Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
1 068
المشتركون
+424 ساعات
-27 أيام
+230 أيام
أرشيف المشاركات
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
ወጣቶች በሰለጠኑበት የሙያ ዘርፍ ቅጥርን ሳይጠብቁ ስራ ፈጣሪ ዜጋ መሆን እንዲችሉ ተገቢውን ድጋፍ ማድረግ ይገባል ተባለ::
ግንቦት 25.2017 ዓ.ም
ADRA ኢትዮጵያ ከኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በመተባበር በኮሌጁ በSolar PV Installation Maintenance ሰልጥነው ለተደራጁ ማህበራት ወደ ስራ እንዲገቡ የሚያስችላቸውን የማቴሪያል እና የመስሪያ ቦታ ድጋፍ አደረገ::
በSolar Maintenance እቃዎችና የመስሪያ ቦታ ድጋፍ መርሀ-ግብሩ ላይ ለወጣቶች መልዕክት ያስተላለፉት የስራና ክህሎት ቢሮ ም/ሀላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በንግግራቸውም በዛሬው እለት ከፍተኛ ድጋፍ ከፕሮጀክቱ ያገኙ ወጣቶች የተፈጠራላቸውን ምቹ እጋጣሚ በአግባቡ ተጠቅመው በቀጣይ በዚህ መንገድ ለሚመጡ ወጣቶች አርአያ የመሆን ከፍተኛ ሀላፊነት አብሮ እንደተጣለባቸው የገለፁ ሲሆን አክለውም በተገኘው የማቴርያልና የመስሪያ ቦታ ድጋፍ በአስተዳደሩ የከተማ ወረዳና የገጠር ክላስተሮች በዘርፉ ያልተነካውን የስራ እድል በአግባቡ ተጠቅመው ራሳቸውን ብሎም ማህበረሰቡን ተጠቃሚ እንዲያደርጉ ምክራቸውን ለግሰዋል::
በፕሮጀክቱ እንደ ግብ የተቀመጠው 120 ሰልጣኞችን በSolar PV Installation Maintenance አሰልጥኖ ከስራ ጋር ማስተሳሰር መሆኑን ያስታወሱት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ሲሆኑ የመጀመሪያ ዙር ሰልጣኞች ስልጠናቸውን አጠናቀው ሲጨርሱ እንደትቋም በራሳቸው ስራ ፈጥረውና ተደርጅተው እዲሰሩ አስፈላጊው ድጋፍ ሁሉ እየተደረገ እንደሚገኝም ገልፀዋል::
የኮሌጁ ዲን አክለውም ኮሌጁ ከፕሮጀክቱ ጋር በመተባበር የማቴሪያል ድጋፉ በADRA ፕሮጀክት አማካኝነት እንደተደረገ ገልፀው እንደተቋም ለወጣቶቹ ድጋፍ በማድረግ ሂደት ውስጥ ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን በመነጋገር ኮሌጁ ለንግድ አገልግሎት የሰራቸውን ቤቶች ወጣቶቹ ተደራጅተው እንዲሰሩበት እድርገናልም ብለዋል::
በእለቱ በሁለት ማህበራት ለተደራጁ 21 ወጣቶች ከ450ሺህ ብር በላይ የሚያወጣ የSolar Maintenance እቃዎች ድጋፍ የተደረገላቸው ሲሆን ወጣቶቹም....
በInstallation
በMaintenance
የSolar እቃዎችን በማቅረብ እንዲሁም ተዛማችነት ያላቸውን ስራዎች ላይ ተሰማርተው እንደሚሰሩ ማወቅ ተችሏል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
በEASE ፕሮጀክት(ኢትዮጵያ) ዋና ሀላፊ ፕሮፌሰር ሀፍቶም ገ/እግዚአብሔር የተመራ ልዑክ በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የስራ ጉብኝት አካሄደ፡፡
ግንቦት 22.2017 ዓ.ም
ልዑካን ቡድኑ በኮሌጁ በነበረው የስራ ጉብኝት መርሃ-ግብር ወቅት የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ በEASE ፕሮጀክት ያለውን የአፈፃፀም ሂደትና እስካሁን የተሰሩ ተግባራትን ጨምሮ በኮሌጁ እየተከናወኑ የሚገኙ የተለያዩ የለውጥ ስራዎች በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ እንዲሁም በኮሌጁ ይEASE ፕሮጀክት አስተባባሪ ኢንጂነር ፋሲል ማዘንጊያ አማካኝነት ገልፃ ተደርጎላቸዋል::
የፕሮጀክቱ ዋና ሀላፊ የተመሪው ልዑክም በኮሌጁ ባደረጉት ምልከታና የተደረገላቸውን ገለፃ መነሻ በማድረግ ውይይቶች የተካሄደዱ ሲሆን የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በEASE ፕሮጀክት አተገባበር ላይ ያሳየው አፈፃፀም ለሌሎችም ፕሮጀክቱ ለሚተገበርባቸው ተቋማት ምሳሌ መሆን የሚያስችል መሆኑንም ዋና ሀላፊው ሀሳባቸውን ገልፀዋል::
በተጨማሪም ልኡካን ቡድኑ በኮሌጁ የሚገኙ የተለያዩ የትምህርትና ስልጠና ክፍሎችና ዎርክ ሾፖችን ጨምሮ የተሰሩ የለውጥ ስራዎችን ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን በመጨረሻም በፕሮጀክቱ ዋና ሀላፊ ፕሮፌሰር ሀፍቶም ገ/እግዚአብሔር አማካኝነት ለኮሌጁ በቀጣይ የፕሮጀክቱ አፈፃፀም ላይ የስራ አቅጣጫን በመስጠት ጉብኝቱን አጠናቀዋል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት ለባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መድረክ አካሄደ::
ግንቦት 22.2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት ከፌደራል በመጡ የፕሮጀክቱ ተጠሪዎች አማካኝነት የፕሮጀክቱ ትግበራ ላይ ከኮሌጁ ጋር አብረው ለሚሰሩ ባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል::
መድረኩን በንግግር ያስጀመሩት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ባስተላለፉት መልዕክትም ይህ ስልጠና በዋነኛነት በEASE ፕሮጀክት አተገባበር ላይ ጉልህ ሚና ላላቸው ባለድርሻ አካላት እንደተዘጋጀ ጠቅሰው ኮሌጁ ብቻውን የሚፈልገውን ውጤት ማሳካት እንደማችልና የሁሉንም ትብብር የሚጠይቅ በመሆኑ በተለይም ድሬዳዋ ላይ እንዲሳኩ የምንፈልጋቸውን ተግባራት እውን ለማድረግ እንዲያስችለን ሁላችንም የየድርሻችንን መወጣት ይጠበቅብናልም ብለዋል::
በዕለቱ ስልጠናውን ለተሳታፊዎች የሰጡት የEASE ፕሮጀክት(ኢትዮጵያ) የማህበራዊ ልማት ባለሙያ አቶ መለስ ይመር ሲሆኑ የፕሮጀክቱን ዋና ዋና አላማዎችን በዝርዝር ለመድረኩ ተሳታፊዎች የሚገልፅ ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን በተጨማሪም በፕሮጀክቱ አፈፃፅም ወቅት የኮሌጁ እንዲሁም የባለድርሻ አካላትን ሚና ምን ምን እንደሆኑ ለይተው በማስቀምጥ ግንዛቤ ሰጥተዋል::
በመቀጠልም በፕሮጀክቱ የአካባቢ ጥበቃ ባለሙያ በሆኑት አቶ ሰለሞን አሊ አማካኝነት በEnvironmental Screening ላይ ለተሳታፊዎች ሰፊ ማብራሪያና ገለፃ መስጠትም ተችሏል::
በቀረበው የግንዛቤ ማስጨበጫ ሰነድን መነሻ በማድረግም ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት የተደረገ ሲሆን የመደረኩ ተሳታፊዎች በፕሮጀክቱ አላማና አተገባበር ላይ የተሻለ ግንዛቤ እንዲያገኙ ያስቻለ መድረክ ሆኖ ተጠናቋል::
+6
#ዜና | ስራ ፈላጊ ወጣቶችን ከስራ ጋር የማገናኘት የንቅናቄ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገለፀ
#DGC ግንቦት 21/2017
በድሬዳዋ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ የተዘጋጀ ስራና ሰራተኛ አገናኝ ኤግዚብሽን ተካሂዷል ።
በመድረኩ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ የስራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ኤግዚብሽኑ ኢንዱስትሪዎች የሚያስፈልጓቸውን በየደረጃው ያለ የባለሙያና የሰራተኛ አቅም ከማቅረብ ረገድ ፋይዳ አለው ብለዋል።
የስራ አጥ ቁጥርን መቀነስ ማህበራዊ ቀውስን እንደሚከላከልል የገለፁት ወ/ሮ ፈጡም ድሬዳዋ የንግድ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ማእከል ለማድረግ እየተሰራ እንደመሆኑ በተለያዩ ሙያዎች እውቀትና ክህሎት ያላቸውን በርካታ ባለሙያዎች እንደሚያስፈልጉ፣ ይህንንም ለማሟላት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን በቅንጅት አየተሰራ እንደሚገኝ ምክትል ቢሮ ኃላፊዋ አስረድተዋል።
በሌላ በኩል በስራና ክህሎት ቢሮ የአሰሪና ሰራተኛ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ መሃመድ ኢብራሂም ቀደም ሲል በተበታተነ መልኩ ይከናወኑ የነበሩ ስራዎች በአንድ ተቀናጅተው በስራና ክህሎት ቢሮ መደራጀታቸው በርካታ ዜጎችን የሚጠቅሙ ስራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል።
የአሰሪና ሰረተኛ ዘርፍ ለአስተዳደሩ ነዋሪዎች በተለይም ለወጣቶች የተለያዩ የስራ ዘርፈች እንዲገናኙ የማድረግ ስራዎች በቋሚነት ከመከናወናቸው በተጨማሪ በየአመቱ በንቅናቂ መልክ የሚተገበሩ ስራዎች መኖራቸውን ዛሬም የተካሄደው ሰራና ሰራተኛ አገናኝ ኤግዚብሽን(ጆብ ፌር)የዚህ አካል መሆኑን ተናግረዋል።
በኤግዚብሽኑ ያገኝናቸው ኢንዱስትሪዎች እነዚ አይነቱ መድረኮች የሚያስፈልጓቸውን ባለሙያዎች ለማግኝት እንዲሁም ለወጣቶች የስራ እድል በመፍጠር እረገድ አስተዋፅኦ እንዳለው ተናግረዋል።
በአስተዳደሩ በየአመቱ የሚካሄደው የሠራተኛ መገናኛ ኢግዚቢሽን የስራ ፈላጊ ወጣቶችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ለመቀነስ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል ሲሉ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ሃላፊ ተናገሩ።
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ሶስተኛው ዙር የስራና ሠራተኛ መገናኛ ኢግዚቢሽን አካሄደ።
በቀጣይ ጊዜያት በአስተዳደሩ 60 ሺህ በላይ የስራ እድል ተጠቃሚ የሚያደርግ በተለያዩ የስራ ዘርፍ ላይ የስራ ዕድል እንደሚኖር የሚታወቅ ሲሆን በድሬዳዋ የሚገኙ ነዋሪዎች የስራ ዕድል ተጠቃሚ እየሆኑም እንደሚገኝ በተለያዩ አጋጣሚዎች ይገለፃል።
በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ አዘጋጅነት የተሰናዳው ሶስተኛው ዙር የስራና ሠራተኞች መገናኛ ኢግዚቢሽን አሠሪዎችንና የስራ ፈላጊ ዜጎች በአንድ መድረክ ያገናኘ መሆኑንም በመርሀግብሩ ላይ ተገልጿል።
በኢግዚቢሽኑ ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ሃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ፈላጊ ወጣቶችን ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊ ቀውስን ለመቅረፍ ምቹ መደላድል የሚፈጥር ኢግዚቢሽን ነው ብለዋል።
በኢንዱስትሪ እና ንግድ ዘርፍ ላይ ለተሰማሩ ድርጅቶች የቴክኖሎጂ እና የዕወቀት ሽግግር ለማድረግ ትልቅ አቅም ይፈጥራል ብለዋል።
ላለፉት አመታት በተሰሩት ተከታታይነት ያለው የስራና ሠራተኛ መገናኛ መርሀግብሮች ከፍተኛ የስራ ዕድል ፈጥሯል ሲሉ ምክትል ቢሮ ሃላፊዋ ተናግረዋል።
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የአሰሪና ሠራተኛ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር መሀመድ ኢብራሂም በበኩላቸው እንደ ድሬደዋ አስተዳደር ምቹ የስራ እድልን ከመፍጠር እና የስራአጥ ቁጥሩን ለመቀነስ የሚደረገውን ጥረት የሚያግዝ የአሰሪ ሰራተኛ የስራ ቀጣሪዎችን በአንድ መዓከል የሚያገናኘው ኢግዝቪሽን አይነተኛ ሚና ይጫወታል ሲሉ ተናግረዋል። ስራ አጥ የሆኑ እና በየቦታው ተበታተነውን የቅጥር አሰራር በቀጥታ የሚያገናኝበት ምቹ መገናኛ መንገድ ነው ያሉት ዳይሬክተሩ ዜጎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ኢግዚቢሽን መሆኑን ተናግረዋል።
የስራ እድሉ ተጠቃሚ የሆኑት ወጣቶች እና የስራ ቅጥር ለመፈፀም በኢግዚቢሽኑ የተሳተፉት የድርጅት ቀጣሪዎች በበኩላቸው በሌሎች ሀገራት የታዘብነው የሰራተኞች እና የአሰሪዎችን የቅጥር ሁኔታ የሚያመቻቸው መርሀግብር በድሬደዋ አስተዳደር መደረጉ የጊዜ ብክነት እና አላስፈላጊ ወጪዎችን እንደሚያስቀርላቸው ተናግረዋል።
አቅም ያላቸውንም ሆነ የተሻለ ክህሎት ብቃት ያላቸውን ድርጅቶች እና የዘርፉ ተዋናዮች ፊትለፊት በማገናኘት ሁሉም በፍትሀዊነት ብቃትን ብቻ ማዓከል ያደረገ የስራ ዕድሉ ተጠቃሚዎችን የሚያገናኝ መድረክ መሆኑን አረጋግጠዋል።
©️ ድሬ ቲቪ
በድሬዳዋ ብዙ አስደሳች ነገሮች እየመጡ ነው !
አለማችን በፈጣን ለውጦች ውስጥ ናት ታዲያ ከዘመኑ ጋር አብሮ መዘመን አማራጭ ብቻ ሳይሆን ግዴታ እየሆነ ነው።
ዛሬም መንግስታዊ አገልግሎቶችን ለማግኘት በአካል እየሄዱ ጊዜና ጉልበቶን እየጨረሱ ነው?
እንግዲያውስ ዲጂታል ድሬን ይቀላቀሉ እና ዛሬውኑ በድሬዳዋ ያሎትን ጉዳይ በስልኮ ይጨርሱ።
ድሬ
ከቤትዎ ሳይወጡ
ድሬዳዋ ይምጡ።
እያለቾት ነው።
አሁኑኑ http://eservice.diredawa.et/ ላይ ይግቡና የሚፈልጉትን መንግስታዊ አገልግሎቶች በፍጥነት ጨራርሰው እፎይ ይበሉ። ለወዳጅ ዘመድዎ በመንገርም ከድካም እርፍ እንዲሉ ያድርጉ።
አሁን የበለጠ ተቀራርበናል። ገና ይቀጥላል።
የድሬዳዋ አስተዳደር ኢኖቬሽን ቴክኖሎጂ ኤጀንሲ
ለኮሌጅና ዩኒቨርስቲ ምሩቃን በሙሉ
****
በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የተዘጋጀ "ሥራና ሠራተኛ ማገናኛ ኤግዚቢሽን(Job Fair)" የፊታችን ሐሙስ ግንቦት 21/2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 ጀምሮ በድሬዳዋ ወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን ሁለገብ ሜዳ የሚካሄድ ይሆናል።
በዚህም ስራ ፈላጊ ምሩቃን የተለያዩ ድርጅቶች በቅጥር ሥራ የምታገኙበትን ሁኔታ ሊያመቻቹ እናንተን ስለሚጠብቁ የትምህርት ማስረጃዎቻችሁን በመያዝና በአካል በመገኘት የዕድሉ ተጠቃሚ ይሆኑ ዘንድ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
የድሬዳዋ አስተዳደር
ሥራና ክህሎት ቢሮ
ከጤና ሚኒስቴር እና ከኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት MPox አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ
ግንቦት 17/2017 ዓ.ም
#Mpox
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
