ወንድሞቻችን ደምና አጥንት የተገነባ መሆኑን አጥብቀን ስለምናምን የጉባኤውን ሙሉ ውሳኔ ተቀብለን ለተግባራዊነቱ የምንሰራ መሆኑን እናስገነዝባለን።
በመሆኑም ከዚህ ቀደም በኮራችን ስም ከእዝ እና ከኃላፊነት ወሰናችን ውጭ የወጡ ማንኛውንም መግለጫዎች 208ኛ ራስ አሞራው ውብነህ ኮርን ፈጽሞ የማይወክሉ እና ከእውቅናችን ውጭ እየተፈጸሙ ያሉ የግለሰቦች ፍላጎት ማርኪያ ፀረ አንድነት ድርጊመቶች መሆናቸውን አበክረን እንገልጻለን።
በመጨረሻም ቀጠናችንን በአስተማማኝ ሁኔታ አስጠብቀን የምንታገል የመርህና የሕዝብ ታጋዮች እንጂ የትኛውንም አካል የግል ፍላጎትና አጀንዳ ማስፈፀሚያ አለመሆናችንን እያረጋገጥን፤ የትኛውም ቅሬታም ሆነ ጥያቄ አለኝ የሚል አካል ወደ ተቋሙ ቀርቦ መስተናገድ እንደሚችል ማስገንዘብ እንፈልጋለን።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን !
አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ ዕዝ የ208ኛ ራስ አሞራው ውብነህ ኮር ስራ አስፈጻሚ!!
ነሐሴ 02/2018 ዓ.ም
አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት የበላይ ዘለቀ ዕዝ ከፍተኛ አመራሮችና በቀጠናው የሚገኙ የድርጅት አመራሮች ፣ የበላይ ጠባቂ አባቶች በጋራ በመሆን ከአንድነቱ ማግስት ቀጣይ በሚሰሩ ስራዎች ዙሪያ ከማህበረሰቡና ከዳግማዊ ቴዎድሮስ 5ኛ ኮር መብረቅ ክፍለ ጦር አመራርና የሰራዊቱ ክፍል ጋር ውይይት አካሄዱ ።
በውይይቱም በሊቦ ከምከም ወረዳ ሚካኤል ደብር ቀበሌ ከመብረቅ ክፍለ ጦር አመራሮች እና ከታችው የሰራዊቱ ክፍል ጋር ነሐሴ 01/2018 ዓ.ም ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን የበላይ ዕዝ ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ ደረጀ በላይ አንድ በመሆናችን እንኳን ደስ አላችሁ በማለት ጀመሩ ሲሆን አሁን የተመሰረተው አንድነት በቀላሉ የተገኘ ሳይሆን በርካታ ውስብስብ ፈተናዎችንና ውጣ ውረዶችን አሸንፎ እዚህ የደረሰ ነው በማለት ገልፀውታል ። አመራሩና ሰራዊቱ ያሳዩት ጽናትና ትዕግስት ለዚህ ታሪካዊ ድል መብቃት ዋና መሰረት መሆኑን አክለው ገልጿል።
የጎንደር አንድነት የተገነባው በታጋዮች ደም ፣ አጥንት እና በሕዝብ አደራ ጭምር የተገነባ መሆኑን ተገንዝቦ አንድነቱ የሚቀልድበት፣ የሚወርዱ መመሪያዎች የሚሸራርፍበት ወይም ለማፍረስ የሚሞክር አካል ቢኖር ፍጹም የማይታለፍ ቀይ መስመር መሆኑ በጥብቅ ተሰምሮበታል ።በቀጠናው አንድ ሕጋዊና መዋቅራዊ ሆኖ የሚንቀሳቀሰው አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ መሆኑን አረጋግጠዋል።
ከዚህ መዋቅር ውጭ በተናጠል ወይም በተበታተነ መልኩ የሚንቀሳቀስ አካል ካለ ማንኛውንም ህጋዊ እርምጃ የምንወስድ መሆኑን የተናገሩት አመራሩ ነገር ግን ጥያቄ አለኝ የሚል አካል ካለ በሰላማዊ እና ድርጅታዊ መርህን እና አሰራርን በተከተለ መንገድ መጠየቅ እንደሚችል አቅጣጫ ተቀምጧል ብለዋል።
አንድ ባለመሆናችን የሚደሰቱ አንድ በመሆናችን የሚከፉ አካላት የታጋዮችን መስዋዕትነት ከንቱ ማስቀረትና እና የሕዝብን እንግልት ለማራዘም የሚሠሩ በመሆናቸው፣ ሰራዊታችንና ሕዝባችን በመቀናጀት ከዚህ አጥፊ እና ፀረ አንድነት ግለሰቦች ጋር አብረው መቆም እንደሌለባቸው አጽንኦት ተሰጥቶበታል።
በመድረኩ ላይ የተገኙት የእዙ ምክትል ሰብሳቢ ለፖለቲካ ጉዳዬች ኃላፊ አርበኛ ኪሩቤል ጎቤ ፣የእዙ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አርበኛ አተነህ ድረስን ጨምሮ ሌሎች የእዙ ከፍተኛ አመራሮች፤ በአንድነቱ ውስጥ ምንም ዓይነት የአላማ ልዩነቶች እንዳይፈጠሩ ከፍተኛ ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተው ምክረ ሀሳባቸውን አጋርተዋል።
ከዚህ በፊት በነበሩ አለመግባባቶች የተፈጠሩ መጠራጠሮችን በግልጽ ውይይት መዝጋት ያስፈፈልጋል ያሉት አርበኞቹ የተቋጠሩ ቂሞችን በይቅርታና በመተማመን መንፈስ ማጥፋት፣ የተራራቁ ወገኖችን በማቀራረብ የቤተሰብን ያህል መተሳሰር መፍጠር እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።
የአላግባብ የተወሰዱ ንብረቶችን ወደ ባለቤቶቻቸው መመለስ፣ በተለያዩ ምክንያቶች ተበታትነው የነበሩ አደረጃጀቶችን በአንድ ጥላ ስር ማሰባሰብ የተጠናከረ መዋቅራዊ አደረጃጀት በመዘርጋት፣ ፍጹም በሆነ መርህና መመሪያ በመመራት ሰራዊቱን ይበልጥ ማደራጀት ፣ውስጣዊ ልዩነቶችን በመፍታት ሕዝብንና አገርን ከሚጎዳው የጋራ ጠላት ጋር በሚደረገው ትግል ድልን መቀዳጀት ላይ ትኩረት ያደረገ ስራ መሰራት አለበት ብለዋል ሲል መረጃውን ያደረሰን የክፍለ ጦሩ የህዝብ ግንኙነት ነው ።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን !
አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!
እሳትነት ያልበገረው የአርበኛ ዘገየ ዳኜ የትግል እና የፅናት ህይወት
ይህ እውነተኛ የታሪክ ድርሳን ስለ አወዛጋቢ የፖለቲካ መንገድ ወይም ተራ የታሪክ ገጽ አይደለም፤ ይህ ታሪክ ሙሉ ህይወቱን፣ ያፈራውን ሀብት እና የደከመበትን ጥረት ሁለት ጊዜ ለቆመለት አላማ አመድ አድርጎ ሰጥቶ፣ አሁንም በፅናት ስለቆመ አንድ የቁርጥ ቀን ልጅ የሚያወራ የህይወት ጀብድ እንጅ
የእምቢተኝነት ዋጋ ከ2002 እስከ 2007 እውነትን አንግቦ ከግዙፍ የመንግስት መዋቅር ጋር መጋፈጥ ቀላል አልነበረም። በ2002 ዓ.ም. የፍትሕ እና የእኩልነት ጥያቄን በልቡ ያነገበው አርበኛ ዘገየ ዳኜ፣ በወቅቱ የነበረውን የወያኔ ጨቋኝ ሥርዓት በግልጽ በመቃወም የመንገዱን መጀመሪያ ያደረገበት ታምራዊ ቀን ነበር። ይህ እምቢተኝነት ግን ያለ ከባድ መስዋዕትነት አልተሻገረም። በ2007 ዓ.ም. በስርዓቱ በደረሰበት የታለመ ጥቃት፣ በዓመታት ወጣትነቱ፣ በደምና ላቡ ያፈራው ንብረት ሙሉ በሙሉ እንዲወድም ተደረገ። ንብረቱ አመድ ቢሆንም፣ በልቡ ውስጥ የተቀጣጠለው የነፃነት እሳት ግን በፍጹም ሊጠፋ አልቻለም። ንብረት ይተካል፤ የማንነት እና የእውነት ትግል ግን አይቆምም።
የሸዋ ምድር እሳት እና የህዝብ አለኝታነት ከአጣዬ እስከ ሸዋሮቢት የወረራው እና የቃጠሎው ጭስ ሲቀጣጠል፣ አርበኛ ዘገየ እጁን አጣጥፎ አልተቀመጠም። የህዝቡ ህልውና አደጋ ላይ መውደቁን በመረዳት፣ ከጓደኞቹ ጋር በመሆን በራሳ አካባቢ ህዝቡን ማስተባበር እና መከላከል ጀመረ። በወቅቱ የነበረውን የብልፅግና ሥርዓት መዋቅር በመበጠስ፣ ህዝቡ በራሱ ተደራጅቶ ህልውናውን እንዲያስከብር የማድረግ ከፍተኛ ተጋድሎ አከናወነ። ይህ ህዝባዊ አለኝታነት፣ የወደፊቱ ወታደራዊ እና ድርጅታዊ አመራር መሰረት የተጣለበት ጊዜ ነበረ።
እሳት ያልበገረው አርበኛ ዘገየ ዳኘ በ2015 ዓ.ም ከባድ ፈተና የህዝቡ ምሬት እና የህልውና ሥጋት እያደገ ሲመጣ፣ አርበኛ ዘገየ የፋኖን አደረጃጀት ተቀላቀለ። በትግል ጉዞውም ከመቶ አለቃነት ጀምሮ በቆራጥነት በማገልገል፣ የይፋት ፋኖ ምክትል አዛዥነት ደረጃ ላይ ደረሰ። ነገር ግን በ2015 ዓ.ም. በሕይወቱ ከባድ የሚባል ሁለተኛው ጥቁር ፈተና ገጠመው። በአብይ አህመድ ወንበር አስጠባቂ መከላከያ ኃይሎች በተወሰደ እርምጃ፣ ሙሉ የመኖሪያ ቤቱ፣ የቤት እቃዎቹ፣ እንዲሁም ለዓመታት ለፍቶ ያቆመው የእንጨት እና ብረታ ብረት ማምረቻ ማሽኖችና ቁሳቁሶች ከነቤቱ ተቃጠሉበት።
በሁለት አጋጣሚዎች የለፋበት ሀብትና ንብረት ሙሉ በሙሉ አመድ ቢሆንበትም፣ የአርበኛ ዘገየ መንፈስ ግን አልተሰበረም። ይህቁስ ትግሌ በንብረት አይለካም!" በማለት መሳሪያውን አጥብቆ በመያዝ፣ የአማራ ህዝብ ጥሪ ተቀብሎ የመስዋዕትነት መንገዱን ቀጠለ። በመጨረሻም የአንድነት እና የአመራር ምዕራፍ የትግሉ ስፋት እና አስፈላጊነት እያደገ ሲመጣ፣ በሸዋ ምድር "የአንድነት ምክር ቤት" ሲመሰረት፣ ቀጠናውን በመወከል በአባልነት ንቁ ተሳትፎ አደረገ። በመቀጠልም በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ውስጥ በነበረው ድርጅታዊ ብቃት እና ታማኝነት ምክንያት የሎጅስቲክስ መምሪያ ምክትል ሀላፊ ሆኖ ተሾመ። በአሳምነው ዕዝ እና የይፋት አውራጃ መሪነት ዛሬ ላይ አርበኛ ዘገየ ዳኜ በቆራጥነት፣ በፅናት እና በብዙ መስዋዕትነት ያለፈ የወቅቱ ቁልፍ አመራር ነው።
በአሁኑ ወቅት በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ውስጥ የሎጅስቲክስ መምሪያ ዋና ሀላፊ በመሆን የዕዙ የቁሳቁስ አቅርቦት ሥራዎችን በበላይነት ይመራል። በተደራቢነትም፣ በስምሪቱ መሠረት የይፋት አውራጃ ሰብሳቢ ተደርጎ የተጣለበትን ህዝባዊ እና ወታደራዊ ሀላፊነት በቁርጠኝነት በመወጣት ላይ ይገኛል።
ከ2002 እስከ ዛሬ የተጓዘበት መንገድ የውድመት፣ የመስዋዕትነት እና የብዙ ፈተናዎች መንገድ ቢሆንም፣ አርበኛ ዘገየ ዳኜ አሁንም ቢሆን የቆመለት ዓላማ ሳይበገር፣ በፅናት ትግሉን በማስቀጠል ላይ የሚገኝ፣ ለብዙዎች አርአያ የሆነ እውነተኛ የታሪክ ባለቤት ነው። ይቀጥላል ....!#Dave #Amhara
ሰበር ዜና!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 15ተኛ ኮር ድል ተቀዳጁ!!
የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄ አ.ፋ.ብ.ን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 15ኛ ኮር ስር የሚገኙት 152 ኛ እና 153 ኛ ክ/ጦሮች ወግድ ወረዳ ለሚ ከተማና ከላላ ቲርቲራ አካባቢ ላይ ባደረጉት አዉደ ዉጊያ በሁለቱም ግንባር አመርቂ ድል አምጥተዋል።
በጥቃቱ ብዛት ያላቸዉ የመከላከያ አባላት የጨዉ ዘር እንደሆኑ ከአካባቢው የህክምና ተቋማት በተገኘው መረጃ መሰረት፣ ቀላል የማይባል ቁጥር ያላቸው የአገዛዙ ቅጥረኞች ቆስለው ሆስፒታል መግባታቸውን አሳዉቀዋል።
ከተገኙ ምርኮዎች መካከል፦ ለጊዜዉ ቁጥራቸዉ ያልታወቁ የድሽቃና የብሬን ጥይቶች ሲኖሩ በተጨባጪ
*እስካሁን ባለው መረጃ 39 የመከላከያ አባላት የተደመሰሰ
*: በወግድ፣ ለሚ እና አቀስታ የሚገኙ የሕክምና ተቋማት በቁስለኞች መሙላታቸው የዉስጥ መረጃወቻችን ያደረሱን መረጃ አመላክቷል!
የተማረኩ መሣሪያዎች:
*25 የነፍስ ወከፍ መሣሪያዎች
*2 የብሬን ሸንሸል
*በቁጥር ያልታወቁ የድሽቃና የብሬን ጥይቶች ተማርከዋል ሲል የ15ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃዉን አድርሷል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ!!
ነሀሴ :- 1/ 2018 ዓ/ም
አምስት የሚሊሻ አባላት ጀብደኛዋን እስቴ ዴንሳ ብርጌድን ተቀላቀሉ‼️
ነሐሴ 01/2018/
አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ ዕዝ ሜጀር ጀኔራል ውባንተ አባተ ፩ኛ ኮር ጉና ክፍለ ጦር እስቴ ዴንሳ ብርጌድ የአገዛዙን ሚሊሻ በማፍረስ ላይ ነው ።
የታሪካዊ ጠላታችን የሆነው የአንባገነኑ የብልፅግና ስርዓት ሲያገለግሉ የነበሩ የሚሊሻ አባላት በሰላማዊ መንገድ እጅ ሰጥተዋል።
በአማራን ህዝብ ላይ ዘርፈ ብዙ ጥቃት በመፈጸም ላይ የሚገኘው የብልጽግናው አገዛዝ በየቀኑ መፍረሱን ቀጥሎበታል ።ስለሆነም በዛሬው ዕለት ነሐሴ 01/2018 ዓ.ም ከነ ሙሉ ትጥቃቸው ብርጌዷን የተቀላቀሉት የአገዛዙ አባላትም:-
1ኛ .ደሳለኝ መስፍን
2ኛ. ይገርማል መንግስቴ
3ኛ .ተሻገር ያለው
4ኛ .ስጦታው አበባው
5ኛ. እንደሻው አታለል
በመጨረሻም በሰላማዊ መንገድ እጅ የሰጡት የሚሊሻ አባላት በጦር ሜዳ ጠበብቶች እስቴ ዴንሳ ብርጌድ ፋኖ በተደረገላቸው አቀባበልና እንክብካቤ ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀው ፣ የሚሊሻ ተቋም አሁን ላይ ወደ መፈራረስ ደረጃ እየመጣ ስለሆነ ወደ ፋኖ ተቆም እንዲቀላቀሉ ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን !
አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!
+3
#_ሻለቃ_አመራሮች_መሀል_አስቴሪዮ ከተማ_በመግባት ሁለት ክላሽ ማርከው ወጥተዋል።
=========================
........ነሐሴ 01/2018 ዓ.ም
በዛሬው እለት የአስቴሪዮ ከተማን ህዝብ ያስመረሩ የተዘጉ የንፁሀንን ቤቶችን ቁልፍ በመስበር እየከፈቱ ዝርፊያ በመፈፀም መሸከም ያልቻሉትን በመሰባበር ከፍተኛ ውንብድና ሲፈፅሙ መቆየታቸውን የተረዳው 54ኛ ክ/ጦር በቅርብ ርቀት በመከታተል መሀል ከተማ ድረስ በመግባት የህዝባችን እንግልት ያሳሳባቸው የሻለቃ አመራሮች
1.ታዘብ አንሙት 2.ዘሪሁን ሀይሉ እና 3.ያብባል ወርቁ ሁለት የአብይ አገልጋይ የሆኑ መከላከያወች ላይ እርምጃ በመውሰድ 2 (ሁለት) ክላሽ ማርከው ይዘው መውጣት ችለዋል።
የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
የምርቃት ዜና!!
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ምስራቅ አማራ 102ኛ ኮር የህክምና ቡድን ሰልጣኞችን በደማቅ ሁኔታ አስመረቀ።
ዛሬ ነሐሴ 01/2018 ዓ/ም የ102ኛ ኮር ለሁለት ተከታታይ ወር ከ3 ክፍለጦሮች የተወጣጡ የመጀመሪያ ረዳት ባለሙያዎችን በሰሜን ወሎ ዞን በራያ ቆቦ ወረዳ የኮር አመራር በተገኙበት ለሶስተኛ ጊዜ በብቃት አስመረቀ።
ጀብደኛው የ102ኛ ኮር ከዚህ በፊት በሁሉም ክፍለጦሮች ብቁ የሆኑ የህክምና ባለሙያዎችን በማሰልጠን ከፍተኛ የሆነ የህክምና ወጭን በመቀነስና የሰራዊታችን የጀርባ አጥንት በመሆን ተስፋ የተጣለበት መሆኑ ይታወቃል።
በአገዛዙ የብልፅግና ካድሬዎች አማካኝነት የአማራ ህፃናትና አዛውንቶች የህክምና አገልግሎት እንዳያገኙ የተለያየ ፖለቲከዊ ስያሜ በመስጠትና የአለም አቀፍ መርህ በመጣስ ህክምናን ለፖለቲካ ፍጆታ በማዋል በተለያዩ አካባቢዎች የህክምና እጥረት እዲፈጠር ተደርጓል ።
በመሆኑም የ102ኛ ኮር የህክምና ቡድን ከወታደራዊ ግዳጅ ጎን ለጎን በተቆጣጠራቸው አካባቢዎች ከሰራዊታችን አልፎ ለአማራ ህዝብ የህክምና አገልግሎት አቅም በፈቀደ መልኩ እየሰጠ ይገኛል።
በዚህ ታሪካዊ የምረቃ መርሃ-ግብር ላይ የዕዝ የህክምና ማዕከል ዳይሬክተር አርበኛ ዶ/ር ተስፋዬ ታደሰ፤ የ102ኛ የኮር ምክትል ህክምና ሀላፊ አርበኛ ሞገስ ቢረስ እንድሁም የ102ኛ ኮር ሎጂስቲክ እና አስተዳደር ሃላፊዎች በቦታው ተገኝተዋል።
ችግሩን በዘላቂነት ለመቅረፍ ተከታታይ ስልሰጠናዎች እንደሚቀጥሉ የህክምና ማዕከሉ ዳይሬክተር አርበኛ ዶ/ር ተስፋየ ታደሰ ገልጿል።
አርበኛው አያይዘው እንደገለፁት ከሆነ ከማንም ጋር ሰላም መፍጠር የማይፈልገው አገዛዙ በመላው ሀገሪቱ የጦርነት አዙሪት በመለኮስ በአማራ፣ በትግራይ እና በኦሮሚያ ክልል እንድሁም ከጎረቤት ኤርትራና ሱዳን ጋር የጦርነት ነጋሪት በመጎሰም ያልተረጋጋች ሀገር ለትውልድ በመፍጠር ዜጎች በኑሮ ውድነት፣በረሐብና ቸነፈር በስራ አጥነትና ጉስቁልና በከፍተኛ ደረጃ ጉዳት ደርሶባቸዋል ሲሉ ሀሳባቸውን ገልፀዋል።
እንድሁም የ102ኛ ኮር አስተዳደር አርበኛ ፈለቀ ደጉ በሰፊው ባስተላለፉት ጥልቅና መሪ መልዕክት በማንኛውም አስቸጋሪ የትግል ውጣ ውረድ ውስጥ ብንገኝም ችግሮችን በጽናት መቋቋም እና ተስፋ ባለመቁረጥ ለሰራዊቱም ሆነ ለህዝባችን ህልውና ወሳኝ መሆኑን ገልፀዋል።
በተጨማሪም በሁለት ሳምንታት ውስጥ ትጥቅ አስፈታለሁ ብሎ ወደ አማራ ክልል የገባው የአብይ አህመድ የግል ወታደር ላይ ጀግናው የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ በየ አውደ ውጊያው የጥላትን እንቅስቃሴ በማንበርከክና የሀይል የበላይነት በመውሰድ ከነፍስ ወከፍ መሳሪያ እስከ ዙ-23ና ሞርተር 120 ድረስ በመማረክና በመታጠቅ እንድሁም ከህክምና ቡድን እስከ ሰራዊት ስልጠና በመስጠት አለምን ጉድ አሰኝቷል ሲሉ ይናገራሉ።
በመጨረሻም የ102 ኮር የህክምና ቡድን ሰልጣኞች በታማኝነትና በልበ ሙሉነት በየትኛዉም አስቸጋሪ የግዜና የቦታ ሁኔታ ቢሆን ከራሳችን በፊት ለወጣንለት አላማና የሙያ መስክ ቅድሚያ እንሰጥአለን
ሲሉ የዕለቱ ተመራቂዎች ቃለ-ምህላ ፈፅመዋል ሲል የህዝብ ግንኙነት መምሪያዉ መረጃዉን አድርሷል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ወሎ(ቤተ-አማራ) ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
ነሐሴ 01/2018 ዓ.ም
እኛ በጊዜያዊ የፖለቲካ ማዕበልና በአሉባልታ ነፋስ የምንናጋ ማኅበረሰብ አይደለንም፤ ምክንያቱም ክብራችንና ማንነታችን በፋኖ አጥንትና ደም የተገነባ፣ ስሩ በጥልቅ የታሪክ አፈር ውስጥ የሰመጠ ጽኑ ዓለት ነውና።
አማራነትን እንደ ጉድለት ወይም እንደ ድክመት ለሚያየው የታሪክ ዕውርነትና የሐሳብ ድህነት ምላሻችን ፋኖ ነው፤ እርሱ የትላንትናው ተጋድሎ፣ የዛሬው ጽናትና የነገው ታላቅነታችን እውነተኛና ሕያው ምስክር ነው!
"የአማራ ልጅ በማንነቱ አንገቱን እንዲደፋና እንዲሸማቀቅ የሚመኝ ኃይል ካለ፣ ከጀርባው የተሰለፈውን፣ ለክብሩና ለነፃነቱ ነፍሱን አሳልፎ የሰጠውን የፋኖን የጀግንነት ማዕበልና የማይበገሬነት ምንነት ፈጽሞ ያላወቀ ብቻ ነው። #Dave #Amhara
የአርበኛ የረመጡ ደጀን አሸብር ነሐሴ 1/2015 ዓ.ም የማትረሳ ዝክረ ሰማዓታት
አማራን አጠፋለሁ ብሎ በቅጀት የተነሳዉ የብልፅግና ሰራዊት ጎንደርን ከተማን በመድፋ በታንክ በዙ23 በሞርተር በድሽቃ በብሬን አገር ሰላም ብሎ በተቀመጠበት ህዝቡ ያላሰበዉ ዶፍ ወረደበት ቅርሶች ተንቀጠቀጡ ቤተክርሲቲያ መስጊዶች ተደበደቡ ህፃናት አዛዉን ተደናገጡ ምኑ ማት መጣ በማለት ተጨነቁ ነበልባሉ ፋኖ አያቶቹ የገነቧት ከተማ የቱሪስ መዳረሻ የሆነችሁ ከተማ እንዲህ በአንድ ፍሽሽት የብልፅግና መንግስት ነኝ በሚል አካል ስትፈርስ ህዝቦቿ ሲጨፈጨፉ ማን ቁሞ ያያል በማለት ጀግና የአማራ ልጅ መሳሪያዉን ወልዉሎ ትጥቁን አንስቶ ለ7 ቀን ከለሊት አንገት ላንገት ተናነቀ አሳሩን አሳየዉ።
ጎንደር ከተማን አጠፋለሁ ብሎ የተነሳዉ ቅጀታም በቁርጥ ቀን ልጆቿ ያሰበዉ ያልተሳካለት የገባዉ ሁሉ መቅረት እንጅ መዉጣት ማይታሰብ መሆኑን የተረዱት አብይ አህመድ ጀኔራሎቹ ዕቅዳቸዉ መክሸፉን ሲያስቡ የመጨረሻ አማራጭ የተጠቀሙት በሰሜን በደቡብ በምዕራብ በምስራቅ በ4ቱም አቅጣጫ ያሰቀመጡጥን የትግል አላማ ያልገባዉን የግሪሳ መንጋ ወደ ጎንደር አዘመቱት።
ከባሻ ጥጋቡ ጠረፉን የተረከበዉ ረመጡ ደጀን አሸብር ጎንደር ላይ እየተፈፀመ ያለዉን ሲሰማ እንቅልፍ ነሳዉ ወደ ትግል ጓደቹ በመደወል አይዟችሁ እንደርስላችኃለን በማለት የትግል ጓዶችን በማነሳሳት እና በማደራጀት ከሱዳን ጠረፍ በመነሳት ከወንድሞቹ ከሻ/ቃ ሲሳይ አሸብር አርበኛ ሸቴ አሸብር አርበኛ ስጦታዉ መልኬ አርበኛ በለጠ አዱኛ አርበኛ ስማቸዉ የሽነህ አርበኛ ገብሬ አቡሃይ አርበኛ ብርሃኑ ሙላዉ የጠገዴ አርማጭሆ ወጣቶችን በማስተባበር ሳንጃ ላይ በመዝጋት ከአዉደራፊ እና ከሁመራ የሚጓዘዉን የጠላት ሃይል ወደ ጎንደር የሚያደርገዉ ጉዞ ህልም ሆነበት ባለበት መቆም ግድ ሆነ።
ረመጡ ደጀን አሸብር በየ አቅጣጫዉ የመጣዉን የአገሪቱ ሰራዊት ነኝ የሚለዉ ሳንጃ ላይ ታጉሯል ወደ ጎንደር ማለፊያ ጠፍቷል የጠገዴ አርማጭሆ ወጣት አይኑን አፍጧል ግንባሩ ተቋጥሯል ፀጉሩ ቁሟል ቦታ ቦታ ይዞ ትዛዝ ይጠባበቃል።
አርበኛዉ ረመጡ ደጀን አሸብር ተቆጥቶ ለመከላከያ የሰራዊት አመራሮች ተመለሱ ዳር ድንበሩን ለማን አስረክባችሁት መጣችሁ ማህል አገር ምን አለ በማለት ሲጠይቃቸዉ ጎንደር ለማረጋጋት ነዉ እኛ ከህዝባችን ጎን ነን በማለት ለማታለል ሞከሩ የእናንተ አማራጭ መመለስ ብቻ እንደሆነ እንቅጩን ሲነግሯቸዉ ትዛዝ ነዉ የሚል መልስ ሰጡ እንግዲያዉስ የአርማጭሆን ጥይት ቅመሱት ዉጊያዉ ተጀመረ።
አርበኛ ረመጡ ደጀን አሸብር ትዛዝ ከወንድሙ ከየሻ/ቃ ሲሳይ አሸብር ተቀበለ ወጣቱ በየአቅጣጫዉ ጃሌ እያለ እየፎከረ የብልፅግና ሰራዊት ላይ እሳት አነደደበት ጠላት ጎንደርን እያሰበ ሳንጃ ላይ ዶፍ ወረደበት በጣም ብዙ ቁጥር የጠላት ሃይል በአልሞ ተኳሾች እችን አለመን ተሰናበቷት።
አርበኛ ረመጡ ደጀን አሸብር ሙሉ ቀን ሲያዋጋ ሲዋጋ ዉሎ በጣም ብዙ ክላሽን ኮፕ ብሬኖች ሲናይፐሮችን ተተኳሽዎች ከጠላት ማርኮ ለትግል ጓደኞቹ ሲያስታጥቅ ዉሏል።
አርበኛ ረመጡ ደጀን አሸብር ነሐሴ 1/2015 ዓ.ም ሲዋጋ ሲያዋጋ ዉሎ ከ650 በላይ ጠላትን ደምስሶ ምሸት አካባቢ ከጠላት በተተኮሰች ጥይት የዛሬ 3 ዓመት ለአማራ ህዝብ ነፃነት ሲል የክብር ሰማዓታትነትን ተቀብሏል።
በአጠቃላይ ብዙ ጀግኖቻችን አርበኞች ደማቸዉን ያፈሰሱለትን አጥንታቸዉ የከሰከሱለትን ሰማዓታትነትን የተቀበሉበትን ዓላማዉን አሳክተን አደርነት እና አንድነትን እናፀናለን።
ክብርና ሞገስ ለሰማዕታት ጀግኖቻችን
ህልዉናችን በተባበረ ክንዳችን
አርበኛ ባንዴራዉ ግርማይ - ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
+4
ሠበር ሰበር ሠበር የድል ዜና !!!
ጀብደኛው ምኒሊክ ዕዝ ወግድ ወረዳ ላይ ድል ተቀናጀ !
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒሊክ ዕዝ 15 ኮር 45ኛ (የመብረቅ) ክፍለ ጦር በዛሬው ዕለት ማለትም በ ዐ1 / 12 / 2018 ዓ.ም ራሱን ጥምር ጦር ብሎ በሚጠራው ሠራዊት ከቀኑ 4፡00 ጀምሮ እልህ አስጨራሽ ትንቅንቅ በማድረግ እያሽመደመዱት ይገኛሉ ። ውጊያው እንደቀጠለ ሲሆን በጠላት ላይ ቀላል የማይባል ቁሳዊና ሠብአዊ ጉዳት አድርሰውበታል ። እስካሁን የደረሰን መረጃ እንደሚያመላክተው አብዛሀኛው የተደመሰሰ ሲሆን ቁስለኛውን እያንጠባጠበ በመሼሽ ላይ የሚገኘው ጠላት ገሚሡ ምርኮ በምርኮ ሆኗል ።
ውጊያው ሲጠናቀቅ መረጃዉን አጠናቅረን እንመለስበታለን ።
ነሐሴ 1/2018 ዓ/ም
ከጎንደር አንድነት ማግስት በሙሉ አቅማችን ለውጊያ ዝግጁ ነን ሲል አርበኛ ወርቁ ዘገየ ተናገረ ።
ከአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ አንድነት ማግስት በሙሉ አቅማችን በአንድነት የብልፅግናን ስርዓት ለመደምሰስ እና የአማራ ህዝብን የህልውና ትግል ዳር ለማድረስ የግዙፉ ጎንደሬ በጋሻው ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ አርበኛ ወርቁ ዘገየ ተናግሯል።
ጎንደሬ በጋሻው ክፍለ ጦር ሰፊ ቀጠና ይዞ የጎንደርን አንድነት ለማምጣት ከፍተኛ ስራ ከሰሩ ክፍለ ጦሮች መካከል አንዱ ሲሆን የጎንደርን ስምና ክብር የሚመጥን ፣ትግሉን ከፊት ሁኖ መምራት እንዲችል ከደንቢያ እስከ ወገራ ድረስ ከአመራር እስከ አባል ገብረን የጎንደርን አንድነት እንዲመጣ አድርገናል ከእንግዲህ በተናጠል ሳይሆን በጋራ ጠላታችንን እናጠፋለን በልዩነት የሚባክን ጊዜ እና የሰው ሀይል የለም ሲል ተናግሯል ።
አርበኛ ወርቁ ዘገየ እንደተናገረው በክፍለ ጦራችን ስር ያሉ ሁሉም ብርጌዶች ከአፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዕዝ ለሚሰጡ ወታደራዊ ትዛዞችን እና ግዳጆችን ለመቀበል 24 ሰዓት ዝግጁ ናቸው ሲል ለመላው የዕዙ አመራርና አባላት መልዕክቱን አስተላልፏል።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን !
አፋብን ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!
በነፃ ቀጠናዎች የሕዝብ አስተዳደር መዋቅር የመዘርጋት ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል!!
ነሐሴ 01/2018 ዓ.ም
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መንዝና ግሼ አውራጃ የሚንቀሳቀሰው የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ፣ ሙሉ በሙሉ በተቆጣጠራቸው ነፃ ቀጠናዎች የሕዝብ አደረጃጀትና አስተዳደራዊ መዋቅሮችን እያዋቀረ እደሚገኝ ተገለፀ።
ዕዙ የማዕከላዊ ኮሚቴውን የመጀመሪያ ጉባዔ ባጠናቀቀ ማግስት ከፍተኛ አመራሮቹን ወደተለያዩ ቀጠናዎች በመመደብ ከህዝቡና ከሰራዊቱ ጋር ሰፊ ጥልቀት ያለው የውይይት መድረክ እያደረገ ይገኛል። በነዚሕ መድረኮች ከህዝቡ የተነሱ ሀሳቦችን በማካተት የትግሉን አላማና ግብ ለማሳካት የሚያስችሉ ውሳኔዎች በጋራ መወሰናቸው ተገለፀ።
በመንዝና ግሼ አውራጃ የሚኖረው ህዝብ ለአስተዳደርና ለአገልግሎት አሰጣጥ ይመቻል ያለውን ጊዜያዊ አደረጃጀት በመከተል ቀበሌዎችን በክላስተር እያዋቀረ ሲገኝ በዚህም መሰረት በግሼ ቀጠና የተቆጣጠራቸውን ቀበሌዎች በአራት(4) ክላስተሮች አዋቅሯል፡
↘ክላስተር አንድ(1)
ወዠድ ክላስተር፦ ወዠድ ከተማን፣ አናዝ ቀበሌን እና ስረገደል ቀበሌን
↘ክላስተር ሁለት(2)
ግራር አምባ ክላስተር፦ ግራር አምባ ቀበሌ እና ጠበል ጫጩራ ቀበሌ
↘ክላስተር ሦስት(3)
አራጣ ክላስተር፦ አራጣና ልጅት ቀበሌ እና አስናፊት ቀበሌ
↘ክላስተር አራት(4)
ኮረብቲት ክላስተር፦ ደል ቀበሌ፣ ጎልታ ቀበሌ እና ኮረብቲት ቀበሌዎችን፡ እና ሌሎች የክላስተር አደረጃጀቶችን እያዋቀረ ይገኛል።
የአማራ ሕዝብ ለዘመናት የተጋረጠበትን የህልውና አደጋ በውል በመረዳ ፖለቲካዊ የትጥቅ ትግልን እየታገለ ሦስት አመታትን አስቆጥሯል። ሆኖም እነዚሕን ዓመታት በሕዝቡ ድጋፍና ደጀንነት "የአማራ ፋኖ ሠራዊት" በመገንባት ከግል ታጋይ እሰከ አታጋይ ድርጅት መምስረት የቻለው ሕዝብ ከአመራሮቹና ሠራዊቶቹ ጋር ጥልቅ ውይይት እያደረገ ቀልጣፋ አስተዳደራዊ መዋቅሮችን ለሕዝቡ ማቅረቡን ቀጥሏል።
በመንዝ ግሼ አውራጃ የሚንቀሳቀሰው የአፋብን ሸ/ጠ/ግ/አ/ዕዝ ዓፄ ዘርያዕቆብ ፩ኛ ኮር ብሩኬ ደምሴ ክፍለ ጦር በተመሳሳይ ከከፍተኛ አመራሮች ጋር ሰፊ የግምገማና የስልጠና መድረክ አድርጎ፡ ከዚሕ በታች በቀረቡት ሀሳቦች ላይ ጥልቅ ውይይት አካሒዷል።
➠ ፖለቲካዊ ግንባታ
▪የድርጅት ተልዕኮ አፈጻጸም
▪የማህበራዊ አኗኗር ደንቦች
▪ቅንጅታዊ አሠራሮች
▪ድርጅታዊ አላማና ግብ እዲሁም አጠባበቅ
➠የሠራዊቱ መብትና ግዴታዎች
▪አካላዊ ብቃት ማሻሻያ
▪አዳዲስ የውጊያ ስልቶች
▪ወታደራዊ ስነ ስርዓቶች
▪ወታደራዊ ስነ ምግባር
▪ወታደራዊ የአወቃቀር ማሻሻያና መሰል አዳዲስ ስልጠናዎች ትምሕርቶች ለሠራዊቱ ተደርጎለታል።
በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ «ጠላትህንና ራስህን ካወቅክ መቶ ውጊያዎችን አትፈራም» የሚለው መሪ ሀሳብ ጎልቶ የተንጸባረቀ ሲሆን፣ የሸዋ አንድነትና አማራዊ ድርጅት፣ አሁናዊ ሁኔታ፣ የቀበሌዎች የስራ እንቅስቃሴና የክላስተር አደረጃጀቶች እውቅና ላይ ውሳኔ በማሳለፍ መድረኩ ተጠናቋል።
ለተዋቀሩት ክላስተሮች የተመደቡት አመራሮችም ህዝቡንና አካባቢያቸውን በቅንነት፣ በታማኝነት፣ በፍትሃዊነትና በጽናት ለማገልገል በህዝቡ ፊት ቃለ መሃላ ፈጽመው ውይይቱ ተጠናቋል።
" ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
