ar
Feedback
ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

الذهاب إلى القناة على Telegram

በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:-  @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

إظهار المزيد
669
المشتركون
-124 ساعات
+37 أيام
لا توجد بيانات30 أيام
أرشيف المشاركات
#በቂ_እውቀትና_ግንዛቤ_ኖሮኝ_በቤተክርስቲያናችን_የሰበካ_ጉባኤ_ምርጫ_ላይ_እሳተፋለው_የልጅነት_ግዴታዬንም_እወጣለው። ሰበካ ጉባኤ እና ዓላማው ሰበካ ጉባኤ በተለይ ቅድስት ቤተክርስቲያን ዘመናዊ መዋቅር ያላት ሆና እንድትተዳደር በተደነገገው ህግ ቃለ ዓዋዲ መመስረት ጋር አብሮ የተጀመረ መንፈሳዊ ጉባኤ ነው፡፡ ሰበካ ጉባኤ በቃለ አዋዲ አንቀፅ 5 መሰረት የሚከተሉት አለማዎች አሉት ፦ 👉 ቅድስት ቤተክርስቲያንን ለመጠበቅና አገልግሎቷም የተሟላ እንዲሆን ለማድረግ፤ 👉 የቤተክርስቲያንን አገልጋዮች ሐዋርያዊ ተግባር ለማደራጀትና እንደዚሁም ችሎታቸውንና ኑሮአቸውን ለማሻሻል፤ 👉 ምዕመናንን ለማብዛት እንደዚሁም በመንፈሳዊ ዕውቀት ጎልምሰው በምግባርና በሃይማኖት ጸንተው በክርስቲያናዊ ህይወት እንዲኖሩ ለማድረግ ፤ 👉 የቤተ ክርስቲያንን አስተዳደር ለማሻሻልና በማናቸውም ጉዳይ ራሷን ለማስቻል ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በቃለ ዓወዲው አንቀጽ 6 ላይ ሰበካ ጉባኤው የሚከተሉትን ተግባራት እንደሚያከናውን ተደንግጎ ይገኛል፡፡ 👉 የእግዚአብሔርን ወንጌል መንግስት ለመስበክና ትምህርቱንም ለማስፋፋት፤ 👉 መንፈሳዊና ዘመናዊ ትምህርት ቤትን ለማቋቋምና ለማደራጅት፤ 👉 መንፈሳዊና ማህበራዊ አገልግሎትን ለምዕመናን ሁሉ ለማደረስ፤ 👉 ሰንበት ትምህርት ቤትን ለማቋቋምና ለማጠናክር፤ 👉 የቤተ ክርስቲያን አገልግሎትን ለምዕመናን ሁሉ ለማድረስ፤ 👉 ለቤተክርስቲያን አገልግሎት የሚያስፈልጉትን ሁሉ ለማሟላት፤ 👉 የቤተክርስቲያን አስተዳደርና አገልግሎት በቅዱሳት መጻህፍት መሰረት በህግና በሥነ-ሥርዓት ለመምራት፤ 👉 ቤተ ክርስቲያንን በሀብትና በንብረት በኩል ራሷን ለማስቻል፤ 👉 የቤተክርስቲያን ሀብትና ንብረት እዳይባክን፣ እየተመዘገበ እንዲጠበቅ፣ እንዲለማና እንዲያድግ ለማድረግ፣ 👉 ህገ ቤተክርስቲያን በሚፈቅደው መሰረት ከበላይ የሚሰጡትን ህግጋት፣ ደንቦች፣ መመሪዎች፣ ትዕዛዞችና ውሳኔዎች ለመፈጸምና ለማስፈጸም፤ 👉 በቅርብም ሆነ በሩቅ የሚገኙ ሰበካ መንፈሳውያን ጉባኤያት በማናቸውም ጉዳይ እርስ በእርሳቸው ተባብረውና ተረዳድተው እንዲሰሩ የተቻለውን ሁሉ ለማድረግ፣ 👉 ልዩ ልዩ የምግባረ ሰናይ ድርጅቶችን ለማቋቋምና አገልግሎታቸውን ለማሟላት፣ 👉 የህንፃ ሥራ፣ እድሳት፣ ጥገናና የመሳሰሉት ሥራዎች ሁሉ ወቅቱን ጠብቀው የሚፈጸሙበት እቅድና መርሃ ግብር ማዘጋጀት በተግባር መዋላቸውንም ለመቆጣጠር፣ 👉 የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት ተከታዮችን ብዛት ፣የሰበካውን ገንዘብና ንብረት ገቢና ወጪ የመሳሰሉትንም እስታቲስቲካዊ መረጃዎችን በወቅቱ እየመዘገቡ በሪፖርት እንዲገለጽ ለማድረግ፤ 👉 በዚህ ቃለ ዓዋዲ መሰረት ማናቸውንም ቤተ ክርስቲያንን የሚመለከት ጉዳይ ለመፈጸምና ለማስፈጸም፤ 👉 በዚህ አንቀጽ ከንዑስ አንቀጽ 4 እስከ 14 የተዘረዘሩትን ተግባሮች በቅድሚያ እያጠና ተገቢውን ለማድረግና አስፈላጊም ሆኖ ሲገኝ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ግለሰቦችና ድርጅቶች ጋር እየተነጋገረ ለማስፈጸም፡፡

የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ አመሠራረት ታሪክ በአጭሩ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ በእጨጌ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሰብሳቢነት፣ በፀባቴ ጥዑመ ልሳን ጸሐፊነት፣ በሰባ ሁለት የአድባራት አስተዳዳሪዎችና አገልጋይ ካህናት አባልነት የቤተ ክርስቲያንን ጉዳይ የሚወስን መንፈሳዊ ጉባኤ መስከረም ፰ ቀን ፲፱፻፲፰ ዓ.ም ተቋቁሞ እንደነበር፤ ከዚያም በ፲፱፻፶፱ ዓ.ም መንግሥት ያወጣው የመሬት ግብር ዓዋጅ በቤተ ክርስቲያን ላይ ችግር በማምጣቱ ቤተ ክርስቲያን የራሷን ተቋማት ለማዋቀር በዓዋጅ ቍጥር ፵፰/፶፱ እና ፹፫/፷፭ ሕጋዊ ፈቃድ እንደተሰጣት፤ በዚህ ሥልጣን መሠረትም ቤተ ክርስቲያናችን በእግዚአብሔር ቃል ተመርታ፣ በሀብቶቿ በምእመናን ተጠቅማ፣ ከመንግሥት ጥገኝነት ነጻ ኾና፣ ራሷን ችላ መተዳደር እንደጀመረች የታሪክ መዛግብት ያስረዳሉ፡፡ ሰማዕቱ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሁለተኛው ፓትርያርክ ሰማዕቱ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ ምእመናንን የሚያሳትፍ የቤተ ክርስቲያን መተዳደሪያ ደንብ (ቃለ ዓዋዲ) አዘጋጅተው በ፲፱፻፷፭ ዓ.ም የሰበካ ጉባኤ አስተዳደርን አቋቁመዋል፡፡ ወጣቶችን ጭምር የሚያሳትፈው ይህ ቃለ ዓዋዲም አገልጋይ ካህናት የወር ደመወዝ እንዲያገኙ ከማስቻሉ ባሻገር በካህናትና በምእመናን መካከል ያለው ኅብረት እንዲጠናከርም አድርጓል፡፡ ስለዚህም ስለሰበካ ጉባኤ መቋቋም ሲነገር ወጥነት ያለው መንፈሳዊ የአስተዳደር መዋቅር እንዲዘረጋ ከፍተኛ ጥረት ያደረጉት ሰማዕቱ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ አብረው ይዘከራሉ፡፡ ቅዱስነታቸው የጀመሩት ይኼው መዋቅራዊ አሠራር እና ያፋጠኑት ሐዋርያዊ አገልግሎትም በሦስተኛው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዘመን ይበልጥ ተስፋፍቷል፡፡ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ዘመን የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ ሓላፊ ኾነው ለበርካታ ዓመታት ያገለገሉት ሊቀ ጉባኤ አባ አበራ በቀለ የሰበካ ጉባኤን በማጠናከር ረገድ ያደረጉት ብርቱ ጥረትም የሚዘነጋ አይደለም፡፡ በዚህ መልኩ እየተጠናከረ የመጣው የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ፣ የቤተ ክርስቲያንን አገልግሎት በማሳደግ፣ አስተዳደሯንም በማቀላጠፍ ዓመታትን አልፎ አሁን ካለበት ደረጃ ላይ ደርሷል፡፡  የአጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ዓላማ እና ተግባር በ፲፱፻፺፩ ዓ.ም ተሻሽሎ በወጣው ቃለ ዓዋዲ አንቀጽ ፭ ላይ እንደተገለጸው የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ዓላማ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን መጠበቅና አገልግሎቷም የተሟላ እንዲኾን ማድረግ፤ የቤተ ክርስቲያንን አገልጋዮች በሐዋርያዊ ተግባር ማደራጀትና ችሎታቸውንና ኑሯቸውን ማሻሻል፤ ምእመናንን ማብዛትና በመንፈሳዊ ዕውቀት ጐልምሰው፣ በምግባር በሃይማኖት ጸንተው በክርስቲያናዊ ሕይወት እንዲኖሩ ማድረግ፤ የቤተ ክርስቲያንን አስተዳደር ማሻሻልና በማናቸውም ጉዳይ ራሳቸውን ማስቻል ነው፡፡ ይህን መንፈሳዊ ዓላማ ለማስፈጸም የተዋቀረው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ መንፈሳዊ ጉባኤም የእያንዳንዱ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጆች፤ ከየመንበረ ጵጵስናው የተወከሉ ካህናት፣ ምእመናንና የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እና ከጠቅላይ ቤተ ክህነት የየመምሪያ ሓላፊዎች ጋር በአንድነት ተሰባስበው የሚመሠርቱት ጉባኤ ሲኾን፣ በዓመት አንድ ጊዜ የሚሰበሰብ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ እንዳለውና ይህም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አጠቃላይ ስብሰባ እንደኾነ በቃለ ዓዋዲው አንቀጽ ፵፮ ላይ ተደንግጓል፡፡ በቃለ ዓዋዲው አንቀጽ ፵፯ ላይ በተቀመጠው ድንጋጌ መሠረት በአጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ዓመታዊ ጉባኤው ላይ ፓትርያርኩ ርእሰ መንበር፤ ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ምክትል ሊቀ መንበር፤ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት አባላት፤ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ምክትል ሥራ አስኪያጅ አባልና ጸሐፊ፤ የአጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤው አስተዳደር ጉባኤ (ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ) አባል፤ የአህጉረ ስብከት ሥራ አስኪያጆች አባላት፤ ከየአህጉረ ስብከት መንፈሳውያን አስተዳደር ጉባኤያት የተወከሉ ካህናት፣ ምእመናን እና የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች አባላት፤ በውጭ አገር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ተወካዮች አባላት ኾነው የሚሳተፉበት ታላቅ የቤተ ክርስቲያን ጉባኤ ነው፡፡

ደሃ ነው፤ ግን ጨዋ። ጠግበህ ስትበላ እያየህ ምንም ያህል ቢርበው ቀምቶህ ግን አይሮጥም። ያስተረፍከው ካለ ይጠይቅሃል እንጂ "እኔ እየራበኝ አንተ ትበላለህ " ብሎ አያፈጥብህም። ምክንያቱም ደሃ ነው ግን ጨዋ ነው። ብርድ እያንዘፈዘፈው ደራርበህ ስትሔድ አይገላምጥህም። ልብስህን ገፍፎ መሮጥ እንደሚችል ሃሳብ አይመጣለትም። የአንተ ትርፍ ልብስ ለእርሱ የዓመት ልብስ መሆን ቢችልም እርሱ ግን ልብስህን ትቶ ልብህን ሊያራራ ይሞክራል እንጂ ገፍፎ ስለመልበስ አያስብም። ምክንያቱም ደሃ ነው ግን ጨዋ ነው። ልጆቹን የሚያበላው ቢያጣም አንተን ግን ስትዝናና ሊረብሽህ አይፈልግም። መደሪያ ቢቸግረውም የአንተን የመኪና ማቆሚያ ቦታ አይጋፋም። የእጅ ሰዓትህ ዋጋ ብቻ የቤት ኪራዩን ሊከፍልለት እንደሚችል አልጠፋውም። የእጅህ ስልክ ብቻ ዓመት እንደሚያኖረው ሳይገባው ቀርቶም አይደለም። ይህን እያወቀ በአክብሮት መጥቶ " ስለ እግዚአብሔር " ይልሃል። ምክንያቱም ደሃ ነው ግን ጨዋ ነው። እግዚአብሔር እንዲህ ይላል:- "ነፍስህንም ለተራበ ብታፈስስ፣ የተጨነቀውንም ነፍስ ብታጠግብ ፣ ብርሃንህ በጨለማ ይወጣል። ጨለማህም እንደ ቀትር ይሆናል።" ኢሳ 58:10 ዲ/ን ሄኖክ ሀይሌ የአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27

✨✨✨🌹✨🌹✨🌹✨🌹✨🌹✨✨✨ የዓለም ሁሉ መድኃኒት የምትሆን ብላቴና እግሯ የተመላለሰበቱን ምድር እስም ዘንድ ማን በከፈለኝ፡፡ ይቅርታን የምታሰጥ ብላቴና ጥላዋ ይነካኝ ዘንድ ማን በከፈለኝ፡፡የብ
✨✨✨🌹✨🌹✨🌹✨🌹✨🌹✨✨✨ የዓለም ሁሉ መድኃኒት የምትሆን ብላቴና እግሯ የተመላለሰበቱን ምድር እስም ዘንድ ማን በከፈለኝ፡፡ ይቅርታን የምታሰጥ ብላቴና ጥላዋ ይነካኝ ዘንድ ማን በከፈለኝ፡፡የብርሃን ልጅ ወደ ሄደችበት እከተላት ዘንድ ማን በከፈለኝ የእግሯንም ጫማ እሸከም ዘንድ ማን በከፈለኝ፡፡ ✨🌹✨ አሁንም ያን ጊዜ በዕብራይስጥ ማሪሃም ከተባለች ከተመረጠች ድንግል ማርያም ጋራ ያን ጊዜ ካሉት አላንስም ሀሳቤን ከዚያ እንዳለሁ አድርጌ አለሁና፡፡ በስጋ አልነበርሁም በመንፈስ ግን አለሁ፡፡ ባነዋወር አልነበርሁም በሃይማኖት ግን አለሁ በገጽ አልነበርሁም በማመን ግን አለሁ፡፡ ሳልኖር እራሴን እንዳለሁ ያረደረግሁ እኔ የተመሰገንሁ ነኝ ጌታችን በወንጌል እንደተናገረ እንዲህ ሲል ሳያዩኝ የሚያምኑብኝ ግን የተመሰገኑ ናቸው፡፡ እኔ ባሪያህ ስለሃይማኖቴ የተመሰገንሁ ነኝ፡፡ ስለ ዕውነቴ አይደለም ስለ መረዳቴም የተመሰገንሁ ነኝ፡፡ ስለ ንጽህናዬም አይደለም በእግዚአብሔር ስም ስለ አመንኩ የተመሰገንሁ ነኝ፡፡ በናቱም ጸሎት ስለ አመንሁ ንዑድ ክቡር ነኝ፡፡ ✨ (አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በአርጋኖን) ✨✨✨🌹✨🌹✨🌹✨🌹✨🌹✨✨✨

እንኳን ለሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ ሰማዕትነት ለተቀበለችበት ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ጌታችን በስምዖን ቤት እያለ 300 ዲናር የሚያወጣ ሽቱ ይዛ ለመጣችውና ጠርሙሱን ሰብራ ላፈሰሰችው ባ
እንኳን ለሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ ሰማዕትነት ለተቀበለችበት ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ጌታችን በስምዖን ቤት እያለ 300 ዲናር የሚያወጣ ሽቱ ይዛ ለመጣችውና ጠርሙሱን ሰብራ ላፈሰሰችው ባለ ሽቱዋ ማርያም ሲመሰክር "መልካም ሥራ ሠርታልኛለችና ሴቲቱን ለምን ታደክሙአታላችሁ? ...እውነት እላችኋለሁ፥ ይህ ወንጌል በዓለም ሁሉ በማናቸውም ስፍራ በሚሰበክበት እርስዋ ያደረገችው ደግሞ ለእርስዋ መታሰቢያ እንዲሆን ይነገራል" ብሎ ነበር:: (ማቴ 26:10-11) ለክርስቶስ በአንዲት ምሽት መልካም ሥራ የሠራችን ሴት ሊንቁ የሞከሩትን ሰዎች ክርስቶስ ከገሠፃቸው ሕይወትዋን ሙሉ በመልካም ሥራ የደከመችዋን ቅድስት አርሴማን [St. Hripsime] የማያከብር ምንኛ ተግሣፅ ይገባው ይሆን? ባለ ሽቱዋ ማርያም በዝሙት ስትሠቃይ ኖራ በመጨረሻ ዕንባዋን ከሽቱ ቀላቅላ ከጌታ እግር ሥር የወደቀች ናት:: ቅድስት አርሴማ ግን በድንግልና ለመኖር ብላ በነገሥታትና ገዢዎች ብዙ መከራን የተቀበለች ውድ ሽቱን ንቃ በክርስቶስ በፍቅሩ መዓዛ ያጌጠች ነበረች:: ክርስቶስ ባለ ሽቱዋ ማርያም ያደረገችው ለእርስዋ መታሰቢያ እንዲሆን በዓለም ሁሉ ይነገራል አለ:: ባለ ሽቱዋ ማርያም ስለ ክርስቶስ ፍቅር የሰበረችው ጠርሙስ ነው ያፈሰሰችው ሽቱ ነው:: ቅድስት አርሴማ ግን የሰበረችው አንገትዋን ነው:: ያፈሰሰችው ደሟን ነው:: ስለዚህ በዓለም ሁሉ ስለ እርስዋ ይነገራል:: አርሴማ አርሴማ አርሴማ ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ

#ለሰይጣን_ጊዜ_የለኝም መምህሩ ተማሪዎችን ሊፈትን በአንድ ሰዓት ውስጥ የሚመለሱ ሁለት ጥያቄዎችን አዘጋጀ። ተማሪዎች ራሳቸውን አዘጋጅተው ወደ ፈተና ክፍል ገበተው ወንበር ወንበራቸውን ይዘው ይጠብቃሉ። መምህሩ የፈተና ወረቀቱን ይዞ ገባ። የፈተናውን መመሪያ ተናግሮ የፈተና ወረቀቱን አደለና ሰዓት ይዞ "መጀመር ትችላላችሁ" አላቸው። የመጀመሪያው ጥያቄ ስለ እግዚአብሔር የምታውቀውን ጻፍ የሚል ነው። ሁለተኛው ጥያቄ ደግሞ ስለ ሰይጣን የምታውቀውን ጻፍ ይላል፡፡ "ለአንዱ ጥያቄ 30 ደቂቃ ነው የተሰጠው ማለት ነው" ብለው ሰዓት ሳያልቅባቸው ሁለቱንም ጥያቄዎች ለመጨረስ ተሎ ተሎ ይጽፋሉ። ፈተና ከተጀመረ 30 ደቂቃ መሙላቱ ሰዓት ያዩ ተማሪዎች ከአንደኛው ጥያቄ ወደ ሁለተኛው አልፈው መስራት ጀምረዋል፡፡ በአእምሮአቸው የመጣላቸውን ሐሳብ በቻሉት ፍጥነት ይጽፋሉ፡፡ መምህሩም ሁሉም ተማሪ የየራሱ መስራቱን እየዞረ ይከታተላል። "ለማጠናቀቅ አስር ደቂቃ ይቀራችኋል" አለ መምህሩ። መልሰን ጨርሰናል ብለው ያሰቡ ተማሪዎች ግማሾቹ ፈተና ወረቀቱን ለመምህሩ ሰጥተው ሲወጡ፥ ሌሎቹም የመለሱትን ደግመው ያነባሉ፡፡ ያልጨረሱም የቀረችውን ደቂቃ ለመጠቀም ይጣደፋሉ። ከአስር ደቂቃ በኋላ "ሰዓት አልቋል ሁላችሁም መስራት አቁሙ" አለ መምህሩ፡፡ እየዞረም ፈተና ወረቀቱን መሰብሰብ ጀመረ፡፡ አንድ ተማሪ ጋር ሲደርስ ግን አሁንም መልስ እየጻፈ ያገኘውና "ሰዓት አልቋል ሲባል አትሰማም እንዴ?" ብሎ ወረቁትን ተቀበለው፡፡ ሁሉም ተማሪዎች ለሁለቱም ጥያቄ የሚያውቁትን የመለሱ ሲሆን አንዱ ተማሪ ግን ለጥያቄ ቍጥር አንድ (ስለ እግዚአብሔር የምታውቁትን ጻፉ ለሚለው) ብቻ ነው መልስ የሰጠው። መምህሩ በዚህ ተማሪ መልስ ተገርሞ "ለምንድ ነው ለሁለቱንም ጥያቄዎች መልስ ያልጻፍከው?" ብሎ ጠየቀው። እርሱም "#ለሰይጣን_ጊዜ_የለኝም" ስለ እግዚአብሔር ራሱ የማያልቅ ቢሆን እኮ ነው የተሰጠን ሰዓት አልቆ ገና እየጻፍኩ ያስቆምከኝ" አለው ይባላል፡፡ እውነት ነው ነገረ እግዚአብሔር ቢጽፉት፣ ቢናገሩት፣ ቢሰሙትና ቢያዜሙት የማያልቅና የማይሰለች ጥልቅ ምሥጢር ነው። የፈለግነው ያህል ጊዜ ብንሰጠው እንኳን በጅምር እያለን ጊዜው ያልቃል። በቃሉ ፍቅር፥ በምሥጢሩ ተመስጦ ውስጥ ሆነን ወደማያልፈው ዓለም እንሻገራለን፡፡ ይህንን ገንዘብ ለማድረግ ግን ለሰይጣንና ለጉዳዮቹ የሚሆን ጊዜ የለኝም ማለት ይገባል፡፡ ከጊዜ ውጭ የሚሰራ ነገር የለምና ለሰይጣን የሚሆን ጊዜ ከሌለን ከኃጢአት ሁሉ መራቃችን አይደል? ለሰይጣን ጊዜ ላለመስጠት ደግሞ ከእርሱ ጋር መጣላት ነው። መቼም ሰው ለጠላው ነገር የሚሆን ጊዜ አይኖረውም። ምንም ስራ ባይኖረውም እንኳ ከጠላው ጋር ላለመገናኘት ምክንያት ፈጥሮ ይርቅ የለ? ስለዚህ ለሰይጣን ጊዜ እንዳይኖርህ ከእርሱ ጋር ተጣላ። የሚገርመው ከሰይጣን ጋር ስትጣላ ደግሞ ከሰው እና ከእግዚአብሔር ጋር በፍቅር መኖር ትችላለህ፡፡ ከ24ቱ ሰዓት ለሰይጣን የሚሆን ጊዜ ከሌለን መቼም ቢሆን ኃጢአት ሊያሰራን የሚችልበት ዕድል ወይም አጋጣሚ አይኖርም። የተሰጠን ጊዜ ለሰጪው አምላክ መልሰን እንሰጠው ዘንድ ማስተዋሉን ያድለን።

🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹 በእንተ ማኅሌተ ጽጌ                            🌹🖋️️️️በዲ/ን አውራሪስ በላይ ማኅሌተ ጽጌ ከሁለት የግዕዝ ቃላት ጥምረት የተገኘ ነው፡፡ #ማኅሌት ማለት ኀለየ ከሚለው ግስ የወጣ ሲሆን ትርጓሜውን ምስጋና፣ መወድስ ማወድስ ማለት ነው፤ #ጽጌ ማለት ደግሞ አበባ፣ የፍሬ ምልክት፤ ውበት፣ ደም ግባት ማለት ነው፡፡ 🌹🌹🌹🌹✨✨✨✨✨ #ማኅሌተ_ጽጌ ተብሎ በአንድነት ሲነገር እና ሲተረጎም ደግሞ የአበባ የፍሬ ምስጋና መዝሙር መወድስ ማለት ነው፡፡ ይህም አበባ ተብላ የተጠራች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እና ፍሬ የተባለው ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ በጎ በጎ መዓዛ ባላቸው አበባዎች እና ፍሬዎች እየተመሰሉ የሚመሰገኑበት ምስጋና ማለት ነው፡፡ 🌹🌹🌹🌹✨✨✨✨✨ #የማኅሌተ_ጽጌ ደራሲ ሊቁ አባ ጽጌ ድንግል ነው፡፡ አባ ጽጌ ድንግል (ጽጌ ብርሃን) የተወለደውም በሰሜን ሸዋ በይፋት አውራጃ ውስጥ ሲሆን፤ ሀገሩ ይፋት ሃይማኖቱ ኦሪት ነበረ፡፡ በዕለታት በአንዱ ቀን በጻዲቁ በአቡነ ዜና ማርቆስ በተገደመው ደብረ ብስራት ተብሎ በሚጠራው ስፍራ ሄዶ ሳለ ጻዲቁ አቡነ ዜና ማርቆስ በትንቢተ ኢሣይያስ የተነገረውን በኅብረ አምሳል ያጌጠውን ‟ ትወጽእ በትር እምሥርወ እሴይ ወየዐርግ ጽጌ እምኔሃ ፤ ከእሴይ ግንድ በትር ትወጣለች ከሥሩም ቁጥቋጦ ያፈራል" የሚለውን ሲያነብ ቢሰማ ቀድሞውንም ቃሉን የሚያውቀው ይሁንና ትርጓሜውን ያልተረዳ መሆኑን ጠይቆ እንዲተረጉሙለት ቢጠይቅ ጻዲቁ አቡነ ዜና ማርቆስ ንባቡን ከትርጓሜ ትርጓሜውን ከምስጢር አስማምቶ ትወጽእ በትር እምሥርወ እሴይ፣ የሚለው ንባብ ከእሴይ ነገድ የሕይወት በትር የኾነች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ትወለዳለች ማለት ነው፡፡ ✨ ✨ ✨ ✨✨✨ ሙሉዉን ያንብቡ 📖📖📖 🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹

✨ የዕለት እንጀራችንን ስንቀበል የአደራውንም መስጠት አንዘንጋ✨ በጸሎት ኃይል የሚያምን አንድ ጽኑዕ ክርስቲያን ነበር ይኽም ክርስቲያን ጥሪት የሌለው ድኻ፣ የሚበላ የሚቸግረው ረኻብተኛ፣ ልብሱ በላዩ ላይ አልቆ የታረዘ ምስኪን ነው፡፡ ከዕለታት አንድ ቀን በጸሎት ሕይወቱ የነበረውን ትጋት በቅርበት ያውቅ የነበረው አንድ ወዳጁ እየተቆጣ "ቢያንስ ለረኻብኽ ማስታገሻ ቁራሽ ዳቦ እንኳን ማሰጠት ካልቻለ የአንተ ጸሎት ፋይዳው ምንድን ነው? ይቅርብኽ በቃ! ፈጣሪኽ አይሰማኽም ማለት ነው" ሲል ተስፋ በሚያስቆርጥ ቃል ተናገረው፡፡ ያም ምስኪን ክርስቲያን እንዲኽ ሲል መለሰለት "እግዚአብሔርማ አልረሳኝም ለአንዱ ሰው ከዕለት እንጀራው የበለጠ አትርፎ በመስጠት ለእኔ እንዲያካፍለኝ መልዕክተኛ አድርጎት ነበር ነገር ግን ይኽን አደራ የተቀበለው ሰው ዘነጋኝ  ስለዚኽ እግዚአብሔር ሳይኾን አድራሹ ሰው ረስቶኛል!" 🙏 የዕለት እንጀራችንን ስጠን ብለን የለመንነው አምላክ ከዓመት እንጀራችን አትርፎ የሚሰጠን የሚበቃንን ያኽል ተመግበን በቀረው ለሌሎች አድራሽ መልዕክተኞች እንድንኾን ነው።

alemnesh (1) (1).mp38.08 MB

የእርዳታ ጥሪ መዘ/ት አለምነሽ በሀሩ የአሰላ ደ/ብ/ቅ/ገብርኤል መ/ሃ ሰንበት ት/ቤት አገልጋይ ስትሆን ሁለቱም ኩላሊቶችዋ ፌል ስላረጉ እና ለህክምና ከፍተኛ ገንዘብ ስለተጠየቀች ሁላችሁም እንድትተባ
የእርዳታ ጥሪ መዘ/ት አለምነሽ በሀሩ የአሰላ ደ/ብ/ቅ/ገብርኤል መ/ሃ ሰንበት ት/ቤት አገልጋይ ስትሆን ሁለቱም ኩላሊቶችዋ ፌል ስላረጉ እና ለህክምና ከፍተኛ ገንዘብ ስለተጠየቀች ሁላችሁም እንድትተባበርዋት ስንል ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። ሁላችሁም በጸሎት እንድታስቧት!

ፎቶ :- መስቀል 2017 ዓ.ም አሰላ
+6
ፎቶ :- መስቀል 2017 ዓ.ም አሰላ

ፎቶ :- መስቀል 2017 ዓ.ም አሰላ
+5
ፎቶ :- መስቀል 2017 ዓ.ም አሰላ

ፎቶ :- መስቀል 2017 ዓ.ም አሰላ
+9
ፎቶ :- መስቀል 2017 ዓ.ም አሰላ

መስቀል ዕፀ ሕይወት ነው። መስቀል ዕፀ መድኃኒት ነው። መስቀል ዕፀ ትንቢት ነው። መስቀል ዕፀ ዕረፍት ነው። መስቀል ሰይጣንን የሚያጠፋ ምሳር ነው። የአጋንንትንም ራሶች የሚቆርጥ ሰይፍ ነው። መስቀል
መስቀል ዕፀ ሕይወት ነው። መስቀል ዕፀ መድኃኒት ነው። መስቀል ዕፀ ትንቢት ነው። መስቀል ዕፀ ዕረፍት ነው። መስቀል ሰይጣንን የሚያጠፋ ምሳር ነው። የአጋንንትንም ራሶች የሚቆርጥ ሰይፍ ነው። መስቀል ርኵሳን መናፍስትን የሚወጋቸው የእሳት ዘገር ነው። የአመስቴማውያንንም ሠራዊት የሚመታ የመብረቅ ጦር ነው። መስቀል ማኅተመ ሥላሴ የሌለው ሰው ወደእርሱ ሊቀር በው የማይቻለው አምባ መጠጊያ ነው። መስቀል ከግራም ከቀኝም ለሚመጣ ጠላት የጽድቅ ጋሻ ነው። ጳውሎስ ውጊያችሁ ከሥጋና ከደም ጋር አይደለምን እንዳለው መስቀል የጦር መሣርያ ነው። መስቀል የጦር ውጋት ሊቀድደው፣ የቀስትና የዘንግም ጫፍ ሊበላው የማይችል የሃይማኖት ጥሩር ነው። መስቀል አማሌቃውያንን ለመዋጋት በራፊድ በረሐ በተዘረጋው በሙሴ እጅ አምሳል የተሠራ ነው። መስቀል በሙሴ እጅ ወደ ውስጥ በተጨመረ ጊዜ መራውን ውኃ በቀር በረሐ ያጣፈጠ ነው። መስቀል የቅድስናና የንጽሕና ማኅተም ነው። መስቀል ለሚጋደሉ የድል አክሊል፤ ወደ በጉ ሰርግ ለተጠሩትም የሰርግ ልብሳቸው ነው። መስቀል የማይነጥፍ ምንጭ፣ በቁዔትም ጥቅምም የሞላበት የክብር ጉድጓድ ነው። (ውዳሴ መስቀል - በአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ)

ፎቶ :- መስቀል 2017 ዓ.ም አሰላ
+5
ፎቶ :- መስቀል 2017 ዓ.ም አሰላ

ፎቶ :- መስቀል 2017 ዓ.ም አሰላ
+9
ፎቶ :- መስቀል 2017 ዓ.ም አሰላ

ለትውስታ! መስቀል በአሰላ 2016 ዓ.ም 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 የአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 የቴሌግራም ቻናል:
+4
ለትውስታ! መስቀል በአሰላ 2016 ዓ.ም 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 የአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel Facebook:-   https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475

ብጹዕ ሥራአስኪያጁ የመስቀል ደመራ የዝማሬ ዝግጅትን በመጎብኘት መመሪያ ሰጡ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የባህር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከ
+4
ብጹዕ ሥራአስኪያጁ የመስቀል ደመራ የዝማሬ ዝግጅትን በመጎብኘት መመሪያ ሰጡ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የባህር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የ፳፻፲፯ ዓ.ም. ለመስቀል ደመራ በዓል የሚደረገውን የመዝሙር ዝግጅት ጎብኝተዋል። በየዓመቱ በድምቀት ለሚከበረው የመስቀል አስቀድሞ ዝግጅት እንደሚደረግ ይታወቃል። ብጹዕነታቸው በደብረ ገሊላ አማኑኤል ካቴድራል በመገኘት አገልጋዮቹን በማበረታታት አባታዊ መልእክት አስተላልፈዋል።