ar
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

الذهاب إلى القناة على Telegram

إظهار المزيد
1 085
المشتركون
+924 ساعات
+207 أيام
+1530 أيام
أرشيف المشاركات
photo content
+9

በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ከድሬዳዋ እና ከኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች ጋር በመሆን ክህሎትን መሰረት ያደረገ ሃገር ወዳድነት እና ሙያዊ ስነ-ምግባርን ለማላበስ በሙያ ደረጃ ውስጥ የተካተቱ ብቃት አሃዶች እና ኮርሶችን የሚያሰለጥኑ አሰልጣኝ መምህራንን ለማፍራት የሚያስችል ስልጠና ለአሰልጣኝ መምህራን ለተከታታይ ቀናት ተሰጠ፤፤ በዚህም የተሰጠውን ስልጠና አስመልክቶ የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ ያለ አሰልጣኝ መምህራን ልማት የትምህርትና ስልጠና ጥራት ማረጋገጥ የሚታሰብ ስላልሆነ ትኩረት ተሰጥቶት በሁለቱም ኮሌጆች ላይ የውስጥ አቅምን በመጠቀምም ሆነ ከተለያዩ አጋር አካላት ጋር በትብብር በኮሌጆቹ በተለዩ የእውቀት እና የክህሎት ክፍተቶችን ለመሙላት የሚያስችሉ ስራዎች መሠራታቸውን አውስተዋል። ይህም ስልጠና አእምሮን፤ ልብን እና እጅን በተግባር ማገናኘት የሚችሉ፤ ሁለንተናዊ ብቃትን የተላበሱ፤ የአስተሳብ፤ የአመለካከት እና የስነ- ምግባር ባህሪ ለውጥ የሚያመጡ ስልጠና አጠናቃቂ ሰልጣኞችን ለማፍራት የሚያስችል የአሰልጣኞች ስልጠና መሆኑን ተናግረዋል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሚያዚያ 22/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

ለተከታታይ 5 ቀናት የሚቆየው የኢትዮጵያ ታምርት ኤግዚቢሽን እና ባዛር በድሬዳዋ ከተማ በይፋ ተከፍቷል። ኤግዚቢሽን እና ባዛሩን የኢፌዴሪ ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል የድሬዳዋ አ
+3
ለተከታታይ 5 ቀናት የሚቆየው የኢትዮጵያ ታምርት ኤግዚቢሽን እና ባዛር በድሬዳዋ ከተማ በይፋ ተከፍቷል። ኤግዚቢሽን እና ባዛሩን የኢፌዴሪ ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ መላኩ አለበል የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሃር ፣ ምክትል ከንቲባ አቶ ሀርቢ ቡህን ጨምሮ የአስተዳደሩ አፈ-ጉባኤ ወ/ሮ ፈትህያ አደን መርቀው ከፍተዋል። በኤግዚቢሽን እና ባዛሩ ላይም የድሬደዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ተሳታፊ የሆነ ሲሆን በኮሌጁ የተሰሩ እና ለተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ያመረታቸው ችግር የፈታባቸው የተለያዩ የማሽነሪ መለዋወጫዎች ፣ በኮሌጁ የተሠሩ የተለያዩ ቴክኖሎጂዎች እንዲሁም የፋሽን አልባሳትና የቆዳ ውጤቶችን ለጎብኚዎች ይዞ ቀርቧል:: የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ሚያዝያ 22/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

Repost from N/a
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በጎ አድራጎት ክበብ መጪው የትንሳዔ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለአቅመ ደካሞች ድጋፍ አደረገ:: የበጎ አድራጎት ክበቡ ያዘጋጀውን የአስቤዛ እና የገንዘብ ድጋፍ የኮሌጁ ዲኖች ተገኝተው ለአቅመ ደካሞች ያስረከቡ ሲሆን አያይዘውም ለመጪው የትንሳዔ በዓል መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል:: በዚህ ክበቡ ባደረገው የአስቤዛ እና የገንዘብ ድጋፍ ተጠቃሚ የሆኑት አካላት በኮሌጁ ማህበረሰብ ጥቆማ ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል ተብለው ለተለዩ 20 እቅመ ደካሞች የአስቤዛና የገንዘብ ድጋፍ ማድረግ ተችሏል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ህዝብ ግንኙነት ሚያዝያ 22/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

Repost from N/a
photo content
+8

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው "ፅዱ ኢትዮጵያን እንፍጠር" ንቅናቄን ተቀላቀሉ! ኢትዮያውያን ከዳር እስከ ዳር አመራሮች፣ ባለሙያዎች እና የተለያዩ
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው "ፅዱ ኢትዮጵያን እንፍጠር" ንቅናቄን ተቀላቀሉ! ኢትዮያውያን ከዳር እስከ ዳር አመራሮች፣ ባለሙያዎች እና የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍል የጠ/ሚንስትር ዶ/ር አብይ አሕመድን የ #ጽዱኢትዮጵያ የዲጅታል ቴሌቶን ንቅናቄን ተቀላቅለው የድርሻቸውን እያበረከቱ ይገኛሉ! ንቅናቄውን ያልተቀላቀላችሁ አመራሮች፣ ባለሞያዎች እና ሁሉም ሰው ያገባኛል በሚል በንግድ ባንክ በተከፈተው ሂሳብ ቁጥር 1000623230248 የ“ጽዱ ጎዳና-ኑሮ በጤና” ንቅናቄን እንዲቀላቀል ጥሪ አቅርበዋል::

በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍ ላይ ያተኮረ የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ውድድር ተካሄደ፤ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱሰትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ችግር ፈቺ የሆኑ ጥናትና ምርምሮችን በዘርፉ የሚገኙ አሰልጣኝ መምህራን እና ባለሙያዎች እንዲሰሩ ምቹ ሁኔታ በመፍጠር ድጋፍ እንደሚያደርግ ይታወቃል፡፡ በዚህም በዘርፉ ላይ በተለይም በኮሌጆች ላይ በአሰልጣኝ መምህሩ የሚነሱ ጥያቄዎች እና በሰልጣኝ ተማሪዎች ላይ የሚስተዋሉ መፍትሄ የሚሹ ጉዳዮች ማለትም ውጤት ተኮር የትምህርትና ስልጠና አሰጣጥ ስርዓት፣ የሰልጣኝ ተማሪዎች ቅበላና መጠነ ማቋረጥ፣ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት አተገባበር ጋር የተያያዙ በዋናነት መሠረታዊ የዘርፉን ችግር ሊፈቱ የሚችሉ ጥናቶች ቀርበው ውድድር የተካሄደ ሲሆን ከተወዳዳሪዎችም አንደኛ ሆኖ ያጠናቀቀው በሀገር አቀፍ ደረጃ ለሚካሄደው ውድድር ድሬዳዋን ወክሎ የሚሳተፍ ይሆናል፡፡ ይህም ውድድር በዋነኛነት ለዘርፉ ችግር ፈቺ የሆኑ ሃሳቦች በማፍለቅ አሰራሮችን ለማሻሻል እና ለመከለስ በግብዓት የሚየገለግሉ እንደሚሆኑና ተወዳዳሪዎች በኮሌጆቻቸው በተግባር ፈትነው ያቀረቧቸው እነዚህ ተግባራዊ ጥናትና ምርምሮች ለዘርፉ መሻሻልና ማደግ ከፍተኛ ሚና የሚጫወቱ መሆናቸውን በዳይሬክቶሬቱ የቴክኒካል ክህሎት አቅም ግንባታ ቡድን መሪ ወ/ሮ አለምፀሀይ ጌታቸው ተናግረዋል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሚያዝያ 19/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ2016 በጀት አመት መደበኛና የEASTRIP እና SIFA ፕሮጀክት የዘጠኝ ወር የስራ አፈጻጸም ሪፖርት የግምገማ መድረክ የኮሌጁ ማህበረሰብ በተገኙበት በዛሬው እለት አካሄ
+7
የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ2016 በጀት አመት መደበኛና የEASTRIP እና SIFA ፕሮጀክት የዘጠኝ ወር የስራ አፈጻጸም ሪፖርት የግምገማ መድረክ የኮሌጁ ማህበረሰብ በተገኙበት በዛሬው እለት አካሄደ። የእቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረኩን የኮሌጁ ዲን አቶ ሳሊም ኡስማን የመሩት ሲሆን በተቋሙ የሚገኙ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና እና የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ዲኖች እንዲሁም የስራ ሂደቶች የዘጠኝ ወር ተቋማዊ እቅድ አፈጻጸም ሪፖርታቸውን በኮሌጁ ፕላንና ፕሮግራም እንዲሁም የፕሮጀክቶችን ደግሞ በፕሮጀክቱ M&E specialist በኩል ለኮሌጁ ማህበረሰብ አቅርበዋል በተጨማሪም skills-based volunteerism በተቋሙ ውስጥ ለማስጀመር አጠቃላይ ገለጻ በአቶ ሳምሶን ተክሉ አማካኝነት ቀርቧል:: በእቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረኩ በመደበኛና በፕሮጀክት ዋና ዋና ቁልፍ ተግባራት ፣ በተቋሙ የማስፈፀም አቅም ፣በሀብት አጠቃቅም እና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ትኩረት ያደረገ የሪፖርት ግምገማ የተደረገ ሲሆን የቀጣይ ሦስት ወር የሚሠሩ ቀሪ ስራዎች ላይ የስራ አቅጣጫን በማስቀመጥ መድረኩ ፍፃሜውን አግኝቷል። የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን ሚያዝያ 19/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት በአስተዳደሩ ከሚገኙ የወረዳ አመራሮችና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር የግንዛቤ ማስጨበጫና የውይይት መድረክ አካሄደ። የዳይሬክቶሬቱ ባለሙያዎች በመድረኩ ለተገኙ ተሳታፊዎች በአጠቃላይ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተልዕኮና ስትራቴጂ እንዲሁም በተቋማት ጥራት ቁጥጥር ላይ ኤጀንሲው እያከናወናቸው ስለሚገኙ ስራዎች ማብራሪያ ሰጥተዋል፤ በመድረኩ ከአመራሮቹና ከሚመለከታቸው ለተወጣጡ አካላት የዘርፉን ተልዕኮ ለማሳካትና ጥራትን ለማስጠበቅ በሚያስችሉና በጋራ መስራት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ በተለይም በአጫጭር ስልጠና እና የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ውጤታማነትን ከማሳደግ አንጻር መግባባት ተፈጥሯል፡፡ ባለፉት ጊዜያት የተከናወኑ የኦዲትና ኢንስፔክሽን ስራዎች ያመላከቱት ከባለድርሻ አካላት ጋር ተቀራርቦ መስራት እንደሚገባ መሆኑን ገልጸው በቀጣይ መሰል መድረኮች በስፋት እንደሚዘጋጁ በቢሮው የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ታሪኩ ለገሰ  ተናግረዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሚያዚያ 18/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት ለቀበሌ አንድ ማዕከላት ባለሞያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጀ፡፡ በዚህም ቅድመ ሞዴል፣ ሞዴል፣ እድገት ሽግግርና ከምርጥ ተሞክሮ ቅመራ ጋር በተያያዘ ኢንተርፕራይዞችን የመለየትና ለሞዴልነት የበቁ ኢንተርፕራይዞችን ድጋፍና ክትትል በሰፊው ለማካሄድና በኢንተርፕራይዞች መረጃ ምዝገባ (LMIS) ዙሪያ የተሰሩትን ስራዎች የገመገመ ሆኗል፤ ኢንተርፕራይዞች የዕድገት ሽግግራቸው እንዲሰራላቸው፣ በሞዴል መመዘኛ መሰረት እንዲመዘኑ ከዛ ውስጥ የተሻለ የሚባሉትን በምርጥ ተሞክሮ በተጨማሪ ታዳጊ መካከለኛ በየአመቱ የሚሸጋገሩትን በመስፈርቱ መሰረት የመለየት ስራ በቀጣይ ተጠናክሮ የሚሰራ መሆኑን የዳይሬክቶሬቱ ተወካይ ወ/ሮ መቅደስ ከፈለኝ ተናግረዋል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሚያዚያ 18/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+6

አድራ ኢትዮጵያ (ድሬዳዋ) በ"Solar Pv instalation and maintenance እያሰለጠናቸው የሚገኙ ሰልጣኞች ስልጠናቸውን እያጠናቀቁ በመሆኑ በቀጣይ ምእራፍ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር የውይይት መድረክ አካሄደ:: አድራ ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ) በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እያሰለጠናቸው የሚገኙ 48 ሰልጣኞች ዋና ስልጠናቸውን ማጠናቀቃቸውና ወደ ምዘና ለመግባት በዝግጅት ላይ እንደሚገኙ የተገለፀ ሲሆን አሁን ላይ ሰልጣኞች ወደ ስራ አለም ሲገቡ የሚያግዛቸውን የኢንተርፕረነርሺፕ ስልጠና ተሞክሮ ባላቸው ባለሙያዎች እየሰለጠኑም ይገኛሉ። ስልጠናው ለስራ እድል ፈጠራ የሚያግዛቸውን ክህሎት በማግኘት ተለዋዋጭ የሆነውን የንግዱን ስርአት ለመቀላቀል ትልቅ አቅም ከመሆኑም ባሻገር በራስ መተማመናቸውን እንዲያጎለብቱ ታሳቢ ተደርጎ እየተሰጠ የሚገኝ ስልጠና ነውም ተብሏል። ከዚህም ጋር በተያያዘ ሰልጣኞችን ወደ ስራ ለማሰማራት የሚመለከታቸው የመንግስት ተቋማት ከ"Job Box " ዝግጅት እና የራስን ስራ ከመፍጠር ጋር ተያይዞ ሰልጣኞችን በማደራጀት ወደ ስራ የሚገቡበትን አቅጣጫ ለማስቀመጥ ከባለድርሻ አካላት ጋር ሰፊ ውይይት የተደረ ሲሆን በቀጣይም በቅንጅት ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር ለመስራት የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል:: በዚህ መሰረትም ሰልጣኞች ከአሰልጣኞቻቸው ጋር በመሆን በገጠር ና በከተማ ያለውን የሶላር ጥገና ስራ እንዲሰሩና ከተቋማት ጋር በፕሮጀክት መልክ ተሰማርተው አቅማቸውን እንዲያሳዩ አቅጣጫ የተሰጠ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ በራሳቸው ተደራጅተው የራሳቸውን የስራ እድል የሚፈጥሩበት ሁኔታ ተለይቶ እንዲመቻችላቸው መደረጉም ተገልፆል። በመጨረሻም ስልጠናቸውን ያጠናቀቁ ሰልጣኞች በተወሰነ መጠን የመንግስት ተቋማት ላይ የሚቀጠሩበትን ሁኔታ ለማመቻቸት እንዲቻል ለሚመለከታቸው አካላት ሀላፊነት በመስጠት መድረኩ ፍፃሜውን አጊኝቷል። የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሚያዝያ 18/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ2016 በጀት አመት የዘጠኝ ወር የስራ አፈጻጸም ሪፖርት የግምገማ መድረክ አካሄደ። መድረኩን የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ የመሩት ሲሆን በተቋሙ የሚገኙ የስራ ሂደቶች የዘጠኝ ወር ተቋማዊ እቅድ አፈጻጸም ሪፖርታቸውን ለኮሌጁ ማኔጅመንት አቅርበዋል:: በመድረኩም በዋና ዋና ቁልፍ ተግባራት ፣ የማስፈፀም አቅም ፣በሀብት አጠቃቅም እና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ትኩረት ያደረገ የሪፖርት ግምገማ መደረጉ የተገለፀ ሲሆን የቀጣይ ሦስት ወር የስራ አቅጣጫን በማስቀመጥም መድረኩ ፍፃሜውን አጊኝቷል። የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሚያዝያ 15/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

በተዘጋጁ የቴክኖሎጂ እሴት ሰንሰለት ትንተናዎች ላይ ያተኮረ ስልጠና ለድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ አመራሮችና ሰራተኞችና የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሄደ፡፡ በድሬዳዋ አስተዳደር በሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖለጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ከትኩረት ዘርፍ መ/ቤት ከተውጣጡ ባለሞያዎች እና የኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን የእሴት ሰንሰለት ትንተና አዘገጃጀት ላይ ከዚህ በፊት በተሰጣቸው ስልጠና መሰረት የተዘጋጁ ሰነዶች ቀርበው ገለጻ ተደርጎባቸዋል፡፡ ከቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ዘርፍ ተልዕኮዎች ውስጥ አንዱ ተወዳዳሪነትን የሚያረጋግጥ አዋጭ ቴክኖሎጂ ለኢንተርፕራይዞች ማሸጋገር መሆኑ ይታወቃል በዚህም የምርት ወይም የአገልግሎት የአመራት ሂደት በመተንተን ክፍተቶችን በመለየት እና ለክፍተቶቹም የቴክኖሎጂዎችን መፍትሄ ለማስቀመጥ የእሴት ሰንሰለት ትንተና ሰነዶች ተዘጋጅተዋል፡፡ በመሆኑም የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናው ዋና አላማ ከትኩረት መ/ቤት የተውጣጡ የተለያዩ ባለሞያዎች የዘርፋቸውን እሴት ሰንሰለት ማዘጋጀታቸውን ተከትሎ የቢሮው አመራሮችና ባለሙያዎች ግንዛቤ እንዲኖራቸውና በተዘጋጀው ሰነድ ላይ ሙያዊ አስተያየት እንዲሰጥበት በማድረግ ሰነዱን በማዳበርና በማስተዋወቅ በሚለዩት ቴክኖሎጂዎች የኢንተርፕራይዞችን፣ የተቋማትን እና የኢንዱስትሪዎችን ምርታማነትና ተወዳዳሪነት በመጨመር ለበርካታ ዜጎች የሥራ-ዕድል ለመፍጠርና እና የገቢ መጠን ለመጨመር ታሳቢ ያደረገ መሆኑን የኤጀንሲው ኃላፊና የቢሮው ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ተናግረዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሚያዚያ 14/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+4

በድሬዳዋ ወጣቶችን በክህሎት የተመራ የስራ ባለቤት ለማድረግ የተጀመረው ስራ መጠናከር እንዳለበት ተመለከተ ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 13/2016(ኢዜአ)፦ በድሬዳዋ አስተዳደር በገጠርና በከተማ ክህሎት መር የስራ ዕድል ለመፍጠር እየተደረገ ያለው ስራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ዳንኤል ተሬሳ አመለከቱ። በአስተዳደሩ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ14ሺህ በላይ ለሆኑ ሰዎች ቋሚ የስራ ዕድል እንደተፈጠረ ተገልጿል። በሚኒስትር ዴኤታ አቶ ዳንኤል ተሬሳ የተመራ የሚኒስቴሩ ከፍተኛ ባለሙያዎች ቡድን በድሬዳዋ አስተዳደር ለአንድ ሳምንት ያካሄደው የድጋፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ ተጠናቋል። የባለሞያዎች ቡድኑ ባካሄዳቸው ጉብኝት ላይ ከአስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህና ከዘርፉ አመራሮች ጋር ተወያይቷል። የስራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ዳንኤል ተሬሳ በወቅቱ እንደገለጹት በአስተዳደሩ ገጠርና ከተማ ክህሎት መር የስራ ዕድል ለመፍጠር እየተከናወኑ የሚገኙ ዘርፈ ብዙ ስራዎች አበረታችና ተጠናክረው መቀጠል ያለባቸው ናቸው። ምቹ ተቋማዊ አደረጃጀትና የአቅም ግንባታ ስራዎች፣ የክህሎት ልማት፣ በስራ ዕድል ፈጠራና ሰላማዊ የኢንዱስትሪ የስራ እንቅስቃሴዎች ለመፍጠር የተከናወኑ የሪፎርም ስራዎች አበረታች ናቸው ብለዋል። ጅምር ስራዎቹን የበለጠ በማጠናከር የሚፈለገውን ውጤት ለማምጣት የተቀናጀ ጥረት መደረግ እንዳለበትም አስገንዝበዋል። ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱም የሚያደርገውን ድጋፍና ክትትል በማጠናከር የድርሻውን እንደሚወጣ ሚኒስትር ዴኤታው አስታውቀዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ በበኩላቸው በድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ዕድል መፍጠርና ወጣቶችን ተጠቃሚ ማድረግ የህልውና ጉዳይ ተደርጎ በትኩረት እየተሠራ ይገኛል ብለዋል። ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለአስተዳደሩ እያደረገ የሚገኘው ድጋፍና ክትትል የጅምር ስራ ውጤቶችን በተሻለ ለማሳደግ አበርክቶው የጎላ ይሆናል ሲሉም አክለዋል። በአስተዳደሩ ባላፉት ዘጠኝ ወራት በተለያዩ መስኮች ከ14ሺህ በላይ ለሚሆኑ ሰዎች የስራ ዕድል መፈጠሩን የገለፁት ደግሞ የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ናቸው። በተካሄደው ድጋፋዊ የግምገማ ሂደት የተቀመጡ አቅጣጫዎችን በተቀናጀ መንገድ በመተግበር አመታዊ ዕቅድን ሙሉ በሙሉ ለማሳካት ጥረት ይደረጋል ብለዋል። በአቶ ዳንኤል ተሬሳ የተመራው የባለሞያዎች ቡድን ከነገ ጀምሮ በሐረሪ ክልል ተመሣሣይ የስራ ጉብኝት እንደሚያደርግ ተመላክቷል። ©️ የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት