ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
الذهاب إلى القناة على Telegram
በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:- @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
إظهار المزيد669
المشتركون
+124 ساعات
+37 أيام
-330 أيام
أرشيف المشاركات
#የአእላፋትዝማሬ
#TheMelodyofMyriads
" በመስቀል አደባባይ የሚካሄደው 3ኛው ዙር የአዕላፋት ዝማሬ መርሐግብር ከቀኑ 9:00 ሰዓት ጀምሮ ምሽት 1:30 ይጠናቀቃል " - ኢጃት
3ኛው "የአዕላፋት ዝማሬ" መርኃግብር ታኅሳስ 28፣ 2018 ዓ.ም በመስቀል አደባባይ እና በድሬደዋ በለገሀር አደባባይ እንደሚከናወን አዘጋጁ የጃንደረባው ትውልድ አጠቃላይ ማኅበር (ኢጃት) በዛሬው ዕለት በሰጠው መግለጫ አስታውቋል።
ባለፉት ሁለት መርሐግብራት ከተሳተፉ ምዕመናን በተሰበሰበ ዳታ ላይ በተሰራ የዳሰሳ ጥናት መሰረት በ3ኛው ዙር በርካታ ማስተካከያዎች መደረጉን አንስቷል።
ለምን በመስቀል አደባባይ እንዲካሄድ ተወሰነ ?
ማኅበሩ በዳሰሳ ጥናቱ በዋነኝነት " የአዕላፋት ዝማሬ የሚካሄድበት ቦታ ጥበትና ከልክ ያለፈ መጨናነቅ" በቅሬታ መነሳቱን ገልጾ "ሰዎች ራሳቸውን እስከመሳትና ብዙ ነጠላዎች በጠዋፍ እስከመቃጠል በመድረሱ" ቦታውን ለመቀየር በዋና ምክንያትነት አንስቷል።
በተጨማሪም " መስቀል አደባባይ እንዲከበር እንፈልጋለን የሚለው የመጀመሪያው ዓመት ጥያቄ መደጋገሙ " ሌላው በምክንያትነት የተነሳ ጉዳይ መሆኑን ማኅበሩ ጠቅሷል።
3ኛው ዙር የአዕላፋት ዝማሬ ስንት ሰዓት ተጀምሮ ስንት ሰዓት ይጠናቀቃል ?
" መርሐግብሩ በመሃርነ አብ ጸሎት፤ በቅዱስ ፖትሪያሪኩ እና በብፁዓን አበው ሊቀ ጳጳሳት ጸሎተ ወንጌልና ጸሎተ ኪዳን ከቀኑ 9:00 ሰዓት ይከፈታል።
ከአባቶች ጸሎት ቃለ ምዕዳን እና ዘማሬ ውጪ ምንም አይነት የክብር እንግዶች ንግግር፣ ገቢ ማሰባሰቢያ እና ሌሎች መልዕክቶች የሚተላለፉበት መድረክ ባለመሆኑ በዚህም ዓመት ይህንን መንፈሳዊ ይዘት ይዘን እናስቀጥላለን።
በዕለቱ 30 መዝሙራት ይዘመራሉ።
መርሐግብሩ ከምሽቱ 1:30 ላይ ይጠናቀቃል። በጊዜ የሚጠናቀቅበትም ምክንያት ያለፉትን ተግዳሮቶች ከግምት ውስጥ በማስገባት እና ምዕመናን እንዲያስቀድሱ ለማድረግ ነው " ሲል ማኅበሩ አስረድቷል።
ፈቃድን በተመለከተ ምን ተባለ ?
የአዕላፋት ዝማሬን በመስቀል አደባባይ ለማከናወን " አስፈላጊ ሰነድ ተሟልቶ አስፈላገው ሰነድ ተገኝቷል " ያለው ኢጃት ከመንበረ ፖትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት የድጋፍ ደብዳቤ ቀድሞ ለከተማ አስተዳደሩ መላኩን ገልጿል።
ከዚህ በተጨማሪ ሁለቱ ዙር መርሐግብራት በሰላም በመጠናቀቁ " የከተማው ከንቲባ ጽ/ቤት እና የከተማው ጸጥታ ቢሮ የአዕላፋት ዝማሬ በመስቀል አደባባይ ይካሄድ የሚለውን በበጎ እንዲመለከተው አግዟል " ብሏል።
ምዕመናን፥ ቀኑ ሲቀርብ የከተማው የጸጥታ አካል ለሚሰጠው ዝርዝር መመሪያ እና በዕለቱ ሁነቱን በሰላም ለማጠናቀቅ ለሚደረገው ፍተሻ በተለመደው መንፈሳዊ ትዕግሥት እንዲተባበሩ ጠይቋል።
አባቶች የበዓሉን አከባበር በተመለከተ ተጨማሪ መግለጫ እና አባታዊ መልዕክት የሚያስተላልፉም ጠቁሟል።
" እድሜያቸው 15 ዓመት በታች የሆኑትን ይዛችሁ ባለመምጣት እንድትተባበሩን " ሲል ማኅበሩ የጠየቀ ሲሆን ቀደም ብሎ እስከ ታኅሳስ 23 ድረስ በግዮን ግራውንድስ በአዕላፋት ሳምንት የህጻናት የአዕላፋት የዝማሬ መርሐግብር መዘጋጀቱን ገልጿል።
ለነፍሰ ጥሩችና አካል ጉዳተኞች የተዘጋጀ ልዩ ስፍራ ስላለ ለአስተባባሪዎች በማሳወቅ ባታ ማግኘት ይቻላል ብሏል። በተጨማሪም ክሊኒኮች፣ ተንቀሳቃሽ ሽንት ቤቶች እና አምቡላንስ መዘጋጀቱን ጠቁሟል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
✨✨✨🌿✨✨🌿
አንደበታችንን እንጠብቅ!
አፉ ውስጥ ያለችውን ይህችን ትንሽዬ ብልት መቆጣጠር የማይችል ሰው ህይወቱ በመከራ እና በብስጭት የተሞላ መሆኑ የማይቀር ነው። ከአንደበታችን የሚወጡት ቃላቶች ከሰይፍ የላቀ፣ ከፈንጂ የባሰ ጉዳትን የማስከተል አቅም አላቸው።
ማሳበባችንን እንተው!
ማንኛውንም ውድቀት ላለመቀበል ሁሉንም ዓይነት ሰበቦች እና ምክንያቶችን እናመጣለን። ይህም ከስህተታችን እንዳንማር ያደርገናል። ለማሳበብ ለማሳበብማ አዳም ሔዋን ላይ አሳቧል፤ ሔዋንም እባብ ላይ አሳባለች… ታዲያ ማን ከእርግማኑ ተረፈ?።
ፀሎት አየራችን ይሁን
ፀሎት ከእግዚአብሔር ጋር የምንገናኝበት ዋነኛው መንገድ ነው… ከፀሎት ጋር ያልተቆራኘ ህይወት አየር በሌለበት ቦታ ላይ እንደመኖር ይቆጠራል! የጭንቀት እና የስጋት ሰንሰለት የትም እንዳንሄድ፣ ምንም ብሩህ ነገር እንዳናስብ ተብትቦ ይይዘናል፤ ፀሎት እንዴት ይህንን የብረት ሰንሰለት ማቅለጥ እንደሚችል እንማርበታለን።
✨🌿
ጭንቀት በእግዚአብሔር ላይ ማመጽ ነው
አምላካችን እግዚአብሔር ጭንቀታችንን ሁሉ ለእሱ እንድንተው መክሮናል። እኛ ግን ብዙ ጊዜ በጭንቀት ራሳችንን ስናሳምም ነው የምንገኘው። የታዘዝነውን ከማድረግ ይልቅ በተፈጠረብን ችግር አማካይነት ሳናውቀው በተቃውሞ ውስጥ እንገባለን። የጭንቀት መድሃኒቱ የሚያስጨንቀንን ነገር ሁሉ ለአምላካችን መተው ነው።
መድኃኒታችንን እንዋጥ
ይቅርታ ከብዙ በሽታዎች የሚፈሰው መድኃኒት ነው፡፡ ራሳችንን ከመመረዝ ነጻ ማውጣት የምንችለው በይቅርታ ነው፡፡ ይቅርታ ልክ የተቀደደ ልብስን እንደሚሰፋ የሚያውቅ መርፌ ዓይነት ነው። በየቀኑ የይቅርታን መድኃኒት እየዋጥን መፈወስ ስንችል ለምን ይሆን ራሳችንን የምንመርዘው?
📝አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ
✨✨✨🌿✨✨🌿
የ2018 ዓ.ም የአእላፋት ዝማሬ ጋዜጣዊ መግለጫ ፡ ዛሬ ታኅሣሥ 21 ፡ ከቀኑ 10፡00 በጃንደረባው ሚድያ የዩቲዩብ ገጽ በቀጥታ ሥርጭት ይከታተሉ ።
እስከ ታሕሳስ 28 ድረስ Profile , History and Post በማድረግ በመስቀል አደባባይ ለሚካሄደው የአንድነት ዝማሬ ማስታወቂያ ይስሩ።
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel
እስከ ታሕሳስ 28 ድረስ Profile , History and Post በማድረግ በመስቀል አደባባይ ለሚካሄደው የአንድነት ዝማሬ ማስታወቂያ ይስሩ።
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel
እስከ ታሕሳስ 28 ድረስ Profile , History and Post በማድረግ በመስቀል አደባባይ ለሚካሄደው የአንድነት ዝማሬ ማስታወቂያ ይስሩ።
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel
+1
እስከ ታሕሳስ 28 ድረስ Profile , History and Post በማድረግ በመስቀል አደባባይ ለሚካሄደው የአንድነት ዝማሬ ማስታወቂያ ይስሩ።
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel
እንኳን ለመጋቤ ሐዲስ ለሊቀ መላእክት ለቅዱስ ገብርኤል አናንያን ፣አዛርያን እና ሚሳኤልን (ሠለስቱ ደቂቅን) ከነደደ እሳት ለዳናቸው ዓመታዊ መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን።
"እኛ የምናመልከው አምላክ ከሚነደው ከእሳቱ እቶን ያድነን ዘንድ ይችላል" ት.ዳን.3፥17
ንጉሡ ናቡከደነጾር በዱራ ሜዳ ላቆምኩት የወርቅ ምስል ካልሰገዳችሁ ከእጄ የሚያድናችሁ አምላክ ማን ነው? ብሎ በኀይልና በዛቻ በጠየቃቸው ጊዜ ሠለስቱ ደቂቅ በልበ ሙሉነት፥ በፍጹም እምነት፥ መልስ የሰጡበት ኀይለ ቃል ነው፡፡ ከኀይለ ቃሉ ቅዱስ ዳዊት አመንኩ በዘነበብኩ /በተናገርሁት አመንሁ፤ እንዳለ መዝ.115፥1 ፍጹም እምነታቸውንና ታማኝነታቸውን፣ ጽናታቸውን እንረዳለን፡፡
እኛም በሃይማኖታችን ፀንተን መንግስቱን እንዲንወርስ የመላእክት አለቃ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል አናንያን፣ አዛርያን፣ ሚሳኤልን እንዲሁም ቅዱስ ቂርቆስን እና እናቱን ቅድስት ኢየሉጣን ያዳነ እኛንም በምልጃው፣ በምህረቱ ዘወትር አይለየን፡፡
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
ሠለስቱ ደቂቅን ያወጣ ከዕሳት
እኛንም አድነን ገብርኤል ሊቀ መላዕክት።
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
እንኳን ለሊቀ መላዕክት ቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ የንግስ በዓል በሰላም አደረሳችሁ🙏የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel
ለአእላፋት ዝማሬ የሚዘመሩ መዝሙሮችን በስልክዎ ያጥኑ
📱 Play store: https://play.google.com/store/apps/details?id=com.janIt.alafat_zmare
📱 AppStore: https://apps.apple.com/hr/app/yeaelafat-zmare/id6739265238
✨️️️️✨️️️️✨️️️️🤲🤲🤲✨️️️️✨️️️️✨️️️️🤲🤲🤲✨️️️️✨️️️️✨️️️️🤲🤲🤲
በጥቂቱ መታመን
✨️️️️🤲
መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል፦
"በጥቂቱ ታምነሃል በብዙ እሾምሃለሁ!.."ማቴ 25፥21፡፡ ይህም ማለት በምድራዊ ነገሮች ላይ ታማኝ ሆነህ ስትገኝ በሰማያዊ ነገሮች ላይ እሾምሃለሁ ማለት ነው፡፡ በዚኛው ዓለም ታማኝ ሆነ ከቆየህ በዘለዓለማዊነት ውስጥ እሾምሃለው ማለት ነው፡፡ ይህ መመሪያ በብዙ መስኮች ላይ ተግባራዊ ሊሆን ይችላል... ዘመዶችህን በመውደድ ላይ ታማኝ ሆነህ ከተገኘህ እግዚአብሔር ጠላቶችህንም በመውደድ ላይ ይሾምሃል፡፡ ጠላትህን የምትወድበት ጸጋ ያድልሃል ማለት ነው፡፡ ✨️️️️🤲🤲 በትርፍ ጊዜዎችህ እግዚአብሔርን የምታገለግል ከሆንህ በሕይወትህ ጊዜ ሙሉ በእርሱ ላይ ትኩረት የምታደርግበትን ፍቅር ያድልሃል፡፡ የፈቃድ ኃጢአቶችን ከአንተ በማስወገድ ላይ ታማኝ ሆነህ ከተገኘህ እግዚአብሔር ያለ ፈቃድ ከሚመጡ ኃጢአቶች ነጻ ያወጣሃል፡፡ ✨️️️️🤲🤲 ንቁ ኅሊናህን ከክፉ አሳቦች የምትጠብቅ ከሆንህ እግዚአብሔር ንቁ ያልሆነው ኅሊናህን ንጽሕና ያድልሃል፤ ከዚህ በተጨማሪ የህልሞችህን ንጽሕናም ያድልሃል፡፡ ልጅ እያለህ ታማኝ ከሆንህ እግዚአብሔር ውጊያዎች በሚበዙበት በወጣትነትህ ዘመን ውስጥም ታማኝነትን ያድልሃል ሌሎች ሰዎች ላይ በቃላት ብቻ የማትፈርድባቸው ሆነህ በመገኘትህ ታማኝ ከሆንህ ይበልጥ አስቸጋሪ በሆነው በአሳብ እንዳትፈርድባቸው ያስችልሃል፡፡ ልክ እንደዚሁ ራስህን ከውጫዊ ንዴት በመጠበቅ ላይ ታማኝ ሆነህ ከተገኘህ እግዚአብሔር ከውስጣዊ ቁጣ፣ንዴትና ቅናት ነጻ ያወጣሃል፡፡ ✨️️️️🤲🤲 በተለመዱ መንፈሳዊነቶች (በመንፈስ ፍሬዎች) ላይ ታማኝ ሆነህ ከተገኘህ እግዚአብሔር የመንፈስ ስጦታዎችን ያድልሃል፤ በመጀመሪያው ላይ ታማኝ ሆነህ ካልተገኘህ ሁለተኛውን ፈጽመህ ልታገኘው አትችልምና፡፡ ✨️️️️🤲🤲 እግዚአብሔር በመጀመሪያ የሚፈትሽህ በጥቂት ነገር ነው፡፡ በዚህች በጥቂቷ ነገር ላይ ታማኝ መሆንህ ካረጋገጥህ እርሱ በሚበልጠው ነገር ላይ ይሾምሃል፡፡ ውድቀትህንና አለመታመንህን በጥቂቷ ነገር ላይ ከገለጽህ ግን እግዚአብሔር በሚበልጠው ነገር ላይ አይሾምህም፡፡ ✨️️️️🤲 መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላልና፦
"ከእረኞች ጋር በሮጥህ ጊዜ እነርሱህ ቢደክሙህ ከፈረሶች ጋር መታገል እንዴት ትችላለህ?"ኤር 12፥5 ብዙ ሰዎች ዝቅተኛውን ኃላፊነት መወጣት ሳይችሉ ከፍተኛውን ኃላፊነት ለመቀበል ማሰባቸው እጅግ አስደናቂ ነገር ነው፡፡ እነዚህ ሰዎች በተሰጣቸው ጸጋ ሳይጠቀሙ ተጨማሪ ጸጋ እንዲሰጣቸው የሚጠይቁ ናቸው፡፡ ይህን ሲያደርጉም "በጥቂቱ ታምነሃል፤ በብዙ እሾምሃለሁ" የሚለውን የእግዚአብሔር ቃል በመዘንጋት ነው፡፡ "መንፈሳዊ ቃላትና ጥቅማቸው" ከሚለው #አያሌው_ዘኢየሱስ ከተረጎመው #የብጹዕ_አቡነ_ሽኖዳ መጽሐፍ የተወሰደ!!! ✨️️️️✨️️️️✨️️️️🤲🤲🤲✨️️️️✨️️️️✨️️️️🤲🤲🤲✨️️️️✨️️️️✨️️️️🤲🤲🤲 የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel
"ሥርዐትህን እማር ዘንድ፣ በመከራ ውስጥ ማለፌ መልካም ሆነልኝ። ከአእላፋት ብርና ወርቅ ይልቅ፣ ከአፍህ የሚወጣው ሕግ ይሻለኛል"
መዝ 119፥72-73
"ነፍሴ ሆይ፥አንቺ ለእግዚአብሔር ተገዢ፥ ተስፋዬ ከእርሱ ዘንድ ናትና።እርሱ አምላኬ መድኃኒቴም ነውና፤ እርሱ መጠጊያዬ ነው፤ አልታወክም"
መዝ 62÷5-6
የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel
የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
"የሰው ልጆች ያርፋባት ዘንድ ሰንበትን አዘጋጀ። ለጻድቃንም ለኃጥአንም ለሞቱትም በሕይወት ላሉትም የሰው ልጆች ያርፋባት ዘንድ ሰንበትን አዘጋጀ! የክርስቶስ ሰንበቱም እሷ ናት ለልዑልም የስሙ ማደርያ ናት።"
✨ሊቁ ቅዱስ ያሬድ✨
መልካም ዕለተ ሰንበት
✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨
