ar
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

الذهاب إلى القناة على Telegram

إظهار المزيد
1 065
المشتركون
-124 ساعات
-47 أيام
+530 أيام
أرشيف المشاركات
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ዋና ስራ ሂደት በተቋሙ ከሚገኙ አሰልጣኝ መምህራን ጋር የውይይት መድረክ አካሄደ:: በትምህርትና ስልጠና አካዳሚክ ካላንደሩ መሰረት
+4
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ዋና ስራ ሂደት በተቋሙ ከሚገኙ አሰልጣኝ መምህራን ጋር የውይይት መድረክ አካሄደ:: በትምህርትና ስልጠና አካዳሚክ ካላንደሩ መሰረት የስልጠና ዘመኑ የአንደኛ ተርም መጠናቀቁን ተከትሎ በተርሙ የተከናወኑ የትግበራ አፈፃፀም እና የሁለተኛ ተርም ማስጀመሪያ የውይይት መድረክ ተካሂዷል:: የውይይት መድረኩ የመሩት የኮሌጁ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ም/ዲን አቶ ኤሊያስ አህመድ በንግግራቸው እንደግለፁት በአካዳሚክ ካላንደሩ መሰረት የትምህርትና ስልጠናው የመጀመሪያ ተርም ተጠናቆ ሁለተኛውን ተርም ምንጀምርበት ወቅት ላይ እንደመሆናችን የነበሩ ክፍተቶችን በሚገባ ለይቶ መፍትሄ ለማበጀትና በሁለተኛው ተርም ላይ ማስተካከያ ለማድረግ ታልሞ የተዘጋጀ መድረክ መሆኑንም ገልፀዋል:: በመድረኩ ተሳታፊ ከነበሩት አሰልጣኝ መምህራንም የመጀመርያውን ተርም የትምህርትና ስልጠና ሂደቱን አስመልክቶ የተስተዋሉ ጠንካራ ጎኖችና ያጋጠሙ ትግዳሮቶችን በዝርዝር ያስቀመጡ ሲሆን አያይዘውም የመፍትሄ ሀሳብ ይሆናሉ ያሏቸውንም በመድረኩ አቅርበዋል:: በመጨረሻም ከመድረኩ በተገኙ ግብዓቶችና አጠቃላይ በተነሱ ሀሳቦች ላይ በመወያየት ሰፊ ማብራርያና ምላሽ የተሰጠባቸው ሲሆን በተጨማሪም በቀጣይ በተቋምና አገር አቀፍ ምዘና ሰልጣኝ ተማሪዎችን ማብቃት፣ፕሮጀክት መሰረት ያደረገ ስልጠና፣የትብብር ስልጠና፣ የዲጂታል ስልጠና አገልግሎት እና አሰልጣኝ መ/ራንን በረጅም ጊዜ የማሰልጠን ስነዘዴ ማብቃት ላይ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ የጋራ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ መድረኩ ተጠናቋል። የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የካቲት 19/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የካይዘን ፍልስፍና ስራ ቦታን ምቹ ከማድረግ ባሻገር ምርትና ምርታማነትን በማሻሻሉ ረገድ ፋይዳው የላቀ በመሆኑ ትኩረት መስጠት እንደሚገባ ተገለፀ። የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በተቋሙ የካይዘን ማሻሻያ ትግበራ ንቅናቄ ማስጀመሪያ የሆነ የግንዛቤ መስጫ መድረክ ለኮሌጁ አጠቃላይ ሰራተኞች አካሄደ:: የካይዘን ፅንሰ-ሀሳብን ተረድቶ በትኩረት መተግበር ከተቻለ ዘርፈ ብዙ ችግሮችን መፍቻ ቁልፍ መሳሪያ መሆኑን የገለፁት የኮሌጁ ም/ል ዲን እና የቴ/ሽ/ኢ/ኤ/አ ዋና ስራ ሂደት ሀላፊ የሆኑት አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ የካይዘን ትግበራ ምቹና ፅዱ የሥራ አካባቢን ከመፍጠር ባሻገር የሀብት ብክነትን ከማስወገዱም በተጨማሪ አሰራርን በማዘመን ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል መሆኑንም ገልፀዋል:: ም/ል ዲኑ አክለውም በቀጣይ ቀናት በተቋሙ በሚተገበረው የካይዘን ማሻሻያ ትግበራ ወቅት ከትግበራው የሚጠበቀውን ውጤት ለማግኘት ሁሉም የኮሌጁ አመራርና ሰራተኞች ተገቢውን ትኩረትና ተሳትፎ ማድረግ ያስፈልጋልም ብለዋል:: በመድረኩ የካይዘን ትግበራ ማሻሻያ ንቅናቄውን አስመልክቶ ለኮሌጁ ሰራተኞች የተዘጋጀውን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ከአስተዳደሩ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመት ቢሮ በመጡ ባለሙያ አማካኝነት የተሰጠ ሲሆን በዚህም በተቋም ደረጃ የካይዘን ትግበራ የሚፈጥራቸው ለውጦችና ዘርፈ ብዙ ጥቅሞችን የዳሰሰ የግንዛቤ ስልጠና መስጠት ተችሏል:: በተጨማሪም በኮሌጁ በቀጣይ ቀናት የሚተገበረውን የካይዘን ማሻሻያ ትግበራ መነሻነት የተዘጋጀውን የካይዘን ማስተግበሪያ እና የአፈፃፀም መከታተያ መመሪያ ሠነድ በኮሌጁ የካይዘን ልማት ቡድን መሪ በሆኑት አሰልጣኝ መ/ር አቤል ዘገየ አማካኝነት ለሰራተኛው የቀረበ ሲሆን በዚህም የትግበራውን አካሄድ እና የትግበራ ሂደቱ የሚያካትታቸውን ዝርዝር ጉዳዮች አስመልክቶ በሰፊው ገለፃ ማድረግም ተችሏል:: "ዛሬን እናሻሽል፣ ብክነትን እናስወግድ ፣ ቅልጥፍናን እንጨምር፣ ነገን እንገንባ!" የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የካቲት 19/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የሙያ ብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ማዕከል ከኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር በISO-17024 አተገባበር ላይ ስልጠና እየሰጠ መሆኑ ተገለጸ። ‎ ‎ስልጠናው ዓለም አቀፍ ስታንዳርድ የጠበቀ የሰነድ ዝግጅት ለማድረግ የሚያስችል ሲሆን  ለተቋሙ አመራሮች እና ባለሙያዎች እየተሰጠ እንደሚገኝም ተመላክቷል። ‎ በስልጠናው ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት በቢሮው የሙያ ብቃት ምዘናና ማረጋገጫ ማዕከል ዋና ዳይሬክተር አቶ አሚን አብዱላሂ ባደረጉት ንግግር ማዕከሉ ከኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት ጋር በገባው ውል መሠረት ISO-17024 ለመተግበርና አለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ሰነድ በመዘጋጀት የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመን ያለመ ነው ብለዋል። ‎ ‎ISO-17024 የተቋማትን አገልግሎት ደረጃ በማሻሻል የሰው ኃይልን በማደራጀት እና የመረጃ ጥራትን በማጎልበት የተገልጋይ እርካታን ለመጨመር አጋዥ የሆነ ዓለም አቀፍ ስታንዳርድ ስለመሆኑም አቶ አሚን አብዱላሂ ተናግረዋል። ‎ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት የካቲት 18/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

በኮሌጁ የሚሰጡ ትምህርትና ስልጠናዎች ጥራታቸውን የጠበቁ እንዲሆኑ አሰልጣኝ መምህራኖች ያላቸውን እምቅ አቅም አውጥተው ሊጠቀሙ ይገባል ተባለ፡፡ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የስልጠና ጥራትን ለማጠበቅ ያለመ ውይይት ከኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራን ጋር በዛሬው እለት አከናወነ፡፡ ኮሌጁ በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ላይ የልህቀት ማእከል እንደመሆኑ መጠን በኮሌጁ የሚሰጡ የተለያዩ ስልጠናዎች ጥራታቸውን የጠበቁና ዘመኑን የዋጁ እንዲሆኑ ይገባል ያሉት በውይይቱ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ ዲኑ አክለውም ኮሌጁ በመደበኛነት ከሚሰጣቸው ስልጠናዎች በዘለለ በየጊዜው በአሰልጣኝ መምህራኖች የሚሰሩ ቴክኖሎጂዎች የአካባቢውን ማህበረሰብ እነዲሁም ኢንዱስትሪዎች ተጠቃሚ ሊያደርጉ የሚችሉ የተለያዩ ቴክኖሎጂዎች የሚፈልቁበት ተቋም እንዲሆን ሁሉም ሊሰራ ይገባል ብለዋል፡፡ አቶ ሰለሃዲን አያይዘውም በኮሌጁ የሚሰጡ ስልጠናዎች ተግባር ተኮር እንደመሆናቸው የግብአት አቅርቦቱ ወጥነት እንዲኖረው የቅድመ ዝግጅት ስራዎች በሙሉ በየትምህርት ክፍል ውስጥ የሚገኙ አሰልጣኝ መምህራኖች በሙሉ የተሳተፉበት እንዲሆን ለቀጣይ አመት ከወዲሁ ዝግጅት እንዲደረግ ያሳሰቡ ሲሆን በተጨማሪም ኮሌጁ በ5 የተለያዩ ዘርፎች ላይ የኢንተርፕራይዝ ፍቃድ ከአስተዳደሩ እንደማግኘቱ መጠን አሰልጣኝ መምህራኖች ያላቸውን ልምድ፣እውቀት እንዲሁም ክህሎት ወደ ገቢ ማስገኛነት ሊለውጡት ይገባል ብለዋል፡፡ በውይይት መድረኩ ላይ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ሂደትን በማሻሻል የስልጠና ጥራትን ማረጋገጥ እንዴት እንደሚቻል በጥናት የተደገፈ ሰነድ በዶ/ር ሲሳይ አበራ የቀረበ ሲሆን በኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራኖች ጋርም ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን በአሰልጣኝ መምህራኖች የተነሱትን ጥያቄዎች የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ እንዲሁም የኮሌጁ ም/ዲን አቶ ቢቂላ ተሰማ በኩል ምልሽ ተሰጥቷል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን የካቲት 18/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

በአስተዳደሩ የሚገኙ የግል እና የመንግስት ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ላይ ለሚሰለጥኑ ሰልጣኝ ተማሪዎች በትምህርትና ስልጠና ተቋማት ኤች አይ ቪ ኤድስን መከላከል ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተዘጋጀ። መድረኩ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ከፍተኛ ቁጥር ያለው ወጣት በአንድ ቦታ የሚገናኙበት እንደመሆኑ መጠን ለኤች አይ ቪ ኤድስ ተጋላጭነቱን ለመቆጣጠር ቢሮዉ ከሚያዘጋጃቸው ተከታታይነት ያላቸው ስልጠናዎች አካል መሆኑ ታውቋል፡፡ ቢሮው ሰልጣኝ ተማሪ ዜጋውን ጤንነቱና ደህንነቱ የተጠበቀና የተረጋገጠ የነገይቱን ኢትዮጵያ ተረካቢ ባለሙያ አድርጎ ለማፍራት የሚያስችል ግንዛቤ እንዲፈጠር ማድረግ ችሏል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት የካቲት 17/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

በአስተደዳደሩ የሚገኙ የግል እና የመንግስት ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ላይ ለሚሰለጥኑ ሰልጣኝ ተማሪዎች በትምህርትና ስልጠና ተቋማት ኤች አይ ቪ ኤድስን መከላከል ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተዘጋጀ። መድረኩ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ከፍተኛ ቁጥር ያለው ወጣት በአንድ ቦታ የሚገናኙበት እንደመሆኑ መጠን ለኤች አይ ቪ ኤድስ ተጋላጭነቱን ለመቆጣጠር ቢሮዉ ከሚያዘጋጃቸው ተከታታይነት ያላቸው ስልጠናዎች አካል መሆኑ ታውቋል፡፡ ቢሮው ሰልጣኝ ተማሪ ዜጋውን ጤንነቱና ደህንነቱ የተጠበቀና የተረጋገጠ የነገይቱን ኢትዮጵያ ተረካቢ ባለሙያ አድርጎ ለማፍራት የሚያስችል ግንዛቤ እንዲፈጠር ማድረግ ችሏል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት የካቲት 17/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+7

የድሬዳዋ አስተዳደር ካቢኔ ወደ ሪፎርም የሚገቡ ተቋማት ለይቶ ወደ ስራ እንዲገቡ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት ቢሮው ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑ ተገለጸ፡፡ ሀገራችን የጀመረችውን የብልፅግና ጉዞ ለማፋጠ
የድሬዳዋ አስተዳደር ካቢኔ ወደ ሪፎርም የሚገቡ ተቋማት ለይቶ ወደ ስራ እንዲገቡ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት ቢሮው ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑ ተገለጸ፡፡ ሀገራችን የጀመረችውን የብልፅግና ጉዞ ለማፋጠን የመንግስት አገልግሎት ዘርፉን የማሻሻል/ሪፎርም/ የማድረግ  ስራዎች በስፋት እየተከናወኑ ይገኛል፤ በድሬዳዋ አስተዳደርም በተተገበሩት የሪፎርም ስራዎች አበረታች ውጤት እንደተመዘገበና ይህንን አጠናክሮ ለማስቀጠልም  ወደ ሪፎርም ከገቡ ተቋማት መካከል የሥራና ክህሎት ቢሮ አንዱ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በዚህም የሥራና ክህሎት ሚንስቴር ዕቅድን መነሻ በማድረግ የቢሮው ዕቅድ መዘጋጀቱንና ሪፎርም አስተግባሪ ኮሚቴዎችንም ከቢሮው እስከ ወረዳ አንድ ማዕከላት ድረስ እንዲሁም በፖሊቴክኒክ ኮሌጆች በማዋቀር በቢሮው ማኔጅመንት እንዲጸድቅ ማድረግ ተችሏል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ሌሎች አስፈላጊ ሰነዶች እየተዘጋጁ መሆኑንና ለአጠቃላይ ሰራተኛው በቀጣይ መድረክ ተዘጋጅቶ የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራ እንደሚሰራ የቢሮው ም/ኃላፊና የቴክክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ተናግረዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት የካቲት 17/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

በድሬዳዋ አስተዳደር ወረዳ 2 ቅርንጫፍ 2 አንድ ማዕከል ስር የሚገኙና በቢሮው ኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት የተለያዩ ድጋፎች የሚደረግላቸው ኢንተርፕራይዞችን ወደ ሞዴል ኢንተርፕራይዝነት ለማሳደ
+7
በድሬዳዋ አስተዳደር ወረዳ 2 ቅርንጫፍ 2 አንድ ማዕከል ስር የሚገኙና በቢሮው ኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት የተለያዩ ድጋፎች የሚደረግላቸው ኢንተርፕራይዞችን ወደ ሞዴል ኢንተርፕራይዝነት ለማሳደግ የሚያስችል የተደረገ የመስክ ምልከታና ልየታ በምስል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት የካቲት 11/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

በአስተዳደሩ ወረዳ 7 አንድ ማዕከል ስር የሚገኙና በቢሮው ኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት የተለያዩ ድጋፎች የሚደረግላቸው ኢንተርፕራይዞችን ወደ ሞዴል ኢንተርፕራይዝነት ለማሳደግ የሚያስችል የመስክ
+9
በአስተዳደሩ ወረዳ 7 አንድ ማዕከል ስር የሚገኙና በቢሮው ኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት የተለያዩ ድጋፎች የሚደረግላቸው ኢንተርፕራይዞችን ወደ ሞዴል ኢንተርፕራይዝነት ለማሳደግ የሚያስችል የመስክ ምልከታና ልየታ ተደረገ። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት የካቲት 11/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለታላቁ የረመዳን ፆም ወር በሰላም አደረሳችሁ። ረመዳን ከሪም !!
+1
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለታላቁ የረመዳን ፆም ወር በሰላም አደረሳችሁ። ረመዳን ከሪም !!

በአጫጭር ስልጠና ዘርፍ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት የ2018 ዓ.ም የመጀመሪያ ስድስት ወራት አፈጻጸም መነሻ በማድረግ የስልጠና ተቋማቱን አቅም ለመገንባት ያለመ  የክትትልና ድጋፍ መርሃግብር ተካሄደ፤ በዚህም የድጋፍና ክትትል መርሃግብር   የአጫጭር ስልጠና የሚሰጡ ተቋማት በዕቅድ መሠረት ስለመመራታቸው፤ በቂ የስልጠና ግብዓት ስለመኖሩ፤ የስልጠና ፍቃድ በተመለከተ በተሰጠው ፈቃድ ልክ እየሰሩ ስለ መሆናቸውና  እንዲሁም የማሰልጠኛ ማንዋሎችና መሳሪያዎች በሚገባ መኖራቸውን ጨምሮ የአጠቃላይ ሰልጣኞችን መረጃ በማደራጀት እረገድ ያሉበትን ሁኔታ ለመመልከትና በቀጣይ በተከታታይ ድጋፍ የሚያገኙበትን አግባብ ለማመቻቸት ተችሏል፡፡ በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ስር የሚገኘው የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ጀማል አደም እንደተናገሩት ይህ የድጋፍና ክትትል ልክ መደበኛ ስልጠና እንደሚሰጡ ተቋማት ሁሉ አጫጭር ስልጠና የሚሰጡ ተቋማትም ዜጎችን በማሰልጠን የሚያበቁ ናቸው ስለሆነም ትምህርትና ስልጠና ተቋማቱን አቅም ለመገንባትና በቅርበት በመከታተል መደገፍ አላማው አድርጎ መከናወኑን ተናግረዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት የካቲት 10/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

የኮሌጁን አሰልጣኝ መምህራንን በየጊዜው የሚሰሯቸውን የሚያሻሽሏቸውን ቴክኖሎጂዎች ተገቢውን የእሴት ሰንሰለት ትንተና በማድረግ ሊሰሩ እንደሚገባ ተገለጸ፡፡ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች በመደበኛው እና በአጫጭ
+6
የኮሌጁን አሰልጣኝ መምህራንን በየጊዜው የሚሰሯቸውን የሚያሻሽሏቸውን ቴክኖሎጂዎች ተገቢውን የእሴት ሰንሰለት ትንተና በማድረግ ሊሰሩ እንደሚገባ ተገለጸ፡፡ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች በመደበኛው እና በአጫጭር ስልጠና ሰልጣኞችን ተቀብሎ ከማሰልጠን በተጨማሪ ለአካባቢው ማህበረሰብ እንዲሁም ለኢንዱስትሪው ግብአት መሆን የሚችሉ የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን በመፍጠር እንዲሁም በማሻሻል የማህበረሰቡን እና የኢንዱስትሪውን ጫና መቀነስ የሚችሉ ቴክኖሎጂዎችን መፍጠር እና ማሻሻል የቴክኒክና ሙያ ስልጠና የትኩረት አቅጣጫዎች ናቸው፡፡ በዚሁ መሰረት በቴክኒክና ሙያ ተቋማት የሚሰሩ ቴክኖሎጂዎች ተገቢውን የእሴት ሰንሰለት ትንተና ሊደረግባቸው ይገባል፡፡ ይህንንም ተግባር ለማከናወን የሚረዳ ስልጠና በዛሬው እለት በድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በተለያዩ ትምህርት ክፍል ውስጥ ስልጠናን ለሚሰጡ አሰልጣኝ መምህራን እየተሰጠ ይገኛል፡፡ የኮሌጁ ም/ዲን እና የኢ/ኤ/ቴ/ሽ ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ትግስት በዙ በስልጠናው መክፈቻ ላይ በመገኘት እንደገለጹት በኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራን የሚሰሩ እንዲሁም የሚሻሻሉ ቴክኖሎጂዎች የማህበረሰቡን ችግር እንዲሁም የኢንዱስትሪውን ጫና መቅረፍ የሚችሉ እንዲሆኑ ተገቢውን የእሴት ሰንሰለት ትንተና ማድረግና ትንተናውን ተከትሎ መስራት ያስፈልጋል ያሉ ሲሆን አያይዘውም የኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራንና ሰልጣኝ ተማሪዎች የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን እንዲፈጥሩና ለማህበረሰቡ ማቅረብ እንዲችሉ ተገቢውን ክትትልና ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልጸዋል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን የካቲት 10/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የአካባቢውን ወጣቶች በቴክኒክና ሙያ ዘርፎች እና በዲጂታል ክህሎት የበቁ እንዲሆኑ ሁሉን አካታች ስራ እየሰራ እንዳለ ኮሌጁ ገለጸ፡፡ አካታችነት፣ዲጂታላይዜሽን፣የደረቅ ቆሻሻ አያያዝና መልሶ የመጠቀም እንዲሁም የኢንዱስትሪ ትስስር የቴክኒክና ሙያ ስልጠና የትኩረት አቅጣጫዎች ናቸው፡፡ በዚሁ መሰረት በቴክኒክና ሙያ ተቋማት የሚሰጡ ስልጠናዎች አካታች እንዲሆኑና ትምህርትና ስልጠና መጪውን ዘመን የዋጀ ከኢንዱስትሪዎች ጋር ትስስር በመፍጠር ለሁሉም ተደራሽ ማድረግ እንደሚኖርባቸው ይጠበቃል፡፡ የትኩረት አቅጣጫውን ወደ ተግባር ለመለወጥ በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራት ምን እንደሚመስሉ በጣሊያን የልማት ትብብር ኤጀንሲ የሚመራው CIFA for People (Second Life) ፕሮጀክት ተወካዮች ተጎብኝቷል፡፡ የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ በጉብኝቱ ወቅት እንደገለጹት የአካባቢውን ወጣቶችን በተለያዩ የቴክኒክና ሙያ ዘርፎች በማሰልጠን ወደ ሥራ እንዲገቡ እያደረገ ይገኛል።ያሉ ሲሆን አያዘውም በኮሌጁ የሚሰጡ ስልጠናዎች ወጣቶችን በቴክኖሎጂ ፈጠራ ላይ እንዲሰማሩና የራሳቸውን ኢንተርፕራይዝ እንዲመሰርቱ የሚያስችል እንዲሁም መጪውን ዘመን የዋጀ የኢንዱስትሪ ትስስር በመፍጠር ሰልጣኞች ገበያው ላይ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ የሚያደርጉ ሰልጠናዎችን እየሰጠ ይገኛል ብለዋል፡፡ በመጨረሻም ከኤጀንሲው ጋር በደረቅ ቆሻሻ አያያዝና መልሶ አጠቃቀም፣በዲጂታላይዜሽን እንዲሁም ከኢንዱስትሪ ትስስር ጋር በስፋት የምንሰራ ይሆናል ብለዋል፡፡ በኮሌጁ ተገኝተው ጉብኝት ያደረጉት በጣሊያን የልማት ትብብር ኤጀንሲ የሚመራው CIFA for People (Second Life) ፕሮጀክት ተወካዮች በበኩላቸው በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እየተከናወነ ያለው ተግባር መልካም መሆኑን ገልጸው በተለይም ወጣቶች የሚያገኙትን እውቀት ወደ ገቢ ምንጭ በመቀየር የተሻለ ህይወት እንዲመሩ እየተደረገ ያለው ድጋፍ የሚበረታታ ነው ይህንንም የኮሌጁን ጥረት በተለያዩ ለመደገፍ በጋራ የምንሰራ ይሆናል ብለዋል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን የካቲት 7/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ