Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
1 068
المشتركون
+424 ساعات
-27 أيام
+230 أيام
أرشيف المشاركات
የሥራና ክህሎት ሚንስቴር የሱፐርቪዥን ቡድን በድሬዳዋ አስተዳደር የሚገኘውን አጠቃላይ የሥራና ክህሎት እንቅስቃሴ ዙሪያ ንቅናቄ ለመፍጠር እንዲያስችል ክትትልና ድጋፍ የማድረግ ሥራ በዛሬው ዕለትም ቀጥሎ የከተማና የገጠር ኢንተርፕራይዞችን በመጎብኘት እና የድጋፍና ክትትሉ አጠቃላይ ግብረመልስ ለቢሮው ቀርቦ ተጠናቀቀ፡፡
በመስክ ምልከታው በዋናነት መልካም አፈፃፀሞችን ለማስፋት፣ ማነቆዎችን ለመፍታት እና ድጋፍ የሚፈልጉ ሥራዎች ተለይተው በቀጣይም በተቋማዊ አቅም ግንባታ፣ በክህሎት ልማት፣ ሥራ ዕድል ፈጠራ እና የኢንዱስትሪ ሰላማዊ ግንኙነት ላይ የተቀመጡ ግቦች እንዲሳኩ መደላድል ለመፍጠር የሚያስችል ድጋፋዊ ጉብኝት እንደነበር በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ የሆኑት ክቡር አቶ ተሻለ በሬቻ አስታውቀዋል፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በበኩላቸው የተደረገው ሱፐርቪዥን እና የቀረበውን የድጋፍና ክትትል አጠቃላይ ግብረመልስ ተከትሎ በ2017 በጀት አመት በአስተዳደሩ በሥራ እና ክህሎት ዘርፍ የተከናወኑ የልማት ስራዎችን በተለይም የክህሎት ልማት፣ የስራ እድል ፈጠራ፣ የአሰሪና ሰራተኛ ጋር የተያያዙ ስራዎችን ተመልክቶ ድጋፍ ያደረገ የስራ ጉብኝት መሆኑ ለመሻሻል እና ለመጠናከር የሚሆን ግብዓት የተገኘበት እንደነበር ተናግረዋል።
የሱፐርቪዥን ቡድኑ ከድጋፍና ክትትል ስራው ጎን ለጎን በድሬዳዋ እየተገነባ የሚገኘውን የመደመር ትውልድ ቤተ መጽሐፍት ግንባታ እና የኮሪደር ልማት ሂደት ከዘርፉ ጋር ባለው ትስስር ያለበትን ደረጃ ምልከታና ጉብኝት አካሂደዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ግንቦት 30/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ተሻለ በሬቻ የሚመራ የሱፐርቪዥን ቡድን በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የተሰሩ ስራዎችን እየጎበኙ እንደሚገኝ ተገለጸ።
በሚኒስትር ዴኤታው የተመራው ቡድን በዛሬው ዕለት በዋናነት በአሰሪና ሰራተኛው ዘርፍ በኢንደስትሪዎች ያለውን አጠቃላይ የስራ ሁኔታ የአሰሪና ሰራተኛ ግንኙነትን በጤናማ መሰረት ላይ ለመገንባት የተሰሩ ስራዎች እና የሙያ ደህንነትና ጤንነት ያለበትን ደረጃ የሥራ ላይ ደህንነትና ጤንነት ቁጥጥርን ለማጠናከር ከኢንደስትሪው ጋር ያለው ተቀራርቦና ተቀናጅቶ የመስራት ሁኔታን የተመለከቱ ሲሆን በአስተዳደሩ ሁለት የመንግስት ኮሌጆች እየተካናወኑ የሚገኙ የተቋም ግንባታና የለውጥ ስራዎችንም በአካል በመገኘት ጎብኝተዋል፤ ከዚህ በተጨማሪም በስራ ዕድል ፈጠራ እና ከኢንተርፕራይዝ ልማት አኳያ በወረዳ 05 እና 06 የተተገበሩና የስራ ዕድል ፈጠራ ተግባራት ያስገኛቸው ውጤቶች በአንድ ማዕከሉ አመራሮች ሪፖርት የቀረበላቸው ሲሆን በቀረበላቸው ሪፖርት መሰረት በቀጣይ በመስክ ምልከታ የሚያደርጉም ይሆናል።
የሱፐርቪዥን ቡድኑ ድሬዳዋ የተገኘበት ዋና አላማ እንደ ሀገር በሥራና ክህሎት በኩል የሚሰሩ ስራዎች በህብረተሰቡ ተጠቃሚነት ረገድ የታሰበላቸውን ውጤት እንዲያስገኙ የእሴት ሰንሰለትን ማእከልነትን ጠብቆ ዝንባሌን መሰረት ባደረገው የዲጂታል ኢንተርፕራይዝ ልማት አማካይነት ክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ ሰፊ የንቅናቄ ተግባራትን ለማከናወንና በአይነቱ የተለየና መሰረተ ሰፊ ተጨባጭ ውጤት ማምጣትን ያለመ ድጋፍና ክትትል ለማድረግ መሆኑን ገልፀው በጉብኝታቸውም በአስተዳደሩ ሥራና ክህሎት በኩል የህብረተሰቡ ተጠቃሚነት ምን ደረጃ ላይ እንዳለ ለመመልከት ነዉ ብለዋል።
ዛሬን ጨምሮ በቀጣይ በአስተዳደሩ በሚኖራቸው ቆይታም የዘርፉ አመራር እና ባለሙያ ከአስተዳደሩ ቢሮ፣ አንድ ማዕከል፣ ቴክኒክና ሙያ ተቋማት፣ ኢንዱስትሪዎች ላይ እየተከናወኑ ያሉ የኢንዱስትሪ ሰላም ተግባራት እና የዘርፉን ተቋማዊ አቅም መሠረት ያደረገ ምልከታ በማካሄድ መዋቅሩን ማጠናከር፣ ክህሎት መር በሆኑ የሥራ ዕድል፣ በክህሎት ልማትና የኢንዱስትሪ ሰላም ዙሪያ ንቅናቄ ለመፍጠር የሚያስችል የክትትልና ድጋፍ በማድረግ ላይ እንደሚገኙ ሚኒስቴር ዴኤታው ገልጸዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ግንቦት 28/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ 1446 ኛው አመተ ሂጅራ የኢድአል-አድሃ ( አረፋ ) በዓል አደረሳችሁ አደረሰን።
አቶ ሮቤል ጌታቸው
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ
ኢድ ሙባረክ !
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ተሻለ በሬቻ የተመራ ልዑክ በድሬዳዋ አስተዳደር በዘርፉ የተሰሩ ሥራዎችን ለመመልከት ተገኝቷል።
ልዑኩ በድሬዳዋ የተገኘው በ2017 በአስተዳደሩ የሥራና ክህሎት ቢሮ የተሰሩ ስራዎችን ድጋፍዊ ሱፐርቪዥን ለማድረግ ነው ።
ተቋሙ በተለይ የዘርፉ አመራር ከአስተዳደር እስከ ወረዳና ቀበሌ፣ የአንድ ማዕከልና ብሎም እስከ ቴክኒክና ሙያ ተቋማት ባሉ ኢንዱስትሪዎች ላይ እየተከናወኑ ያሉ የኢንዱስትሪ ሰላም ተግባራት እና የዘርፉን ተቋማዊ አቅም መሠረት ያደረገ ምልከታ በማካሄድ መዋቅሩን ማጠናከር፣ ክህሎት መር በሆኑ የሥራ ዕድል፣ በክህሎት ልማትና የኢንዱስትሪ ሰላም ዙሪያ ያለውን አፈፃፀም ለማየት እና ድጋፍ ለማድረግ እንደመጡ ሚኒስትር ዴኤታው ዶ/ር ተሻለ በሬቻ በወቅቱ አብራርተዋል::
የሥራና ክህሎት ቢሮም በበጀት አመቱ የተሰሩ ስራዎችን የሚገልጽ ሰነድ ለሱፐርቪዥን ቡድኑ በዝርዝር አቅርቧል። የድጋፍዊ የሱፐርቪዥን ቡድኑ ከነገ ሐሙስ ጀምሮ ለተከታታይ ቀናት በድሬዳዋ በገጠርና በከተማ በቢሮው የተሰሩ ስራዎችን ተዟዙሮ እንደሚጎበኝ ከመርሃ ግብሩ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
©️ Dire Tv አማርኛ
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
