ar
Feedback
ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

الذهاب إلى القناة على Telegram

በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:-  @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

إظهار المزيد
671
المشتركون
+324 ساعات
+77 أيام
+430 أيام
أرشيف المشاركات
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የሁለተኛ ቀን በተለያዩ አጀንዳዎች ውሳኔ አሳለፈ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ በዛሬው ሁለተኛ ቀን ውሎው በአጃንዳ ቁጥር 5 እና 6 ላይ በሁለት አጀንዳዎች ውይይት በማድረግ ውሳኔዎችን አሳልፏል፡፡ ረዳት ፕሮፌሰር መምህር ዳንኤል ሰይፈሚካኤል የጥናትና ምርምር መምሪያ እና የቅዱስ ሲኖዶስ የኮሚዩኒኬሽን ኃላፊ ለመገናኛ ብዙኃን አገልግሎት ድርጅት #EOTCTV የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በዛሬው ጥቅምት 13 ቀን 2018 ዓ.ም በወሰናቸው ውሳኔዎች ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል። ቅዱስ ሲኖዶስ አጀንዳ ቁጥር 5 የነበረው ውይይት ከተለያዩ የቤተክርስቲያኒቷ አህጉረ ስብከቶች ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት እንዲመደብላቸው ጥያቄ የቀረቡትን የተመለከተ ነበር፡፡ ይህንንም ጥያቄ መልስ ለመስጠትና ውሳኔ ለማሳለፍ አስቀድሞ ምልዓተ ጉባኤው አምስት ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትን ለኮሚቴነት በመሰየም የቀረቡትን ጥያቄዎች በማየት የውሳኔ ሐሳብ ለምልዓተ ጉባኤው እንዲያቀርቡ  በማድረግ አምስት  አባቶችን ሰይሟል፡፡የተሰየሙት ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትም ከምልዓተ ጉባኤው ጎን ለጎን  የቀረቡትን ሦስት ጥያቄዎች  በኮሚቴው በማየት የምክረ ሐሳብና የውሳኔ ሐሳብ  ለምልዓተ ጉባኤው አቅርበዋል፡፡ ብፁዓን አባቶችም ባቀረቡት የውሳኔ ሐሳብም ምክንያት  ምልዓተ ጉባኤውም ሰፊ ውይይት በማድረግ  አሳልፏ በዚህም መሠረት፡   1ኛ. የምሥራቅ ጎጃም  ሀገረ ስብከት ያቀረበውን አባት  ይመደብልን የሚል ጥያቄ  በተመለከተ ብፁዕ አቡነ ቶማስ የአዊና የመተከል አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከትን  ደርበው የምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከትን እንዲመሩና እንዲይዙ ምልዓተ ጉባኤው ወስኗል፡፡ በ2ኛ ደረጃ ደግሞ ከደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት ብፁዕ አቡነ አትናቴዎስ ያቀረቡት  እንዲሁ አባት እንዲመደብ ጥያቄ ነው፡፡ ብፁዕነታቸው በሚመሩአቸው የደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት  የከሚሴ የደቡብ ወሎ ልዩ ዞን  ሁለቱን ሀገረ ስብከቶች አባት እንድመደብላቸው  ባቀረቡት ጥያቄ መሠረት የብፁነታቸውን ጥያቄ ተቀብሎ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በአቀረቡት የውሳኔ ሐሳብ መሠረት  ለአግልግሎትም እንዲመች በአቅራቢያ የሚገኙትን የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ ደርበው እንዲመሩ ምልዓተ ጉባኤው  ወስኗል፡፡      በ3ኛ ደረጃ ከምሥራቅ ወለጋ፣ ከምዕራብ ወለጋ ከሆሮ ጉድሩ ወለጋ የቀረቡ አባት እንዲመደብ የቀረቡ ጥያቄዎችን በአጀንዳ ቀርጾ በብፁዓን አባቶች በቀረበው የውሳኔ ሐሳብ መሠረት የምሥራቅ ወለጋንና የሆሮ ጉድሩን ብፁዕ አቡነ ኒቆዲሞስ የምሥራቅ ሐረርጌ ጳጳስ ሀገረ ስብከታቸውን እንደያዙ  ደርበው እንዲመሩ የቅዱስ ሲኖዶስ  ምልዓተ ጉባኤ ወስኗል፡፡ የምዕራብ ወለጋን በተመለከተ ደግሞ ብፁዕ አቡነ ኤውስጣቴዎስ  የአሉባቦር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ  የምዕራብ ወለጋና ደርበው እንዲመሩ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ወስኗል፡፡  እነዚህን ውሳኔዎች ሲወስንም ቅዱስ ሲኖዶስ አሁን በተደራቢ እንዲመሩ የተያዙት አህጉረ ስብከት   በዘላቂነት ሊቃነ ጳጳሳት  ተመድበው እስከፈታ ድረስ የተወሰነ ውሳኔ መሆኑን ነው  ረዳት ፕሮፌሰር መምህር ዳንኤል ሰይፈሚካኤል ለመገናኛ ብዙኃን አገልግሎት ድርጅት #EOTCTV  የገለጹት። በ6ኛ ተራ ቁጥር የነበረው አጀንዳ የኢትዮጵያ ገዳማት ኅብረት ያቀረበውን ጥያቄ በተመለከተ ውይይት የተደረገበት አጀንዳ ነው፡፡  በዚህ አጀንዳ ላይ  የገዳማቱ የሥራ አስፈጻሚ አባላት የሆኑት  አባቶች ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ቀርበው ጥያቄአቸውን በንባብ አሰምተዋል፡፡ የኢትዮጵያ ገዳምት ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ  ያደረጋቸውን ሥራዎች የሚገልጽ በዚያም በየደረጃው በገዳማት መምሪያና በቋሚ ሲኖዶስ  በተሰጡአቸአቸው የመተዳደሪያ ደንቦች ሥራቸውን እያካሄዱ እንደሆነ ከዚያም ደግሞ የገዳማቱ አባቶች ለተልዕኮና ለተለያዩ ጉዳዮች ወደ አዲስ አበባ በሚመጡበት ጊዜ ማረፊያ ስለሚያስፈልጋቸው ለቅዱስ ሲኖዶስ ባቀረቡት መሠረት ይህን የመሰለውን አጀንዳዎቻቸውን ለቅዱስ ሲኖዶስ በንባብ አሰምተዋል፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስም የአባቶችን  በመስማት  ውይይት በማድረግ ውሳኔ አሳልፏል፡፡  በዚሁ መሠረት በአንደኛ ደረጃ የገዳምቱ ኅበረት ያቀረቡት  ከገዳም ለአገልግሎትና ለተለያየ ተልእኮ  ወደ  አዲስ አበባ ሲመጡ የሚያርፉበት ቦታ ያለውን አስፈላጊነት  ምልዓተ ጉባኤው በመገንዘብ  በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ተመቻችቶ  በዚያ መልስ እንዲሰጣቸውና  በሁለተኛ ደረጃ የገዳማት ኅብረቱ  ለገዳማት ዘላቂ ልማትና ራስን ለመቻል  በልማት ለሚያካሂዷቸው እንቅስቃሴዎች  ጥያቁዎችን የተመለከተ ነው፡፡  ይህንንም ጥያቄ ምልዓተ ጉባኤው በሰፊው በመወያየት  ጉዳዩ ጥናት የሚያስፈልገው፣ የሕግ አስተያየት የሚያስፈልገው በመሆኑ ጥያቄው ለመንበረ ፓትርየርክ ጠቅላይ ቤተክህነት  በቋሚ ሲኖዶስ ክትትል ወደፊት ውሳኔ  ይሰጠዋል በማለት ምልዓተ ጉባኤው ወስኗል፡፡  በዛሬው ዕለት በአጀንዳ ቁጥር 5 እና 6  ቅዱስ ሲኖዶስ  ያደረገው ውይይት ይህን ይመስላል፡፡ በቀጣይ በቀሪዎቹ አጀንዳዎች ላይ  ምልዓተ ጉባኤው ውይይቱን የሚቀጥል ይሆናል፡፡ ©EOTC TV

" የሰውን ሥራ አፌ እንዳይናገር ፈቃዴ ነው፤ ስለ ከንፈሮችህ ቃል ጭንቅ የሆኑ መንገዶችን ጠበቅሁ።"              መዝሙረ ዳዊት 17: 4

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ የመጀመሪያ ቀን ውሎው በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ውሳኔ ሰጠ። (ጥቅምት ፲፪ ቀን ፩፻፲፰ ዓ.ም) የቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤትን በመወከል መግለጫውን የሰጡት መምህር ዳንኤል
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ የመጀመሪያ ቀን ውሎው በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ውሳኔ ሰጠ። (ጥቅምት ፲፪ ቀን ፩፻፲፰ ዓ.ም) የቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤትን በመወከል መግለጫውን የሰጡት መምህር ዳንኤል ሰይፈሚካኤል  ጉባዔው በመጀመሪያውን ቀን ጉባዔው ፲፮ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ማጽደቁን ገልጸዋል። በጠዋቱ ውሎ  ፯ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን አጀንዳ እንዲቀርጹ ውሳኔ ያሳለፈ ሲሆን እነዚህም ሊቃነ ጳጳሳት ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ፣ ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል ፣ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ፣ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል፣ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ፣ ብፁዕ አቡነ ሩፋኤልና ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ናቸው ፡፡ ኮሚቴው በብፁዕ አቡነ ጎርጎሬዎስ በሰብሳቢነት በብፁዕ አቡነ ዲዎስቆሮስ በአስረጂነት ተሰብስቧል። ምልዓተ ጉባኤው በከሰዓቱ ውሎም ከ፲፮ቱ አጀንዳዎች በ፬ቱ ላይ ውሳኔ የሰጠ መስጠቱን ለመገናኛ ብዙኃን ድርጅት ያስታወቀ ሲሆን እነዚህም ውሳኔዎች ፩- ቅዱስነታቸው በጠዋቱ የመክፈቻ ጸሎት ያስተላለፉት መልዕክት በቀጣይ የሥራ መመሪያ አድርጎ ምልዓተ ጉባዔው አጽድቋል፡፡ ፪-ከጥቅምት ፬-፲ በነበረው የሰበካ መንፈሳዊ ዓለም ዓቀፍ ጉባኤ የነበሩ የቡድን ውይይቶች በቃለ ጉባኤ ቀርቦ ቃለ ጉባዔውን ምልዓተ ጉባዔው የ፳፻፲፰ ዓ.ም የሥራ መመሪያ አድርጎ አፅድቋል፡፡ ፫-ሀገራዊ ሰላምን አስመልክቶ ምልዓተ ጉባዔው በግንቦት ተወያይቶ ሊቃነ ጳጳሳትን የያዘ ኮሚቴ ያዋቀረ ሲሆን ኮሚቴው የተሰጠውን ኃላፊነት አጠንክሮ እንዲቀጥል ተወያይቶ አጽድቋል፡፡ ፬-በትግራይ የተፈጠረው ወቅታዊ ክፍፍልን አስመልክቶ የተወያየ ሲሆን በውይይቱም ህዝቡ ህዝባችን አብያተ ክርስቲያናቱም የቤተክርስቲያን ሀብት እንደመሆናቸው ቀደም ብሎ የተዋቀረው የሰላም ኮሚቴ ሥራውን አጠንክሮ እንዲቀጥል በምልዓተ ጉባኤው ወስኗል። ©ኢኦተቤ

የእስጢፋኖስ መንገድ ለእውነት እስከ ሞት መታመን። እኒህ ድንጋይ ያነሡትኮ አላዋቂነታቸው ሸፍኗቸው እንጂ ዘለዓለማዊ ሕይወት የሚገኝበትን ትምህርት የሚነግራቸውን ሰው አይገድሉትም ነበር። ብንችል እንደ
የእስጢፋኖስ መንገድ ለእውነት እስከ ሞት መታመን። እኒህ ድንጋይ ያነሡትኮ አላዋቂነታቸው ሸፍኗቸው እንጂ ዘለዓለማዊ ሕይወት የሚገኝበትን ትምህርት የሚነግራቸውን ሰው አይገድሉትም ነበር። ብንችል እንደ ቅዱስ እስጢፋኖስ እንሁን። አርአያ እናድርገው። ባንችል ግን ቢያንስ ዘለዓለማዊ የሕይወት ትምህርት በሚያስተምሩን ላይ ድንጋይ አናንሳ። ድንጋይ ለእስጢፋኖስ የሰማዕትነትን ክብር ያገኘበት ሲሆን፣ ድንጋይ ላነሡት ደግሞ የሕይወት ትምህርትን የሚነግራቸውን ሰው ያጡበት ነው። የንግግራችን፣ የሐሳባችን፣ የድርጊታችን ማዕከል ዘለዓለማዊው ሕይወት ይሁን። እውነት ሐሳባችን ወይም ንግግራችን ወይም እያንዳንዱ ተግባራችን ወደ ዘለዓለማዊው ሕይወት ለምናደርገው ጉዞ ግብአት ይሆናል??! ራስን ቆም ብሎ መመርመር ይገባል። የሰማዕቱ በረከት ይደርብን ጥቅምት 17/2018 ዓ.ም የሰማዕቱ በዓለ ንግስ በአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል በድምቀት ይከበራል። ኑ አብረን እናንግስ!

"ዳዊት በቀንም በማዕልትም ሕጉን የሚያነብ ብጹዕ ነው ብሏልና ፡፡ በጎዳናም ቢሆን ፤ በቤትም ቢሆን ፤ ስትተኛም ቢሆን ፤ ከእርሱ ይቅርታንና ቸርነትን ታገኝ ዘንድ ፤ ፈጣርህ እግዚአብሔርን በፍፅም ህሊናህ ፤ በፍፅም አእምሮህ ፤ በፍጹም ልቦናህ ፤ ውደደው" !! ።        መፅሐፈ ዲዲስቅልያ

የጥቅምት ቅዱስ ሲኖዶስ የመክፈቻ ጸሎት።
+5
የጥቅምት ቅዱስ ሲኖዶስ  የመክፈቻ  ጸሎት።

ካህናት ዲያቆናትን መስቀል ሲያሳልሙ "በረከተ እስጢፋኖስ ይኅደር በላዕሌከ ፣ የቅዱስ እስጢፋኖስ በረከት በላይህ ይደር" ይላሉ። ይህች በረከት መብል ለማሰናዳት ብትሾምም ቃለ እግዚአብሔርን በጸጋ እና
ካህናት ዲያቆናትን መስቀል ሲያሳልሙ "በረከተ እስጢፋኖስ ይኅደር በላዕሌከ ፣ የቅዱስ እስጢፋኖስ በረከት በላይህ ይደር" ይላሉ። ይህች በረከት መብል ለማሰናዳት ብትሾምም ቃለ እግዚአብሔርን በጸጋ እና በሞገስ ወደ ማስተማር የተሻገገረች፣ ክርስትናን በአንድ ቦታ ብቻ ይጸና ዘንድ ብትሰየምም፣ በውግረተ አእባን ክርስቲያኖችን በትና ወንጌልን በዓለም ሁሉ ያዳረሰች በረከት ናት።   የቅዱስ እስጢፋኖስ በረከት አይሁድ ሊቃወሟት ስለማይችሉ ላለመሰማት ጆሮአቸውን የሚደፍኑባት፣ የሐሰት ክስ ማዕበል ቢወርድባትም በቅዱሱ ፊት ከፀሐይ ሰባት እጅ የምታበራ፣ በድንጋይ ወግረው ሊያስቀሯት ቢሞክሩም ከድንጋዩ ዝናብ አሻግራ ቅድስት ሥላሴን አይታ የመንፈስ ቅዱስን መውረድ ፈጽማ የምታደንቅ በረከት ናት።   እኛም በረከተ እስጢፋኖስን ተስፋ እና ኃይል በማድረግ ሰማዕቱ በዕሪና ባያቸው በአብ፣ በወልድ፣ በመንፈስ ቅዱስ ስም አምነን ክቡር የሆነውን የእግዚአብሔርን ቃል መማር ማስተማር እንጀምራለን። ንዑድ ክቡር የሚሆን የሰማዕታት መጀመሪያ ቅዱስ እስጢፋኖስንም እንዘክራለን።   ጥቅምት 17/2018 ዓ.ም ቅዱስ እስጢፋኖስ በተሰየመበት ዓመታዊ ክብረ በዓሉ ነው። ስለሆነም በአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል በዓለ ንግሱ በድምቀት ይከበራል። ኑ አብረን እናንግስ🙏

"ከንቱ ውዳሴ በመንገድ ሁሉ የሚከተልህ የተሸሸገና ጭንብል ያጠለቀ ሌባ ነው። አሳዳጅ በመሆኑ በጣም ደኅንነት በሚሰማህ አሳቻ ሰዓት ሳታውቀው ይዘርፈሀል፤ ይገድልህማል። " ቅዱስ ጎርጎርዮስ

✨✨✨🍂🍂✨✨✨🍂🍂✨✨✨ ምጽዋት ብዛት ወይስ ጥራት? የማትፈልገውን ሳይሆን ለአንተ ምርጥ የምትለውን መስጠት ልመድ። የአገልግሎት ዘመኑን የጨረሰ ልብስ፣ ለመመገብ አስቸጋሪ የሆነ፣ የሻገተ ወይንም የደረቀ ምግብ መስጠት የተለመደ በሆነበት ዘመን ላይ ስላለህ የምታደርገውን ሁሉ ተጠንቅቀህ አድርግ። ✨✨🍂 አንተ የማትለብሰው ስለማይለበስልህ ነው። የማትበላው በጤናህ ላይ ችግር ስለሚያስከትልብህ ነው፤ ታድያ ለወንድምህስ የምትሰጠው ለሕመም የሚዳርገውን ነውን? መሆን የለበትም። ይልቁንም ለወንድምህ ከምትበላው አካፍለው። ከምትለብሳቸው ሁለቱ ልብሶች አንዱን ስጠው። የሚጎዳውን ብዙ ነገር ከምትሰጠው የሚጠቅም ትንሽ ነገር ስጠው። ለአንተ የምትመኝውን ጥራት ለወንድምህም አድርግ። "እውነት እላችኋለሁ ከሁሉም ከሚያንሱት ከነዚህ ወንድሞቼ ያደረጋችሁት ለኔ አደረጋችሁት" ማቴ 25፥40 ያለውን ቃል መለስ ብለህ አስብና የምትሰጠውን ጎጂ ነገር ለክርስቶስ እንደምትሰጠው ተረዳ። ✨✨🍂 አቤልና ቃየል ለእግዚአብሔር ያቀረቡት መሥዋእት እንዴት እንደነበረ አሰብ። "አቤልም ደግሞ ከበጎቹ በኩራትን ከስቡ አቀረበ። እግዚአብሔርም ወደ አቤልና ወደ መሥዋእቱ ተመለከተ።"ዘፍ 4፥4 ለምን መረጠለት? ብትል አቤል ካለው ሁሉ መርጦ የተሻለውን ለእግዚአብሔር መስዋዕት አድርጎ ስላቀረበ ነው። በሐዋርያት ሥራ 4፥34-35 ላይ ሰፍሮ የሚገኝውን የሐዋርያቱ ሕይወት ምን ይመስል እንደነበረ የሚናገረውን ቃል አስተውለህ አንብበውና የአንተ ምጽዋት የአንተ ሥጦታ የትኛው ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ራስህን ጠይቅ። "
እውነት እላችኋለሁ ከሁሉም ከሚያንሱት ከነዚህ ወንድሞቼ ያደረጋችሁት ለኔ አደረጋችሁት" ማቴ 25፥40
   ✨ብጹዕ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ ✨✨✨🍂🍂✨✨✨🍂🍂✨✨✨

"አቅቶት ወደ ቀደመ አኗኗሩ ይመለሳል"                        ~ ቅዳሴ ማርያም ቁ ፹፮ ..........................................................   የብሕንሳው አባ ሕርያቆስ በቅዳሴ ማርያም ድርሰቱ እንዲህ ብሎ ነበር :- " ይህንንም (አምላክን ስለመጽነስሽ) ባሰብኩ ጊዜ ኅሊናዬ የልጅሽን የባሕሩን ጥልቅነት ሊዋኝ ይወዳል፤ የወዳጅሽ የመሠወሪያው ማዕበልም ያማታዋል። ዳግመኛም ባሰብኩ ጊዜ ኅሊናዬ ተሠውሮ ወደላይ ወጥቶ የሕያው መሠወሪያ የሆነውን ሊገልጥ ይወዳል ። ከነደ እሳትነቱ የተነሣ ይፈራል፣ ከዐየራት ከእርቧቸው እርቦ አይደርስም ። ይህንንም ባሰብኩ ጊዜ ኅሊናዬ በነፋስ ትከሻ ተጭኖ በምሥራቅና በምዕራብ በሰሜንና በደቡብ በዳርቻዎችም ሁሉ ሊበር ይወዳል ። የፍጡራንን አኗኗር ያይ ዘንድ የአብሕርትንም ጥልቅነታቸውን ይለካ ዘንድ የሰማይን ርዝመቱን ያውቅ ዘንድ በሁሉ ዘንድ በሁሉም ይዞራል ። አቅቶት ወደ ቀደመ አኗኗሩ ይመለሳል።"   እመቤቴ ሆይ እኔም እኮ የልጅሽን ቸርነት፣ ደግነት፣ ርኅራኄውን ባሰብኩ ጊዜ ኅሊናዬ ኃጢአቴን በንስሐ አራግፎ በልጅሽ የፍቅር ባሕር ውስጥ ሊዋኝ ይወዳል። ግን ምን ዋጋ አለው? የኃጢአት ፍቅር ገና ከልቡናዬ አልተነቀለምና የፍትወቴ ማዕበል ወደ ቀደመ አኗኗሩ ያማታዋል። ዳግመኛም የልጅሽ ይቅር ባይነቱ፣ እንደ በደሌ ብዛት እኔን ያልቀሰፈበት ትዕግሥቱ እያስደነቀኝ እግረ ኅሊናዬ ኃጢአቴን ይናዘዝ ዘንድ ወደ ልጅሽ ሹማምንቶች ካህናት ሊበር ይወዳል። ከአንድ ካህን ፊት ኃጢአቱን ተናግሮ ራሱን ለማዋረድ ግን ከትዕቢቱ የተነሳ ይፈራል። አቅቶትም ወደ ቀደመ የኃጢአት አኗኗሩ ይመለሳል።   ማርያም ሆይ፤ ዳግመኛም ኅሊናዬን በኃጢአቴ ከልጅሽ ተለይቼ የኖርኩበት ዘመን በቁጭት ዕረፍት ነስቶት በንስሐ ወደ ልጅሽ ዕቅፍ ለመግባት ይናፍቃል። የቀረ ሕይወቴን በጽድቅ ልጅሽን እያስደሰትኩ እኖር ዘንድ፣ የልጅሽን የትህትናውን ጥልቅነት እየለካሁ፣ የምሕረቱን ስፋት አውቅ ዘንድ ኅሊናዬ በሁሉ ዘንድ በሁሉም ይዞራል። ግን አቅቶት ወደ ቀደመ አኗኗሩ ይመለሳል።   እመብርሃን ሆይ ይህ ብቻ መሰለሽ? ኃጢአት ልሰራ በተዘጋጀሁ ጊዜ በኅሊናዬ የልጅሽ መስቀል ይታሰበኛል። ልጅሽን ከመበደል ያድኑኝ ዘንድ በምሥራቅ እና በምዕራብ፣ በሰሜንና በደቡብ፣ በዳርቻዎች ሁሉ ያሉ ቅዱሳንን አፌ ይጠራቸዋል። የልጅሽ የወዳጅሽ ፍቅር ግን በልቤ አልጸናምና አካሌ አቅቶት ወደ ቀደመ ኃጢአቱ ክፉኛ ወድቆ ይመለሳል።   "እስመ ተነድፈ ልብየ በፍቅርኪ ፤ ልቤ በፍቅርሽ ተነድፏልና" ብዬ ስንቴ እያዜምኩ ሰዓታት ቆሜልሽ ነበር። እንደ አባ ጊዮርጊስ እኮ እኔም ልቤ በአንቺ ፍቅር ይሰወር ዘንድ፣ በልጅሽ ቃልኪዳን በተሰጠኝ እናትነትሽ ይከለል ዘንድ እልፍ ጊዜ ደጅ ይጠናል። ግን ምን ዋጋ አለው? የክፋቴ፣ የበደሌ ብዛት ከንጽሕናሽ እርቦ አያደርሰኝም።   እመአምላክ ሆይ አሁንም ኅሊናዬ የልጅሽን ሕግ በቀን እና በሌሊት ያነብ ዘንድ፣ ኃያላንን በሚያጸናቸው በልጅሽ ቃል ልቤ ይታነጽ ዘንድ ቅዱሳት መጻሕፍትን ሊገልጥ ይወዳል፣ በልጅሽ ቃል መሰረት መኖር አቅቶት ግን ወደ ቀደመ አኗኗሩ ይመለሳል። ዳግመኛም ኅሊናዬ የቅዱሳንን አኗኗር አይቶ የእግዚአብሔርን ቃል በተግባር የነገሩትን ዋኖቹን ያስብ ዘንድ፣ የኑሮአቸውን ፍሬ እያየሁ በእምነት እመስላቸው ዘንድ በገድላቸው እና በድርሳናቸው ትከሻ ተጭኖ ይዞራል። ቅዱሳንን መምሰል አቅቶት ግን "እንደሚጠፉ እንስሶች" ወደመምሰሉ ይመለሳል። ዕብ 13፥7 ፣ መዝ 48 ፥ 12   ድንግል ሆይ፣ አሁንም ሰውነቴ ልጅሽ ይቅር ብሎኝ ወደረሳው ኃጢአቴ እንዳይመለስ የጾም ጸሎት፣ ስግደት ትሩፋትን አብዝቶ ሊፈጽም ይወዳል። አላደርገውም ብሎ የተገዘተበትን ኃጢአት ግን አቅቶት ወደ ትፋቱ እንደሚመለስ ውሻ ተመልሶ ይጨማለቅበታል። እመቤቴ ሆይ፣ ዳግመኛም ኅሊናዬ ያንቺን ቅንጣት ንጽሕና ገንዘብ ያደርግ ዘንድ፣ ልቤም ካንቺ የማይወሰን ርኅራሄሽ ተካፍሎ የልጅሽ ማደሪያ ይሆን ዘንድ ይወዳል። ግን አቅቶት ባንቺ ንጽሕና ልክ በኃጢአት ወደ መቆሸሹ ይመለሳል።   ድንግል ሆይ መልሺኝ እኔም እመለሳለሁ። ወደ ቀደመ የኃጢአት አኗኗሬ አይደለም፤ ወደ ቀደመ ጥቂት ጽድቄ እንጂ! ወደ ቀደመ በደሌ አይደለም፣ ወደ ቀደመ ቅንጣት ንጽሕናዬ እንጂ። ወደ ቀደመ ድካሜ አይደለም፣ ወደ ቀደመ በልጅሽ ኃይል ወደበረታሁበት ማንነቴ እንጂ! አቅቶኝ ወደ ምመለስበት ኃጢአት ሳይሆን ተመልሼ ወደምነሳበት ጽድቅ መልሺኝ!   ድንግል ሆይ ልጅሽ መሐሪ ይባል ዘንድ "ለጻድቃን ያይደለ ለኃጥአን አሳስቢ፣ ለንጹሐን ያይደለ ለተዳደፉት አሳስቢ።" ቅዱስ ዲዮስቆሮስ በቅዳሴው ልጅሽን እንዲህ ይለዋልና :- "ጻድቃንን ግን ከሥራቸው የተነሳ ትምራቸዋለህ፣ እንደ ጽድቃቸውም ትሰጣቸዋለህ፤ እኛን ኃጥአንን ብትምረን ያን ጊዜ መሐሪ ትባላለህና።" .......................................... ዲያቆን ዮሐንስ

✨✨✨✨ማኅሌተ ጽጌ✨✨✨✨ ክፍል ፪ 👉"ክበበ ጌራ ወርቅ" ሲባል መዞሩ ደግሞ ቅዱስ ጊዮርጊስን ስለሚያነሣ ነው፤ ቅዱስ ጊዮርጊስ በኢትዮጵያ ጉዳይ እመቤታችንን ይጋራታልና፤ ይኸውም ኢትዮጵያን ከእመቤታችን ቀጥሎ በዐሥራትነት ተቀብሏታል፡፡ ይኸውም የኢትዮጵያ ገበዝ እስከ መባል አድርሶታል። ይሀን በሚያስተባብር መልኩ #ሊቁ_እንዲህ_ብሏል ✨✨✨ "ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ እምዕንቈ ባሕርይ ዘየሐቱ፥ ዘተጽሐፈ ብኪ ትእምርተ ስሙ ወተዝካረ ሞቱ፥ አክሊለ ጽጌ ማርያም ለጊዮርጊስ ቀጸላ መንግሥቱ፥ አንቲ ኵሎ ታሰግዲ ሎቱ፥ ወለኪሰ ይሰግድ ውእቱ::" "የስሙ ምልክትና የሞቱ መታሰቢያ የተጻፈብሽ ከሚያበራ ወርቅ ይልቅ እንደ ዕንቍ የጠራ ንጽሕና ያለሽ የጊዮርጊስ የመንግሥቱ ሽልማት የአበባ አክሊል ማርያም ሆይ አንቺ ለእርሱ ሁሉን ታሰግጂለታለሽ፣ እርሱም ለአንቺ ይሰግዳል:: " በማለት ዘምሯል። ሊቃውንቱ ይህን እየወረቡ ቀሳውስቱ የእመቤታችንን ሥዕልና የቅዱስ ጊዮርጊስን ሥዕል ይዘው ይዞራሉ፤ ይኸውም ስደቷን ለማዘከር እንዲሁም የኢትዮጵያን መልክአ ምድር ዞራ መጎብኘቷንና ሀገሪቱን በቃል ኪዳን መረከቧን ለማሰብ ነው፤ የጊዮርጊስ ሥዕል አብሮ መዞሩ ስለሦስት ምክንያት ነው ✨✨✨ #የመጀመሪያው-ምክንያት ከላይ ለመግለጥ እንደተሞከረው እመቤታችን በስደቷ ወራት የኢትዮጵያ ባለአደራ ሆና እንደተሰጠች ቅዱስ ጊዮርጊስም የኢትዮጵያ ጠባቂ ሆኖ ተሰጥቷል፡፡ ስለዚህ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ይህንን ጥምር ምሥጢር ለማዘከር የጊዮርጊስን ሥዕል ከእመቤታችን ሥዕል ጋር ይዛ ሥርዓተ ዑደት ታከናውናለች። #ሁለተኛው_ምክንያት ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊቀ ሰማዕታት ሲኾን ሰማዕትነት ደግሞ እሳትና ስለት ብቻ አይደለም፤ ስደትም ሰማዕትነት ነው እሞሙ ለሰማዕት›› የተባለች እመቤታችን ሰማዕትነትን ባርካ ለሰማዕታት አለቃ ለቅዱስ ጊዮርጊስ እንደሰጠችው ለማስረዳት ነው፡፡ #ሦስተኛው_ምክንያት ቅዱስ ጊዮርጊስ ለእመቤታችን ካለው ልዩ ፍቅርና አክብሮት የተነሣ ‹ደምርኒ ፍልሰትየ ምስለ ፍልሰትኪ ፍልስቴን ከፍስስትሽ ጋር ደምሪልኝ::› ✨✨✨ብሎ ተማፅኗት ነበርና፤ ይኸውም አልቀረም የቅዱስ ጊዮርጊስ ፍልሰተ ዐፅሙ እመቤታችን ከሞት ተነሥታ ከመቃብር በፈለሰችበት በነሐሴ ፲፮ ቀን አብሮ ይከበራል፡፡ ይህ ከሥዕሉ ጋር ምን ያገናኘዋል ያልን እንደኾነ ✨✨✨ ፍልሰት የሚለው ቃል ብዙ ትርጉም ያለው ቃል ነው፤ ፈለሰ ተሰደደ ተንከራተተ ሀገር ጥሎ ቁርበት ጠቅልሎ ሄደ ማለት ነው ፍልሰቴን ከፍልስትሽ ጋር ደምሪልኝ ማለቱ ስደቴን ከስደትሽ መከራዬን ከመከራሽ ጋር ደምሪልኝ ማለቱ ነው፤ ይህን ምሥጢር የተረዳች ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዘመነ ጽጌ የሰማዕቱን መከራና ስደት ከእመቤታችን መከራና ስደት ጋር ታስባለች። #ባሕረ_ጥበባት_ቅዱስ_ያሬድ -✨✨✨ "አእሚረ ጊዮርጊስ ንጽሐ ሥጋሃ ሊቀ ሰማዕታት ሰገደ ላቲ ወአምኃ ለንግሥተ ሰማይ፤ ወይቤላ ጊዮርጊስ ለማርያም ደምርኒ እም ከመ ኅቡረ ንባዕ ሠናየ ገድለ ተጋደሉ፡፡ " "የሰማዕታት አለቃ ቅዱስ ጊዮርጊስ ለሰማይ ንግሥት ለእመቤታችን ንጽሕናዋን አውቆ እጅ በመንሣት ሰገደላት ጊዮርጊስ ማርያምን እንዲህ አላት እናት ሆይ በአንድነት እንገባ ዘንድ ከገድል ከትሩፋትሽ አንድ አድርጊኝ አላት፥ መልካም ገድልንም ተጋደለ።» ✨✨✨ በማለት ከላይ የተገለጠውን ኀይለ ቃል ይበልጥ አጉልቶ አምልቶ ይነግረናል። ይቆየን..... ✨✨✨✨💐💐💐💐✨✨✨✨

✨✨✨✨ማኅሌተ ጽጌ✨✨✨✨ ክፍል ፩ እንዘ ተሐቅፊዮና ክበበ ጌራ ወርቅ ሲባል ✨✨✨ መዞሩ ምሥጢሩ ምንድ ነው? ማኅሌተ ጽጌ በሚቆምበት ጊዜ “እንዘ ተሐቅፊዮና ክዘበ ጌራ ወርቅ ሲባል የሚዞርበት ምሥጢሩ በጽጌ ማሕሌት ጊዜ የሚባሉ ብዙ ወረቦች ነበሩ ለሥርዓተ ዑደቱ እነዚህ ወረቦች ለምን ተመረጡ ስንል በመጀመሪያ እነዚህ ሁለት ወረቦች ሁሉንም ምሥጢር ያስተባበረ መልእክት ስላላቸው ነው፤ ይኸውም "እንዘ ተሐቅፊዮ ለሕፃንኪ ጽጌ ፀዓዳ ወቀይሕ፥ አመ ቤተ መቅደስ ቦእኪ በዕለተ ተአምር ወንጽሕ፥ ንዒ ርግብየ ትናዝዝኒ እምላሕ፥ ወንዒ ሠናይትየ ምስለ ገብርኤል ፍሡሕ፥ ወሚካኤል ከማኪ ርኅሩኅ፡፡" 🌹🌸🌹🌸🌹🌸🌹🌸🌹🌸🌹🌸🌹🌸🌹🌸 ነጭና ቀይ መልክ ያለው አበባ ልጅሽን ይዘሽ ወደ ቤተ መቅደስ #ዕለተ_ንጽሕ ተብሎ በሙሴ እንደተጻፈው በወለድሽ በ፵ ቀን ወደ ቤተ መቅደስ እንደ ገባሽ ርግቤ ሆይ ከኀዘን ታረጋጊኝ ዘንድ ነዪ፤ አዛኝቱ ድንግል ሆይ! ደስተኛ ከሆነው ከገብርኤልና እንደ አንቺ ሩኅሩኅ ከሆነው ከቅዱስ ሚካኤል ጋር ነዪ።» በማለት ፀዓዳ በመለኮቱ ወቀይሕ በትስብእቱ የሚባል ልጇን ታቅፋ ወደ ቤተ መቅደስ እንደገባች ወደ ልቡናዬ ግቢ ከኀዘኔም አረጋጊኝ ብሎ ይማፀናል። ሊቁ እንዘ ተሐቅፊዮ ለሕፃንኪ ጽጌ ፀዓዳ ወቀይሕ፤ ነጭና ቀይ የኾነ አበባ ልጅሽን ታቅፈሽ ሲል ✨✨✨ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ይዞ ነው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በነጭና በቀይ ይመሰላል፡፡ መፍቀሬ ጥበብ ሰሎሞን ከመዝሙራት በሚበልጥ መዝሙሩ ላይ "ወልድ እኁየ ጸዐዳ ወቀይሕ፤ ውዴ ነጭና ቀይ ነው... ከእልፍ የተመረጠ ነው" መሐ 5÷10 ብሎ ከዘመረው መዝሙር ወስዶ ነው፡፡ ይኸውም ነጭ የድል አድራጊነት ምልክት ሲሆን ቀይ የመሥዋዕትነት ምሳሌ ነው፤ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ በከፈለው መሥዋዕትነት አዳምንና ልጆቹን ከሞት ባርነት አድኗል፤ ዲያብሎስንና ሠራዊቱን ድል አድርጓልና፡፡ ነጭ የመለኮቱ ቀይ የትስብእቱ ምሳሌ ነው፡፡ ጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተለየ አካሉ ሰው ሆኗልና፡፡ ደስተኛ ከሆነው ከገብርኤል ጋር ነዪ››✨✨✨ ማለቱ ገብርኤል ደስተኛ የሆነው በምን ምክንያት ነው? ያሉ እንደሆነ እርሷን ያበሥር ዘንድ በተላከ ጊዜ ራሱን ከመላአክት መካከል እንደ ዕድለኛ በመቁጠር እጅግ ተደስቶ ነበርና፡፡ ይህንን #ሊቁ_ቅዱስ_ኤፍሬም ✨✨✨ "ዐቢይ ውእቱ ክብር ዘተውኅበ ለከ ኦ ገብርኤል መልአክ ዜናዊ ፍሡሐ ገጽ ሰበከ ለነ ልደተ እግዚእ ዘመጽእ ኀቤነ፤ ወአብሠርካ ለማርያም ድንግል ዘእንበለ ርስሐት ወትቤላ ተፈስሒ ኦ ምልዕተ ጸጋ እግዚአብሔር ምስሌኪ::" ደስተኛ ሆነህ የምሥራችን የተናገርክ መልአኩ ገብርኤል ሆይ ለአንተ የተሰጠህ ክብር ታላቅ ነው፤ ወደ እኛ የመጣ የጌታን ልደቱን ነገርከን ለድንግል ማርያም ጸጋን የተመላሽ ሆይ እግዚአብሔር ካንቺ ጋር ናውና ደስ ይበልሽ ብለህ አበሠርካት።››   ብሎ ገልጾታል። ቅዱስ ገብርኤል መጋቤ ብሥራቷ መሆኑ ለእርሱ ትልቅ ክብር ነውና፡፡ ✨✨✨ እንደ_አንቺ_ርኅሩኅ ከሆነው ከሚካኤል ጋር ነዪ ማለቱ ደግሞ ቅዱስ ሚካኤል #ለሰው_ልጅ_በመራራት ይመስላታልና ነው፡፡ ይቆየን... ክፍል ፪ን ማታ ከ ፪ሰዓት በኋላ የምንለቅ መሆኑን ከወዲሁ ለመግለጽ እንወዳለን። ✨✨✨✨💐💐💐💐✨✨✨✨

የእግዚአብሔር ልጅነት ባገኘንባት ቅጽበት ክርስቲያን የሆንን እኛ እንደተተከለ ተክል ነንና በሕይወት መንገዳችን ሁሉ የእግዚአብሔር ቃልና የቤተ ክርስቲያን ድምጽ እየተመገብን የምንፈካ አበባ ነን።
የእግዚአብሔር ልጅነት ባገኘንባት ቅጽበት ክርስቲያን የሆንን እኛ  እንደተተከለ ተክል ነንና  በሕይወት መንገዳችን ሁሉ የእግዚአብሔር ቃልና የቤተ ክርስቲያን ድምጽ እየተመገብን የምንፈካ አበባ ነን።  

፦ በእግዚአብሔር ቤት በመቅደሱ ውስጥ እንገናኝ — ነሀምያ 6፥10
፦ በእግዚአብሔር ቤት በመቅደሱ ውስጥ እንገናኝ  — ነሀምያ 6፥10

"ኃጢአትን ባትሠራት መልካም ነው። ኃጢአትን ከሠራህ ሳትቆይ ንስሐ ብትገባ መልካም ነው። ንስሐ ከገባህ ዳግመኛ ወደ ኃጢአት ባትመለስ መልካም ነው። ወደ ኃጢአት ካልተመለስክ ይህ በእግዚአብሔር እርዳታና ቸርነት መሆኑን ብታውቅ መልካም ነው። ይህንን ካወቅህ ስለአለህበት ሁኔታ እግዚአብሔርን ብታመሰግን መልካም ነው።" ቅዱስ ባስልዮስ

የእግዚአብሔር ፍቅር በልብህ ውስጥ ጠልቆ ከገባ ድካምህ ይጠፋል ። ከእግዚአብሔርና ከትእዛዛቱ የበለጠ ኃጢአትን የምትወድ ከሆነ ደካማ ትሆናለህ ። ነገር ግን ፍቅሩ ወደ ልብህ ከገባ በውስጥህ ያለውን የኃጢአት ፍቅር አውጥቶ ይጥለዋል ። ስለሆነም ማንኛውንም ዓይነት ፈተና ለመቃወም ብርቱ ትሆናለህ ። "ንስሓ ማለት ፍላጎትን በፍላጎት መቀየር ማለት ነው ።" ይህ ማለት የእግዚአብሔር ፍቅር የአለምን ፍቅር ይተካል ማለት ነው ። ስለዚህ ወደ እግዚአብሔር ፍቅር የሚመሩህን ማንኛውም አይነት መንፈሳዊ መንገዶች ሁሉ ተከተል ። ከዚህ በተጨማሪ እግዚአብሔርን ከሚወዱት ጋር ተባበር !  እርሱን ስለ ወደዱት ሰዎች የተጻፈውንም አንብብ ! በመጨረሻም ምሳሌያቸውን ተከተል ።     አቡነ ሺኖዳ  ሳልሳዊ

#ጥቅምት_፭ አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ጥቅምት አምስት ቀን የታላቁ አባት #አቡነ_ገብረ_መንፈስ_ቅዱስ (ገብረ ሕይወት) የዕረፍታቸው መታሰቢያ በዓል ነው ⚜⚜⚜💫💫💫⚜⚜⚜ #አቡነ_ገብረ_መንፈስ_ቅዱስ (ገብረ ሕይወት) ጻድቁ የተወለዱት ግብፅ (ንሒሳ አካባቢ) ሲሆን አባታቸው ስምዖን እናታቸው አቅሌስያ ይባላሉ። አባታችን ገብረ ሕይወት የጻድቃን አለቃ የቅዱሳን የበላይ ተጋድሎአቸውና ድንቅ ተአምራቸው እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ቅዱስ ሰው ናቸው። የጻድቁን ክብር መናገር የሚችል ምን አነደበት ይኖራል? እንደ ምንስ ባለ ብራና ይጻፋል? ዜናቸውንስ ለመስማት የታደለ እንደ ምን ዓይነት ሰው ይሆን? አባታችን ገብረ መንፈስ ቅዱስ ለ562 ዓመታት በዚህች ዓለም ሲኖሩ እህል ያልቀመሱ /ምግባቸው ምስጋና ነውና/ ልብስ ያልለበሱ /ጠጉር አካላቸውን ይሸፍን ነበርና/ ሐዋርያዊ ሆነው ከግብፅ እስከ ኢትዮዽያ ብዙ ነፍሳትን ያዳኑ አባት፤ ሃገራችንን አስምረው አስራት እንድትሆናቸውም ተቀብለው ምድረ ከብድ አካባቢ አርፈዋል። ጻድቁ ገብረ መንፈስ ቅዱስም ገብረ ሕይወትም ይባላሉ። በ562 ዓመታት ሕይወታቸው እንደ ሐዋርያት ከምድረ ግብፅ እስከ ኢትዮዽያ ወንጌልን ሰብከዋል። በዚህም በሚሊየን (አእላፍ) ለሚቆጠሩ ነፍሳት የድኅነት ምክንያት ሆነዋል። ጻድቁ እንደ ሰማዕታትም ከከሃዲ ሰዎች ብዙ መከራን ተቀብለዋል። እንደ ባሕታውያን ለብዙ መቶ ዓመታት ሰው ሳያዩ ቆይተዋል። ለየት የሚለው ግን የጽድቅ ሕይወታቸው ነው፤ ከእልፍ አዕላፍ አጋንንት ጋር ተዋግተው ድል ማድረግ ችለዋልና። የንሒሳው ኮከብ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ለኢትዮጵያ ልዩ ፍቀር አላቸው። ስለ ሃገሪቱና ሕዝቧ ፍቅር ሲሉ ለ100 ዓመታት በደብረ ዝቋላ መከራን ተቀብለዋል። ምሕረትን ሲለምኑ ሥጋቸው አልቆ በአጥንታቸው ቁመው ነበርና ሃገራችን አሥራት ሆና ተሰጠቻቸው። ስለዚህም ነው በሃገሪቱ ውስጥ ከ2,000 በላይ የጻድቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳማትና አድባራት ዛሬም ድረስ ያሉት። በ8ኛው ክ.ዘ አካባቢ የተወለዱት አባታችን ያረፉት በ14ኛው መቶ ክ.ዘ አካባቢ ነው። ፍጥረታትን ሁሉ አዘው መጋቢት 5 ቀን ሲያርፉ ግሩማን መላእክት ገንዘው አካላቸውን ሠውረዋል። ሥላሴን የተሸከመ አካላቸው በጐልጐታ ተቀብሯል የሚሉም አሉ። "ሰላም ለመቃብሪከ ዘኢተከሥተ ለባዕድ: ከመ መቃብሩ ለሙሴ ወልደ ዮካብድ: ዜና መቃብሪከሰ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ጸማድ: ቦ ዘይቤ በኢየሩሳሌም አጸድ: ወቦ ዘይቤ ኀለወ በከብድ።" እንዲል። ጻድቁ አባታችን አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ እረፍቱ መጋቢት 5 ቀን ነው ይህ ደግሞ በታላቁ ዓብይ ጾም ወቅት ነው ፍትሃ ነገስት አንቀጽ 15 ላይ በዓብይ ጾም በዓል ማክበር ይከለክላል የሀዘን ወቅት ነውና ከበሮ አይመታም እልልታና ጭብጨባ የለም ፍጹም ሀዘን እንጂ የመጋቢት 27 ስቅለት ጥቅምት 27 ቀን እንደሚከበረው ሁሉ ወደ ጥቅምት 5 ቀን ተዛውሮ እንዲከበር ተደረገ፡፡ ስንክሳር ዘወርኃ ጥቅምት