ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
الذهاب إلى القناة على Telegram
በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:- @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
إظهار المزيد668
المشتركون
-124 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
لا توجد بيانات30 أيام
أرشيف المشاركات
"የናሱን እባብ ባየ ጊዜ ዳነ" - መጋቤ ሐዲስ ለይኩን ብርሃኑ | New Ethiopian Orthodox Sibket ...
https://youtube.com/watch?v=-_RqD3_CPig&si=Vd-lFLoazhQsTPFS
+9
“ተርቤ አብልታችሁኛል ፤ ተጠምቼ አጠጥታችሁኛል ፤ ብታረዝ አልብሳችሁኛል” ማቴ 25 ፥ 35-36 የሚለውን ቅዱስ ቃል መሠረት በማድረግ ለብዙ ዓመታት በትንሳኤ ዕለት ብዙ ነዳያንን በመመገብ / በማስፈሰክ ያሳለፈው የደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት ዘንድሮም ከምዕመናን እና ከየለያዩ ወገኖች በተገኘ ድጋፍ በዛሬው ዕለት ነዳያንን አስፈስኳል። በዚህ መርሐግብር ላይ በገንዘብ እንዲሁም በጉልበት ለተሳተፋችሁ አካላት እጅግ ላቅ ያለ ምስጋና እናቀርባለን። ድካማችሁን፣ ልፋታችሁን የሰማይ ዋጋ ያድርግላችሁ። እግዚአብሔር ይስጥልን።
የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
👇👇👇 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27
Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel
Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel
Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475
"ስቅለተ ክርስቶስ" - እጅግ ልዩ ያሬዳዊ ዝማሬ - በደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል | Seklet Mezmu...
https://youtube.com/watch?v=t6OSweHUlWA&si=Y-ka8fx6rcKOivl5
ዕለት ቀዳም
⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺
▸ ቀዳም ሥዑር በጾም የተሻረ፡- ጦም ውሎ የሚታደርበት የአክፍሎት ቀን ማለት ነው፡፡ መዝ 88፥44 (ወስዓርኮ እምንጽሁ) እንዳለ ሥዑር የሚለው መሻር የሚለውን ትርጉም ይሠጠናል፡፡
▸ ቀዳም ስዑር፡- የለመለመ ዕለት ቄጤማና ግጫ የሚታደልበት ዕለት በመሆኑ ነው፡፡ ስዑር ያለው ልማላሜ እንደሚሆን ‹‹ውስተ ብሔር ስዑር ህየ የሀድረኒ›› መዝ.22፥2 በለመለመ መስክ ያሳድረኛል ያለው ያስረዳል፡፡ በኖኅ ዘመን የተላከች ርግብ ሐጸ ማይ አይኅ ነትገ ማየ አይኅ.... የጥፋት ውኃ ጎደለ›› ስትል ቆጽለ ዕፅ ዘይት ይዛ ለኖኅ አብስራለች ዛሬም ካህናት የሲኦል መከራ ቀለለ ዓመተ ኩነኔ ኣለፈ ሲሉ ለምዕመናን የቄጤማ ዝንጣፊ ያድላሉ፡፡
▸ አክፋሎት፡- የሚለው ኣክፈለ ኣካፈለ፣ ደረበ ( አክፋሎት ማካፈል ማጣፋት መደረብ (ሁለት ቀን ኣንድ አድርጎ መጦም ሁለት የተባለው ጌታ ከተያዘበት እስከ ተነሳበት ያለው አርብ እና ቅዳሜ ነው) ይህ ሥርዓት የመጣው እመቤታችን ያዕቆብ ዮሓንስ (ሌሎች ሓዋርያት) የጌታን ትንሣኤ ሳያዩ እህል ውኃ ኣንቀምስም ብለው በመቆየታቸው ምክንያት ነው፡፡ ስለዚህ የቻለ ሁለቱን ቀን ያልቻለ ግን ቀዳም ስዑርን መጾም ይገባል፡፡
የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
👇👇👇 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27
Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel
Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel
Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475
✨ቀዳም ሥዑር(የተሻረች ቅዳሜ)
ቀዳም ስዑር ለምለም ቅዳሜ፣ ቅዱስ ቅዳሜ ትባላለች፡፡
ቀዳም ሥዑር መባሉ ከወትሮው ዕለታት በተለየ ይህችኛዋ ዕለት በጾም ስለምትታሰብ የተሻረች ቅዳሜ እንላታለን፡፡
ለምለም ቅዳሜ መባሏም ካህናቱ የምሥራች አብሳሪ የሆነውን ቄጤማ ይዘው ወደ ምእመናን ቤት ስለሚሔዱ ለምለም ቅዳሜ ትባላለች፡፡
ቅዱስ ቅዳሜ መባሉም ቅዱስ እግዚአብሔር አምላካችን በጥንተ ተፈጥሮ ሃያ ሁለቱን ስነ ፍጥረታት የሚታዩትንና የማይታዩትን፣ በእግር የሚሄዱትን እና በክንፍ የሚበሩትን፣ በባሕር የሚዋኙትንና በመጨረሻም ሰውን በአርአያውና በአምሳሉ የፈጠረው በዕለተ ዐርብ ሲሆን ቅዳሜ ዕለት ደግሞ ከሥራው ያረፈበት ዕለት ናት፡፡
በዘመነ ሐዲስም የማዳን ሥራውን አከናውኖ በከርሰ መቃብር አድሮ በአካለ ነፍስም ሲዖልን በርብሮ ተግዘው የነበሩትን ነፍሳት ያወጣበት ዕለት በመሆኑ ቅዱስ /ልዩ/ ቅዳሜ ተብላ ተሰይማለች፡፡ ዕለቱ ዝርዘር አድርገን ስንመለከተውም ይህች የመጀመሪያው ቅዳሜ ለእግዚአብሔር የዕረፍት ዕለት ናት፤ እግዚአብሔር ሥነ ፍጥረትን ፈጥሮ ስላረፈባት ሰንበት ዐባይ (ታላቋ ሰንበት) ትባላለች (ዘፍ. 1፡3)
ይህችን ታላቋን ሰንበትም እንዲያከብሯት ሕዝበ እግዚአብሔር የተባሉ እስራኤላውያን ታዘው ነበር፡፡
ዕለተ ቀዳሚት (ሰንበት ዐባይ) በዘመነ ሐዲስም የተለየ የድኅነት ሥራ ተከናውኖባታል፡፡ ጥንት ሥነ ፍጥረትን በመፍጠር ዕረፍት እንደተደረገባት ሁሉ በሐዲስ ኪዳንም አዳምን ለማዳን ሕማምና ሞት የተቀበለው ቸሩ አምላክ በሐዲስ መቃብር አርፎባታል (ማቴ. 27፡61)፡፡
በዚህች ዕለት ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በከርሰ መቃብር ዐርፎ የዋለባት ዕለት በመሆኗ በምሥጢር ከሰንበት ዐባይ ጋር ትገናኛለች፡፡
ቀዳም ስዑር (የተሻረች ቅዳሜ) የተሰኘችውም በዓመት አንድ ቀን ስለምትጾም ነው፡፡
እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም፣ ወዳጆቹ ቅዱሳን ሐዋርያት ጌታ ተላልፎ ከተሰጠበት ዕለት አንስተው ብርሃነ ትንሣኤውን እስከሚያዩ ድረስ እህል ውኃ በአፋቸው አልዞረም፡፡ ይመኩበትና ተስፋ ያደርጉት የነበረ መምህራቸው በመቃብር ስላረፈ ዕለቷን ነገረ ሞቱን በማሰብና ትንሣኤውን በመናፈቅ በጾም አክብረዋታል፡፡
ከቅዱሳን ሐዋርያት ሲወርድ ሲወራረድ በመጣው ትውፊት መሠረት ቅዱሳን ሐዋርያት በሐዘን፣ በጾምና በጸሎት ዕለቷን እንዳከበሯት ክርስቲኖችም የተቻላቸው ከዓርብ ጀምረው በማክፈል፣ አሊያም ዓርብ ማታ በልተው ቅዳሜን በመጾም የጌታን ትንሣኤን ያከብራሉ፡፡
ቅዳሜ ጧት ምእመናኑና ካህናቱ ወደ ቤተ ክርስቲያን ይሰበሰባሉ፡፡
የጧቱ ጸሎት ሲፈጸም ”ገብረ ሰላመ በመስቀሉ” በመስቀሉ ሰላምን መሠረተ፣ ሰላምን ፈጠረ፤ የምሥራች እየተባለ በቤተ ክርስቲያን ለተሰበሰበው ሁሉ ቄጠማ ይሰጣል፡፡ የምሥራች ምልክት ነው፡፡ ምእመናኑም እየሰነጠቁ በራሳቸው ያስሩታል፡፡ ወደ ቤተ ክርስቲያን ላልመጡት ምእመናንም ካህናት በየሰበካቸው ልብሰ ተክህኖ ለብሰው መስቀልና ቃጭል ይዘው ቄጠማውን የምሥራች እያሉ ያድላሉ፡፡
የዚህ የቄጠማው ታሪክ መነሻው የኖኅ ዘመን ታሪክ ነው፡፡ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚነግረን በጻድቁ ኖኅ ዘመን የነበሩ ሰዎች በማየ አይህ ከጠፉ በኋላ የውኃውን መጉደል እንድትመለከት የተላከች ርግብ የምሥራች ምልክት የሆነ ለምለም ቄጠማ በአፏ ይዛ ተመልሳለች፡፡ በዚህም የውኃው መጉደል፣ የቅጣቱ ዘመን ማለፍ ተረጋግጧል (ዘፍ. 9፡ 1-29)፡፡
ቄጠማ ለጥፋት ውኃ መድረቅ የምሥራች መንገሪያ እንደሆነው ሁሉ አሁንም በክርስቶስ ሞት ሞተ ነፍስ ከሰው ልጆች ተወገደ ስትል ቤተ ክርስቲያን ለልጆቿ ቄጠማ ታድላለች፡፡ ምእመናንም የምሥራች ተምሳሌት የሆነውን ቄጠማ በግንባራቸው ያስሩታል፣ በጣታቸው ቀለበት ያደርጉታል፡፡
የክርስቶስ ተከታዮች ሁሉ ከጨለማ ወደሚደነቅ ብርሃን፣ ከሚያቃጥለው ዋዕየ ሲዖል (የሲዖል ቃጠሎ) ወደ ልምላሜ ገነት፣ ጥንተ ማኅደራቸው መመለሳቸውን በዚህ አኳኋን እየገለጡ በዓለ ትንሣኤን በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ያከብራሉ፡፡
ምንጭ :- አትሮንስ ዘተዋህዶ
የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
👇👇👇 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27
Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel
Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel
Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475
"ስቅለተ ክርስቶስ" - እጅግ ልዩ ያሬዳዊ ዝማሬ - በደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል | Seklet Mezmu...
https://youtube.com/watch?v=t6OSweHUlWA&si=CC_AgLWiDsubcFdJ
"ስቅለተ ክርስቶስ" - እጅግ ልዩ ያሬዳዊ ዝማሬ - በደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል | Seklet Mezmu...
https://youtube.com/watch?v=t6OSweHUlWA&si=8t-GaDjwmEAs4vb-
🎲 Quiz 'Qophii Gaafii fi Deebii Daandii Wangeelaa Carra Gaarii🛎🛎🛎'
🖊 5 questions · ⏱ 30 sec
🎲 Quiz 'ፍኖተ ወንጌል የጥያቄ እና መልስ መርሐ ውድድር 👉"start the quiz"የሚለውን ይጫኑ"i am ready"ሲጫኑ ጥያቄና መልሱ ይጀምራል።መልካም ዕድል!🛎🛎🛎'
🖊 8 questions · ⏱ 30 sec
ዘጠኝ ሰዓት ሲሆን
ዘጠኝ ሰዓት ሲሆን አባት ሆይ
በመስቀል ሆነህ አባት ሆይ
ድምፅህን በማሰማት አባት ሆይ
ነፍስህን ሰጠህ አባት ሆይ
የሰማያት ከዋክብት በሙሉ ረገፉ
ጨረቃም ፀሐይ ደምን አጎረፉ
ብርሃናት ጨለሙ ተለያዩ
ሥጋ በመስቀል ላይ ተገልጦ ስላዩ
ጌታችን ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሳለ
አሰምቶ ጮኸ ተጠማሁ እያለ
ማር እና ወተቱን የሚመግበው
ሐሞት አመጡለት ይቅመሰው ብለው
አካሉ ሲወጋ ውሃ ደም ፈሰሰው
በምድር ተረጭቶ ዓለምን ቀደሰው
የገሊላ ሴቶች ዋይ ዋይ ሲሉልህ
ለእነርሱ አዘንክ እንጂ ላንተስ አላዘንክህ
እናትህ ስታለቅስ በመስቀል ስር ሆና
ዮሐንስን ሰጠህ ጠብቆ እንዲያፅናና
መላዕክትም ታዩ አጋንንትም ሸሹ
የአይሁድ ሰራዊት ፈርተው ተረበሹ
የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
👇👇👇 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27
Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel
Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel
Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475
+4
“ለችግረኛና ለምስኪን የሚያስብ ምስጉን ነው፤ እግዚአብሔር በክፉ ቀን ያድነዋል።” መዝ ፵፩ ፥ ፩
እንኳን አደረሳችሁ!!!
✨✨✨✨✨✨ ✨✨✨✨✨✨✨✨
ሰንበት ትምህርት ቤታችን እንደወትሮው ሁሉ ዘንድሮም የትንሣኤን በዓል ምክንያት በማድረግ ችግረኞችንና ነዳያንን የምገባ አገልግሎት ለመሥጠት በዝግጅት ላይ ይገኛል። በመሆኑም እርስዎም አቅምዎ የፈቀደውን ልብዎም የወደደውን በገንዘብም ሆነ በዓይነት አስተዋጽኦ እንዲያደርጉና አገልግሎቱን እንዲደግፉ እንጠይቃለን።
ስለሚያደርጉትም አስተዋፅኦ በእግዚአብሔር ስም ከወዲሁ እናመሰግናለን።
ለበለጠ መረጃ:- 09 53 68 53 53
:- 09 64 64 55 52
የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
👇👇👇 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናል:- https://T.me/Finote_Wongel
የቴሌግራም ግሩፕ:- https://T.me/FinoteWongel27
የቲክቶክ ገጽ:- https://tiktok.com/@finotewongel27
Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel
Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel
Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475
Waan tokko illee dhokatee utuu hin mul'atin kan hafu hin jiru, dhoksaatti kan eegames bakkeetti ba'ee utuu hin dhaga'amin kan hafu hin jiru Luq.8፥17#Sagantaa gaafii fi deebii torbee daandii wangeela Yeroo hundaa jimataa sa'atii 2-4 Hirmaadha! Kaatediraala faayisaa adunyaa asallatii mana barumsa sanbata daandii wangeela. * sararii teelegiramaa፦ http://T.me/Finote_Wongel *Gaareen teelegramaa፦http://T.me/FinoteWongel27 *Torii tiktokii ፦http://tiktok.com/@finotewongel27 *yutuubidhaan፦http: youtube.com/@Finote_Wongel *Instagramaan፦http://www.instagram.com/finote_wongel
ልዩ መንፈሳዊ በፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት እየተዘጋጀ የሚቀርብ የጥያቄ እና መልስ መርሐ ግብር።ዘወትር በየሳምንቱ አርብ ምሽት ከ2:00 ⏰ ጀምሮ እስከ 4:00 ⏰ ድረስ ወደ እናንተ ይደርሳል። ይሳተፋ! የአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475
"የአቋም መግለጫ" - የአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል | Asella Debre Medhanit Medha...
https://youtube.com/watch?v=e9HmB9kgwD4&si=L07bWegjj0WcT904
+8
#ጸሎተ_ሐሙስ
የሕፅበተ እግር ስነ ሥርዓት ተከናወነ።
የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
👇👇👇 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27
የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27
Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel
Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel
Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475
