Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
1 065
المشتركون
-124 ساعات
-47 أيام
+530 أيام
أرشيف المشاركات
Repost from Abiy Ahmed Ali 🇪🇹
+9
የድሬ የኮሪደር ልማት ምቹ የህዝብ መዝናኛ ቦታዎች፣ የተሻሻለ የአካባቢ ውበትን እና ጥራታቸውን የጠበቁ የማህበረሰብ መሰብሰቢያ ስፍራዎች በድሬ እውን እንዲሆኑ አስችሏል። በኮሪደሩ ለከተማዋ ነዋሪዎች ገቢ ለማስገኘት የሚያስችሉ የኤሌክትሪክ መኪና ቻርጂንግ ስቴሽን፣ ሱቆች፣ ካፍቴሪያዎች እንዲሁም ደረጃቸውን የጠበቁ የፓርኪንግ ቦታዎች እንዲካተቱበት ተደርጓል።
ኢፍጣር በድሬደዋ
የረመዳን ኢፍጣር ከድሬደዋ ነዋሪዎች ጋር።
Iftar in Dire Dawa
Breaking bread with the local community during Ramadan.
#PMOEthiopia
Repost from Abiy Ahmed Ali 🇪🇹
+7
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት የምርቶች እና አገልግሎቶች ጥራት የማረጋገጥ ስራ ዓለም አቀፍ አሰራር ስርዓትን መሰረት በማድረግ ለአምራቾች፣ ለአገልግሎት ሰጪዎች፣ ለላኪዎች፣ ለአስመጪዎች፣ ለተቆጣጣሪ መስሪያ ቤቶች፣ ለምርምር ተቋማት እና በአጠቃላይ ለሸማቹ ማህበረሰብ የጥራት ማረጋገጫ አገልግሎትን የሚሠጥ መንግስታዊ ድርጅት ነው።
በድሬዳዋ አካባቢ ለሚገኙ አምራቾችና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት፣ ነፃ የንግድ ቀጣና እንዲሁም የደረቅ ወደብን መሰረት በማድረግ ቀደም ብሎ ይሰጡ ከነበሩ የጥራት ማረጋገጫ አገልግሎቶች በተጨማሪ በምግብ ዘይት፣ ፔትሮሊዬም ወይም የነዳጅ ምርት፣ የተለያዩ የምግብ ምርቶች፣ የማስዋቢያና የዲተርጀንት ምርቶች፣ የተለያዩ የኮንስትራክሽን ምርቶችንና ግብዓቶች የጥራት ማረጋገጫ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል አዲስ የፍተሻ ላቦራቶሪ በማደራጀት አገልግሎቱን ተደራሽ አድርጓል ።
Repost from Abiy Ahmed Ali 🇪🇹
+6
ድሬ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፤ በውስጡ 10 ተቋማት ይዞ 73 የሚሆኑ አገልግሎቶችን ለዜጎች በመስጠት ላይ ይገኛል። አንድ ማዕከሉ ተገልጋዬችን የሚያስተናግዱ 96 ካውንተሮች እንዲኖሩት ተደርጎ የተደራጀ ነው። ማዕከሉ ስራ ከጀመረበት ስድስት ወራቶች ውስጥ በአጠቃላይ ከ23 ሺ በላይ ተገልጋዮችን አስተናግዷል። ከፍ ብሎ የተጀመረውን የተቀላጠፈ የዲጅታል አገልግሎት ይበልጥ ለማስፋት አቅዶም እየሠራ ነው።
በአስተደዳደሩ ኢንዱስትሪ ፓርክ በተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ውስጥ ለሚሰሩ ሰራተኞች በስራ ቦታ ኤች አይ ቪ ኤድስን መከላከልና መቆጣጠር ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተዘጋጀ።
መድረኩ ኢንዱስትሪዎች ከፍተኛ ቁጥር ያለው የሰው ሃይል ከተለያዩ ቦታዎች በስራ የሚገናኙበት እንደመሆኑ መጠን ለኤች አይ ቪ ኤድስ ተጋላጭነቱን ለመቆጣጠር ቢሮዉ ከሚያዘጋጃቸው ተከታታይነት ያላቸው ስልጠናዎች አካል መሆኑ ታውቋል፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ አሰሪና ሰራተኛ ዳይሬክቶሬት የሙያ ደህንነትና ጤንነት የስራ ሁኔታ ቁጥጥር ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ ሲገኝ በኢትዮጵያ የሥራ ቦታዎች የኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከልና መቆጣጠሪያ ፖሊሲ ማዕቀፍ ላይ ሰራተኛው ግንዛቤ እንዲፈጠርለት ማድረግ ችሏል።
ቢሮው ሰራተኛ ዜጋውን ጤንነቱና ደህንነቱ የተጠበቀና የተረጋገጠ አምራች ሃይል ባለሙያ በማዘጋጀት የሚሰሩበት ኢንዱስትሪ ድረስ በተከታታይ በመሄድ ግንዛቤ እንዲፈጠር በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 29/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ለሪፎርም አስተግባሪ ኮሚቴ አባላት ሲሰጥ የነበረው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተጠናቀቀ፡፡
የቢሮው ም/ኃላፊ እና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በመድረኩ ተገኝተው ባደረጉት የማጠቃለያ ንግግርና ባስተላለፉት ቀጣይ የስራ አቅጣጫ መመሪያ የሪፎርም አስተግባሪ ኮሚቴ አባላት የተሰጣቸውን ኃላፊነት ከመደበኛው ስራ ጎን ለጎን በትጋትና በላቀ ብቃት መፈጸም እንደሚገባቸው አሳስበዋል።
በዚህም የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የሪፎርም አስተግባሪ አብይ እና ንዑሳን ኮሚቴዎች በቀረቡ ሰነዶች ላይ ያላቸውን ሀሳብና አስተያየት በማንሳት ሰፊ ውይይት ያደረጉ ሲሆን ከዛሬ ጀምሮም በምልዓት ወደ ስራ ገብተዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 28/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት በአስተዳደሩ ከሚገኙ አምራች ኢንዱስትሪዎች ጋር በኢንዱስትሪው ፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ላይ የምክክር መድረክ አካሄደ::
በመድረኩ በቴክኒክና ሙያ ስልጠና፣ በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት አሰጣጥ እንዲሁም በቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ እንዱስትሪውን ከመደገፍ አኳያ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን ለመፍታት ታልሞ በሚዘጋጀው ጥናት ላይ ከኢንዱስትሪ ባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ ተካሂዷል::
በEASE ፕሮጀክት ትግበራ ትኩረት ተደርጎባቸው ከሚከናወኑ ቁልፍ ተግባራት መካከል ኢኮኖሚውን የሚያንቀሳቅሱ የአምራች እንዱስትሪዎችን አቅም ማጎልበት አንደኛው መሆኑን የጠቀሱት የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ኢ/ር ፋሲል ማዘንጊያ ሲሆኑ በዚህም በሰለጠነ የሰው ሀይል፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር እና የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ላይ በኢንዱስትሪው ፍላጎት መሰረት በዘላቂነት ድጋፍ ለማድረግ እንዲቻል የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ቡድን በማዋቀር በተቋም ደረጃ ጥናት እያካሄድን እንገኛለንም ብለዋል::
በመድረኩ ለፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ውይይቱ መነሻ የሚሆን ሰንድ በጥናት ቡድኑ አማካኝነት ለባለ ድርሻ አካላቱ ገለፃ የተደረገ ሲሆን በተጨማሪም ኢንዱስትሪዎችን በዘርፍ በመክፈል በቡድን እንዲወያዩ ማድረግ ተችሏል::
በተካሄደው የቡድን ውይይት ወቅትም ኢንዱስትሪዎች በሰለጠነ የሰው ሀይል፣ ተኪ በሆኑ ቴክኖሎጂዎች እና በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ ላይ ያሏቸውን ፍላጎቶች ለይተው በዝርዝር ያስቀመጡ ሲሆን በቀጣይ በቅንጅት መስራት በሚቻልበት እግባብ ላይም አመርቂ ውይይቶችን በማድረግ ለጥናቱ አስፈላጊ ግብዓቶች የተገኙበት መድረክም ነበር::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
የካቲት 28/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በአስተዳደሩ የሥራ ዕድል ፈጠራ እና ኢንተርፕራይዝ ልማትን የሚደግፉ ፕሮጀክቶች ከቢሮውና ብድር ከሚያቀርቡ ድርጅቶች ጋር ያላቸው ቅንጅታዊ አጠቃላይ የስራ አፈጻጸም ግምገማ እና የመስክ ምልከታ ተደረገ፡፡
በዚህም አቶ ተፈሪ ታደሰ የኢኔብሊንግ ኢትዮጵያ ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ፣ አቶ ንጉሱ ጥላሁን የኢኔብሊነግ ኢትዮጵያ ሲንየር አማካሪ፣ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊ እንዲሁም የቢሮው አመራሮችና የፕሮጀክት አስተባባሪዎች በተገኙበት የፕሮጀክቶቹ አፈጻጸም ቀርቦ በመስክ ምልከታ የታዩ ጉዳዮችን ጨምሮ ውይይት ተካሂዶባቸዋል፡፡
በዚህም ሳፊ፣ መስመር፣ ጥላ፣ መስራት እና ሲድ የተሰኙ ፕሮጀክቶች በአስተዳደሩ የሚገኙ የጥቃቅን፣ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን የብድር አገልገሎት ተጠቃሚ የማድረግ ስራ ተጠቃሚዎችን በአካል በማነጋገር ያሉበትን ሁኔታ መመልከት ተችሏል፡፡
ቢሮው ከማስተር ካርድ አጋር ድርጅቶች ጋር በቅንጅት የሚሰራ ሲሆን ያለፉት ስድስት ወራት የአምስቱም አጋር ድርጅቶች ሪፖርት በቢሮው የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲትት 27/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በአስተዳደሩ ገጠር ወረዳዎች ለሚገኙ የ2017 ዓ.ም ቅድመ ሞዴል የ2018 ዓ.ም ለሞዴል ኢንተርፕራይዞች በኢንተርፕርነርሽፕ እና በቢዝነስ ዴቨሎፕመንት ላይ ሰልጠና ተሰጠ።
በዚህም ስልጠና የኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾችን ባገኙት ዕውቀትና ክህሎት ምርትና ምርታማነታቸውን ለማሳደግና ያላቸውን ልምድ እርስ በእርሳቸው እንዲለዋወጡ ለቀጣይም የዕድገት ደረጃ ለማብቃት አቅማቸውን የሚገነባ ይሆናል።
በስልጠና መድረኩ ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት በአስተዳደሩ ገጠር የሚገኙ ኢንተርፕራይዞች ተጠቃሚነታቸውን ለማረጋገጥ የተለያዩ ድጋፎች እየተደረጉ መሆኑን አስታውሰው መሰል ስልጠናዎች ከፍ ባለ ደረጃ አቅማቸውን እንዲጠቀሙ የሚያግዝ ነው ብለዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 27/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ ምሩቅ ስራ ፈላጊዎች በድሬዳዋ ሰርቶ መለወጥ እንደሚቻል ለማሳየት ፍላጎትና ተነሳሽነታቸውን ከፍ የሚያደርግ ለዩኒቨርሲቲ እና ኮሌጅ ምሩቃን ስራ ፈላጊዎች ሲሰጥ የነበረው የማይንድ ሴት ስልጠና ተጠናቀቀ።
በአስተዳደሩ የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ስልጠናው የነገ ሃገር ተረካቢ የሆኑ ወጣት ምሩቃንን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችል አስተሳሰብ እንዲይዙ የሚያስችል ስልጠና መሆኑን ተናግረዋል።
ስልጠናው የአስተዳደሩን ወጣቶች የስራ ባህል በማዳበርና የወጣትነት አቅማቸውን በመጠቀም ውጤታማ ተግባራትን መስራት እንዲችሉ ያበረታታል ያሉት አቶ ሮቤል ወጣቱ በተሰጠው ዕድል ተጠቅሞ ሀገርን ለመገንባት የሚያስችሉ ስራዎችን መስራት የሚጠይቅ መሆኑንም ገልጸዋል።
ኃላፊው አክለው ወጣትነት ሙሉ አቅምን፣ እውቀትንና ክህሎትን ተጠቅሞ ለመጪው ጊዜ መሰረት የሚሆን የህይወት መስመር የሚዘረጋበት አልባሌና አላስፈላጊ የሆኑ ነገሮችን ንቆ በመተው ጊዜን ሙሉ በሙሉ ለጠቃሚ ነገሮች በማዋል ተዓምር የሚመስሉ ነገሮችን ማሳካት የሚቻልበት የዕድሜ ክልል መሆኑን በማውሳት በስልጠና ያገኙትን እውቀት እንደ ጥሩ አጋጣሚ በመጠቀም በህይወታቸው ተጨባጭ ለውጥና ስኬት ለማምጣት መትጋት እንደሚኖርባቸውም ተናግረዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
የካቲት 27/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
