Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
1 083
المشتركون
+924 ساعات
+207 أيام
+1530 أيام
أرشيف المشاركات
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በተቋሙ ለሚገኙ የጋራ አገልግሎት ሰራተኞች በአንድ እቅድ አንድ ሪፖርት አዘገጃጀት ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መድረክ አካሄደ::
የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ ያስፈለገበት ዋና አላማ ፈፃሚዎች ላይ ከዚህ ቀደም የሚታየውን የእቅድና ሪፖርት አዘገጃጀትን ክፍተት ለመሙላት እንዲሁም ሰራተኛው የተሰጠውን የስራ ሀላፊነት በዝርዝር ተረድቶ በሀላፊነት ስሜት እንዲተገብርና የሚጠበቅበትን እቅድን ሪፖርት በወቅቱ እንዲያዘጋጅ በማድረግ በሚፈለገው አቅጥጫ ለማስኬድ ታልሞ የተዘጋጀ የግንዛቤ መስጫ ስልጠና ነው::
ኢትዮ-ጣሊያን ፓሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
ነሃሴ 29/2016 ዓ.ም
የውጭ ሃገር የስራ ዕድል ምዝገባን በተመለከተ !
ለሚመለከተው ሁሉ
በውጪ ሃገር የስራ እድል ላይ ለመሳተፍ መመዝገብና የዕድሉ ተጠቃሚ መሆን የምትፈልጉ በርካታ አመልካቾች እንዳላችሁ ይስተዋላል፤
ምዝገባ በማድረግ የአማራጩ ተጠቃሚ መሆን የምትፈለጉ ዜጎች ምዝገባ ማድረግ የምትችሉበትን ሁኔታ በቅደም ተከተል በተዘጋጀው ቪዲዮ መመልከት ትችላላችሁ።
መልካም ዕድል !
የሥራዎ ባለቤት እርስዎ ነዎት !
Repost from Ministry of Labor and Skills - Ethiopia
#ለ2ኛ ዙር የሠመርካምፕ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ሀሳቦች ማበልፀጊያ መርሃ ግብር ምዝገባ ተጀመረ።
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና የኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ያዘጋጁት በአይነቱ ልዩ የሆነ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ሀሳቦች ማበልጸጊያ መርሃ ግብር ወጣቶች የፈጠራ ሐሳባቸውን እና ችሎታቸውን ወደ ተጨባጭ ሥራ እንዲለውጡ በማስቻል ለአገራችን ሁለንተናዊ እድገት ትልቅ አበርክቶ ያላቸው ቴክኖሎጂዎች ማስገኘት የሚያስችል ነው።
በዚህ መርሃ ግብር ለሁለተኛ ዙር ምዝገባ ተጀምሯል። ስለሆነም በማንኛውም መስክ የቴክኖሎጂ እና የሥራ ፈጠራ ሐሳብ ያላችሁ በሙሉ ከነሐሴ 27/2016 ዓ/ም ጀምሮ ከታች ባለው ሊንክ ገብታችሁ እንድትመዘገቡ ተጋብዛችኋል።
https://forms.office.com/r/CNMFUUSZZe
#ማሳሰቢያ
📌 ምዝገባው የሚካሄደው በተቀመጠው ድህረገጽ ብቻ ነው
📌ከምዝገባ በኋላ በሚካሄድ ልየታ መሠረት ለሚመረጡ የፈጠራ ባለሙያዎች የሠመር ካምፕ ፕሮግራሙ የሚካሄደው አዲስ አበባ ላምበረት መነሀሪያ አካባቢ በሚገኘው የኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ዋናው ካምፓስ ነው።
ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መረጃ
ነሃሴ 27/2016
በድረገጽ፡- http://mols.gov.et/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/MolsFDRE
ቴሌግራም፦https://t.me/fdre_mols
በአገር አቀፍ ደረጃ ለቴክኒክና ሙያ ስልጠና አሰልጣኞችና አስተባባሪዎች እየተሰጠ ያለው ስልጠና ቀጥሎ እየተካሄደ ይገኛል፡፡
በዚህም በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ሥር የሚገኙ ሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች ማለትም ድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ እና ኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች ላይ የሚያሰለጥኑ አሰልጣኝ መምህራን በሀሮማያ ዩኒቨርሲቲ የስልጠና ማዕከል ስልጠናቸውን እየተከታተሉ የሚገኝ ሲሆን ከስልጠናው ጎን ለጎን በበጎ አድራጎት ስራዎች የደም ልገሳ መርኃግብር አካሂደዋል፤
ዘርፉን ከስልጠና በላይ በማሰብ የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ላይ በምንሰራው ስራ አጠቃላይ ኢኮኖሚውን ትራንስፎርም የሚያደርግ ምቹ ሁኔታ ከመፍጠርም አልፎ የዘርፉን አቅም በመጠቀም ፈጥነን ከድህነት እንድወጣም የሚያስችል ነው፤ ከዚህ በመነሳት እነዚህን እሳቤዎች የዘርፉ ሁሉም አሰልጣኝ መምህራን በግንዛቤ የጨበጧቸውን ወደ ተግባር በመቀየር በቀጣይም በስልጠና ማዕከሉ አካባቢ የሚገኙ ማህበረሰቦችን በበጎ አድራጎት ስራዎች ተደራሽ ለማድረግ መዘጋጀታቸውንም ገልጸዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ነሐሴ 28/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የአስተዳደሩን አሰልጣኝ መምህራን በአዲሱ የትምህርትና ስልጠና እና የዘርፉ እሳቤ ላይ ያላቸውን ግንዛቤ ለማሳደግ እንዲሁም የአሰልጣኞችን ባህሪያዊና ቴክኒካዊ ብቃት ለማሳደግ ያለመ ስልጠና በሀገር አቀፍ ደረጃ በሀሮማያ ዩኒቨርሲቲ የስልጠና ማዕከል እየተሰጠ ይገኛል።
በሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እና ም/ኃላፊ ክብርት ፈጡም ሙስጠፋ ሀሮማያ ዩኒሸርሲቲ በመገኘት የስልጠና ሂደቱን ተመልክተዋል። በምልከታው ላይ ከድሬዳዋ አስተዳደር በስልጠናው የሚሳተፉ አሰልጣኝ መምህራን ጋር በመነጋገር አበረታቸዋል፡፡
የቢሮው ኃላፊዎች በቆይታው ከሰልጣኞችና ከስልጠና አስተባባሪዎች ጋር ቆይታ ያደረጉ ሲሆን ስልጠናው በጥሩ ሁኔታ እየሄደ እንደሆነ እና እንደ አስተዳደር የተሰሩ ስራዎች በተሞክሮ መቅረባቸው ተጠቁሟል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ነሐሴ 27/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
"ብቃት ለቴክኒክና ሙያ ልህቀት" በሚል መሪ ሃሳብ በድሬዳዋ አስተዳደር ለሚገኙ የቴክኒክና ሙያ አሰልጣኝ መምህራንና የስልጠና አስተባባሪዎች ስልጠና ተጀመረ፡፡
በዘርፉ ፖሊሲ፣ ስትራቴጂዎችና አዳዲስ እሳቤዎች ላይ የአሰልጣኞችን ግንዛቤ ከማሳደግ ባለፈ ቴክኒካዊና ባህሪያዊ ብቃቶችን በማሳደግ ለላቀ ውጤት ማዘጋጀት ዓላማ ያደረገ ሲሆን እንደ አገር 17 የስልጠና ማዕከላት 24 ሺህ የሚጠጉ የቴክኒክና ሙያ አሰልጣኞች ተሳታፊ የሚሆኑ ሲሆን ስልጠናው ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ 12 ቀናት ይካሄዳል፡፡
በዚህም በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ስር የሚገኙ ሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ እና የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች ላይ የሚያሰለጥኑ 285 የሚሆኑ አሰልጣኝ መምህራንና የስልጠና አስተባባሪዎች በሀሮማያ ዩኒቨርሲቲ የስልጠና ማዕከል ስልጠናውን የሚከታተሉ ይሆናል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ነሐሴ 22/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት ከትምህርት ሚኒስቴርና ከድሬዳ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በግብርና ናሙና ቆጠራ ላይ ለተዘጋጀው ስልጠና የመክፈቻና የኦረንቴሽን ፕሮግራም በማዘጋጀት ስልጠና መሰጠት ተጀመረ።
በዚህም በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራ እና የአንድ ማዕከል ዳይሬክቶሬት አስተባባሪነት በአስተዳደሩ የከተማና የገጠር ወረዳዎች የተመዘገቡ ዜጎችም ተሳታፊ ሆነዋል።
የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ እንደተናገሩት በመንግስትም ይሁን በግል የሚካሄዱ የሥራ ዕድል ፈጠራ ስራዎች ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መስሪያቤት ጀምሮ በዘመናዊና ዲጂታላይዝ ስርዓቶች የሚመሩ መሆናቸው ውጤት እያስገኙ እንደሚገኝ ማሳያ ይሆናል ብለዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ነሐሴ 20/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የሥራና ክህሎት ቢሮና የተጠሪ ተቋማቱ አመራሮችና ሰራተኞች‹‹የምትተክል ሀገር፣ የሚያፀና ትውልድ!›› በሚል መሪ ሀሳብ በአስተዳደሩ ወረዳ 05 የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር አካሄዱ፡፡
በመርሃ ግብሩ የሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊ እና ቴ/ሙ/ስ ኤጀንሲ ኃላፊ ክብርት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋን ጨምሮ የቢሮው እና የኮሌጆች አመራሮችና ሰራተኞች ተሳትፈዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ነሐሴ 17/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የሥራና ክህሎት ቢሮና የተጠሪ ተቋማቱ አመራሮችና ሰራተኞች‹‹የምትተክል ሀገር፣ የሚያፀና ትውልድ!›› በሚል መሪ ሀሳብ በአስተዳደሩ ወረዳ 05 የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር አካሄዱ፡፡
በመርሃ ግብሩ የሥራና ክህሎት ቢሮ ክብርት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋን ጨምሮ የቢሮው እና የኮሌጆች አመራሮችና ሰራተኞች ተሳትፈዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ነሐሴ 17/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
+9
የሥራና ክህሎት ቢሮና የተጠሪ ተቋማቱ አመራሮችና ሰራተኞች‹‹የምትተክል ሀገር፣ የሚያፀና ትውልድ!›› በሚል መሪ ሀሳብ በአስተዳደሩ ወረዳ 05 የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር አካሄዱ፡፡
በመርሃ ግብሩ የሥራና ክህሎት ቢሮ ክብርት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋን ጨምሮ የቢሮው እና የኮሌጆች አመራሮችና ሰራተኞች ተሳትፈዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ነሐሴ 17/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+4
በአንድ እቅድ አንድ ሪፖርት አተገባበርና የአንድ እቅድ አንድ ሪፖርት KPI ባህርያት ላይ ትኩረት ያደረገ ለድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና ለኢትዮ ጣልያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የማኔጅመንት አባላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በዛሬው እለት በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ውስጥ ተሰጠ፡፡
በአንድ እቅድ አንድ ሪፖርት አተገባበርና የአንድ እቅድ አንድ ሪፖርት KPI ባህርያት ላይ ትኩረት ተደርጎ የተሰጠው ይህ ስልጠና በሁለቱም የመንግስት ኮሌጆች የሚሰሩ ስራዎች ወጥነት እንዲኖራቸውና በአመቱ መጨረሻም የኮሌጆቹ አመራሮች በእቅድና ሪፖርቱ አተገባበሩ ላይ ወጥነት ያለው አሰራር ክፍተት እንዳይኖር ለማድረግ ታልሞ የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑን በእለቱ ለማወቅ ተችሏል፡፡
በአንድ እቅድ አንድ ሪፖርት አተገባበርና የአንድ እቅድ አንድ ሪፖርት KPI ባህርያት ላይ ያተኮረው ይህ ስልጠና ከድሬዳዋ ፕላንና ልማት ኮምሽን የተውጣጡ ከፍተኛ ባለሞያዎች ለሁለቱም ኮሌጆች የማኔጅመንት አባላት ስልጠናው ተሰጥቷል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ነሀሴ 16/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ
ቢዝነስዎን ስኬታማ ለማድረግ እንደግፍዎታለን 🤝
በ https://forms.gle/aG8JwtHPGwh8CaWn8 ተመዝግበው የመስራት ስራ ፈጠራ ፕሮግራም የሚሰጣቸውን ድጋፎች ይወቁ።
ነሃሴ 20, 2016 ዓ.ም
ከቀኑ 9:00 - 10:00 ሰዓት
ቀድመው ይመዝገቡ ቦታዎን ያሲዙ!
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+7
በዛሬው እለት በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ስር ያሉ የተለያዩ የትምህርት ክፍሎች በ2017 ዓ.ም በትምህርት ክፍሎቹ ላይ ስለሚተገበሩ የተለያዩ እቅዶች በየትምህርት ክፍል ቢሮ ውስጥ እንዲሁም የትምህርት ክፍል ተጠሪዎች በጋራ በመሆን ከውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ምክትል ዲን አቶ ሰልሃዲን አብዱልሃሚድ ጋር ውይይት የተደረገ ሲሆን፡፡
በውይይቱ ላይ የተሳተፉትና ስብሰባውን የመሩት የኮሌጁ ም/ዲንና የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ አቶ ሰልሃዲን አብዱልሃሚድ እንደገለጹት ሁሉም ትምህርት ክፍሎችበተናጥል ከማቀድ ይልቅ ሁሉም የትምህርት ክፍል አባላቶች በየትምህርት ክፍሎቻቸው የጋራ እቅድ በማቀድ ስራዎችን ለመስራት እንዲሁም ተፈጻሚ ለማድረግ በጋራ የታቀደ እቅድ አስፈላጊ ነው ስለዚህ ሁሉም የትምህርት ክፍል አባላቶች በቀረበው የ2017 ዓ.ም እቅድ ላይ በትኩረት እንዲሳተፉ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
ሁሉም የኮሌጁ የትምህርት ክፍል ተጠሪዎች ከትምህርት ክፍል አባላቶቻቸው ጋር የ2017 ዓ.ም የትምህርት ክፍል እቅዶች በትምህርትና ስልጠና፣በደመምህራን የደረጃ እድገት፣የኮሌጁ ውስጠ ገቢ ማሳደግ፣የመምህራን አቅም ግንባታ፣ኮሌጁን ከማስተዋወቅ አንጻር እንዲሁም የክረምት በክህሎት ስልጠና አተገባበር ላይ በጋራ በመሆን ስራዎችን እንደሚሰሩ መግባባት ላይ ደርሰዋል በዚህም ኮሌጁን በከተማው ብቻ ሳይሆን በምስራቅ ኢትዮጵያ ብሎም በመላ ሀገሪቱ ግንባር ቀደም ኮሌጅ እናደርገዋልን ብለዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ነሃሴ 14/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
