ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
الذهاب إلى القناة على Telegram
በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:- @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት
إظهار المزيد669
المشتركون
+124 ساعات
+37 أيام
-330 أيام
أرشيف المشاركات
እኛ ግን ሥሉስ ቅዱስ በመለኮት አንድነት የተካከሉ በሦስት አካላት ፍጹማን እንደሆኑ እንዲህ እናምናለን፤ እነዚህም አንዱ ቅዱስ አብ አንዱ ቅዱስ ወልድ አንዱ ቅዱስ መንፈስ ቅዱስ ናቸው፤ ከዓለም አስቀድመው የነበሩ ዓለምን አሳልፈው የሚኖሩ ናቸው አሜን በእውነት።
✨️️️️️️️✨️️️️️️️✨️️️️️️️🍂✨️️️️️️️✨️️️️️️️✨️️️️️️️🍂✨️️️️️️️✨️️️️️️️✨️️️️️️️🍂
✨️️️️️️️ልዩ ፍርድ ቤት✨️️️️️️️
ብዙዎቻችን ወንድሞቻችንን ለማማት የፈጠንን ነን፡፡ የራሳችንን ግንድ ትተን የሰውን ጉድፍ ለማውጣት የምንቻኮል ነን፡፡ በወንድሞቻችን ላይ ለመፍረድ፥ እኅቶቻችንን ለመኰነን የምንጣደፍ ነን፡፡
ወዳጄ ሆይ! መፍረድ የእግዚአብሔር እንጂ ያንተ ሥልጣን አይደለምና ተጠንቀቅ፡፡ እህቴ ሆይ! በአምላክ ዙፋን ላይ ለመቀመጥ አታስቢ፡፡ወዳጄ ሆይ! መፍረድ አማረኽን? እንኪያስ ምንም ወቀሳ የሌለበት፣ ይልቁንም ብዙ ጥቅም የሚያስገኝ የፍርድ ችሎት አለልህ፡፡ በራስህ ላይ መፍረድ ትችላለህና ተቀመጥ፡፡ ከኹሉም አስቀድመህ የበደልህን መዝገብ በፊትህ አኑረው፡፡ ነፍስህ የሠራችውንም ወንጀል በሙሉ በጥንቃቄ መርምር፡፡ ከዚያም “ነፍሴ ሆይ! ይኽንና ያንን በደል የፈጸምሽው ስለምንድነው?” በላት፡፡ የበደለችበትን ምክንያት ትታ በሌሎች ላይ ለማሳበብና በሌሎች ላይ ለመፍረድ ከዠመረችም “የተከሰስሽው በራስሽ ወንጀል እንጂ በሌላ ሰው ወንጀል አይደለም፡፡ እዚኽ ፍርድ ቤት የመጣሽው ስለእነዚያ ሰዎች ለመመስከር አይደለም፡፡ ስለዚኸ ንገሪኝ! ይኽን ያኽል በደል የፈጸምሽው፣ ይኽን ያንን ኹሉ ጥፋት ያጠፋሽው ስለምንድነው?” በላት፡፡ ዘወትር ይኽን የመሰለ አስጨናቂ ጥያቄ ጠይቃት፡፡ አፍራ የምትመልሰው ከሌላትም አስፈላጊውን ፍርድ (ቀኖና) ወስንባት፡፡ ይኽን ልዩ ፍርድ ቤት ዘወትር የምትቀመጥ ከኾነ ያንን የእሳት ባሕር፣ ያ እሳቱ የማይጠፋው ትሉ የማያንቀላፋው ስቃይ በልቡናህ ይቀረጻል፡፡ ✨️️️️️️️🍂 “ወደ እኔ መጥቶ ነው፤ እርሱ አታልሎኝ ነው፤ እርሱ ፈትኖኝ ነው" እያለች በዲያብሎስ እንድታመካኝም አትፍቀድላት፡፡ ይልቁንም፡- "አንቺ ባትፈቅጂ ነው እንጂ እነዚኸ ኹሉ በአንቺ ላይ ሥልጣን የላቸውም" ብለህ ንገራት፡፡ "እኔ እኮ ሥጋ ለባሽ ነኝ፤ የምኖረውም በዚኽ ኃጢአት በሞላበት ዓለም ነው" ካለችህም "ይኽ ኹሉ ሰበብና ምክንያት ነው፡፡ ብዙዎች አንቺ የለበስሽውን ሥጋ ለብሰው በዚኽ ዓለም ኑረው ጻድቃንና ሰማዕታት ኾነዋል፡፡ አንቺ ራስሽ አንዳንድ ጊዜ መልካም ምግባራትን ስታደርጊ ይኸ አኹን የምታሳብቢበትን ሥጋ ለብሰሽ ነው" በላት፡፡ ይኽን ስትላት ቢያማትም እጅህን አታንሳባት፡፡ ምክንያቱም ቀኖናው ከሞት የሚታደጋት መንፈሳዊ ልምምድ እንጂ የሚገድላት ቅጣት አይደለምና፡፡ ስለዚኽ ምክንያት የምታበዛብህ ከኾነ “እባብ አሳተኝ" ብላ ከተጠያቂነት ያለመለጠችውን ሔዋንን አስታውሳት፡፡ ይኽን ኹሉ ስታደርግም ከአጠገብህ ማንም አይኑር፡፡ የሚረብሽህ ሰው ከአጠገብህ አይገኝ፡፡ ይልቁንም ዳኛ በፍርድ ወንበር ላይ እንደሚቀመጥ አንተም በፍርድ ወንበር ፈንታ በምቹ ጊዜና ቦታ በጽሞና ተቀመጥ፡፡ ነቢዩ “በመኝታችሁ ሳላችሁ በልባችሁ የምታስቡት ይታወቃችሁ" እንዳለው /መዝ.4፥4/ ይኽ ቦታና ጊዜ ከኹሉም ይልቅ ተስማሚ ነውና እራትህን ከበላህ በኋላ ዘወትር ይኽን የፍርድ ወንበር ወደ መኝታ ክፍልህ ይዘኸው ሒድ፡፡ ዕለት ዕለት ይኸን የምታደርግ ከኾነ ሐዋርያው “እኛ በራሳችን ብንፈርድ ኖሮ ባልተፈረደብንም ነበር" እንዲል (1ኛ ቆሮ.1፥31) በዚያ አስፈሪው የፍርድ ወንበር ፊት ያለ ፍርሐት ትቆማለህ፡፡ 📝ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ 📚ሰማዕትነት አያምልጣችሁ እና ሌሎች ✨️️️️️️️ገጽ 42-42 📝በገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተተረጎመ ✨️️️️️️️✨️️️️️️️✨️️️️️️️🍂✨️️️️️️️✨️️️️️️️✨️️️️️️️🍂✨️️️️️️️✨️️️️️️️✨️️️️️️️🍂
✨☘✨🌿✨☘✨🌿✨☘🌿✨
ቤተክርስቲያንን በሁለት መንገድ ማወቅህን አረጋግጥ። እንደ አሕዛብ ጠላቷ እንዳትሆን በትምህርት ዕወቃት፤ እንደ ፈሪሳውያን እንዳትሆን በኑሮ ዕወቃት። ለሥርዓቷ ታማኝ ሁን፥ አንተ ወደ ሥርዓቷ እደግ እንጅ ሥርዓቷ ወደ አንተ ፈቃድ እንዲወርድልህ አትውደድ፤ ሰማያውይቷን ቤተክርሰቲያን ምድራዊት እንድትሆንልህ አትፍቀድ።
በቤተክርስቲያን መንፈሳዊ አንድነቶች ካልተሳተፍክ ከቤተክርስቲያን አንድነት እየተለየህ እንደሆነ እወቅ። አሊያም፦ ኪዳን ማስደረስ፥ ማስቀደስና ንስሐ ገብቶ መቁረብ፥ በምህላ ጸሎቶቿ በአዋጅ አጽዋማቷ መተባበር ናቸው።
ከቤት ከሚጸለይ አሥር ጸሎት ይልቅ በቤተክርስታያን የሚደረግ አንድ ጸሎት እንደሚበልጥ አውቀህ በየቀኑ ወደ እርስዋ ገሥግሥ። በሕይወትህ ሁሉ ቤተክርስቲያናዊ ሁን!
🖋ርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን
✨☘✨🌿✨☘✨🌿✨☘🌿✨
“ዳዊትም በራሱ ዘመን የእግዚአብሔርን አሳብ ካገለገለ በኋላ አንቀላፋ፥ ከአባቶቹም ጋር ተጨምሮ መበስበስን አየ፤
የሐዋ ፲፫÷፴፮
‹‹ምነው ዝም ብላችሁ ብትኖሩ!
ይህ ጥበብ በሆነላችሁ ነበር።››
(ኢዮብ 13፡5)
❇️ ቅዱስ ኢዮብ ❇️*አብርሃም ይስሐቅን *ይስሐቅ ኤሳውን *ኤሳው ራጉኤልን *ራጉኤል ዛራን *ዛራ ኢዮብን ይወልዳሉ:: +ቅዱስ ኢዮብ የነበረው እሥራኤል በግብፅ በባርነት ሳሉ ነበር::ኢዮብ ይሕ ቀረህ የማይሉት ባለጠጋ: ደግና እግዚአብሔርን አምላኪ ነበር:: የኢዮብ ደግነት የተመሰከረው በሰው(በፍጡር) አንደበት አልነበረም:: በራሱ በፈጣሪ አንደበት እንጂ::በዚህ የቀና ጠላት ዲያብሎስ ግን ኢዮብን ይፈትነው ዘንድ ከአምላክ አስፈቀደ::ጌታችን የጻድቁን የትዕግስት መጠን ሊገልጥ ወዷልና ሰይጣን ኢዮብን በሐብቱ መጣበት::በአንድ ጀምበርም ድሃ ሆነ:: እርሱ ግን ፈጣሪውን ባረከ:: +ሰይጣን ቀጠለ:- የአብራኩን ክፋዮች (ልጆቹን)አሳጣው:: ኢዮብ አሁንም አመሰገነ::በሦስተኛው ግን ሰውነቱን በቁስል መታው:: ቁስል ሲባልበዘመኑ እንደምታዩት ዓይነት አልነበረም:: ከሰው ሕሊናበላይ የሆነ አሰጨናቂ ደዌ ነበር እንጂ::ጻድቁ የአንድ ወጣት እድሜ ያሕል በመከራው ጽናት እየተሰቃየ ገላውን በገል ያከው ነበር::ከአፉ ግን ተመስገን ማለትን አላቁዋረጠም:: በመጨረሻም ሰይጣን በሚስቱ መጣበት::"እግዚአብሔርን ተሳደብ" አለችው::እርሱ ግን መለሰ:- "እግዚአብሔር ሰጠ:እግዚአብሔርም ነሣ:የእግዚአብሔር ስም የተባረከ ይሁን አለ::"ከዚሕ ሁሉ ነገር በኋላ እግዚአብሔር ሰይጣንን ከጎዳናው አስወገደው:: ጤናውን: ሐብቱን: ልጆቹን ለኢዮብ መለሰለት::ካለው እድሜ ላይ 140 ዓመት ጨመረለት:: ጻድቅና የትዕግስት ሰው ቅዱስ ኢዮብ በ248 ዓመቱ በዚችም ቀን ዐረፈ:: =>እግዚአብሔር አምላክ ከጻድቁ ኢዮብ ትዕግስትና በረከትን ያድለን።
💐ኢያቄም ወሐና ወለዱ ለነ ሰማየ ፤ ሰማዮሙኒ አስረቀት ለነ ፀሐየ ። 💐ኢያቄምና ሐና ሰማይን ወለዱልን፤ ሰማያቸው ደግሞ ፀሐይን አስገኘችልን ። 📚ቅዱስ ያሬድ💐 ግንቦት አንድ ፦ 💐ከፀሐይ ሰባት እጅ የምታበራ ፤ 💐የመልኳ ደምግባት ከስኳርና ከማር ይልቅ ደስ የሚያሰኝ ፤ 💐የመዓዛዋ ሽታ ከሽቶ ሁሉ የሚበልጥ፤ 💐የእግዚአብሔር ስጦታ የሆነች፤ 💐ድንግል ማርያም ተወለደች ። 💐እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የልደት በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ❗️ 💐 ድንግል ሆይ የልደትሽ ቀን ልደታችን ነው ። 💐 መልካም💐 በዓል 💐 💐 💐💐💐💐💐 💐💐💐💐💐 💐💐💐 💐
እንኳን አደረሳችሁ
በሐኪ ማርያም ማርያም ዘገነት ኮል።
ዕፀ ጳጦስ ዕፀ ጳጦስ መዝገቡ ለቃል።
ድንግል ማርያም የሱፍ አበባ ትባላለች። የሱፍ ተክሉ እሾሃም ሲሆን አበባው እሾህ የለውም። ድንግል ማርያምም መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ ከነበረባቸው የሰው ልጆች የተገኘች መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ የሌለባት ንጽሕት ናት።
ድንግል ማርያም ሶምሶን ከሞተ አንበሳ ያገኛትን የማር ወለላ ትመስላለች። በመርገም ከነበሩ የተገኘች መርገም የሌለባት ንጽሕት ናትና።
ድንግል ማርያም ሙሴ ባያት ዕፀ ጳጦስ ትመሰላለች። እሳተ መለኮትን በሥጋ ስትፀንስ እሳተ መለኮት አላቃጠላትም። ለጨለማው ዓለም የሚያበራ ብርሃንን የያዘችልን መቅረዝ ናት። ለተራበው ዓለም ዘለዓለማዊ ሕይወትን የሚሰጥ ምግብን ይዛልን የመጣች መሶበ ወርቅ ናት። የሕይወት ፍሬን የወለደችልን የሕይወት ዛፍ ናት።
የብርሃን እናት ዛሬ ተወለደች
"ሐና አንቺን ያፈራችባት
ኢያቄምም አንቺን ለሕይወት ያፈራባት
የደስታ ሰዓት ምንኛ የተባረከች የተቀደሰች ናት
የዓለሙ ሁሉ መድኃኒት አንቺ ነሽና
አንዲት ርግቤ ሆይ ተአምርሽን አመሰግናለው "
ማኅሌተ ጽጌ
የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የልደት ቀን ለክርስቲያኖች ሁሉ የደስታ ዕለት ናት ቅዱስ ያሬድ " ከኢያቄምና ከሐና ስለተወለደች ስለማርያም ልደት ዛሬ ደስታ ሆነ የብርሃን እናት በእውነት ተወለደች" እንዳለ ይህ ቀን የደስታችን ቀን ነው ለምን ቢሉ የመመኪያችን ዘውድ የንጽሕናችን መሠረት ድንግል ማርያም የተወለደችበት ዕለት ነውና፣ የነቢያት የትንቢታቸው ፍጻሜ የዓለም ብርሃን የተባለ መድኃን ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስን የምትወልድን የብርሃን እናቱ ድንግል ማርያም የተወለደችበት ዕለት ነውና ነው ፡፡
በአሰላ መ/ጵ/ር/ገ/ወአ/ደ/ም/ቅ/ማ/ቤ/ክርስቲያን እንገናኝ።
✨✨✨🍁✨✨✨
✨ኑ አንጾኪያን እንጎብኛት✨
ደቀ መዛሙርት በአንፆኪያ ክርስቲያን ተባሉይህንን የተቀደሰ ስም የተቀበልንባት፣ በ ኢየሩሳሌም ታላቅ ስደት በቤተ ክርስቲያን ላይ በተደረገ ጊዜ ምዕመናን መጥተው የተጠጉባት ታላቋ የሮማውያን ሦስተኛዋ መናገሻ ከተማ አንፆኪያን ለማየት ጉዞ ጀምረናል። አውሮፕላኑ ማኮብኮብ ሲጀምር ከቀኑ 1:15 ሆኖ ነበር። ቀኑ በ ኢትዮጵያ አቆጣጠር ሚያዝያ 27/2018 ዓ.ም ነው። ለአሕዛብ የመጀመሪያው ወንጌል የተሰበከ በዚህ ከተማ ነው። ✨🍁✨ ከምድረ እስራኤል በስደት አንፆኪያ የደረሱ ምእመናን ወንጌልን ለአይሁድ ካልሆነ በቀር ለማንም አይነግሩም ነበር፤ በኋላ ግን የቆጵሮስና የቀሬና ሰዎች መጥተው ለግሪክ ሰዎች ወንጌልን መስበክ ሲጀምሩ በአሕዛብም ዘንድየ እግዚአብሔር ጸጋ በዛ። በ ኢየሩሳሌም የነበሩ ሐዋርያትም ይህንን ዜና ሲሰሙ ደስ ሳይላቸው አልቀረምና አከታትለው ከታመኑ መምህራን መካከል በርናባስን ላኩላቸው። በርናባስ ባየው ነገር ደስ በመሰኘቱ ጳውሎስ የተባለውን ሳውልን ከጠርሴስ ፈልጎ አምጥቶ ለአንድ ዓመት በዚህች ከተማ በኅብረት አስተምረዋል። ✨🍁✨ በቀላውዴዎስ ቄሳር የተደረገው ረሀብ እንደሚመጣ አስቀድመው የተናገሩ ነቢያት የነበሩትም በዚህችው ከተማ ነበር። የመጀመሪያው የሐዋርያት ሲኖዶስ ውሳኔ ተጽፎ በጳውሎስና በበርናባስ እጅ የተላከው ለአንጾኪያ ቤተ ክርስቲያን ነው ። ቅዱስ ጴጥሮስን ጨምሮ ታላላቅ ሐዋርያት መጥተው ያስተማሩባት የክርስቲያኖች አገር አንጾኪያ እንደምን ሆና ይሆን? ጳውሎስ ያስተማራቸው ደቀ መዛሙርት ተተኪ ይኖራቸው ይሆን? የወንጌላዊው ሉቃስ የትውልድ ስፍራናት ምናልባት ዛሬም እንደ ሉቃስ ያሉ ጠቢባን ክርስቲያኖች ተወልደውባት ይሆን? አንጾኪያ እንደምናት? እስከማያት ቸኩያለሁ። 📝ሊቀ ሊቃውንት ስምዓኮነ መልአክ ✨✨✨🍁✨✨✨
ቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባውን ማካሄድ ጀመረ።
በቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረት ከበዓለ ትንሣኤ በኋላ በሃያ ኣምስተኛው ቀን የሚካሄደው ዓመታዊው የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ተክለሃይማኖት የመግቢያ ንግግር ተጀምሯል።
ጉባኤው በይፋ መጀመሩን ተከትሎ የቋሚ ሲኖዶስ ሪፖርት ለምልዓተ ጉባኤው ቀርቧሎ
በመቀጠልም የሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የሚወያይባቸውን አጀንዳዳዎች የሚያቀርብ አርቃቂ ኮሚቴ አባላት ተመረጠዋል።
የኮሚቴ አባላቱም
1. ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ሊቀ ጳጳስ
2. ብፁዕ አቡነ ኤውስጣቴዎስ (ዶ/ር) ሊቀ ጳጳስ
3. ብፁዕ አቡነ እንጦንስ ሊቀ ጳጳስ
4.ብፁዕ አቡነ ቴዎፍሎስ ሊቀ ጳጳስ
5. ብፁዕ አቡነ ኤርሚያስ ሊቀ ጳጳስ
6. ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ ሊቀ ጳጳስ
7.ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ ጳጳስ
መሆናቸውን የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት የሚዲያ ኃላፊ መምህር ዳንኤል ሰይፈሚካል ለመገናኛ ብዙኃን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት (#EOTCTV) ገልጸዋል።
የመጀመሪያዎቹ ሰዎች በፈጸሙት ስሕተት መነሻነት ምድርንና ምድራውያንን ለከባድ ቅጣትና መርገም የዳረገው ይህ መለያየት ለሰማያውያኑም ተርፎኣል፤
ምክንያቱም መለያየቱ በእግዚአብሔርና በሰው፣ በመላእክትና በሰው፣ በሰውና በሰው፣ በነፍስና በሥጋ ጭምር የጥል ግድግዳን ገንብቶ እስከ ክርስቶስ ዕለተ ስቅለት መዝለቁን በቅዱስ መጽሓፍ የምናውቀው ስለሆነ ማለት ነው።
ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ ኣባላት!
ቀዳማዊና ዘላለማዊ የሆነው ወልደ እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ሰብእናችንን ተዋሕዶ በዚህ ዓለም የተገለጸው ሰማያውያንንና ምድራውያንን የለያየው የጥል ግድግዳን ለማፈራረስ ነው፤
ለመለያየት ምክንያት የሆነችውን ኃጢኣት በሰውነቱ በመቅጣት የሕግን ትእዛዝ ከፈጸመ በኋላ የዕርቁን ተግባር በወሳኝ መልኩ ኣከናውኖታል፤
በክርስቶስ ቤዛነት የሆነው ይህ ዕርቅ በእግዚአብሔር ዘንድ እጅግ የተወደደ ነበረና እሱ ራሱ በክርስቶስ ሆኖ ዓለሙን ከራሱ ጋር ኣስታረቀ፤
ለዚህም ነው ተበዳይ እሱ፣ ቤዛዊ መሥዋዕት ሆኖ የቀረበው እሱ፣ ኣስታራቂ እሱ፣ ታራቂ እሱ ሆኖ የምናገኘው፤ ለሱ የሚሳነው ነገር የለምና ለኛ ግር የሚል ቢመስልም ለሱ ቀላል ነበረ።
በዚህ የዕርቅ ተግባር ሰውና እግዚአብሔር፣ ሰውና መላእክት፣ ሰውና ሰው፣ ነፍስና ሥጋ ታርቀው በይፋ ተገናኙ፤ በኅብረትና በኣንድነትም መኖር ቻሉ፤ በቀኙ ለተሰቀለው ሽፍታ “ዛሬውኑ ከኔ ጋር በገነት ትኖራለህ” የሚለው ቃለ ምሕረትና “ኣባት ሆይ፥ ነፍሴን በእጅህ ኣደራ እሰጣለሁ” የሚለው ቃለ ኣማሕፅኖ የዕርቁ፣ የግንኙነቱና የኣንድነቱ ማሳያ ኣስረጅ ናቸው።
ስቅለተ ክርስቶስ ነፍሶቻችን ወደ ግዞት ቤት ሳይሆን ወደ ገነት እንዲገቡ፣ የሚቀበላቸውም ራሱ እግዚአብሔር እንዲሆን ያስቻለ ታላቅ መለኮታዊ ፍጻሜ ነው፤
እኛ “ክርስቶስ መድኃኒታችን ነው፤ ኣድኖናል” ብለን በልበ ሙሉነት የምንመሰክረው፣ እሱም “ሰላሜን ሰጠኋችሁ” ብሎ የሚያረጋጋን በመሰቀሉ ይህንን ውጤት ስላስገኘልን ነው።
ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ ኣባላት!
የድኅነታችንና የሰላማችን መሠረት የሆኑትን የክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ለዓለም ማኅበረ ሰብ የማብሰርና የማሥረጽ ተግባር የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ቍጥር ኣንድ ተልእኮ ነው፤
ነገረ ሞቱና ነገረ ትንሣኤው በኣስተውሎት፣ በጥልቀትና በተመሥጦ ስናስተምር በውስጡ የምናገኘው የዕርቅ፣ የሰላምና የኣንድነት ምስጢር ነው፤
እንደ እውነቱ ከሆነ እኛ የክርስቶስ መልእክተኞች እንደ ቃሉ ራሳችንን ክደን በሚጠበቀው መጠን ተልእኮኣችንን መወጣት ብንችል ኖሮ፣ ኣሁን በዓለማችን የተፈጠረው መለያየትና ግጭት ኣይኖርም ነበር፤
ችግሩን ሙሉ በሙሉ ማስቀረት ባንችልም በእጅጉ መቀነስና ዓቅሙን ማዳከም እንችል ነበር፤ ነገር ግን ተልእኮኣችንን በኣግባቡ ኣለመወጣት ኣንድ ነገር ሆኖ የዓለሙ መሳሪያ ሆነን መገኘታችን “በዕንቅርት ላይ…” ሆኖ ይስተዋላል።
ይሁንና ኣሁንም ሕዝቡን ወደ ኣንድነት፣ ወደ ፍቅር፣ ወደ ሰላም፣ ወደ ዘላቂ የጋራ ጥቅምና ወደ ፈሪሐ እግዚአብሔር ማምጣት የጉባኤያችን ዓቢይ ተግባር ሊሆን ይገባል፤ እነዚህ ካሉ የምናጣውም ሆነ የሚያመልጠን የለምና ነው፤
ሃገርን በኃላፊነት ተረክባችሁ በላዕላዊ፣ በማእከላዊና በታሕታዊ መዋቅር የምትገኙ፣ እንደዚሁም ኣማራጭ ሓሳብ ኣለን ብላችሁ የምትንቀሳቀሱ ልኂቃነ ሃገር ፣ ሁላችሁም እግዚአብሔርን ከሚያውቅ፣ ከሚያመልክና ከሚፈራ ሕዝብ የተገኛችሁ ናችሁና በልባችሁ እግዚአብሔርን ፍሩ፤ ድምፁንም ስሙ፤ የሱ ገንዘብ በሆኑ ፍጡራንም ኣትጨክኑ፤ ሰውን መያዝ የሚቻለው ኅሊናን በመርታት እንጂ በሌላ ኣይደለምና፣
የሕዝቡን ፍላጎትና የልብ ትርታ በሚገባ ኣዳምጡ፤ ሕዝቡ የሚፈልገው በኣንድነትና በእኩልነት መኖር፣ በሰላም ወጥቶ መግባት፣ ፍትሕን ማስፈን፣ ለኑሮው የሚበቃ ምጣኔ ሃብትን ማግኘት፣ የእምነት ነጻነትና እኩልነት መረጋገጥ የመሳሰሉት ናቸው።
ሕዝቡ እነዚህ ከተሟሉለት ተደመጠ ማለት ነው፤ ከተደመጠ ደግሞ እሱም በበኩሉ ያደምጣል፤ ይከተላልም፤
ስለሆነም ለሁሉም ልጆቻችንና ወገኖቻችን የምናስተላልፈው ወቅታዊ ጥሪ ሁሉንም ችግሮቻችን በሰላምና በሰላም ብቻ ለመፍታት ተባበሩ የሚል ነው፤ ከዚህ ውጭ የሚደረገው ኣማራጭ ሁሉ ለዘላቂ ሰላማችን ኣይበጅም እንላለን።
በመጨረሻም፦
በቀኖና ቤተ ክርስቲያን መሠረት ከበዓለ ትንሣኤ በኋላ በሃያ ኣምስተኛው ቀን የሚካሄደው ዓመታዊው የረክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልኣተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት የተጀመረ መሆኑን ለሕዝበ ክርስቲያኑና ለመላው ኢትዮጵያውያን እናበስራለን!!!
እግዚአብሔር ጉባኤያችንን ይባርክ!
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ወስብሓት ለእግዚአብሔር፤
አሜን!!!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ
ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘኣኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፤
ሚያዝያ 28 ቀን 2018 ዓ.ም
ኣዲስ ኣበባ - ኢትዮጵያ
መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
በስመ ኣብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ኣሓዱ ኣምላክ ኣሜን!
ብፁዕ ኣቡነ ሳዊሮስ
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ስራ ኣስኪያጅ፤
ብፁዕ ኣቡነ ዲዮስቆሮስ
የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሓፊ፤
ብፁዕ ኣቡነ ሕርያቆስ
የኣዲስ ኣበባ ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣
ብፁዓን ኣበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ ኣባላት፣
በኣጠቃላይ በዚህ ዓመታዊ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልኣተ ጉባኤ የተገኛችሁ በሙሉ፦
ማሕየዊት በምትሆን ሞቱ ሰማያውያንና ምድራውያንን ያስታረቀ፣ በቅድስት ትንሣኤውም የሙታንን ሕይወት በተስፋ ያለመለመ ጌታችን፣ ኣምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ፣ እንኳን ለዓመታዊው የረክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልኣተ ጉባኤ ኣደረሰን ኣደረሳችሁ!
“እስመ ተዋለጠ እግዚአብሔር ዓለመ በክርስቶስ ኣናኅስዮ ኃጢኣቶሙ ወኢነጺሮ ጌጋዮሙ፤ ወረሰየ ላዕሌነ ቃለ ሥምረቱ፤ ወወሃበነ መልእክተ ሣህሉ፡- እግዚአብሔር በክርስቶስ ሆኖ ዓለሙን ከራሱ ጋር ያስታርቅ ነበርና በደላቸውን ኣይቈጥርባቸውም ነበር፤ በእኛም የማስታረቅ ቃል ኣኖረ” (2ቆሮ. 5፥19)።
የእግዚአብሔርም ልጅ፣ የሰውም ልጅ የሆነው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ዓለም በሰብእነት ሲገለጽ ግልጽ የሆነ ዓላማና ግብ እንደነበረው ቅዱስ መጽሓፍ ይነግረናል፤ እሱም በሰማይም፣ በምድርም ያሉትን በሙሉ ማስታረቅ፣ ማገናኘትና ኣንድ ማድረግ ነበረ፤
ጌታችን ይህንን ሲያደርግ ሰማያውያኑንና ምድራውያኑን የለያየው ምክንያት በማስወገድ ነው፤ የመለያየቱ ምክንያት ክፉ ኅሊና ኣምጦ የወለደው በደልና እሱን ተከትሎ የተከሠተው ኃጢኣት ነበረ፤ በኃጢኣት ምክንያት የገባው ሞት ደግሞ የቅጣቱ ማሳያ ፍርድ ነበረ።
✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።እንኳን ለትንሣኤ ሃያ አምስተኛ (፳፭) ቀን ርክበካህናት (ዕለተ ጥብርያዶስ) እግዚአብሔር አምላክ በሰላም በጤና አደረሰን። ርክበ ካህናት (ዕለተ ጥብርያዶስ)፦ የሀገራችን የቅዱስ ሲኖዶስ መሰብሰቢያ ቀን ርክበ ካህናት፣ ዕለተ ጥብርያዶስ፣ ዳግሚት ዕለት አግብኦተ ግብር ምንድን ነው? ርክበ ካህናት የሁለት ቃላት ጥምረት ሲኾን እነዚህም፤ ፩ኛ. ረክብ የሚለው ቃል ተራከበ ተገናኘ ከሚለው የግእዝ ግስ የወጣ ሲሆን ትርጕሙም ማግኛ፣ መገኛ፣ መገናኛ ማለት ነው፡፡ /ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ገጽ ፰፴፩/፡፡ ፪ኛ. ክህነት የሚለው ቃል ከዲቁና ጀምሮ እስከ ከጵጵስና ድረስ ያሉትን መዓርጋት (በጥቅሉ ዲያቆናትን፣ ቀሳውስትንም ኾነ ጳጳሳትን) የሚያጠቃልል ስያሜ ነው፤ ካህን (ነጠላ ቍጥር) ሲኾን ካህናት ደግሞ (ብዙ ቍጥር) ነው፤ ብዙ ጊዜ ግን ይህን ባለማወቅ ካህናት የሚለውን ለቀሳውስት ብቻ መጠሪያ ሲኾን እናያለን፤ አለማወቅ ነው! (ለምሳሌ በቅዳሴ መጨረሻ ላይ ዲያቆኑ በእደ …… ካህን ይባርከነ ቢል ለኹሉም ያስኬዳል፥ ሰዋስዉም ያዛል፥ ሥርዐቱም ይኸው ነው፤ ነገር ግን ዛሬ ዛሬ በእደ … ካህን ይባርከነ በማለት ፈንታ በእደ ብፁዕ ፓትርያርክ፣ በእደ ብፁዕ ሊቀ ጳጳስ፣ በእደ ቆሞስ …. ሲባል ይታያል፤ መስተካከል ያለበት ጉዳይ ነው፡፡)
ርክበ ካህናት ማለትም የአባቶች ካህናት (ማለትም በጵጵስና ማዕረግ ያሉ፦ ኤጲስ ቆጶሳት፣ ጳጳሳት፣ ሊቃነ ጳጳሳትና ርዕሰ ሊቃነ ጳጳስን ያጠቃለለ (የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት) ጕባኤ፤ የካህናት መገኛ፥ መገናኛ ጉባኤ (መሰባሰቢያ፣ መወያያ) ማለት ነው፡፡✨🌿 በዓሉ በየዓመቱ የትንሣኤ በዓል በዋለ በ፳፭ኛው ቀን ሁልጊዜ በዕለተ ረቡዕ ይውላል፤ ወሩና የሚውልበት ቀን ግን በኢየዓርግና በኢይወርድ (በባሕረ ሓሳብ የበዓላትንና የአጽዋማትን) ቀመር ተከትሎ የሚወጣ ስለኾነ ከፍና ዝቅ ይላል፡፡ የአጽዋማትና የበዓላት ቀመር በቅዱስ ድሜጥሮስ አማካኝነት ከመዘጋጀቱ በፊት (ዐቢይ ጾም ሰኞ፣ ስቅለት ዓርብ፣ ትንሣኤ እሑድ፣ ርክበ ካህናት ረቡዕ፣ ዕርገት ሐሙስ፣ ጰራቅሊጦስ እሑድ እንዲሆን ከመደረጉ በፊት) ርክበ ካህናት በየዓመቱ ግንቦት ፳፩ ቀን ይውል ነበር /መጽሐፈ ግጻዌ ግንቦት ፳፩/፡፡ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን ድል አድርጐ ከተነሳ በኋላ ለደቀ መዛሙርቱ በየጸጋቸው መጠን እየተገለጠ ያጽናናቸው፥ ያጸናቸው፥ ያስተምራቸው፥ ይባርካቸውም ነበር፤ ጌታችን እስከ ዕርገቱ ባሉ ፵ ቀናትም መጽሐፈ ኪዳንን፣ ትምህርተ ኅቡዓትን፣ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያንን አስተምሯቸዋል፤ በልቡናቸውም አሳድርድሮባቸዋል፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ በዮሐንስ ወንጌል፤ ከዕርገቱ አስቀድሞ ጌታ ለደቀ መዛሙርቱ ፫ ጊዜ በጕባኤ መገለጡ ተዘግቦ ይገኛል፡፡ እነዚህም፤ 1ኛ. የትንሣኤ (ዮሐ. 20፥19) 2ኛ. የአግብኦተ ግብር (ዳግም ትንሣኤ) /ዮሐ. 20፥:26/ 3ኛ. የጥብርያዶስ፤ (ዮሐ. 21፥1) ለድንግል ማርያም ግን በኹሉም እለታት መገለጡን አበው ያስተምራሉ፡፡ በጥብርያዶስ ባሕርም ከዐሥራ አንዱ ቅዱሳን ሐዋርያት ጋር ምሳ በልቷል፡፡ የርክበ ካህናት በዓል መነሻም ጌታችን ለሦስተኛ ጊዜ ከተገለጠበት ከጥብርያዶስ ባሕር ካለው ታሪክ ጋር የተያያዘ ነው፡፡ በዚህች ዕለት በቅዱስ ዼጥሮስ መሪነት ሐዋርያቱ ወደ ጥብርያዶስ ባሕር ሔዱ፡፡ አሶችን ሊያጠምዱም በብዙ ደከሙ፤ ነገር ግን ጌታችን በረድኤት አብሯቸው አልነበረምና አንዳች አሣ በመረባቸው ሊገባ አልቻለም፡፡ ማጥመድ (አስተምሮ ከክህደት ወደ ሃይማኖት፤ ከኀጢአት ወደ ጽድቅ መመለስ) የሚቻለው በረድኤተ እግዚአብሔር እንጂ በእውቀት ብዛት ወይም በአንደበተ ርቱዕነት ብቻ አይደለምና፡፡ ሲነጋ ግን መድኀኒታችን ወደ ቅዱሳን ደቀ መዛሙርቱ መጣ፤ በጥብርያዶስ ባሕር ዳርቻም ቆሞ ታያቸው፤ ከሚወደው ደቀ መዝሙሩ ከቅዱስ ዮሐንስ በቀር ጌታችን መሆኑን ያወቀው ግን አልነበረም፡፡ ቸሩ አባት "ልጆቼ! አንዳች የሚበላ ነገር አላችሁ?" ሲል ጠየቀ፤ "ጌታ ሆይ! የለም" አሉት፡፡ "የለንም" ብሎ የሌለንን ነገር በጌታ ፊት ማመኑ እጅግ መልካም ነው፤ ምክንያቱም ያጣነውን ነገር ሊሰጠን፥ የጎደለንን ሊሞላልን፥ የጠፋብንን ሊጠቁመን ቸርነቱ ብዙ ነውና፡፡ ያን ጊዜ ሐዋርያቱን መረባቸው በመርከብ ቀኝ እንዲጥሉ አዘዛቸው፡፡ እነርሱም በደስታ ጣሉ፤ በአግራሞት እስኪሞሉ ድረስ መረባቸውን መሳብ አቅቷቸው ሊቀደድ እስኪደርስ ድረስ 153 ዓሦች ተያዙላቸው፡፡ ያን ጊዜም የሚወደው ደቀ መዝሙሩ ቅዱስ ዮሐንስ ጌታችን መኾኑን ለቅዱስ ዼጥሮስ "ጌታ እኮ ነው" አለው፤ ሽማግሌው ቅዱስ ግን ራቁቱን ነበርና ወደ ባሕሩ ተወረወረ፡፡ ከአፍታ በኋላም ጌታችን ከሐዋርያቱ ጋር በድጋሚ (ለ፪ኛ ጊዜ) ለምሳ ተቀመጠ፤ ባርኮ ሰጥቶ ልባቸውን ሊያጸና አብሯቸው በላ፡፡ በዚያች ሰዓት ቅዱስ ዼጥሮስን ፫ ጊዜ "ትወደኛለህን?" ሲል ጠየቀው፤ ቅዱሱ አረጋዊም እየደጋገመ "ለሊከ ተአምር ከመ አነ አፈቅረከ (እንድወድህ አንተ ታውቃለህ" ሲል መለሰ፡፡ ጌታም በበጐች ሐዋርያት (ካህናት)፤ በጠቦቶች አርድእት (ዲያቆናት)፤ በአባግዕት ፴፮ቱ ቅዱሳት አንስት (ምዕመናን ወምዕመናት) ላይ ሁሉ እረኛ እንዲሆን ሾመው፡፡ ይህ ምሥጢር ለጊዜው ጌታችን ሐዋርያትን፣ ሰብዐ አርድእትንና ሠላሳ ስድስቱን ቅዱሳት አንስት በአጠቃላይ መቶ ሃያውን ቤተሰብእ እንዲጠብቅና እንዲከባከብ ቅዱስ ጴጥሮስን ማስጠንቀቁን፤ ፍጻሜው ግን የቤተ ክርስቲያን አባቶች (ጳጳሳት) መምህራንንና መላው ሕዝበ ክርስቲያንን እንዲጠብቁና እንዲያስተዳድሩ በእግዚአብሔር መሾማቸውን የሚያስረዳ ትርጕም አለው ዮሐ ፳፩፥፩-፲፯ (አንድምታ ትርጓሜ)፡፡ ቀጥሎም የቅዱስ ጴጥሮስን የሰማዕትነቱን ምሥጢር ገልጦለት "ተከተለኝ" (ለጊዜው በእግር፤ በኋላ ግን በግብር ምሰለኝ) ብሎታል፡፡ ወልደ ነጐድጓድ ወፍቊረ እግዚእ ቅዱስ ዮሐንስም ሞትን እንደማይቀምስ እንዲሁ ተናግሮለታል። ✨🌿 ጌታ ለሐዋርያት በአንድነት የተገለጠባትን ይህች ቀን እነዚህ ሁሉ ተግባራት የተከናወኑባት ናትና (የትንሣኤ በዓል ፳፭ኛ ቀን) መሠረት በማድረግ፤ የኋላ ሊቃውንት በየዓመቱ የትንሣኤ በዓል በዋለ በ፳፭ኛው ቀን ዐራቱ ሊቃነ ጳጳሳት የሚሰበሰቡበት የካህናት መገናኛ ቀን ርክበ ካህናት ይሁን ብለው ወስነዋል፡፡ ከዚህ በኋላ ርክበ ካህናት በዓለ ትንሣኤ በዋለ በ፳፭ኛው ቀን፣ በበዓለ ሃምሳ እኩሌታ በዕለተ ረቡዕ ይዘከራል፤ በያዝነው ዓመት በ፳፻፲፰ (2018) ዓ.ም የትንሣኤ በዓል ከተከበረበት ዕለት (ሚያዝያ ፬ (4) ቀን) ጀምሮ ብንቆጥር ፳፭ (25) ኛው ቀን ሚያዝያ ፳፰ (28) ቀን ይኾናል፡፡ በመኾኑም የዘንድሮው ርክበ ካህናት ሚያዝያ ፳፰ (28) ቀን በዕለተ ረቡዕ ይውላል ማለት ነው፡፡ ✨ ይህ በዓል ከቅዱሳን ሐዋርያት ጀምሮ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ሲያስተዳድሩ የቆዩ አባቶቻችን ጌታንና ደቀ መዛሙርቱን አብነት በማድረግ በጋራ በመሰባሰብ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን የተቀላጠፈ አገልግሎት እንደዚሁም ለምእመናን አንድነትና መንፈሳዊ ዕድገት የሚበጁ መንፈሳውያን መመሪያዎችን የሚያስተላልፉበት እለት ነው፡፡ © ተአምኆ ቅዱሳን ✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨
