Bashewam Primary & Junior School 1-8
الذهاب إلى القناة على Telegram
2 757
المشتركون
+424 ساعات
+87 أيام
+5630 أيام
أرشيف المشاركات
ለወላጆች:- ከላይ ባለው ፕሮግራም መሰረት የ8ኛ ክፍል ማክሰኞ በቀን 22/08/2016 ዓ.ም 5:00 ሰዓት ላይ ፈተናዉን እንደጨረሱ እንዲሁም 6ኛ ክፍሎች ሐሙስ በቀን 24/08/2016ዓ. ም 4:00ሰዓት ላይ ፈተናዉን እንደጨረሱ ወደ ቤት የሚለቀቁ መሆኑን እየገለፅን ማክሰኞ ሰርቪስ የሚጠብቁ ተማሪዎች ግቢ ዉስጥ ቆይተዉ መሄድ የሚችሉ መሆኑን እንገልፃለን::
ለ 6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ::
የ2016ዓ.ም የ2ኛው ሴሚስተር የከተማ አቀፍ ሞዴል ፈተና ከሚያዚያ 21-24/2016ዓ.ም የሚሰጥ መሆኑን መግለፃችን ይታወቃል:: በመሆኑም በፈተና ወቅት 8ኛ ክፍሎች ከ500-700 ሰዓት ባለው ሰዓት ዉስጥ ቤታችሁ ቅርብ የሆነ ተማሪዎች ምሳ በልታችሁ መመለስ የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን 6ኛ ክፍሎች ግን ከግቢ መዉጣት የማይቻል ስልሆነ ሁላችሁም ምሳችሁን ይዛችሁ እንድትመጡ እያሳሰብን የፈተና ፕሮግራም ከዚህ በታች የተላከ ምሆኑን እንገልፃለን::
(ቀን 18/08/2016 ዓ.ም) በክፍለ ከተማ ደረጃ በተደረገው የሳይንስና የቴክኖሎጂ ፈጠራ ስራዎች በወረዳችን ስር የሚገኙ ት/ ቤቶቾ:-
1. በተማሪ ከባሸዋም ት/ቤት
1.1. በአይቲ ት/ት ዘርፍ የ1ኛ ደረጃ
1.2. በፊዚክስ ት/ት ዘርፍ የ3ኛ ደረጃ
2. በመምህር ከባሸዋም ት/ቤት
2. 1. በአፋን ኦሮሞ የሬዲዮ ት/ት Modification
2.2. በሂሳብ ት/ት ዘርፍ የ2ኛ ደረጃ
3. በተማሪ ከሚኪሊላንድ ት/ቤት
3.1. በአካባቢ ሳይንስ ት/ት ዘርፍ የ3ኛ ደረጃ
4. በውዝዋዜ የሚኪሊላንድ ት/ቤት የ1ኛ ደረጃ በማግኘት በድምሩ እንደወረዳ 6 ሽልማቶችን በማግኘት ተጠናቋል።
ስለሆነም በቀጣይ መምህራንና ተማሪዎች ለፈጠራ ስራዎች ትኩረት ሰጥተው እንዲሰሩ ትልቅ መነቃቃትን ፈጥሯል።
ተሸላሚ ተማሪዎች፣መምህራን፣ ት/ቤቶች ብሎም ወረዳው የድካማችሁ ውጤት ነውና እንኳን ደስ አላችሁ፣ ደስ አለን።
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
