ar
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

الذهاب إلى القناة على Telegram

إظهار المزيد
1 071
المشتركون
+224 ساعات
+37 أيام
+230 أيام
أرشيف المشاركات
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከGrand group Entrepreneurship, Training and promotion PLC ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ በጋራ መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ የመግባቢያ
+3
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከGrand group Entrepreneurship, Training and promotion PLC ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ በጋራ መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ፡፡ በስምምነቱ ላይ በመገኘት የመግባቢያ ስምምነቱን የፈረሙት የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ በንግግራቸውም የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች በዋነኝንት ትምህርትና ስልጠናዎችን ከመስጠት በዘለለ የሚያሰለጥኑዋቸውን ሰልጣኞች እውቀት ክህሎት ካገኙ በኃላ ከስራ ጋር ማስተሳሰር ይጠበቅባቸዋል፡፡ ስለሆነም በዛሬው እለት ከGrand group ጋር የተፈራረምነው ይህ የመግባቢያ ስምምነት ሰልጣኞቻችን ከሰለጠኑ በኃላ ከስራ ማስተሳሰር እንዲሁም በአጫጭር ስልጠናዎች የተቀጣሪዎችን ብቃት ከማሳደግና ለቀጣሪዎች ብቁ የሰዉ ሃይል ከማቅረብ አንፃር ስራዎችን በጋራ መስራት እንድንችል ያደርገናል ብለዋል፡፡ አያይዘውም ለሰልጣኞች ከምንፈጥረው የስራ ትስስር ውጪ ለአሰልጣኞችና ሰልጣኞች የክህሎት ክፍተታቸውን መሙላት ሁለቱንም አካላት የሚያሳድጉ ቢዝነስ ተኮር ፕሮጀክቶች በጋራና በትብብር ከማስፋት አንፃር በጋራ በመሆን እንድንሰራ የሚያስችለን ስምምነት ነው ብለዋ፡፡ በመቀጠልም ድርጅቱን በመወከል የጋራ ስምምነቱን የፈረሙት የGrand group ኃላፊ አቶ ኤልያስ አብዲ እንዳሉት በዛሬው እለት የምንፈራረመው ይህ የጋራ የመግባቢያ ስምምነት በኮሌጁ ውስጥ ብቻ ሳይሆን የአካባቢው ህብረተሰብ የበለጠ የሚጠቅሙ የስልጠና ዘርፎችን በመለየትና ወደ ተግባር በማስገባት እንዲሁም ተጨማሪ ፋይናንስ፣ ቴክኖሎጂ እና የእዉቀት ሽግግር ከመፍጠር አንፃር ትልቅ ፋይዳ ያለው ስምምነት ከኮሌጁ ጋር በማድረጋችን ትልቅ ደስታ ይሰማናል ብለዋ፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን የካቲት 19/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍ ውስጥ አላሰራ ያሉ ችግሮችን ለመፍታት ከሁለቱ የመንግስት ኮሌጆችና ከጎል ኮሌጆች ለተወጣጡ በተግባራዊ ጥናትና ምርምር (action research) ስራ ላይ ከሚገኙ አሰልጣኝ መምህራን ጋር እስካሁን የደረሱበትን የመገምገም ስራ ተከናወነ። በዚህም ከድሬዳዋ ዩኒቨርስቲ በመጡ አማካሪ ለአጥኚዎች ምክር እና ድጋፍ የተደረገ ሲሆን በዋናነት የዘርፉን ችግሮች ለመፍታት የሚጠቅሙ ጥናትና ምርምሮችን ማድረግን አላማው ቢያደርግም እንደ አስተዳደር በሚቀጥለው ወር መጀመሪያ ተከትሎም በአገር አቀፍ ደረጃ ለሚካሄደው ውድድር አስተዳደሩን የሚወክሉ የሚለዩበትም ይሆናል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት የካቲት 18/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+6

ለሴት አሰልጣኝ መምህራንና ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ፤ በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ስር የሚገኘው ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ከድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ Eastrip ፕሮጀክት ጋር በመተባበር ለቢሮው ሴት ሰራተኞች፣ ለትምህርት ክፍል ተጠሪዎች፣ ለሴት የኮሌጆች አሰልጣኝ መምህራንና ባለሙያዎች አቅም ለማሳደግ የሚያስችሉ የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ከሀሮማያ ዩኒቨርሲቲ በመጡ አሰልጣኝ መስጠት ተቸሏል፡፡ በዚህም ስልጠናው በኮሌጆች የሚገኙ አሰልጣኝ መምህራንና ባለሙያዎች ከጀንደር ጉዳዮች ጋር የተገናኙ ሃሳቦችና ተሞክሮዎችን የተመለከቱ ሲሆን ከዚህ ባለፈ የእርስበርስ ግንኙነትን ሊያጠናክሩና ወደ መጡበት ተቋም ሲመለሱ ግብ ተኮር የሆነ ውጤት የሚያስገኝ ስራ መስራት የሚያስችላቸውን ግንዛቤ እዲፈጥሩ የሚያስችል መሆኑን የቢሮው ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ተናግረዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት የካቲት 18/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

የግብርና ውብ ማዕድንና ኢነርጂ ቢሮ የቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻል ፕሮጀክት በአነስተኛና ጥቃቅን የአደረጃጀት መመሪያ ዙሪያ ለአንድ ማዕከል ባለሙያዎች እና ባለድርሻ አካላት ያዘጋጀው ስልጠና ተካሄደ ወጣቶችን ፣ ሴቶችን ብሎም ሌሎች የማህበረሰቡ ክፍሎችን በማህበር በማደራጀት አዋጭ በሆኑ የስራ መስኮች ተሰማርተው የገቢ ምንጫውንም በማስፋት ኑሯቸውን የሚያሻሽሉበትን መንገድ ለማመቻቸት ያቀደ ስልጠና እንደሆነ ተነግሯል፡፡ መድረኩን በንግግር የከፈቱት ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ የአስተዳደሩ ስራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ኃላፊ ሲሆኑ በአስተዳደራችን የተገኙ የፕሮጀክት ዕድሎች ስኬታማ እንዲሆኑ ማህበረሰባችን ደግሞ ኑሮውን እንዲያሻሽል ሁሉም ሰው ትልቅ ሃላፊነት አለብን ብለዋል፡፡ከቢሮው እና ስራና ክህሎት ቢሮ ሙያዊ እና በሌሎች መስኮች በትብብር እንሰራለን ብለዋል፡፡የስራ ባህል መቀየር ላይም ከፕሮጀክቱ ጋር በመሆን ዘመናዊ አሰራሮችን በመከተል ለውጤታማቱ ልንረባረብ ይገባል ሲሉም ተናግረዋል፡፡ የቆላማ አካባቢዎች ኑሮ ማሻሻል ፕሮጀክት ሴት ፣ ወጣቶችንም እንዲሁም አካል ጉዳተኛ የማህበረሰብ ክፍሎችን አጠቃሎ ተጠቃሚ እንዲሆን የሚሰራ ፕሮጀክት መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡ከአመራር እስከ ባለሙያ በትብብር ይሰራል ብሏል ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ፡፡ በስልጠናው የስራ ክህሎት ቢሮ ባለሞያዎች፣የወረዳ የአንድ ማዕከል ባለሙያ እና ሃላፊዎች ፣ ፕሮጀክት የወረዳ አስተባባሪዎች ፣ከአስተዳደሩ የሴቶችና ህፃናት ቢሮ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ናቸው፡፡ ©️ Dire Dawa Agriculture Bureau

photo content
+9

በ3ኛ ዙር የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ላይ ለሚሳተፉ አሰልጣኞች ስልጠና መስጠት ተጀመረ:: የአሰልጣኞች ስልጠናው በዘንድሮ አመት በአስተዳደሩ ለሚሰጠው የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ 3ኛ ዙር ፕሮግራም ላይ ለወጣቶች ስልጠና ለሚሰጡ አሰልጣኝ መምህራን በዛሬው እለት መሰጠት ተጀምሯል:: የ3ኛ ዙር ፕሮግራሙ በስራና ክህሎት ቢሮ አማካኝነት በቅርቡ በኮሌጁ ለሚጀምረው የወጣቶች ስልጠና በኮሌጁ ToT ላላቸው አሰልጣኝ መምህራን በተከለሰው የህይወት ክህሎት ስልጠና እንዲሁም የስራ አፈላለግ ስልጠና ላይ የሪፍሬሽመንት ስልጠና እየተሰጠ ሲሆን ይህም የ3ኛው ዙር ስልጠና ፕሮግራም ቅድመ ዝግጅት አንዱ አካል እንደሆነም ተገልፇል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን የካቲት 17/2017 ዓ.ም

በ3ኛ ዙር ብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ስልጠና ላይ ለሚሳተፉ አሰልጣኝ መምህራኖች የማነቃቂያ ስልጠና በዛሬው እለት መሰጠት ተጀመረ:: ይህ የ3ኛ ዙር ፕሮግራም በስራና ክህሎት ቢሮ አማካኝነት
+3
በ3ኛ ዙር ብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ስልጠና ላይ ለሚሳተፉ አሰልጣኝ መምህራኖች የማነቃቂያ ስልጠና በዛሬው እለት መሰጠት ተጀመረ:: ይህ የ3ኛ ዙር ፕሮግራም በስራና ክህሎት ቢሮ አማካኝነት በቅርቡ በኮሌጁ ለሚጀምረው የወጣቶች ስልጠና በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በኩል የአስልጣኞች ስልጠናውን ከዚህ ቀደም ለወሰዱ አሰልጣኝ መምህራን በተከለሰው የህይወት ክህሎት ስልጠና እንዲሁም የስራ አፈላለግ ስልጠና ላይ የማነቃቂያ ስልጠና የተሰጠ ሲሆን ይህም የ3ኛው ዙር ስልጠና ፕሮግራም ቅድመ ዝግጅት አንዱ አካል እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል:: በአምስት አመት ውስጥ 70 ሺህ ወጣቶችን ተጠቃሚ ለማድረግ ያለመው እና የስራና ክህሎት ሚኒስቴር በአለም ባንክ ድጋፍ እየተገበረው የሚገኘው ብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ እድሜያቸው ከ18 እስከ 25 አመት የሆኑ ወጣቶችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ሲሆን ወጣቶቹ በዋነኝነት ምንም አይነት የስራ እድል ያላገኙ በትምህርት ብዙም ያልገፉ ወይም ያቋረጡ ከዚህ በፊት ምንም ስራ ሰርተው የማያውቁ ወጣቶችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ሲሆን ከዚህ በፊት 1ኛ ና 2ኛ ዙር ስልጠናዎችን በስኬት መጠናቀቃቸው ይታወሳል፡፡ ብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም በድሬዳዋ አስተዳደር በ3 ዙር ውስጥ በአጠቃላይ 2916 ወጣቶች ተጠቃሚ የሚያደርግ መርሃ ግብር እንደሆነ ይታወቃል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን የካቲት 17/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የግማሽ አመት ዕቅድ አፈፃፀምና የቀጣይ ስድስት ወራት የተከለሰ ዕቅድ ላይ ከቢሮው ከሰራተኞችና ከባለድርሻ አካላት ጋር የውይይት መድረክ ተካሄደ፡፡ በዚህም በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያው ስድስት ወራት በዕቅድ ተይዘው ተግባራዊ ሲደረጉ የነበሩ ዓበይት ስራዎችን እንዲሁም በዕቅድ አፈፃፀሙ ላይ የተስተዋሉ አጠቃላይ አውንታዊና አሉታዊ ሁኔታዎችን በመተንተን የቀጣይ ስድስት ወራት አፈጻጸም በልህቀት ለመፈጸም የሚያስችል መግባባትን የሚፈጥር መድረክ እንደሆነ የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ተናግረዋል፡፡ ባለፉት ስድስት ወራት የተከናወኑ ስራዎች ከብዙ በጥቂቱ፤   የ6 አቅመ ደካማ ነዋሪዎች ቤቶችን የመገንባት ስራ ተከናውኗል፣   የአዲስ ሰልጣኞች ቅበላ ወንድ 1955 ሴት 2862 በድምሩ 4817 የአዳዲስ ሰልጣኞች ቅበላ ተከናውኗል፡፡ በእቅድ ከተያዘው 5956 የቅበላ መጠን አንፃር የ80.8 በመቶ አፈፃፀም አለው፡፡   የነባር ሰልጣኞች ቅበላ ወንድ 2029 ሴት 3053 በድምሩ 5082 የነባር ሰልጣኞች ቅበላ ተከናውኗል፡፡ ይህም በእቅድ ከተያዘው 5380 የቅበላ መጠን አንፃር የ94.4 በመቶ አፈፃፀም አለው፡፡   2384 የመደበኛ ስልጠና አጠናቃቂዎችን ለመመዘን ታቅዶ 2024 (ወንድ 910፣ ሴት 1114) መመዘን የታቻለ ሲሆን ይህም ከእቅድ አንፃር የ84.9 ፐርሰንት አፈጻፀም አለው፡፡   1000 የአጫጭር ስልጠና አጠናቃቂዎች ለመመዘን ታቅዶ 859 (ወንድ 86፣ ሴት 773) መመዘን የተቻለ ሲሆን ይህም ከዕቅድ አንፃር 85.9 በመቶ አፈፃፀም ተመዝግቦበታል፡፡   በ6 ወራት ውስጥ በሦስቱም ዘርፎች 10,474 ቋሚ ያስራ እድል ለዜጎች ለመፍጠር ታቅዶ ወንድ 4873 ሴት 3981 በድምሩ 8854 የስራ እድል መፍጠር ተችሏል ይህም ከእቅድ አንፃር የ84.5 በመቶ አፈፃፀም አለው፡፡   ከአንቀሳቃሾች ጋር በተያያዘ 1500 የሚሆኑ የተለያዩ አንቀሳቃሾችን የብድር ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዶ 655 ወንድ እና 1067 ሴት በአጠቃላይ 1718 አንቀሳቃሾን የብድር ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል፡፡ ይሄም ከ100% በላይ አፈፃፀም የተመዘገበበት ሆኗል፡፡   የስራ ተቆጣጣሪዎችን አሰልጥኖና አደራጅቶ ወደ ስራ ለማስገባት የሚያስችል የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ስራን በ384 ኢንድስትሪዎች ላይ ማከናወን  ተችሏል፡፡ በጥናቱም ውጤት መነሻነት 31 የሙያ ደህንነት ባለሞያዎችን አሰልጥነን አስመርቀናል፡፡ ስምሪትም እንዲወስዱ ተደርጓል፡፡   በግማሽ ዓመቱ ከመንግስትና የግል ማሰልጠኛ ተቋማት፣ ከብቃት ምዘና ማዕከልና ከግል አሰሪና ሰራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች ጋር በመቀናጀት ለውጪ አገር ስራ ስምሪት 360 ሴት የግል ሰራተኞች እንዲሰለጥኑ ተደርጓል፡፡ ከነዚህም ውስጥ 185 የግል ሰራተኞች ወደ አረብ አገር የመላክ ስራ ተከናውኗል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት የካቲት 16/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

photo content
+9

#ዜና|በፋብሪካዎች ውስጥ የሚሰሩ የተለያዩ ሞያተኞችን በክህሎትና በአመለካከት ብቁ እንዲሆኑ መስራት እንደሚያስፈልግ ተገለጸ፡፡ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ የተውጣጡ ባለሙያዎ
+4
#ዜና|በፋብሪካዎች ውስጥ የሚሰሩ የተለያዩ ሞያተኞችን በክህሎትና በአመለካከት ብቁ እንዲሆኑ መስራት እንደሚያስፈልግ ተገለጸ፡፡ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ የተውጣጡ ባለሙያዎችን በተለያዩ የሙያ መስኮች ስልጠናዎችን እየሰጠ ይገኛል፡፡ ስልጠናው ለ11 የናሽናል ሲምንቶ መካኒካል ክፍል ባለሙያዎችና 5 የኤሌክትሪካል ክፍል ባለሙያዎች በብየዳ ሙያ በMMAW (manual metal arc welding) Advance welding training module one እንዲሁም በ pneumatic, Electro Pneumatic, Hydraulic & Electro Hydraulic & Advance PLC ተግባር ተኮር ስልጠናዎችን እየሰጠ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ስልጠናው ሙሉ በሙሉ በከፍተኛ ባለሞያዎች በሆኑ አሰልጣኞች እየተሰጠ ሲሆን በቀጣይም ስልጠናውን አጠናቀው ወደ ተቋማቸው ሲመለሱ በሰለጠኑት ሙያ ለውጥ ማምጣት እንደሚያስችላቸው ሰልጣኞቹ በስልጠናው ወቅት ገልጸዋል፡፡ ይህን ስልጠና የኮሌጁ EASTRIP ፕሮጀክት አማካኝነት የተዘጋጀ ሲሆን ኮሌጁ ከተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ጋር ባለው ትስስር ለተለያዩ ፋብሪካ ባለያዎችን ቀጣይነት ባለው መልኩ አቅማቸውን የማጎልበት ስራዎች የሚሰራ ይሆናል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን የካቲት14/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

#ዜና| በኮሌጁ ውስጥ የተሰሩ ተቋማዊ ስራዎችን ለተቋሙ ሰራተኞች እንዲሁም ለባለድርሻ አካላት በየግዜው ማሳወቅ እንደሚገባ ተገለጸ፡፡ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ የ2017 ዓም የ6 ወር የኮሌጅ መደበኛና የፕሮጀክት አፈጻጸም ሪፖርት በዛሬው እለት በኮሌጁ አዳራሽ ለኮሌጁ ማህበረሰብ ቀረበ፡፡ በተያዘው በጀት አመት የመጀመሪያው 6 ወር በኮሌጁ በርከት ያለ ስራ በውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና፤በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር በመምህራንና በአስተዳደር ሰራተኞች ልማት፣የተለያዩ የገቢ ማስገኛ ስራዎችን በመስራት ውስጠ ገቢን ከማሳደግ አንጻር እንዲሁም ማህበረሰቡን ሊጠቅሙ የሚችሉ የበጎ አድራጎት ስራውችን፤የEASTRIP ፕሮጀክት ስራዎችን በተሻለ ለመስራት አቅዶ የተንቀሳቀሰ እንዳለ የገለጹት የኮሌጁ ም/ዲን እና ውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ አቶ አብዱልፈታህ አፈንዲ ሲሆኑ አያይዘውም ከአዲሱ የቴክኒክና ሙያ እሳቤ አንጻር ኮሌጁ አመርቂ ስራዎችን በ6 ወር ውስጥ ለመስራት ተችሏል ያሉ ሲሆን፡፡ለቀጣይ 6 ወር እቅድ አፈጻጸም ደግሞ ሁሉም የኮሌጁ ማህበረሰቦች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ ሆነን ልንሰራ ይገባል ብለዋል፡፡ የኮሌጁን የ6 ወር እቅድ አፈጻጸም በአቶ ዘየደ ተክሌ በኩል የቀረበ ሲሆን የፕሮጀክቱን አፈጻጸም ደግሞ አቶ በአቶ መሳይ ጥላሁን የፕሮጀክቱ M & E specialist ቀርቧል፡፡ የቀረበውን ሪፖርት መሰረት በማድረግ የኮሌጁ ማህበረሰብ ለኮሌጁ አመራሮች እና ለፕሮጀክት ማስፈፀሚያ ዩኒት የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ያቀረቡ ሲሆን የኮሌጁ አመራሮች በቀረቡት ጥያቄዎችና አስተያየቶች ላይ መልስ የሰጡ ሲሆን በመጨረሻም የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከሉን ግንባታ ሂደት በጋራ ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን የካቲት 14/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ የሰልጣኝ ልማትና የተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሮክቶሬት በአስተዳደር ደረጃ የሥራ ገበያ ፍላጎት ጥናት ዝግጀት መጀመሩን አስታወቀ፡፡ ጥናቱ የሥራ ገበያውን ፍላጎት መሰረት በማድረግ ክህሎት መር የቴክኒክና ሙያ ስልጠና በማቅረብ የአምራችና አገልግሎት ኢንዱስትሪውን የሰለጠነ ሰው ኃይል ፍላጎት ቀጣይነት ባለው ሂደት ማሟላት የሚጠበቅበት ሲሆን የአምራችና አገልግሎት ሰጪ ኢንዱስትሪውን ቀጣይ የመካከለኛ ደረጃ የሰለጠነ የሰው ሃይል አቅርቦት መለየት ላይ አተኩሮ እንደሚዘጋጅ የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ጀማል አደን አስረድተዋል፡፡ በተለይም የጥናቱን ተዓማኒነትና እውነተኛነት ለማረጋገጥ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ  በአስተዳደሩ ከሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት የጥናት ባለሙያዎችን በመምረጥና በማደራጀት አንድ የጥናት ቡድን በማዋቀር በልምድና በትምህርት ዝግጅታቸው የተሻለ ብቃት ያላቸውን በመምረጥ ጥናቱን እንዲያከናውኑ ማስጀመር መቻሉን አቶ ጀማል ገልጸዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት የካቲት 14/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+6

በአስተዳደሩ ከአራቱም ክላስተሮች ለተወጣጡ ወጣቶች በ Sanitation Concrete Slab ላይ ስልጠና ተሰጠ:: ስልጠናው በጤና ቢሮ አማካኝነት ከአራቱም የገጠር ክላስተሮች ለተወጣጡ 20 ሰልጣኞች በMarketing Based Sanitation Concrete Slab Training የተሰጠ ሲሆን ሰልጣኞችም ለሰባት ተከታታይ ቀናት በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮንስትራክሽን ዲፓርትመንት በአጫጭር ስልጠና ማዕቀፍ የተሰጠውን ስልጠና በአግባቡ ተከታትለው አጠናቀዋል:: በስልጠናው ማጠናቀቂያ ላይ ለሰልጣኞች የእውቅና ሰርተፊኬቱን ያበረከቱት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ሲሆኑ በእለቱ ባስተላለፉት መልዕክትም ሰልጣኞች እዚህ በኮሌጁ የወሰዱትን ስልጠና መሰረት እድርገው በየአካባቢያቸው የሚስተዋለውን የመፀዳጃ ቤት ችግሮችን ለመቅረፍ መስራት እንደሚገባቸውም ተናግረዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን የካቲት 12/2017 ዓ.ም