cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

Al EHSAN አል_ኢህሳን

የቻናሉ አላማ 1 ባለን አቅም እስልምናን በአግባቡ ለኡማው ማድረስ 2 ሙስሊሞችን በድናቸውም ይሁን በዱኒያ እውቀታቸው የነቁ እንድሆኑ መገፋፋት 3 ለወጣቶች ምክር 4 በልዩ መልኩ ሴቶችን ማንቃትና ሌሎቹም አለማዊና መንፈሳዊ ት/ቶች ይገኙበታል። ውድና የተከበራቹ የአል ኢህሳን ቻናል ቤተሰቦች ሆይ ውብና ማራኪ የሆኑ ሀሳብ አስተያያታቹ እንዳይለይን ♥♥ ለአስተያት @S1u9l አሁኑኑ ይቀላቀሉን 👇

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
190
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-27 أيام
-730 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

የትናንቱን ወንጀላችንን ሳንረሳ፣ የምሽቱ ኃጢታችን ሳይደርቅ ዛሬም በማለዳ ተነስተን ሌላ የምንጀምረው ነገርስ። አላህ ሆይ!አልፋታ ብሎ ዕድሜ ልካችንን የሚከታተለንን ጥፋታችንን ቁረጥ። ኃጢአቱ አብሮት ያልተነሳ ሰው ምንኛ ታደለ!ለንፁህ ተውበት አድለን - ያ ረብ። =t.me/+CL_1nL1UHLFhZjU8
إظهار الكل...
فقد يكرهك البعض لأنك مختلف ...لكن في داخلهم يتمنون أن يكونو مثلك.. ስለተቃረንካቸው ብቻ ከፊሎቹ ሊጠሉህ ይችላሉ ግን በውስጣቸው አንተን መምሰልን ይመኛሉ። http://t.me/nuredinal_arebi
إظهار الكل...
✍ያልገባኝ ነገር ይህ ነው። ➯እንደምንሞት በርግጠኝነት እናውቃለን ነገር ግን ከሞት በኋላ ላለው ህይወት አልተዘጋጀንም በጤና ነው ወይ ቤተሰብ!!!?
إظهار الكل...
01:44
Video unavailableShow in Telegram
#Palestine ዛሬ አይርላንድ ፣ ኖርዌይ እንዲሁም ስፔን ለፍልስጤም የነጻ ሀገርነት እውቅና እንደሚሰጡ በይፋ አስታወቁ። " የዛሬው ቀን ለፍልስጤም እጅግ ታሪካዊ ቀን ነው " ተብሏል። የአየርላንድ ጠ/ሚኒስትር ሲሞን ሃሪስ " ዛሬ አየርላንድ ፣ ኖርዌይ እና ስፔን ለፍልስጤም የነጻ ሀገርነት እውቅና ሰጥተናል። ውሳኔውን ተግባራዊ ለማድረግ እያንዳንዳችን ማንኛውንም አይነት ብሔራዊ እርምጃ እንወስዳለን " ብለዋል። ጠ/ሚኒስትሩ ፥ " #በሚቀጥሉት_ሳምንታት ተጨማሪ ሀገራት ይህን ጠቃሚ እርምጃ ለመውሰድ ከእኛ ጋር እንደሚተባበሩ እርግጠኛ ነኝ " ሲሉ አክለዋል። የአይርላንድ መንግሥት ይህ የሀገርነት እውቅና የሁለት ሀገር መፍትሄን እንደሚደግፍና ለቀጠናው ዘላቂ ሰላም አስፈላጊ መሆኑን ገልጿል። የስፔኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ፔድሮ ሳንቼዝ እና የኖርዌይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የሆኑት ኢስፔን ባርት ኢይድ ሀገራቸው ከግንቦት 28 (እ.ኤ.አ) ጀምሮ ለፍልስጤም ግዛት እውቅና እንደሚሰጡ በይፋ አሳውቀዋል። የስፔኑ ጠ/ሚኒስትር ፔድሮ ሳንቼዝ ፥ " ምንም እንኳን ከአሸባሪው ቡድን #ሃማስ ጋር የሚደረገው ውጊያ ህጋዊ ቢሆንም ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ ለፍልስጤም የሰላም ፕሮጀክት የላቸውም " ብለዋል። የኖርዌይ ጠ/ ሚኒስትር ጆናስ ጋህር ስቶር በበኩላቸው ፥ " እውቅና ከሌለ (የፍልስጤም) በመካከለኛው ምስራቅ ምንም ሰላም ሊኖር አይችልም " ብለዋል። " ሽብር የተፈፀመው በሃማስና የሁለት ሀገር መፍትሄን በማይቀበሉ እንዲሁም የእስራኤልን መንግሥት በማይደግፉ ታጣቂ ቡድኖች ነው። " ሲሉ አክለዋል። " ፍልስጤም ነጻ አገር የመሆን መሠረታዊ መብት አላት " ብለዋል። የፍልስጤም #የነጻ_ሀገርነት እውቅና መስጠት በይፋ ከተሰማ በኃላ የእስራኤል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር #በኖርዌይ እና #በአይርላንድ የሚገኙ አምባሳደሮችን በአስቸኳይ ወደ እስራኤል እንዲመለሱ አዘዋል። ሚኒስትሩ፤ " የዛሬው ውሳኔ ሽብርተኝነት እንደሚከፍል ለፍልስጤማውያን እና ለዓለም መልእክት ያስተላለፈ ነው " ብለዋል። መረጃው የስካይ ኒውስ ነው። More - @thiqahEth
إظهار الكل...
ኢማሙ አሽ _ሻፊዒይ ከኢማሙ አህመድ ጋር ኢማሙ አህመድ ከኢማሙ አሽ _ሻፊዒይ ከትልልቅ ተማሪዎች አንዱ ነው። ኢማሙ አህመድ ኡስታዛቸውን በጣም ይወዷቸው ነበር በሰዎች እና በልጆቻቸውም አጠገብ ያወድሷቸው ነበር ስለ ጀግንነታቸውም ያነሱ ነበር።ከዚህ የተነሳ የኢማሙ አህመድ ልጃቸው ሁልጊዜ ኢማሙ አሽ _ሻፊዒይን ለማየት ዒባዳቸው እንዴት እንደሆነ ለማየት ትጓጓ ነበር።         ከእለታት አንድ ቀን ኢማሙ አሽ _ሻፊዒይ ወደ ኢማሙ አህመድ ቤት እንግድነት ሄደው አደሩ ።የኢማሙ አህመድ ልጅ ሁኔታቸውን በማየት ነበር እና ከኢማሙ አሽ _ሻፊዒይ የማይጠበቅ 3 ነገራቶችን ተመለከተች። 1ኛ  ምግብ ቀረበላቸው እና ኢማሙ አሽ _ሻፊዒይ ምግቡን አብዝተው በሉ ሆዳቸው እሰከሚሞላ ድረስ። 2ኛ   ከበሉ በኋላ ገብተው ተኙ ሰላተ ለይል ሳይሰግዱ አደሩ። 3ኛ  የሱብሂ አዛን ሲደረግ ውዱእ ሰያደርጉ ወደ መስገጃ ቦታ ሄደው ሰገዱ። ከእነዚህ ክስተቶች የተነሳ ኢማሙ አሽ _ሻፊዒይን በጠበቀቻቸው መንገድ ስላላገኘቻቸው በጣም ደነገጠች ፈዘዘችም መታገስ አቃታት ። አባቷን እንዲህ ብላ ጠየቀች፦ እንዴት ኢማሙ አሽ _ሻፊዒይን በመሰለ ትልቅ ዓሊም እነዚህ ነገሮች ይታያሉ? ኢማሙ አህመድም ይህን ጉዳይ ከራሳቸው መስማት አለብኝ ብለው ሄደው ስለ ሁሉም ነገር ጠየቋቸው። ኢማሙ አሽ _ሻፊዒይም እንዲህ ብለው መለሱላቸው፦ 1ኛ  ምግቡን ሆዴ እስከሚሞላ የበላሁት ምግብህ ከሀላል መሆኑን ስላወኩኝ እና የደጋግ ሰዎች ምግባቸው መዳኒት መሆኑን ስላወኩኝ ነው።የበላውት ስለራበኝ ሳይሆን ለመዳኒትነት ነው የበላውት። 2ኛ ስለመተኛቴ ደሞ ወሏሂ አይኖቼ ሳይተኙ ነው ያደሩት ምክንያቱም ፊቅሃዊ በሆነ በአንድ መስአላ( በአንድ ሀዲስ)  ላይ እያስተነተንኩኝ ነው ያደርኩት በአንዷ ሀዲስ ውስጥ 72 ለሙስሊሞች የሚጠቅሙ ነገራቶችን አውጥቼበታለው በእውቀት ፍለጋ ቢዚ መሆን ከሌሊት ሰላት ስለሚበልጥ ነው። 3ኛ  ውዱእ ሳላደርግ የሰገድኩት ስላልተኛውኝ ውዱእ አልፈታውም። ባላወቅነው ነገር ሰውን ከመፈረጅ እንጠንቀቅ ኢንሻአላህ በሌላ እውነተኛ ታሪክ እመለሳለው። قصة الإمام الشافعي مع الإمام أحمد كان الإمام أحمد من أبرز طلاب الإمام الشَّافعي وكان يحبُّه حباً كبيراً، وكان دائم الثناء عليه أمام النَّاس وأمام أبنائه، فلمَّا قام الإمام أحمد باستضافة الإمام الشَّافعي في بيته، كانت ابنة الإمام أحمد متشوِّقة إلى رؤية الشَّافعي وعبادته.[٣] ولمَّا وُضع الطعام أكثر الشَّافعي من تناول الطَّعام، ثمَّ نام إلى الفجر ولم يقم الَّليل، وقام فصلَّى بهم الفجر بدون وضوء، فذُهلت ابنة الإمام أحمد لما رأته، ولم تطق صبراً، فسألت أباها عن ذلك إذ كيف يمكن أن يصدر هذا من إمامٍ بوزن الشافعي؟.[٣] فدخل الإمام أحمد إلى الشَّافعي وسأله عن تلك الأمور، فقال له الإمام الشافعي: أمَّا الطعام فما أكثرت منه إلَّا لأنِّي أعلم أنَّ طعامك حلالٌ، وطعام الصَّالحين شفاءٌ، فما أكلت جوعاً إنَّما أكلت تداوياً، وأمَّا نومي بعد الطعام وعدم قيامي لليل فوالله ما نامت عيني وإنَّما كنت أتفَّكر في مسائلَ من الفقه، فاستنبطت اثنتين وسبعين مسألةً ينتفع بها المسلمون، أمَّا صلاتي بكم الفجر بدون وضوء، فما نمت حتى أتوضأ، إنَّما كنت مستيقظاً طول الَّليل.
إظهار الكل...
Photo unavailableShow in Telegram
🎊🎊ታላቅ የምስራች🎊🎊 🎉🎉🎓🎓በአይነቱ ልዩ የሆነ የዳዕዋ እና የተመራቂ ተማሪዎች WELL GO ፕሮግራም በወራቤ ዩኒቨርሲቲ🎓🎓🎉🎉 🎓🎓እነሆ የወራቤ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ የዘንድሮ ተመራቂ ሙስሊም ወንድም እህቶቻችንን ምክንያት በማድረግ የፊታችን እሁድ ማለትም በ ቀን 11/09/2016 ዓ.ል በአይነቱ ልዩ የሆነ የዳዕዋ እና የ WELL GO ፕሮግራም አሰናድቶ ይጠብቃችኃል።🎓🎓 በፕሮግራሙ ከሚታደሙ እንቁ ተጋባዥ የሱና ዱዓቶች እና እንግዶች መካከል:- 🎋(ከአዲስ አበባ)🎋 🔖ኡስታዝ ጂብሪል አክመል (ኢንጂነር) 🔖ኡስታዝ ኢብራሂም ሙሳ 🎋(ከወራቤ)🎋 🔖ሸይኽ ኑረዲን ኸሊል 🔖ኡስታዝ ሙሀመድ ሰኢድ 🔖ኡስታዝ ኻሊድ ሙሀመድ 🎋(ከሻሸመኔ)🎋 🔖ወንድም አብዱልመሊክ አደም 🎋(ከጂማ)🎋 🔖ወንድም ሙባረክ ሙኽታር
🎋🎋በእለቱም የግጥም ፣ የሰነፅሁፍ እንዲሁም አጓጊ ሽልማቶችን የያዙ ጥያቄ እና መልሶችም ይኖራሉ።🎋🎋
🛍🎁በአላህ ፍቃድ ከ G.C ተማሪዎች ብዙ ተሞክሮዎችን እንቀስማለን ፣ ዲናችንን እንማማራለን ፣ የማይረሳ ጊዜን አብረን እናሳልፋለን!!!🎊🎓
N.B 1.በእለቱም የሻይ ቡና & የምሳ ፕሮግራም ተሰናድቶ ይጠብቃችኋል። 2. ዉድ ተመራቂ ተማሪዎች በእለቱ የፕሮቶኮል ጉዳይ ይታሰብበት።
https://t.me/wru_ms_officialgroup https://t.me/WRU_MSJ_Official_channel
إظهار الكل...
በኮንትራት ለስራ የሄዳችሁ ወገኖች ~ ከአሰሪያችሁ ጋር ለምሳሌ የሁለት አመት የስራ ውል (ኮንትራት) ገብታችሁ የተቀጠራችሁ ወገኖች ቃላችሁን ጠብቁ። የተሻለ ደመወዝ ፍለጋ በሚል ምክንያት አትጥፉ። ማንም ቢሆን ወጭ አውጥቶ ቃል አስገብቶ ካገሩ ያስመጣው ሰራተኛ ቃሉን አፍርሶ ጥሎት ቢጠፋ ደስ አይለውም። ራሳችሁ ላይ እንዲሆን የማትፈልጉትን ነገር ሌሎች ላይ አታድርጉ። ቃል ያስጠይቃል። አላህ እንዲህ ይላል፦ { وَأَوۡفُوا۟ بِٱلۡعَهۡدِۖ إِنَّ ٱلۡعَهۡدَ كَانَ مَسۡـُٔولࣰا } "በቃል ኪዳናችሁም ሙሉ፡፡ ቃል ኪዳን የሚጠየቁበት ነውና። [አልኢስራእ: 34] አስገዳጅ ሁኔታ ካልገጠመ በስተቀር። = የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor
إظهار الكل...
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

كناشة ابن منور

Photo unavailableShow in Telegram
ስለ የታላቁ ነጃሺ ዜሮ ዜሮ (00) መንደር አጭር ማብራሪያ (Grand Al Najashi 00 Village Project) 📎የፖሮጀክቱ ሰያሜ ፡ የታላቁ ነጃሺ 00 መንደር 📎 የሚሰራበት ቦታ፦ ትግራይ ክልል፣ ውቅሮ ነጃሺ 📎የዜሮ ዜሮ [00] መጠሪያ ሃሳብ የሸክ ሃጂ ኢበራሂም ቱፋ ሲሆን የታሪኩ መነሻና መገኛ ስፍራ (ትግራይ፣ ነጃሺ) ያመላክታል። ®የዚህ ፕሮጀከት የበላይ መሪ ሸክ ሃጂ ኢብራሂም ቱፋ (የኢትዮጵያ እሰልምና ጉዳይች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት) የፕሮጀክቱ አጋር ተቋማት። ©የትግራይ ክልል እሰልምና ጉዳዮች ጠቅላይ መክርቤት ©የአልነጃሺ መልሶ ግንባታና ልማት ኢኒሼቲቭ( Al-Nejashi Reconstruction and Development initiative (ARDI) የፖሮጅክቱ ዓላማ 📎በኢትዮጵያ ብሎም የአለም ትልቁ የሙሰሊሞች የታሪክ ቅርሰ የሆነው፤ ለሙሰሊሞች በከባዱ ፈተና ወቅት ከለላ(መጠጊያ) የሆኑት ንጉስ ነጃሺ መካነ ቀርስ አሻራ ያለበት ቦታ በትግራይ ክልል በነጋሺ ከተማ ክብራቸውና ታሪካችው የሚመጥን አለም አቀፍ የቱሪሰት መዳረሻ ቦታ አንዲሆን ሁሉም አቀፍ መንደር (ቪሌጅ) ለመገንባት ያለም ነወ፡፡ የሚገነበው መንደር Educational, health and Development facilities የሚያካትት ሲሆን በውስጡ የተለያዩ ንኡስ ፕሮጀክቶች የሚኖሩት ሲሆን በዋናነት:- 📌መስጂድ እና መድረሳ 📌ሙዚየም 📌ሐላል ሆቴል እና ሎጅ 📌የስፖርት ማዘውተሪያዎች 📌ኢስላሚክ የጥናትና ምርምር ተቋም 📌የቴከኒከና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች 📌ሆስፒታል እና ሌሎች Mohammedawel Hagos
إظهار الكل...
👍 1
00:30
Video unavailableShow in Telegram
በሱፊያው ዓለም በርካታ የሚመለኩ ቀብሮች አሉ። ቀብሮቹ ዘንድ በመሄድ ልጅ፣ ዝናብ እና የተለያዩ ሐጃዎችን ይማፀናሉ። የሞተ ሰው እንኳን የነሱን ጉዳይ ሊፈፅም ከራሱ፣ ከተሰራለት ዶሪሕ እንኳ መከላከል አይችልም። ይሄው ይሄ "ወሃቢ" የሆነ ጎርፍ ዶሪሑን ነቅሎ እየወሰደው ነው። { أَیُشۡرِكُونَ مَا لَا یَخۡلُقُ شَیۡـࣰٔا وَهُمۡ یُخۡلَقُونَ (191) وَلَا یَسۡتَطِیعُونَ لَهُمۡ نَصۡرࣰا وَلَاۤ أَنفُسَهُمۡ یَنصُرُونَ (192) } "ምንንም የማይፈጥሩትንና እነርሱም የሚፈጠሩትን (በአላህ) ያጋራሉን? ለእነርሱም መርዳትን የማይችሉትን ነፍሶቻቸውንም የማይረዱትን (ያጋራሉን)?" [አልአዕራፍ፡ 191-192] = የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor
إظهار الكل...
አሠላምአለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካትሁ ውድና የተከበራችሁ እህት ወንድሞች ይች እህታችን ስሟ ተምሬ አራጋው ጎቸል ትባላለች ከፓስፖርቱላይ እንዳለው በጠለብ ከአራትና አምስት ወር በፊት ሳኡድ ጂዳ ከተማ ገብታ ነበር እናም አሰሪዋ መንገድ ላይ ጥላታለች አሉን። አእምሮዋም ትክክል አይደለም ቪዶወውላይ እንደምታዩት።የቀረጿትም ልጆች ልንወስዳት ስንል ሴትየዋ እምቢአለችን አሉ በሰአቱ ዘወር ብለው ሲመለሱም ከቦታው እንዳላገኙዋት ነው የተናገሩት እና ጂዳ አካባቢ ያላችሁ በተለይ እባካችሁ ይችን እህታችንን ያያት ካለ እንድትተባበሩን በአክብሮት እንጠይቃለን። አላህ ሁላችንም ይጠብቀን እሷንም ያስገኛት!! እኔ የሰፈሯ ልጂ ነኝ ካገኛችኋት 0532053175 Bint Mohammed በዚህ ቁጥር በዋሳብም ወይም በመስመር ያገገኙኛል ይደውሉ የሠማችሁም አደራ ሸር አድርጉልኝ
إظهار الكل...