ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
الذهاب إلى القناة على Telegram
በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:- @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
إظهار المزيد672
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
+37 أيام
-130 أيام
أرشيف المشاركات
"ይህ ዓለም መድረክ ነው ፤ ገብተህ ትሰራበታለህ ፣ አይተህ ትማርበታለህ፣ ወጥተህ ትሄዳለህ። ስለዚህ ጥበበኛ የሆንክ አንተ በተሰጠህ ጊዜ መልካሙን ስራ።"
ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ
ሁለቱ ምናምንቴዎች!
አንድ ወዳጄ ከት ብሎ እየሣቀ ናማ ጉድ ልንገርህ አዲስ የሥራ ዘርፍ እኮ መጥቷል አለኝ። ከወትሮ የተለየ አሣሣቅና ፊቱ ላይ ያለው ፈገግታ ቢያስደንቀኝ ምን ተከስቶ እንደሆነ ለማወቅ ጉጉት ስላደረብኝ ስለጉዳዩ እንዲያስረዳኝ ጠየኩት። ይህ ወዳጄ ፍርድ ቤት ለሆነ ጉዳይ እንደሄደና እዛም በሄደበት ጊዜ ከፍርድ ቤት ውጪ ሆነው እንዲመሰከርላቸው የሚፈልጉ ሰዎች የሐሰት ምስክርን የሚመሰክሩ እንዳሉና ብዙ ጊዜም በዚህ አይነት ስራ ላይ ተሰማርተው እንደሚገኙ ነገረኝ። ጉዳዩን ሰምቼው ስለነበር ይሄ ነገር በጣም የቆየ ጉዳይ እንደሆነ ብነግረው፤9 "እንዴት መሐላ አይፈሩም አይጎዳቸውም? እናንተ የምታስተምሩት ትምህርት ከንቱ ነው ሰው እንዴት የወለድኩት ይሙት እንደ እዚህ አጥንት ያድርቀኝ ብሎ ይምላል? ሌላ ሰውን ለመጉዳት እንዴት የማያውቁትን ነገር እንዲህ ነው ብለው ይመሰክራሉ" አለኝ።
የዚህ ወዳጄ አነጋገርና መገረም የዜና መዋዕል ላይ ያሉትን ሁለቱ ምናምንቴዎችን አስታወሰኝ። ናቡቴ ርስቴን አልተውም የአባቶቼን ርስት አሳልፌ አልሰጥም በማለቱ በወቅቱ ከነበረው ንጉሥ ከአክአብ ጋር ይጋጫል። አክዓብ ርስቱን መውሰድ እንዳለበትና የናቡቴ ቢሆንም የራሱ ለማረግ በመሻቱና ናቡቴም አልሰጥም ብሎ እምቢ በማለቱ በሁለቱ መካከል ቅያሜ ተፈጠረ። ይሄን ደሞ ንጉሥ አክዓብ ቤቱ ሲገባና ለሚስቱ ኤልዛቤል ቢነግራት እንደሚስትነት ንግሥናውን ባለማስከበሩ ብትበሳጨም የናቡቴን ርስት የተከፈለው ተከፍሎ ግን የራሷ ማድረግ እንዳለባት ስለወሰነች ናቡቴን የሚከሱ ሁለት ምናምንቴዎችን አዘጋጅታ ስለጾም አዋጅ እንዲነገርና ናቡቴ ያለጥፋቱ እንዲከሰስና እንዲፈረድበት አስደረገች። እነኚ ሁለት ምናምንቴዎች ናቡቴን በቅጡ እንኳን የሚያውቁት አይደለም በዘመናችን አሽቃባጭ የምንላቸው ሰዎች ዓይነት ናቸው። ለሐሰት የተቻኮሉ የሰውን ርስት ለማይጠቅማቸው ለማስወረስ የሚሮጡ ከተሳካላቸው ለራሳቸው ማድረግ የሚሹ ናቸው።
በመንፈ ቅዱስ ገላጭነት አባቶቻችን የማይስማሙ ብዙ ተቃራኒ የሆኑ ነገሮችን አነፃፅረው በምሳሌ አስተምረውናል። ለምሳሌ ኃጢአትና ፅድቅ ብርሃንና ጨለማ ቤልሆርና ክርስቶስ ጣኦትና ታቦት እባብና ርግብ... ወዘተ ከእነዚህ ጌታችን በልዩነት ካስቀመጣቸው ነገሮች መካከል በጠላትነት የሚኖሩ ፈፅመው አብረው ሊኖሩ ከማይችሉት ፍጡራን መካከል በግ እና ተኩላ ይገኙበታል። ሁለቱ ሰፊ የወንጌል ማብራሪያ ቢኖራቸውም ጉልህ ምስክሩ በግ የተባሉት የእግዚአብሔር ወገኖች ምሳሌ ሲሆን ተኩላ ደግሞ የሰይጣን ወገኖች ምሳሌ ናቸው። እነዚህ ሁለቱ ፈፅመው የማይስማሙና ተቃራኒ ሲሆኑ፤ የሚኖሩት በርቀት ነው አንዱ ከዱር አንዱ ከቤት፣ አንዱ በዪ አንዱ ተበዪ፣ አንዱ ኤልዛቤል ሌላኛው ናቡቴ። ታዲያ በአንድ ወቅት አንድ ሌላ አካል ለማስታረቅ ተነሳ ለማስታረቅ የመጣው ማን ቢሆን ጥሩ ነው? የበግ ሌላኛዋ ጠላት ቀበሮ! ወቸው ጉድ! ይልሀል ይሄ ነው። ቀበሮ ሽማግሌ ሆነች በግ ምን የምትመልስ ይመስላሃል? በግ ሽምግልናው ብትወደውም ሌላኛው ጠላቷ አጥንቷን እየሰበረች ደሟን እየመጠጠች ስጋዋን እየነጨች የምትገላት ቀበሮ በዳኝነት መምጣት ባይዋጥላት ሽምግልናውን አልቀበልም አለች። የተኩላው ሌሎች ወዳጆች ማለትም እነነብር ፣ አያ ጅቦ፣ አሞራዎች ወዘተ ተሰበሰቡና በግን መተቸት ጀመሩ። እንዲህም ይሉ ጀመር "መፅሀፋችን የሚያስታርቁ ብፁአን ናቸው ይላል፤ በሀገር ባህልም ሽማግሌ የተከበረ ነው" እያሉ ጥቅስ መጥቀስ ማስማማት ጀመሩ። ያቺ ምስኪን በግም; ቀበሮዋም ሆነች ጓደኞቻቸው የመጡበት ዓላማ እሷን ለመብላት እንደሆነ ተረዳች። አእዋፋቱም ቢሆኑ ትንሽ መቦጨቃቸው እንደማይቀር ስለገባት በጊቷ ያላት አማረጭ ያሉትን ይበሉ ብላ ሽምግልናው ብፁእ የሚያሰኝ መሆኑ ከእነሱ በላይ ብታውቅም ሽማግሌ ሆኖ የመጣው ቀበሮ ስለሆነ እራሷን ከመበ'ላት ለማዳን ስትል እንቢ አለች። ያልተነካ ግልግል ያውቃል አሉ! በግና ተኩላን ለማስታረቅ ቀበሮ ሽማግሌ ስትሆን አጃኢብ ነው መቼስ። ወዳጄ ቀበሮ ስብከት ስትጀምር "ሰውን ማመን ቀብሮ ነው" ብላ ነወ። ከቀበረችህ በኋላ ማመን ትጀምራለች። ቀበሮዎቹ እነኚህ ናቸው ምናምንቴዎቹ!
አንድ ሊቅ ስለመጽሐፈ ጨዋታ ሥጋዊ ወመንፈሳዊ እያወሩኝ ያሉኝን ነገር መቼም አረሳም መጽሐፈ ጨዋታ ሥጋዊ ወመንፈሳዊ ጨዋታ በሚመስል ለዛ ጥሩ ትምህርትን ያስጨብጣል። ሚካኤል እስኪሻር ሳጥናኤል ንስሐ እስጊገባ ምነው በኖርኩኝ ብሎ ይጀምራል ቅሉ ዘላለም አኑረኝ ማለቱ ነው። ታድያ ሚካኤልና ገብርኤል ቢጣሉ(አይጣሉም እንጂ) ሳጥናኤል ሊያስታርቅ ይመጣልን? ወዳጄ የሳጥናል አስታራቂነት ሳይሆን እነ ቅዱስ ሩፋኤል የት ሄደው ነው? ነው ጥያቄው። ብቻ በእነኚህ ሁለት ምናምንቴዎች ናቡቴ ቢከሰስና ቢሞት አክዓብ ርስት ሊወስድ ሄደ! ግን ደሞ እግዚአብሔር አምላክ መሐላውን አይረሳምና ኤልያስን ላከ አክዓብ ገና ኤልያስን ሲያይ ጠላቴ ሆይ ኬት መጣህ አገኘኸኝን? ብሎ ጠየቀ ለዲያቢሎስ ጽድቅ ኩነኔው ነውና! ተንኮል እንጂ እውነት መጥፊያው ነውና! ኤልያስ እግዚአብሔር ልኮኛል የናቡቴን ደም ውሾች የላሱት ቦታ የአንተንም ደም ይልሱታል አለው። አክዓብን በእግዚአብሔር ፊት ክፉን በማድረጉም ገጸጸው! ከአክዓብ በላይ ሁለቱ ምናንምንቴዎች ናቡቴና አክዓብ ጨርሰውት የነበረውን ጉዳይ በኤልዛቤል በኩል እንደገና ቆስቁሰው ናቡቴን አስገደሉት። ናቡቴን ገድለው ርስቱን አሳልፈው ሰጡ ብዙዎቻችን እንደዚህ ነን ያለቀ ነገር ላይ ገብተን መፈትፈት እንወዳለን። በጉን ገለን ተኩላውን ማንገስ እንሻለን ጻድቁን አባረን ኃጥአኑን እንሾማለን። እግዚአብሔር ያለ እስከማይመስል ድረስ በተንኮል እንጠመዳል፣ ምድራዊውን እንጂ ሰማያዊው ትዝ አይለንም የሰው ዓይን እንጂ የእግዚአብሔር አይን የሚያየን አይመስለንም። የሰው ርስት ለመቀማት እንደ አክዓብና ኤልዘቦል ብዙ ባለርስቶችን እናፈናቅላለን። ሁለቱን ምናምንቴዎች በመሆን በሰው ላይ እንፈርዳለን። ቀበሮ ሆነን በተኩላና በበግ ጸብ በጓን ለመብላት እንሽቀዳደማለን። ሳጥናኤልን ሆነን በቅዱሳኑ መላእክት በሚካኤልና በገብርኤል መካከል የሚጣሉ እየመሰለን አስታራቂ እንሆናለን። ናቡቴን ሆነን የተገኘን ግን የለንም ርስታችንን አሳልፈን እንሰጣለን እንጂ አንጠብቅም አናስጠብቅም። በሐሰት እየመሰከርን የብዙኃኑን ህይወት አመሰቃቅለናል ዛሬ ቢመስለንም በእግዚአብሔር ፊት መውደቃችን ግን አይቀሬ ነው።ያኔ እንደ አክዓብ ጠላቴ ሆይ አገኘኸኝን ብለን ከምንሳቀቅ ዛሬውኑ ግብራችንን ማስተካከል ይኖርብናል። እኔ ናቡቴን ነኝ የአባቶቼን ርስት አልሸጥም አልለውጥም!
እናንተስ?
ዲ/ን ናትናኤል አቢቲ ዘፍኖተ ወንጌል
+4
የወጣቶች የበዓል ዝግጅት በብፁዓን አባቶች ተጎበኘ።
በመስቀል በዓል ላይ የበዓሉ ዋና ውበትና ድምቀት የሆኑትን የወጣቶች ዝማሬና ልዩ ልዩ የዝግጅት አፈጻጸሞች በተመለከተ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በዝግጅት ላይ ላሉ ወጣቶች
#ብፁዕ አቡነ ቀለሜንጦስ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት እና የሰንበት ትምህርት ቤት ማደረጃ መምሪያ ሊቀ ጳጳስ እና ብፁዕ አቡነ ዳንኤል የአፋር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያ ኃላፊዎች በተገኙበት ወጣቶቹ ለበዓሉ የሚያቀርቡትን ዝግጅቶች በማየትየተደረሰበት ይዘት አመስግነው በሁለቱም ብፁዓን አባቶች መልዕክት ተላልፏ ።
#መጨረሻም ማደራጃ የመምሪያው ሊቀ ጳጳስ ወጣቶቹን በመባረክ የቤተ ክርስትያንም የሀገርም ተስፋዎች እናንተ ናችሁ በማለት አባታዊ መልዕክት አስተላልፈዋል።
© EOTC PR
✨✨✨🍂🌿✨✨✨🍂🌿
✨✨ኑሮየን ንገረኝ
ታላቁ ቅዱስ አርሳንዮስ ቤተ መንግሥትን ለቆ ወደ በረሃ ለምናኔ ሲገባ ጌታን የለመነበት ትልቅ ጸሎት ነበር። "ጌታ ሆይ" አለው። ጌታም "አርሳኒ ምን ትሻለህ" አለው። ቅዱስ አርሳንዮስም "ጌታ ሆይ ኑሮየን ንገረኝ" ሲል ጠየቀ። ዳግመኛም "ጌታ ሆይ" ሲል ጮኸ። ጌታም "አርሳኒ ምን ትሻለህ" አለው። እርሱም "ጌታይ ሆይ ኑሮዬን ንገረኝ" አለው። ሦስተኛም አለ "ጌታ ሆይ" አለ። ጌታም "አርሳኒ ምን ትሻለህ?" አርሳኒም "ጌታ ሆይ ኑሮየን ንገረኝ" አለ ከሰማይም እንዲህ የሚል ቃል መጣ፦ጌታም መለሰ። ቦታ ምረጥ፣ ከሰው ተለይ፣ ዝም በል አለው። አርሳኒም ገዳም ገብቶ ለፍጹምነት በቃ።
✨🍂🌿
ሰው መንገድ ሲሄድ በሁለት መንገድ ሊወድቅ ይችላል። አንደኛ በጠማማ መንገድ በመሄድ። ሁለተኛ በቅን መንገድ ሳያስተውሉ በመሄድ ነው። በጠማማ መንገድ በመሄድ መውደቅ ማለት በጠማማ ሃይማኖት መኖር ነው። በቅን መንገድ ሳያስተውሉ መጓዝ ማለት ደግሞ በቀናች ሃይማኖት እየኖሩ አካሄድን አለማወቅ ነው። መንገዱ የቀና ቢሆንም አረማመዱ ባለማየት ከሆነ እግሮቹ ተጣልፈውም ቢሆን ይወድቃል። አካሄዱ ካላማረ በክርስቶስ ማመንም ያስኮንናል። የምናውቀው ክርስትና በማናውቀው መንገድ ከኖርነው ያጠፋል።
አውቀን ለምናደርጋቸው እንኳ ቢሆን እንዴት ላድርገው እያልን መጠየቅ በየዕለቱ እናደርገው ዘንድ ይገባል። በየጊዜውና በየሰዓቱ ወደ ክርስቶስ የምንጓዝ ነንና ጥያቄያችን የዘወትር ነው። ጸሎት አይቋረጥም መባሉ ስለዚህ ነው። ቅዱስ አርሳንዮስ ኑሮው ምንኩስና እንዲሆን ወስኖ ነበር። ግን መነኩሴ መሆን እንዳለበት እያወቀ ኑሮየን ንገረኝ ይል ነበር። ለምን ቢሉ ኑሮውን ብናውቀውም አኗኗሩን ግን ካልጠየቅን የሚጠቅመውን በማይጠቅም መንገድ ልንኖረው እንችላለን።
✨🍂🌿
ለምሳሌ ከቅዱስ መጽሐፍ ቅዱስ ጳውሎስን እንይ። ቅዲስ ጳውሎስ ምሑረ ኦሪት ነበር። 46ቱን የኦሪት መጻሕፍት ተምሯል። መጻሕፍቱ ግን የሚተረጎሙት በክርስቶስ መገለጥ ነው። ቅዱስ ጳውሎስ ግን ጌታን ያሳድድ ነበር። የሚያሳደደውም ለሕግ የተቆረቆርሁ መስሎት ነበር። ጌታም ቅንነቱን አይቷልና ጌታን እያገለገለ መስሎት ጌታን ያሳድድ የነበረውን አልተወውም። መንገዱን ያቀናለት ዘንድ መንገገድ ላይ በመብረቅ ተገለጠለት። ሊያሳድድበት የሄደውን መንገድ ወደ ክርስቶስ እንዲደርስበት መራው። እውቀትን ቅንነት ይመራዋል፤ ቅንነትን እውቀት ያበራዋል። ስለዚህ ስለምናደርገው ነገር በቂ እውቀት ቢኖረንም ያንን ግን እንደ መርከብ የሚመራው ረድኤተ እግዚአብሔር ነውና አዘውትረን ኑሮየን ንገረኝ እንበል!
📝ርዕሰ ሊቃውን አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
✨✨✨🍂🌿✨✨✨🍂🌿
ኑ! ለመስቀል ደመራ በዓል
እሁድ መስከረም 11/2018 ዓ.ም በአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል የደብሩ ወጣቶች ሁላችሁ እንድትገኙ። ለበዓሉ ዝግጅቶቻችንን እንጀምራለን።
"አንተ ለሕይወትህ ካቀድከው የተሻለ እግዚአብሔር እንደሚያቅድልህ ታውቃለህ? አንተ ስለአንተ ልትሳሳት ትችላለህ፤ እግዚአብሔር ግን አይሳሳትም። አንተ ስለህይወትህ ስታቅድ ልትሳሳት ወይም ያነሰውን ልታስብ ትችላለህ እግዚአብሔር ግን ላንተ የሚገባውንና የተሻለውን በፍፁም ትክክለኝነት ያዘጋጅልሃል።"
አቡነ ሺኖዳ
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም መስከረም ሦስት በዚህች ቀን የከበረ አባት ሊቀ ጳጳሳት አባ ዲዮናስዮስ ከተሾመ በሁለተኛው ዓመት በእስክንድርያ ከተማ የኤጲስቆ ጶሳት የአንድነት ጉባዔ ተደረገ።
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ይህም ጉባዔ የሆነው ነፍስ ከሥጋዋ ጋር ትሞታለች በዕለተ ትንሣኤም ከሥጋዋ ጋር አብራ ትነሣለች ስለሚሉ ክፉዎች በዐረቢያ አገር ስለተነሡ ሰዎች ነው።
እነርሱም ለከፋችና ብልሹ ለሆነች ሃይማኖታቸው የፈጠራ ድርሰትን ደርሰው በእስክንድርያ ከተማ ወደሚኖሩ ሰዎች ላኩ። አባታችን ሊቀ ጳጳሳት አባ ዲዮናስዮስም ይህን ነገር በሰማ ጊዜ እጅግ አዘነ ከዚህ ከክፉ ሥራም እንዲመለሱ አስተማራቸው ገሠጻቸውም እነርሱ ግን አልሰሙትም አልተመለሱም። ስለዚህም በእነርሱ ላይ ይህን ጉባዔ ሰብስቦ ተከራከራቸው ስሕተታቸውንም ገልጾ አስረዳቸው እነርሱ ግን ሰይጣን አሳውሯቸዋልና ተጸጽተው አልተመለሱም ይህም ጉባኤ ረግሞ ከቤተ ክርስቲ ያን አንድነት ለይቶ አሳደዳቸው። ይህም አባት ዲዮናስዮስ ስለእርሳቸው ድርሳናትን ደረሰ በውስጣቸውም እንዲህ የሚል "በዚህ በቸርነቱ ስጦታ ውስጥ የእግዚአብሔር ፍቅር የጎላ የተረዳ ሆነ ነፍስ ረቂቅ ስለሆነች እንደ መላእክት በሕይወት እንድትኖር እንጂ እንዳትሞት እንዳትጠፋ ማድረጉ ነው። ከሥጋዋም በምትወጣ ጊዜ ስለ በጎ ሥራዋ እንደሚገባት መጠን ወደ ሕይወት ቦታዋ ይወስዷታል ወይም እንደሥራዋ ክፉነት ወደ ሥቃይ ይወስዷታል። በትንሣኤ ቀንም 'ንቃሕ መዋቲ' ተብሎ ዓዋጅ ሲነገር በፈጣሪያቸው ትእዛዝ የሙታን በድኖች ሲነሡ ነፍሳት እንዲህ ይሆናሉ እያንዳንዲቱ ነፍስ ከሥጋዋ ተዋሕዳ አብራ ትነሣለች።"
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን አባቶቻችን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ትድረሰን ለዘላለሙ አሜን።
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በዚህችም ቀን የገዳመ ሲሓት አባ ሙሴ አረፈ። ይህም ቅዱስ ከመነኰሰ ጀምሮ ዓለምን ትቶ ከበረሀ ገብቶ በጾም በጸሎት በመጠመድ ተጋደለ። እግዚአብሔር ዘይቶንና የተምር አትክልት ያለባትን የአትክልት ቦታ በማየት ልቡን ብሩህ እስከ አደረገለት ድረስ በወሩ መባቻም ከዘንባባ ዕንጨትና ከዘይቶን የወደቀውን ፍሬ ወስዶ ይበላል። ምግቡም ታናሽ ወፍ በሚመገበው መጠን ልክ ነው ልብሱም ከዘንባባ ቅጠል የተሠራ ሰሌን ነው። ስለዚህ ለሚያስጨንቅ ለክረምት ቅዝቃዜና ለቃጠሎ የተጋለጠ ሆነ ከዚህም ጋር በጾምና በጸሎት የተጠመደ ነው። ነገር ግን መጻሕፍትን የሚያውቅ አይደለም የዱር አራዊትም በየወገናቸው ወደእርሱ ይመጡ ነበር እርሱም ያረጋጋቸዋል። የጸሎት ጊዜም ሲደርስ በእጁ ሲጠቅሳቸው ይሔዳሉ። ድርቅ የሆነ እንደ ሆነም ሊያነጋግሩት እንደሚሹ ሁነው መጥተው በፊቱ ይቆማሉ እርሱም የሚሹትን በመንፈስ ቅዱስ አውቆ በጸሎቱ ዝናብን ያወርድላቸዋል። እንዲሁም እያደረገ ከእርሳቸው ጋር አርባ አምስት ዓመት ኖረ። ሰይጣንም ቀናበት ዘመኑ በአለፈና እጅግ በአረጀ ሽማግሌ አምሳል በጥቂት በጥቂት ሲያዘግም ከበዓቱ ውስጥ ሁኖ አየው ለዚህ ቅዱስ አባ ሙሴም ገዳማዊ መናኒ መስሎት ወደእርሱ ሔዶ አምጥቶ ወደ በዓቱ አስገባው አራዊት ግን በሽማግሌ የተመሰለውን ሰይጣን በአዩት ጊዜ ከእርሱ ሸሹ።
ከዚህ በኋላአባ ሙሴን አገሩንና ሃይማኖቱን ጠየቀው እርሱም ሁሉን ነገረው ደግሞ አባ ሙሴ ኑሮው እንዴት እንደሆነ ሽማግሌውን ጠየቀው። በሽማግሌ የተመሰለ ሰይጣንም እንዲህ ብሎ መለሰለት እኔ በዓለም ኃጢአት በመሥራት ብዙ ዘመናት ኖርኩ አንዲት ሴት ልጅንም ወለድኩ። ከዚያም የዓለምን ኃላፊነትና ጠፊነት አሰብኩ ከዓለምም ወጥቼ በበረሀ ውስጥ አርባ ዓመት ኖርኩ። ልጄን ያገባት እንደሌለ በአሰብኩ ጊዜ በዚህ ነገር ፕምክንያት ወዳንተ መጣሁ ከአንተ በቀር የሚያገባት የለምና። በሞትኩም ጊዜ የምትቀብረኝ አንተ ነህ ብዙ ስፍራዎችና የአታክልት ቦታዎችም ስላሉኝ ሁሉንም አንተ ትወርሳለህ። አባ ሙሴም ሰምቶ ደነገጠ እኔ መንኰሴ ስሆን ይህን እንዴት አደርጋለሁ አለ የተመረጡ ጻድቃን ሲሆኑ ሚስቶች የነበሩአቸው አብርሃምን ሙሴን ዳዊትን ከብሉያት መጻሕፍት ምስክር ማስረጃ አድርጎ አመጣለት በዚህም ወደ ተንኰሎ ልቡን አዘነበለው። በውስጡ ያጌጠች ሴት ልጅ ያለችበትን የተሸለመ አዳራሽ አሳየውና ከዚያም በኋላ እንደሞተ ሆነ አባ ሙሴም አይቶ በላዩ አለቀሰ ገንዞም ቀበረው ልጅቷ ወዳለችበት ለመግባት በፈለገ ጊዜ ጥቅል ነፋስ ነፍሶ የኋሊት ጣለው ከዚህ በኋላ ልቡ ሲመለስለት አዳራሹንም ልጅቷንም የአትክልት ቦታዎችንም አጣ ፈጽሞ እያደነቀ ወደ ማደሪያው ተመለሰ ከዕንጨቱም ፍሬ ምግቡን ሊመገብ ፈለገ በአፉም ውስጥ መራራ ሆነበት በረኃብም ስለ ተጨነቀ ወደ ዱር ወጥቶ ሔደ። ከዚህም በኋላ በአህያው ላይ ተቀምጦ ወደ እስክንድርያ በሚሔድ በሽማግሌ ነጋዴ አምሳል ሰይጣን ተገናኘው መብልና መጠጥም ይዞ ነበር አባ ሙሴንም ከርሱ ጋር ወሰደው ወደአንድ አገርም አድርሶ በዚያ ተወው። ዳግመኛም በገዳማዊት በመናኒነት በምትኖር ሴት አምሳል ሰይጣን ታየው እርሷም ውኃ የምትቀዳ መስላ ሥራውን ጠየቀችው ሰይጣን እንደፈተነው ሁሉን ነገራት በልቧም ሣቀችበት ወደቤቷም ወስዳው አብልታ አጠጥታ ከዚያ በኋላ የጋብቻን ነገር አሳሰበችው ብዙ ገንዘብም እንዳላት እርሷም የሟች ንጉሥ ልጅ እንደሆነች ነገረችው ልቡም እንደአዘነበለ አይታ እኔ አይሁዳዊት ነኝ እኛም ብዙዎች ነን ሃይማኖቱንም እስከካደ ድረስ በብዙ ተንኰል ተስፋ አስደረገችው። ዳግመኛም እንዲህ አለችው ና ወደ በረሀ እንውጣና ያኖርኩትን ገንዘብ እንውሰድ ብላ ሰው ወደሌለበት በረሀ ወሰደችው ከተራራ በላይም ወጥታ ተለወጠችበት እንዲህም አለችው እኔ ብዙዎችን ያሳትኩ ሰይጣን ነኝ። አንተንም ከገዳምህ አስወጣሁህ ሃይማኖትህንም አስካድኩህ እነሆ በዚህ በረሀም ሙተህ ነፍስህ ወደገሃነም ትወርዳለች ይህንንም ብሎ ሰይጣን ከርሱ ተሠወረ። በተመለሰም ጊዜ በቀኝም በግራም መንገድ አጣ የሚጠጣውም ውኃን አላገኘም ምድር ጠበበችው በምድር ላይም ወድቆ በፊቱ ውስጥም አፈርን በተነ ነፍሱም ከሥጋው ለመለየት እስከደረሰች ደረስ ተንከባለለ ጮኸ። መሐሪና ይቅር ባይ ሰውን የሚወድ እግዚአብሔርም ራራለት ያጽናናው ዘንድ መልአኩን ላከለት እርሱም ኃጢአትህ ተሠረየልህ እስከ ሰባት ቀንም ታርፋለህ የእግዚአብሔር አገልጋይ ሳሙኤልም ይቀብርሃል ብሎ አጽናናው ሰላምታም ሰጥቶት ዐረገ። ያን ጊዜም ሳሙኤል መጣ ንጉሥ ኢጋቦም በበረሃ ውስጥ ወደ አነፃት ቤተ ክርስቲያን ወሰደው እርሷም ገዳማውያን የሚሰበሰቡባት ተሠውራ የምትኖር ናት ወደርሷም በደረሱ ጊዜ ቅዱሳን ተሰብስበው መሥዋዕትን ሲያሳርጉ አገኙና በአንድነት ሥጋውንና ደሙን ተቀበሉ ስንብትም ከሆነ በኋላ ከቅዱሳን መቃብር በረከትን ሊቀበሉ ከአባ ሳሙኤል ጋራ አብረው ሔዱ ከዚያም ደርሶ አባ ሙሴ ሰገደ ወዲያውም አረፈ። አባ ሳሙኤልም ቀበረው ገድሉንም ጻፈ።
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በሁሉም ቅዱሳን በጸሎታቸው ይማረን ለዘላለሙ አሜን።
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
በዚህችም ቀን የኢትዮጵያዊው የአባ አንበስ የሰማዕት አባ ዲዮስቆሮስ ሰማዕት የሆነ የሊቀ ጳጳሳት ዲዮናስዮስ የዲያቆን በትንከል የብዙዎች የፋርስ ሰማዕታት የዕረፍታቸው መታሰቢያ ነው
በረከታቸውም ከእኛ ጋር ለዘላለሙ ትኑር አሜን።
🙏አሜን።🙏
🍀🍀🍀🍀✨✨✨✨🍀🍀🍀🍀
👉እንቁጣጣሽ’’
✍️ብዙ ዓይነት ትርጉም ያለው ሲሆን ይህ ስያሜ ለዓውደ ዓመቱ ተጨማሪ መጠሪያም ነው።
✍️ትርጓሜው እንደሚከተለው ነው፦፩ኛ፦ኖኅ ከማየ አይኅ ከዳነ በኋላ ዓለምን ለሦስቱን ልጆቹ በዕጣ አካፍሏቸዋል።
✍️ዕጣ ሲጣጣሉም አፍሪካ(ኢትዮጵያ)ለካም ደርሳዋለች ለጊዜው ደስ አላለውም ነበር ከዕጣው በኋላ በዚህ ወር ማለትም በመስከረም ወደ ዕጣው (ወደ ኢትዮጵያ)ገባ።
✍️ገብቶ ሲመለከታት የነበረባት ሀገር በጋ (ድርቅ)ወቅት ነበርና ይህች(ኢትዮጵያ)ግን ለምልማ፣አብባ፣መሬት በአበቦቿ አሸብርቃ፣ውኆቿ ወተት መስለው ሲፈሱ፣ነፋሳቶቿ፣ለሰው ልጆች የሚመጥኑ ሁነው ሲነፍሱ ባየ ጊዜ ኢትዮጵያ ከጠበቀው በላይ ሁና ስላገኛት በዚህ ወር“እንቁ ዕጣ ወጣሽ!!’’ብሏል
✍️፪ኛ፦የንግሥት ማክዳ ልጅ “ምኒልክ’’ከአባቱ ዘንድ ማለትም ከሰሎሞን ዘንድ ሂዶ ቢዘገይባት ልጀን አባቱ በዚያው ያስቀርብኝ ይሆን ብላ ንግሥተ ሳባ ስተክዝ ልጇ በዚህ ወቅት ማለትም በዓውደ ዓመት በመስከረም ሲመጣላት ስትተክዝ ያያት ሁሉ ወደእርሷ በመሄድ“እንቋዕ መጣልሽ’’(እንቋዕ ከጣጣ ወጣሽ)ብለዋታል።እርሷም የልጇን አንገት አቅፋ “እንቋዕ እንቋዕ’’ብላለች።እሰይ እሰይ ማለት ነው።
✍️፫ኛ፦አዕናቁ ክረምቱን በሙሉ በየብስ ያሉትን እፀዋቱ አዝርዕቱ አድገው ዳዋ ውጧቸው በባሕር ያሉት የክረምቱ ጎርፍ እና ናዳው አብሕርትን መልካቸውን ወደጭቃ በመቀየር እና በጥልቀቱ ውጧቸው(እንዳይታዩ አድርጓቸው)ይከርማል።
✍️ከዚህ ወር በኋላ ግን እፀዋቱ እየደረቁ አብሕርቱ እየጠሩ እየጠሩ ስለሚሄዱ አዕናቁ መታየት ይጀምራሉ ከዚህ የተነሳ ኢትዮጵያውያን በአዕናቁዕ እጅግ ፈላስፋዎች ነበሩና ከአዕናቁዕ አፍቅሮታቸው የተነሳ በዓውደ ዓመቱ“እንቁ እንቋዕ ወጣሽ’’ይሉ ነበር።
✍️፬ኛ፦ፀሐይ ክረምቱን በሙሉ ዝናም ባዘለው ደመና ተጋርዳ በምድር ላይ ቅዝቃዜ ይጸናል። ውርጭ እና ቅዝቃዜ ደግሞ ለሰው ልጅ አይመችም እና ፀሐይን ሁሉም እየተመኛት ባለማግኘቱ ውድ እና ብርቅዬ ሁና ነው የምትከርመው በዚህ ወር(በመስከረም) ግን ፀሐይም ፍንትው ብላ ትታያለች ውርጭ የከረመበት ሰውም ሙቆ አይጠግባትም ከዚህም የተነሳ ኢትዮጵያውያን በዚህ ወር(በዓውደ ዓመቱ) ፀሐይን እየተመለከተ “እንቋዕ ወጣሽ’’ይላታል።
✍️፭ኛ፦እንቁጣጣሽ የሚለው ቃል ነጭ እና ቢጫን ቀለምን ያመለክታል ስለሆነም በዚህ ወቅት አበቦቹ የሚበዙት የሚፈነድቁ ነጭ እና ቢጫ ከመሆኑ የተነሳ አበቦቹም እንቁጣጣሽ ይሰኛሉ።አዕናቁ በራሱ የሚበዙት ወደዚህ ቀለም ያደሉ ናቸው።
👉የእንቁጣጣሽ ስያሜ ዓውደ ዓመቱ ጋር እሄን ይመስላል።
"በቸርነትህ ዓመትን ታቀዳጃለህ" መዝ 64 ÷ 11
እንኳን ከዘመነ ቅዱስ ማቴዎስ ወደ ዘመነ ቅዱስ ማርቆስ በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ!
🪷🌼🌼🪷አዲሱ ዓመት በበረከት፥ በምሕረት፥ በይቅርታ እና በፍቅር ታጅበን የመንግሥቱ ልጆች ያደርገን ዘንድ አምላከ ቅዱስ ያሬድ ይርዳን። መልካም አዲስ ዓመት።🪷🌼🌼🪷
"አኹንም እግዚአብሔርን ፍሩ። በእውነተኛም ልብ አምልኩት . . . እግዚአብሔርን ማምለክ ክፉ መስሎ ቢታያችኹ . . . የአሞራውያንን አማልክት ታመልኩ እንደኾነ: የምታመልኩትን ዛሬ ምረጡ:: እኔና ቤቴ ግን እግዚአብሔርን እናመልካለን።"
ኢያሱ ፳፬:፲፬
"ለሰዎች የምትሰጠው ምንም ነገር ባይኖርህ ሞቅ ያለ ፈገግታ እና መልካም ቃልን ስጣቸው፣ ፍቅርን ስጣቸው፣ መልካምነትን ስጣቸው፣ የማበረታቻ ቃልን ስጣቸው፣ልብህን ስጣቸው..
ሰዎችን በማሳዘን ፈንታ ሁሌም ይህንን ብናደርግ ኢየሱስ በእኛ እንዳለ ያኔ ይታወቃል።
(አቡነ ሽኖዳ)
ሩፋኤል ግሩም በመንፈስ ቅዱስ ኅቱም
መዓዛ ቅዳሴከ ጥዑም ከመ ጽጌ ገዳም
ነዓ ነዓ ማዕከሌነ ቁም
በበዓልከ ባርከነ ዮም
እንኳን አደረሳችሁ🙏
