بسم الله الرحمن الرحيم
🎓Exit ወደክ?🎓🛍~~
🪭🪭 ምን አልባት እኮ መውደቅህ ከማለፍህ ተሽሎ ሆኖ ይሆናል አላህ ለኸይር ሽቶልህ ቢሆንስ፣የማለፍና የመውደቅ ሁኔታ የህይወትህ ስኬት ነፀብራቅ አታርገው ህይወት ከexit በሆላም ይቀጥላል ብቻ አልሀምዱሊላህ በል፣ግን ግን ምንአልባት እኮ ወተህ አልፈህ የረባ ነገር ላታገኝበት ስለሆነ አላህ ሌላ እድል እየሰጠህ ቢሆንስ አንድ መልካም ነገር ለማረግ chance እየሰጠህ ቢሆንስ?በቃጨአለ አደል የተሻለ ነገር እ... አላህ ምን ይላል በቁርአኑ🛍📕
{كُتِبَ عَلَيۡكُمُ ٱلۡقِتَالُ وَهُوَ كُرۡهٌ لَّكُمۡۖ وَعَسَىٰٓ أَن تَكۡرَهُواْ شَيۡئًا وَهُوَ خَيۡرٌ لَّكُمۡۖ وَعَسَىٰٓ أَن تُحِبُّواْ شَيۡئًا وَهُوَ شَرٌّ لَّكُمۡۗ وَٱللَّهُ يَعۡلَمُ وَأَنتُمۡ لَا تَعۡلَمُونَ}
{መጋደል እርሱ ለእናንተ የተጠላ ሲሆን በእናንተ ላይ ተጻፈ፡፡ አንዳች ነገርን እርሱ ለናንተ የበለጠ ሲሆን የምትጠሉት መኾናችሁ ተረጋገጠ፡፡ አንዳችንም ነገር እርሱ ለናንተ መጥፎ ሲሆን የምትወዱት መሆናችሁ ተረጋገጠ፡፡ አላህም (የሚሻላችሁን) ያውቃል ግን እናንተ አታውቁም፡፡}በቀራ 2/216.📕
📚አንድ የመስጂድ ኢማም ምን ሲሉ ሰማሁኝ መሰለህ የሆነ ጊዜ ረመዳን ላይ አንዳንድ ሰዎች መስጂድ መምጣት ከተከለከሉበት ምክንያት ዒባዳቸው ነው ይላሉ ዒባዳህ በአላህ ቤት እንኮን ደንቡን ጠብቆ መከናወን ሳይችል ሲቀር አላህ አንተን እቤት እንዳትመጣ ይከለክልሀል፣ከምን ጋር ላያይዘው ፈልጌ ነው አኺ/ኡኽቲ ምንአልባት አልፈህ ቢሆን ኖሮ ላንተ ህይወት ጥሩ ባይሆን ኖሮስ አለማለፍህ ደሞ ይበልጥ የተሻለ ቢሆንስ ለተሻለ ስብእናና ማንነት፣ለተሻለ ዝግጅት፣ለተሻለ personality train እያረገህ ቢሆንስ እ?፣አለ አደል በቃ አንተ ምታስበው እኮ ሁሌ ጥሩ ላይሆን ይችላል ማስበውን ጥሩ ከሆን ኸይር አርግልኝ ነው ሚባለውና፣ህይወትህ ቀለል አርጋት የመጨረሻህ አደለም ይሄ ውድቀት፣ትልቁ ኪሳራ አላህን ሳያውቁ ማለፍ ነው በዚ ዱንያ እሱ አውቀውና ፈርተው ከሚገዙት ባሮቹ ያርገንና እ....📚
~
🕐🏹🤲እና ግን አደራ አደራ ምልህ/ሽ በሰብር ላይ ነው። ትግስት ደሞ በዋነኝነት ችግሩ ሲፈጠር ብቻ ነው አደራ አንዴ ችግሩ ሲከሰት ሰብር ካለረግን ልክ ድንጋይ ላይ ውሀ ማፍሰስ ነገር ነው ሚሆነው በትግስት ላይ የመጣው ማስረጃችንን ደሞ ወደ ሆላ ሄድ ብለን ማጤን አለብን እስቲ ረሱል ﷺ የመጣውን ንግግር እንይ .....
ትእግስት ችግሩ በደረሰ በመጀመሪያው ወቅት ላይ የሚደረገው ነው!
ከአነስ ቢን ማሊክ (ረድየላሁ አንሁ) ተይዞ: እንዲህ ይላል፦
﴿مَرَّ النَّبِيُّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ بِامْرَأَةٍ تَبْكِي عِنْدَ قَبْرٍ، فَقَالَ : " اتَّقِي اللَّهَ وَاصْبِرِي ". قَالَتْ : إِلَيْكَ عَنِّي فَإِنَّكَ لَمْ تُصَبْ بِمُصِيبَتِي، وَلَمْ تَعْرِفْهُ. فَقِيلَ لَهَا : إِنَّهُ النَّبِيُّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ فَأَتَتْ بَابَ النَّبِيِّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ، فَلَمْ تَجِدْ عِنْدَهُ بَوَّابِينَ، فَقَالَتْ : لَمْ أَعْرِفْكَ. فَقَالَ : " إِنَّمَا الصَّبْرُ عِنْدَ الصَّدْمَةِ الْأُولَى﴾
“ነቢዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ከአንድ ቀብር አጠገብ ሆና በምታለቅስ ሴት ዘንድ አለፉ ‘አላህን ፍሪ ትዕግስት አድርጊ’ አሏት። ‘ዞር በልልኝ! በኔ የደረሰው አልደረሰብህም’ ብላ መለሰችላቸው። አላወቀቻቸውም ነበር። ከዚያም ነቢዩ መሆናቸው ተነገራት። ወደ ነቢዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ቤት ሄደች። ቤታቸው ስትደርስ ጠባቂ (ዘበኛ) አልነበራቸውም። እንዲህም አለቻቸው፦ ‘እርሶ መሆኑን ባለማወቄ ነው ይቅርታ።’ እሳቸውም፦ ‘በርግጥም ትዕግስት ሊኖር የሚገባው በመጀመሪያ ችግሩ በደረሰ ግዜ (ወቅት)ነው።’ አሏት።”
ቡኻሪ ዘግበውታል: 1283
~
=============================
🦺👒አንተስ/ቺስ exit አለፍክ/ሽ?ፈሊላሂል ሀምድ ምን ይሳነዋል እሱ ፣ግን ግን exit የህይወትህ ትልቁ ስኬት አታርገው ስኬትህ ሌላ ትልቅ ነገር ነዋ ምንድነው ካልከኝ ስኬትህ/ሽ ለምሳሌ ላስረዳህ/ሽ አኺ/ኡኽቲ?🦺✈️
~
እንደማንኛውም ወጣት የምትወዳትን ሴት ለማግባት ብዙ ትመኛለህ የተመኛሀትም ሴት ያንተ እንድትሆንም ብዙ ትኳትናለህ ፣ ትወጣለህ ትወርዳለህ ትለፋለህ • • • ከዛ አላህም አያስፍርህም ምኞትህን ይሞላልሀል ያንተ ትሆናለች አግብተሀት መኖር ትጀምራላቹ ከዛስ? ከዛማ ያ የጓጓህለት ብዙ የሆንክለት ነገር የሆነ ሰዓት ላይ ኖርማል ሆኖ ታገኘዋለህ ትለምደዋለህ - አንቺም እንደዛው • • • ካስታወስክ ሀይስኩል እያለህም ዩኒቨርስቲ መግባት ትመኝ ነበር ገባህ - ቀጥሎም መመረቅና ስራ መያዝ ያጓጓህ ነበር እሱም ሆነ - ከዛ ስራ ይዘህ ራስህን ቻልክ ። በዚህ አያበቃም መኪናና ቤት እንዲኖርህ ትመኛለህ - አሁንም ጌታህ ቸር ነው ይሰጣሀል -
~
የተመኘሀቸውን ነገሮች ስታገኝ ደስታህ እንደሚሞላና ሁሌም በሀሴት እንደምትኖር ነበር አንተ ምትጠብቀው ነገር ግን ብዙ የሆንክላቸውና ይሳኩ ማይመስሉህ ነገሮች ሁሉ ጊዜያቸውን ጠብቀው ሲሆኑ ትለምዳቸውና ያ ጉጉትህ ብን ብሎ ሲጠፋ ታየዋለህ ። ምድራዊ ነገሮች እንዲህ ናቸው ። ጣዕማቸው የሆነ ቦታ ላይ ይቆማል ። ፍላጎቶች ሁሉ ሚሟሉበት ፀጋዎች ማይለመዱበት የራህማን የእዝነት ካፊያ ዳኢም ሚዘንብበት የድሎት ሀገር ጀነት ብቻ ነው - ለሚለመድና ጣዕሙ ለሚያልቀው ዱኒያ ብዙ መጓጓት አያስፈልግም ። 👐🏻
ስኬትህ/ሽ (ግብህ)ጀነት ይሁን።
በመጨረሻም ታላቁ ዓሊም 🔖
💦ኢብኑል ቀይም አላህ ይዘንለትና እንዲህ ብሏል።
📚አብዘሀኛው በሰውነታችንም ሆነ በቀልባችን ላይ ለሚገኙ አካላዊም ሆነ መንፈሳዊ በሽታዎች የመፈጠር ሰበብ ትእግስት (ሶብር) ማጣት ነው።📚
📜زاد الـمعاد ٣٠٦/٤
~
✨ ✍rawna