Abdulkarim 🇵🇸
الذهاب إلى القناة على Telegram
فاصل الايمان مشروط باصل الحب وكمال الايمان مشروط بكمالالحب "እውነተኛ እምነት በእውነተኛ ፍቅር ይጀምራል፤ ፍጹም እምነት ደግሞ በፍጹም ፍቅር ላይ የተመሰረተ ነው። ይህም የነቢዩ (ﷺ) ፍቅር ነው፡፡''
إظهار المزيد471
المشتركون
-224 ساعات
-47 أيام
-630 أيام
جاري تحميل البيانات...
القنوات المماثلة
لا توجد بيانات
هل تواجه مشاكل؟ يرجى تحديث الصفحة أو الاتصال بمدير الدعم الخاص بنا.
سحابة العلامات
لا توجد بيانات
هل تواجه مشاكل؟ يرجى تحديث الصفحة أو الاتصال بمدير الدعم الخاص بنا.
الإشارات الواردة والصادرة
---
---
---
---
---
---
جذب المشتركين
يوليو '26
يوليو '26
+9
في 2 قنوات
يونيو '26
+27
في 3 قنوات
Get PRO
مايو '26
+20
في 1 قنوات
Get PRO
أبريل '26
+44
في 5 قنوات
Get PRO
مارس '26
+46
في 3 قنوات
Get PRO
فبراير '26
+25
في 5 قنوات
Get PRO
يناير '26
+37
في 5 قنوات
Get PRO
ديسمبر '25
+80
في 7 قنوات
Get PRO
نوفمبر '25
+63
في 5 قنوات
Get PRO
أكتوبر '25
+391
في 6 قنوات
Get PRO
سبتمبر '250
في 5 قنوات
Get PRO
أغسطس '25
+11
في 13 قنوات
| التاريخ | نمو المشتركين | الإشارات | القنوات | |
| 12 يوليو | +1 | |||
| 11 يوليو | 0 | |||
| 10 يوليو | 0 | |||
| 09 يوليو | 0 | |||
| 08 يوليو | 0 | |||
| 07 يوليو | +2 | |||
| 06 يوليو | +2 | |||
| 05 يوليو | +1 | |||
| 04 يوليو | 0 | |||
| 03 يوليو | 0 | |||
| 02 يوليو | +1 | |||
| 01 يوليو | +2 |
منشورات القناة
| 2 | 🧡በምንም ሁኔታም ሆነ በማንም ሰው ምክንያት መራራ በመሆን አታባክኗት! የቀኑ መልካም ጎን ላይ በማተኮር አጣጥሟት!
#ፏ_ያለ ቀን 💚 | 333 |
| 3 | 😘እሷ ~ በአመት 365 ቀናት እና ሌሊቶች ስላንተ ያላሰብኩበት ጊዜ የለም ፍቅር ነው አይደል ውዴ??
🥴እሱ ~ አረ ይሄማ ካላንደር ነው | 42 |
| 4 | #👨🦳 አባት : 1+1 ስንት ነው?
# 👶ልጅ: 11
አባትየው "መልሱ ሁለት ነው "
ብሎ ቢያስረዳው ልጁ ገገመ።
በዚህ ሰአት የተናደደው አባት
" ሂድና 2 ብስኩት ገዝተህ ና "
አለና ሱቅ ላከው ።ልጁ ከሱቅ ሲመለስ
#👨🦳 እባት: በል አሁን አንዱን ብስኩት ለኔ
አንዱን ደሞ ለእህትህ ስጣት
#👶 ልጅ: እንዴ ለኔስ???
# 👨🦳አባት: ዘጠኙን ብስኩት ብላ 😜
♡ ㅤ ❍ㅤ ⎙ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢᵃᵛᵉ ˢʰᵃʳ | 81 |
| 5 | አንገቴን ደፍቼ "ሰሙ ዛሬ እንደትናንት አይደለሁም። ትናንት ባለማወቅ ህይወትሽን አመሰቃቅያለሁ። በአላህ ይሁንብሽ ይቅር በይኝ!" አልኳት።
ሰሚራ ዝም ካለች በኋላ እያለቀሰች "ሀቢብ ትናንት የገፈፍከዉ ክብሬ ሊመለስ የሚችል አይደለም። ባሌ ድንግል አለመሆኔን ካወቀ ጀምሮ በትንሽ ነገር በተጣላን ቁጥር እያነሳ ያሸማቅቀኛል። ሁሌም በሀፍረት ነዉ ኑሮዬ! በሰዉ ዘንድ እንዲህ ካሸማቀቀኝ አላህ ዘንድ እኔንጃ!" አለች። እንባዋ ፊቷን ሸፍኖታል። በራሴ ተሸማቀቅኩ።
ሳግ ድምፄን እያነቀዉ "ሰሚራ ለሁሉም ነገር ጥፋተኛዉ እኔ ነኝ።ህይወትሽን አበላሸሁ። ፀፅቶኛል። ሰላም እያጣሁ ነዉ። ቢያንስ ይቅር በይኝ።" አልኳት።
"አላህ ይቅር ይበለን።" አለችና እንባዋን እየጠረገች "እኔም ከፈጣሪዬ ምህረትን ፈላጊ ነኝ። ይቅር ብዬሀለሁ።" አለችና ባለሁበት ትታኝ ሮጥ እንደማለት እያለች ወደ ቤቷ ሄደች።
ዉስጤ በሰራሁት ወንጀል ሲደማ ተሰማኝ። ምን አይነት ጨለማ ዉስጥ ነበርኩ?
.
የተሰጠን እረፍት ሲያልቅ ወደ መርከዝ ተመለስኩ። መርከዝ ሀይማኖታዊ ትምህርት የምንማርበት ተቋም ነዉ። ወደ መርከዝ ስመለስ ዉስጤ ላይ ትልቅ አላማ ተፈጠረ። በመሀይምነቴ ያበላሸኋቸዉን ህይወቶች መጠገን ባልችልም በደንብ ተምሬ ንፁሀን እንዳይበላሹ መንገዱን ማሳየት! አዎን በጣም ማወቅ አለብኝ ፤ አዉቄም ህዝቡን ማሳወቅ! የኔ አይነቱ እንዳያጠፋቸዉ ሚስጥሩን ማዉጣት! ከተሳካልኝ ደግሞ አምሪን ማግባት!
.
ወደ መርከዝ ከተመለስኩ በኋላ ህይወቴ ሁሉ ትምህርቴ ሆነ። ከትምህርት ሰዓታት ዉጪ ሳይቀር ኡስታዞቹን እያስቸገርኩ ተጨማሪ ሰዓት የተለያዩ ትምህርቶችን እማራለሁ። የሁለተኛዉ መንፈቀ አመት ትምህርት ተጀምሮ ሁለት ወራት አለፉ። እሁድ ነዉ። በጠዋቱ የትምህርት ቤቱ ግቢ ዉስጥ ከተማሪዎች ጋር ሆነን የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እየሰራን ነዉ። ነስሩ ፑሽአፕ እየሰራ ያስቆጥረኛል። ከኔ እኩል ለመስራት እየተፍጨረጨረ ነዉ። እላዩ ላይ እጄን ጭኜ መሬት ላይ ጣልኩትና እየሳቅኩ ወደ መኝታ ክፍል ሄድኩ። ወደ መኝታ ክፍል እየሄድኩ መተላለፊያ ላይ ስደርስ አዳራሽ ከምንለዉ ክፍል በጣም በሚያምር ድምፅ ቁርዓን ሲነበብ ሰማሁ። አህመድ ነበር። ገና አስራስድስት አመቱ ነዉ። ቁርዓን ሲያነብ በጣም ያለቅሳል። አሁንም እያለቀሰ ነዉ። የአዳራሹን በር ከፍቼ ገባሁ። አህመድ እየተንሰቀሰቀ ነዉ። ጀርባዉን ስለሰጠ አያየኝም። አህመድ "አለም የዕኒለዚነ አመኑ አንተኽሸዓ ቁሉቡሁም ሊዚክሪላህ?" የሚለዉን የቁርዓን አንቀፅ እየደጋገመ እያነበበ ያለቅሳል። ሰዉነቴ ተንዘፈዘፈ ፣ አይኔን እንባ ሸፈነዉ። በእንባዬ ዉስጥ ብዥታ ይታየኛል። አህመድ ያነበበዉ የቁርዓን አንቀፅ ተቀራራቢ ትርጉሙ "እነዚያ በአላህ ያመኑ ሰዎች ለጌታቸዉ ግሳፄ ልባቸዉ የሚፈራበት ጊዜ አልደረሰምን?" የሚል ወቀሳ አዘል ተግሳፅ ነዉ።
ሰዉነቴ እየተንዘፈዘፈ "ደርሷል ጌታዬ!" አልኩ። ትናንት ሳልፈራ የተዳፈርኳቸዉ ወንጀሎች ሁሉ ፊቴ ተደቀኑ። አህመድ መንሰቅሰቁን ትቶ ዞሮ አየኝ። ሰዉነቴ ከብዶኝ እንሰቀሰቃለሁ። ከተቀመጠበት ተነስቶ መጣና አቅፎኝ መንሰቅሰቅ ጀመረ።
ተላቅሰን ስንጨርስ ልብሴን ለመቀየር ወደ መኝታ ክፍል ሄድኩ።
ላይመለሱ ያጠፋኋቸዉ የሰዉ ህይወቶች መረጋጋት ነሱኝ። ሰላም ፣ ሰሚራ እና ፌቨን! ህይወታቸዉን የቀማኋቸዉ ሚስኪን እንስቶች!
.
ይቀጥላል...
. | 91 |
| 6 | Fuad Muna (Fuya):
የማይፋቅ ስህተት
ክፍል አስራሁለት
(ፉአድ ሙና)
.
ከኦፊስ ቀጥታ ወደ መስጂድ ሄጄ ሰገድኩና ጌታዬን ተንሰቅስቄ ምህረቱን ለመንኩት። አምስቱን ወር በሙሉ የወንጀልን ምንነት ጠንቅቄ ብማርም አንድም ቀን የራሴ ወንጀል ታይቶኝ አያዉቅም ነበር። በህይወቴ ያበላሸኋቸዉ ህይወቶች ሰላም ነሱኝ! ከስንቱ ጋር አንሶላ እንደተጋፈፍኩ ሳስበዉ ሰቀጠጠኝ። ወንጀሌ ምንም ቢገዝፍ የፈጣሪዬን ይቅርታ አይሸፍነዉም ብዬ ተንሰቀሰቅኩ። ከመስጂድ እንደወጣሁ በቀጥታ ወደ ቤት ሄድኩ። ገና ስገባ አምሪ በታብሌት የሆነ ስዕል ያለበት ነገር እያነበበች "እሺ የኔ ማፍያ ትተኸኝ ሄድክ አይደል?" አለች።
ታብሌቱን እየተቀበልኳት "ምን እያነበብሽ ነዉ?" አልኳት።
"ባክህ 'ስላይድ' ነዉ። ግቢ የምንማርበት ነዉ።" አለችኝ።
ዘግቼ መለስኩላትና "ኡሚ አትጋብዘንም እንዴ?" አልኳት።
ከተቀመጠችበት እየተነሳች "አንተ እስከምትመጣ እየጠበቅንህ ነበር። መጥታለች። መኝታ ቤት ናት!" አለችኝና በደንብ እያየችኝ "ደሞ ጀለቢያህን አዉልቀህ በሱሪ የት ሄደህ ነዉ?" አለችኝ።
"እነሚኪ ጋር ሄጄ ነዉ!" አልኳት።
አምሪ እንደመሳቅ እያለች "ሀቢቤ ከዚህ በፊት የሰራኸዉ ወንጀል ከፀፀተህ ወንጀል ወደሰራህበት ቦታ መመላለስ አታብዛ! ድጋሚ ወንጀል ላይ ይጥልሀል!" አለችኝ። አምሪ ትሰልለኝ ይሆን እንዴ ብዬ መጠርጠር ጀምሬያለሁ። ወንጀል ወደሰራሁበት ቦታ እንደሄድኩ እንዴት አወቀች? ከነሚኪ ጋር ስላልኳት ይሆን? እኔንጃ!
.
አምሪ በግድ ሱሪዬን አስወልቃ ጀለቢያ አስለበሰችኝ። ሴት ያዘዘዉ ሆኖብኝ ጀለቢያ ለብሼ ከወ/ሮ ለይላ እና ከአምሪ ጋር ሰፈራችን ወዳለ ታዋቂ ሬስቶራንት ሄድን። አዝዘን እንደተቀመጥን አንድ ወንድና አንድ ሴት ወደ ሬስቶራንቱ ገብተዉ ወደኛ ጠረጴዛ መጡ። ሲቀርቡ ወንዱን አወቅኩት የኛን ቤት የተከራየዉ ሰዉዬ ነዉ። ሴቷ ሚስቱ መሰለችኝ። መጥቶ እኔን ጨበጠኝ። ልጅቷ ደግሞ እነአምሪን እያቀፈች ሰላም አለቻቸዉ። ልጅቷን ትክ ብዬ ሳያት ድንጋጤ መላ ሰዉነቴን ወረረዉ። አቀረቀርኩ። ሰሚራ ነበረች። የድሮ ፍቅረኛዬ! አንሶላ የተጋፈፍኳት! አግብታለች! ሲገርም! እንዴት ባልጠፋ ቤት የኛን ቤት ተከራዩ!? ከአምሪ እና ከወ/ሮ ለይላ ጋር አዉርተዉ እስኪጨርሱ ቀና አላልኩም። ሲሄዱ ቀና ብዬ አምሪያን አየኋት! እየሳቀች ነዉ። ከዚህ በፊት "የናንተን ቤት የተከራዩትን ሰዎች ታዉቃቸዋለህ ወይ?" ብላኝ ነበር። እማዬን ስናስታምም አምሪ የሰሚራን ፎቶ ከቁምሳጥኔ ዉስጥ አግኝታ አይታዉ ነበር። የሰሚራ ባል ይገባዉ የነበረዉን የሰሚራን ክብር እኔ እንደገፈፍኩት ቢያዉቅ ምን ይል ይሆን? ድንግል እንዳልሆነች ሲያዉቅ ምን ብሏት ይሆን? በራሴ ተሸማቀቅኩ።
.
በልተን እንደጨረስን ወደ ቤት ተመለስን። አምሪ ወ/ሮ ለይላ ክፍላቸዉ ሲገቡ ጠበቀችና "ሀቢቤ ልጅቷን አስታወስካት?" አለችኝ። በአዎንታ ጭንቅላቴን ነቀነቅኩላት። "እኔ እኮ ያየኀት መስሎኝ ነበር። ዛሬ ገና ነዉ እንዴ ያየኀት?" አለችኝ። ከሰሚራ ጋር ያደረግነዉ ሁሉ አይኔ ላይ ድቅን እያለብኝ "ኧረ ዛሬ ነዉ ያየኋት።" አልኩ።
"ምክንያቱን ባላዉቅም ብዙ ጊዜ ከባሏ ጋር ይጣላሉ።" አለችኝ። እኔ ግን ምክንያቱን መገመት አልከበደኝም።
ምንም በደሌ ጣራ ቢነካም ሰሚራን ይቅርታ ለመጠየቅ አሰብኩ። አምሪ ፍቅረኛዬ እንደነበረች ልትገምት እንደምትችል ግልፅ ነዉ። ከሷ ጋር ከእንስሳ በታች ሆኜ እንደማዉቅ አምሪ ብታዉቅ ምን ትለኝ ይሆን?
.
በነጋታዉ ከፌቪ ጋር ተቀጣጥረን ነበር። ግን አምሪ ወንጀል የሰራሁበት ቦታ መመላለሴ ወንጀል ላይ ሊጥለኝ እንደሚችል የነገረችኝ ሀቅ ስለሆነ ላላገኛት አሰብኩ። ደሞ ያመሰቃቀልኩትን ህይወቷን ለማስተካከል መሞከር አለብኝ። ለጥቂት ደቂቃ አግኝቼያት ለመመለስ አሰብኩና ጠዋት ወደ አራት ሰዓት አካባቢ ወደ ኦፊስ ሄድኩ። ሀሳቤ ኦፊስ ሆኜ ልደውልላት ነዉ። ስገባ ፌቪ ፣ አብነት ፣ ከሪም ፣ ሚኪና አንድ የማላዉቃት ልጅ ክፍሉ ዉስጥ ተዘርረዋል። ሚኪና ያላወቅኳት ልጅ ተቃቅፈዉ ተኝተዋል። የሚኪም የሷም ሱሪ ወልቋል። ከሪም የአብነት ደረት ላይ ተመቻችቶ ተኝቷል። ፌቪ ሸሚዟ ቁልፉ ተከፋፍቶ ፀጉሯ ተንጨባሮ ተዘርራለች። ክፍሉ ዉስጥ የቢራ ጠርሙሶች ወዳድቀዋል። በፌቪ በኩል ትዉከት ትራሱን አጨማልቆታል። ክፍሉ በጣም በሚቀፍ ጠረን ታምቋል። እኔን ከነሱ ዉስጥ እንደዚህ ከመዝቀጥ ያተረፈኝን ጌታዬን አመሰገንኩት። ከክፍሉ ልወጣ ስል አብነት አይኑን እያሸ "እንዴ ሀቢቤ! ግቢ! ግቢ!" አለና ከሪምን ከደረቱ ገፍትሮ ቀሰቀሰዉ። ሁሉም ተነሱ። ፌቪ ተነስታ ሸሚዟን ቆላልፋ ወደኔ መጣች። ልትስመኝ ስትሞክር ከለከልኳት። "ኤጭ ሙድህ አይነፋም!" ብላ አልጋዉ ላይ ተቀመጠች። ሚኪና ልጅቷ ተነስተዉ ሱሪያቸዉን ለባበሱ። ሚኪ አይኑን እየጠራረገ "ሀቢቤ ተዋወቃት! አዲሷ ህይወቴ ናት!" አለኝ። ህይወቷን ሊቀማት ህይወቴ ሲላት አሳቀኝ።
ልጅቷ ፍልቅልቅ እያለች "ኤልዳና እባላለሁ" አለችና እጇን ዘረጋችልኝ። እጇን እያየሁ "ይቅርታ ይለፈኝ!" አልኳት።
ሚኪ እየሳቀ "ሀቢቤ ግን አክራሪ ሆነሻል!" አለ።
ፌቪ "ዉጡ ዛሬ ኦፊሱ የኔና የሀቢቤ ነዉ!" አለች።
ከሪምና አብነት የፈጣሪ ትዕዛዝ ይመስል ወዲያዉ ብድግ አሉ። ብሽቅ እያልኩ "ተቀመጡ! ምነዉ ለደህና ነገር እንዲህ በሮጣችሁ!" አልኳቸዉና ወደ ፌቨን ዞሬ "ክለብ አትዉጪ! አትጠጪ! አላልኩሽም ለምን ጠጣሽ?" አልኳት።
ፌቪ ፈገግ እንደማለት አለችና "ሀቢቤ ማስተካከል የማበላሸትን ያህል ቀላል አይደለም እኮ! በአንዴ እኔን ሁኑ ትላለህ እንዴ! ዛሬ አብረኸኝ ከተኛህ ልስተካከል! ትተኛለህ?" አለችኝ።
ንዴቴ እየተቀጣጠለ "አልተኛም!" አልኳት።
ፌቪ ከመቀመጫዋ ተፈናጥራ ተነሳችና "ገና ከመጀመሪያዉ ገብቶኛል! አታፈቅረኝም! አታስመስል! ያበላሸኸዉ እኔነቴ አሳዝኖህ ከሆነ ተወኝ! መመለስ የማልችላቸዉ ብዙ ነገሮቼን አሳጥተኸኛል! ሲፈልግህ የፈጣሪ በግ ሲሻህ የሰይጣን ፈረስ አድርገህ የምትጠፈጥፈኝ ጭቃ አይደለሁም!" አለችኝ። "ምናለ የፈጣሪ በግ ሳደርግሽ ከምትነቂ የሰይጣን ፈረስ ሳደርግሽ በነቃሽ" አልኩ በልቤ።
ፌቪ ተነስታ መጥታ "ደስ ሲልህ ልትተወኝ አትችልም!" አለችና ልትስመኝ ታገለች። ገፍትሬ አልጋዉ ላይ ወረወርኳት። እልህ እየተናነቃት ተንደርድራ ልትስመኝ ተመልሳ መጣች። በጥፊ አልጋዉ ላይ ዘረርኳት። እነሚኪ መሀል ገብተዉ ያዙን።
ፌቪ እያለቀሰች "ሀቢቤ አትተወኝ እንደ ድሮዉ ሁንልኝ!" አለች። ላስተካክላት ብል እራሴን ወደ ዝቅጠት ልመልስ ማለቴ እንደሚሆን ስለገባኝ ቤቱን ለቅቄ ወጣሁ።
.
ወደ ቤት እየተመለስኩ በማይመለስ መልኩ ያበላሸኋቸዉን ህይወቶች አሰብኩ። ፌቪ ምንም የማታዉቅ የቤት ልጅ ነበረች። ዛሬ እኔ በለኮስኩት እሳት ክብሯን ተነጥቃ መጠጥ የሚሉት እርኩሰት ላይ ወደቀች። ትምህርቷን አቋረጠች። አሁን እኔ ማነኝ? ብዙዎችን ያቆሸሽኩ ንፁህ? አላዉቅም።
ወደ ሰፈር ስደርስ ሰሚራ ከሱቅ እቃ ገዝታ ስትመለስ ተገጣጠምን። ባላየ ልታልፈኝ ስትል "ሰሙ አንዴ ላናግርሽ!" አልኳት። ቆመች። ተጠጋኋት። | 81 |
| 7 | oQgwpOGTeIqGoilDIUIAWuGXLxeAEC7ACIdkAe.mp3 | 82 |
| 8 | ህመም....
ቀይስ የለይላን መታጨት በሰማበት ጊዜ የተሰማው ስሜት እሱ ነው ህመም ማለት!💔
| 81 |
| 9 | 🏪#የስራ ቅጥር #ማስታወቂያ 🏦
👱♀ የስራ አይነት - ፀሀፊ
ፆታ - ሴት
እድሜ - 20-28
ልምድ - 0 አመት
የስራ ሰአት - በቀን 5 ሰአት
ደሞዝ - 8000ብር
👨💼ፆታ - ወንድ
እድሜ - 20-25
ልምድ - 20 አመት
የስራ ሰአት - በቀን 14 ሰአት
እንስሳትን ማውራት የሚችል, በ1ኛው እና በ2ኛው የአለም ጦርነት የተሳተፈ እና ቢያንስ 5ሰው የገደለ, 2ጎል በአለም ዋንጫ ላይ ያስቆጠረ, በአክሱም እና በላሊበላ ግንባታ ላይ የተሳተፈ 🤝
- ከሂትለር ጋ ሰልፊ ፎቶ ያለው ✊
- ዳይኖሰር የጋለበ💪
- የማቱሳላ ጎረቤት የነበረ🦾
-ደሞዝ - 4000 ብር | 94 |
| 10 | አቧራን የጠገበ ምንጣፍ የምትመታው አቧራውን ለማራገፍ እንጂ ምንጣፉን ለመግዷት አደለም ...
የሰውን ድክመት የምትነግረው ስህተትን እንዲያርም እንጂ በስህተቱ ተስፋ እንዲቆርጥ አይደለም👌 | 96 |
| 11 | ቁርአን 🌷
መልካም አዳር 🫀 | 107 |
| 12 | መኪና እየነዳህ ሰው ሰላም ካልክ ጉረኝነት ነው
ዝም ብለክ ካለፍክም #ጉረኝነት ነው
አልሃምዱሊላህ መኪና የለኝም😁 | 103 |
| 13 | #እሷ:- ሚስትና ልጆች እንዳሉህ ለምን አልነገርከኝም
#እሱ:- አይናፋር ነኝ ማሬ😔😔😔 | 113 |
| 14 | እኔ በአደኩበት ቦታ ፍቅር በአፍ አደለም ሚነገረው ይታያል ነው እኔን የሚወደኝ እናቴ አባቴም ጓደኞቼም አይነግሩኝም ምን ያህል እንደሚወዱኝ እንደሚጨነቁልኝ በአይናቸው ነው ሚያስታውቀው ለኔ በሚሆኑት ነገር | 111 |
| 15 | ፍቅር ማለት❤ | 116 |
| 16 | አሰላሙአለይኩም ቤተሰብ
ጁምዓ ተሰገደ ወይ? | 104 |
| 17 | የአሕዛብ ምዕራፍ الأحزاب 33:56
إِنَّ اللَّهَ وَمَلَائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ ۚ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا
አላህና መላእክቱ በነቢዩ ላይ የአክብሮት እዝነትን ያወርዳሉ፡፡ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በእርሱ ላይ የአክብሮት እዝነትን አውርዱ፡፡ የማክበርንም ሰላምታ ሰላም በሉ፡፡ | 106 |
| 18 | በነቢዩ ﷺ ላይ ሰለዋት ማውረድ የሚገኘው መልካም ነገር (ኸይራት) እና በረከት ለሰዎች ቢገለጥላቸው ኖሮ፤ ምላሶቻቸው እርሳቸውን በመውደድና በማላቅ ሰለዋት ከማውረድ ፈጽሞ አይቦዝኑም ነበር።
ከሀዲስ
ውዱ ነብይ ﷺ እንዲህ ብለዋል
"በጁመዓ ቀን እና ለሊት(ሐሙስ ማታ) በኔ ላይ ሰለዋትን አብዙ በኔ ላይ 1ሰለዋት ያወረደ አላህ በሱ ላይ 10 ሰለዋት ያወርድበታል"
اللهم صل على محمد وعلى آل محمد كما صليت على إبراهيم وعلى آل إبراهيم إنك حميد مجيد اللهم بارك على محمد وعلى آل محمد كما باركت على إبراهيم وعلى آل إبراهيم إنك حميد مجيد | 97 |
| 19 | ቁርአን 🌷
መልካም አዳር 🫀 | 96 |
| 20 | ችግር በበዛብህ ጊዜ ያ መልካሙን አርዓያህን ነብዩ ﷺ አስታውስ!
.....ገና በጨቅላ ዕድሜያቸው የቲም ሆኑ። ድግምተኛ፣ እብድ፣ ውሸታም… ተባሉ ክብራቸውን ጎደፈ፣ ጥርሳቸው ተሰበረ፣ በድንጋይ ተፈነከቱ፣ ከሀገራቸው አባረሯቸው፣ ሊገድሏቸውም ሞከሩ… ድሀ ሆነው ይህችን ዱንያ ኖሯት፣ ከረሀብ የተነሳ ሆዳቸው ላይ ድንጋይ ያስሩ ነበር፣
..... ከ7 ልጆቻው ስድስቱን አጡ… ይህን ሁሉ መከራን ተጋፍጠው አላህን አመስጋኝ ነበሩ።
አርዓያህ ሀቢቢ (ﷺ ) ናቸው?
ለችግሮችህ አመስጋኝና ታጋሽ ሁን💚 | 77 |
