Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
1 064
المشتركون
-124 ساعات
-47 أيام
+530 أيام
أرشيف المشاركات
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
#ዜና | የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቲክኒክ ኮሌጅ በሙያ ደህንነት እና ጤንነት (occupational Safty and Health) ዙሪያ ሲያስለጥናቸው የቆየውን ከአስር ስድስት(16) በላይ የኢንዱስትሪ አንቀሳቃሽ ባለሞያዎችን አስመርቋል::
ኮሌጁ ይህን ስልጠና ሲያከናውን ለመጀመሪያ ጊዜ ሲሆን ከሽንብሮ ፕላስቲክ ፋብሪካ ጋር በመዋዋል የፋብሪካውን ከአስራ ስድስት (16 ) በላይ የሆኑ ሰራተኞችን አሰልጥኖ ማስመረቁን በወቅቱ ተጠቅሷል ።
በወቅቱ ንግግር ያደረጉት የስራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ቢሮ ሀላፊና የቴክኒክና ሞያ ኤጀንሲ ዳሬክተር ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ቢሮው በስሩ ዘርፈብዙ ስራዎችን እንደሚሰራ ጠቅሰው ከስራዎቹም መካከል የፋብሪካን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ የሞያ ክፍተቶችን በመሙላት ደህንነታቸው የተጠበቀ የበቁ ዜጎችን ማብቃት ነው ብለዋል ::
ቢሮው የሞያ ክፍተትን በስልጠና ማጠናከር ብቻ ሳይሆን በሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች በኩል በአስተዳደሩ ለሚገኙ የተለያዩ ፋብሪካዎች መለዋወጫዎችን በማምረት የውጭ ምንዛሬን ከማስቀረት ባሻገር ከውጪ ግብዓቱ የሚመጣበትንም ጊዜ እንዲቆጠብ እያደረገ ይገኛልም በማለት ሀላፊዋ አክለው ተናግረዋል ::
የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በበኩላቸው ይህ የፋብሪካ ውስጥ የሞያ ደህንነትና የጤና አጠባበቅ ስልጠና እንደ ሀገር ያለ ክፍተት መኖሩን ጠቅሰው ኮሌጁ ይህን ችግር ለመቅረፍ ለመጀመሪያ ጊዜ ከሽንብሮ ፕላስቲክ ፋብሪካ ጋር በመዋዋል የፋብሪካውን ከአስር ስድስት (16) በላይ ሰራተኞች ማሰልጠናቸውን ተናግረዋል ::
ስልጠናውን ተከታትለው የተመረቁት ስልጣኖች በበኩላቸው የወሰዱት የሞያ ደህንነትና የጤና ስልጠና ከፋብሪካ ውስጥ ስራችን ውጪም የግል ሕይወታችንን ለምን መራበት አካባቢም የሚጠቅመን ነው ብለዋል ::
በምረቃና ማጠቃለያ መርሃ ግብሩ ላይም ስልጠናቸውን
ላጠናቀቁ ሰልጣኖች የእውቅና ስርተፊኬት ተሰጥቷል ::
#DireTvአማርኛ |ጥር 16 ፥ 2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ
የ2017 ዓ.ም ቅድመ ሞዴልና የ2018 ዓ.ም ሞዴል ኢንተርፕራይዞች በኢንተርፕርነርሽፕ እና በቢዝነስ ዴቨሎፕመንት ላይ ሰልጠና ተሰጠ።
በዚህም ስልጠና የኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾችን ባገኙት ዕውቀትና ክህሎት ምርትና ምርታማነታቸውን ለማሳደግና ያላቸውን ልምድ እርስ በእርሳቸው እንዲለዋወጡ ለቀጣይም የዕድገት ደረጃ ለማብቃት አቅማቸውን የሚገነባ ይሆናል።
በመሆኑም ኢንተርፕራይዞቹ በቀጣይ በሞዴል መመዘኛ መሰረት ተመዝነው ከዛ ውስጥ የተሻለ የሚባሉትን ምርጥ ተሞክሮ የሚቀመር ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ ታዳጊ መካከለኛ በየአመቱ የሚሸጋገሩትን በመስፈርቱ መሰረት የመለየት ስራ ተጠናክሮ የሚሰራ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሙሉጌታ ሀ/ማርያም ገልጸዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥር 15/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የአሰሪና ሰራተኛ ዳይሬክቶሬት ለአገር ውስጥ ስራና ሰራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጀ።
በመድረኩም ከተለያዩ በአስተዳደሩ ከሚገኙ የአገር ውስጥ ስራና ሰራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች ለተወጣጡ አሰሪና ሰራተኞች በሁለትዮሽ ማህበራዊ ምክክር ዝርጋታ እና በአሰሪና ሰራተኞች አዋጅ ቁጥር 1156/2011 ላይ ማብራሪያ ተሰጥቷቸዋል።
በዚህም አዋጁን በመረዳት የአሰሪውንና ሰራተኛውን ግንዛቤ ማሳደግ ዓላማው አድርጎ ከዚህ ጎን ለጎን የሚኖሩ አለመግባባቶችን በመቀነስ የስራ ክርክሮችን በምክክር መፍታት የሚያስችላቸው ይሆናል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥር 15/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍን ለማሻሻልና ለማዘመን መነሻ የሚሆን የአምስት አመታት ትግበራ አፈጻጸም ጥናት ቀርቦ ውይይት ተደረገ፡፡
በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የሚተገበረው ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ አስመልክቶ ከ2013-2017 ዓ.ም ድረስ በኢንተርፕራይዞች ላይ ያመጣው ለውጥ ምን ይመስላል የሚለውን የሚያሳይ የተጠና ጥናት ለባለድርሻ አካላት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡
በዚህም የሚሰጠውን ድጋፍ ለማሻሻልና ለማዘመን የሚያግዙ ሃሳቦች በመድረኩ የተነሱ ሲሆን የኢንተርፕራይዞች የብቃት ማረጋገጫ ምዘና በሁሉም ባለ ድርሻ አካላት ተሳትፎ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተመላክቷል፡፡
በመድረኩ የግል ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ ላይ ያላቸው ተሳትፎ ምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ የተገመገመ ሲሆን ቀጣይ የስራ አቅጣጫ በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊና በቢሮው የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ተሰጥቷል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥር 15/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት የስራ አፈፃፀም ግምገማ እና የመውጫ ግብረ-መልስ ተሰጠ፤
የሥራና ክህሎት ቢሮ የስድስት ወር የስራ አፈፃፀም በድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት የበጀት ኢኮኖሚ፣ ንግድና ኢንዱስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ተገምግሟል።
በግምገማው መድረክ ቢሮው የ2018 በጀት አመት ስድስት ወራት ያከናወናቸውን ተግባራት ቋሚ ኮሚቴው ለተከታታይ ቀናት ያካሄዷቸውን የመደበኛ እና የካፒታል ፕሮጀክቶች በተመለከተ መስክ ምልከታ የተለዩ ጉዳዮች እና የተዘጋጀውን ቼክ ሊስት መነሻ በማድረግ ከቋሚ ኮሚቴ አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች እና ግልፅነት የሚፈልጉ ስራዎች ላይ በቢሮው አመራሮች ሀሳብ አስተያየት ተሰጥቶባቸዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ከቋሚ ኮሚቴው ከተነሱ ጥያቄና ማብራሪያ የሚያስፈልጋቸው ለቢሮው የተስጡ ግብረ መልሶች፣ የውክል አወጣጥ መድረኮች የተነሱ ጥያቄዎች በገጠርና ከተማ የተፈጠሩ ስራ ዕድሎች፣ የኢንተርፕራይዞች ልማት እንቅስቃሴ፣ የ100 ቀን ዕቅድ የሪፎርም ስራንም ጨምሮ በ6 ወራት ታቅደው የተከናወኑ ተግባራት፣ የተገኙ ውጤቶችና ሊፈቱ የሚገቡ ተግዳሮቶች ላይ ሰፋ ያለ ማብራርያ የሰጡ ሲሆን የቢሮው የማኔጅመንት አባላትም በሚመለከታቸው ጉዳዮች ላይ ምላሽ ሰጥተዋል።
የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ወ/ሮ አይናለም ተዘራ በበኩላቸው የዝግጅት ምዕራፍ አፈፃፀማቸው፣ የቢሮው ስትራቴጂክ ግቦች ዋና ዋና እና በዝርዝር የታቀዱ ተግባራት የተፈፀሙ መሆናቸው በስራቸው ያሉ ተቋማት ጋር ያላቸው ቅንጅታዊ አሰራር በመጠናከሩ የተቋሙ የ6 ወር የስራ አፈፃፀም ጥሩና የሚበረታታ መሆኑን በመግለጽ ጥንካሬዎችን በማስቀጠል እና የስራ ክህሎት ምክር ቤት መደበኛ ግዜውን ጠብቆ መድረክ በማዘጋጀትና ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ በማድረግ በመስክና በመድረክ የተገመገሙ ውስንነቶችን በሚገባ ማረም እንደሚያስፈልግ ገልፀው የቢሮውን የመውጫ ግብረ መልስ ሰጥተዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥር 14/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት የስራ አፈፃፀም ግምገማ እና የመውጫ ግብረ-መልስ ተሰጠ፤
የሥራና ክህሎት ቢሮ የስድስት ወር የስራ አፈፃፀም በድሬደዋ አስተዳደር ምክር ቤት የበጀት ኢኮኖሚ፣ ንግድና ኢንዱስትሪ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ተገምግሟል።
በግምገማው መድረክ ቢሮው የ2018 በጀት አመት ስድስት ወራት ያከናወናቸውን ተግባራት ቋሚ ኮሚቴው ለተከታታይ ቀናት ያካሄዷቸውን የመደበኛ እና የካፒታል ፕሮጀክቶች በተመለከተ መስክ ምልከታ የተለዩ ጉዳዮች እና የተዘጋጀውን ቼክ ሊስት መነሻ በማድረግ ከቋሚ ኮሚቴ አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች እና ግልፅነት የሚፈልጉ ስራዎች ላይ ቡቢሮው አመራሮች ሀሳብ አስተያየት ሰጥቶባቸዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ከቋሚ ኮሚቴው ከተነሱ ጥያቄና ማብራሪያ የሚያስፈልጋቸው ለቢሮው የተስጡ ግብረ መልሶች፣ የውክል አወጣጥ መድረኮች የተነሱ ጥያቄዎች በገጠርና ከተማ የተፈጠሩ ስራ ዕድሎች፣ የኢንተርፕራይዞች ልማት እንቅስቃሴ፣ የ100 ቀን ዕቅድ የሪፎርም ስራንም ጨምሮ በ6 ወራት ታቅደው የተከናወኑ ተግባራት፣ የተገኙ ውጤቶችና ሊፈቱ የሚገቡ ተግዳሮቶች ላይ ሰፋ ያለ ማብራርያ የሰጡ ሲሆን የቢሮው የማኔጅመንት አባላትም በሚመለከታቸው ጉዳዮች ላይ ምላሽ ሰጥተዋል።
የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ወ/ሮ አይናለም ተዘራ በበኩላቸው የዝግጅት ምዕራፍ አፈፃፀማቸው፣ የቢሮው ስትራቴጂክ ግቦች ዋና ዋና እና በዝርዝር የታቀዱ ተግባራት የተፈፀሙ መሆናቸው በስራቸው ያሉ ተቋማት ጋር ያላቸው ቅንጅታዊ አሰራር በመጠናከሩ የተቋሙ የ6 ወር የስራ አፈፃፀም ጥሩና የሚበረታታ መሆኑን በመግለጽ ጥንካሬዎችን በማስቀጠል እና የስራ ክህሎት ምክር ቤት መደበኛ ግዜውን ጠብቆ መድረክ በማዘጋጀትና ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ በማድረግ በመስክና በመድረክ የተገመገሙ ውስንነቶችን በሚገባ ማረም እንደሚያስፈልግ ገልፀው የቢሮውን የመውጫ ግብረ መልስ ሰጥተዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥር 14/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የፋይናንስ ዘርፉ ግስጋሴ!💰
******
በኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት የተተገበረው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ፣ የተዛባውን ኢኮኖሚ ከማረጋጋት ባለፈ በፋይናንስ ዘርፉ ላይ አዳዲስ ስኬቶችን እያስመዘገበ ይገኛል።
የዘርፉ ዋና ዋና ለውጦች፡-
🔹 ዲጂታል ኢትዮጵያ እውን እየሆነች ነው፡ የባንክ አሰራርን ዘመናዊና ተደራሽ በማድረግ፣
የገንዘብ ዝውውርና የዲጂታል አገልግሎቶች በከፍተኛ ፍጥነት እንዲስፋፉ አስችሏል።
🔹 ቴክኖሎጂና የኢኮኖሚ እድገት፡ በቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት ለዜጎች ምቾትን ከመፍጠር
ባለፈ፣ ለሀገራዊ የኢኮኖሚ እድገት የላቀ አበርክቶ እያደረገ ይገኛል።
🔹 የፋይናንስ አማራጮችና የቦንድ ሽያጭ፡ መንግሥት የቦንድ ሽያጭን እንደ አንድ የፋይናንስ
አማራጭ መጠቀሙ፣ ዜጎች በሀገራዊ ሜጋ ፕሮጀክቶች ላይ "የእኔነት" ስሜት ኖሯቸው
እንዲሳተፉ በር ከፍቷል።
ባለሙያዎች ምን ይላሉ? 🎙️ በካፒታል ገበያ ባለሥልጣን የፈቃድና ምዝገባ ዳይሬክቶሬት ኃላፊ አቶ ኢድሪስ ሰልማን ከኢቢሲ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት፤
"ዜጎች የመንግሥት ቦንድ በመግዛት ለሀገር ግንባታ የፋይናንስ አቅም ከመፍጠር ባለፈ፣ ገንዘባቸውን አዋጭ በሆነ ኢንቨስትመንት ላይ እያዋሉ መሆኑን መገንዘብ ይገባቸዋል።"
በማህበረሰቡ ተሳትፎና በሀገር ውስጥ ሀብት የሚገነቡ ግዙፍ ፕሮጀክቶች፣ ለሀገር ትልቅ አቅም ከመሆናቸውም በላይ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን የሚያረጋግጡ ናቸው። 🇪🇹
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+3
በዛሬው እለት በመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ የሚከበረው የከተራና ጥምቀት በዓልን ምክንያት በማድረግ በጀርባ ሰፈር ለሚገኘው ፖሊስ ጣቢያ ለምእመናኑ የሚታደል የታሸገ ውሃና ለማእድ ማጋራት የሚሆኑ የተለያዩ ነገሮችን በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ማህበረሰብ ስም ለፖሊስ ጣቢያው አስረክበናል።
በዚሁ አጋጣሚ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ በዓሉ የፍቅር የአንድነት እንዲሆንላችሁ በኮሌጁና በኮሌጁ ማኔጅመንት ስም መልካም ምኞቴን ለመግለጽ እወዳለሁ፡፡
ጥር 10/2018 ዓ.ም
አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን
+2
አቶ ሮቤል ጌታቸው የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ለከተራና ለጥምቀት በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ።
የተከበራችሁ የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ጥምቀት መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን።
በዓሉ ከኃይማኖታዊ በዓልነቱ ባሻገር የአብሮነታችን መገለጫ ከመሆኑም በተጨማሪ የሀገርና የህዝብ ሃብት እንዲሁም የዓለም ቅርስ ሆኖ በዩኔስኮ የተመዘገበ ስለሆነ በዓሉን ስናከብር ሀገራዊ ገፅታን በሚያሳድግ መልኩ ማክብር ይገባናል።
ህዝበ ክርስቲያኑም በዓሉን ሲያከብር የተቸገሩ ወገኖቻችንን በማብላት በማጠጣት እንዲሁም ከሁሉም ህብረተሰብ ጋር ሠላምና አብሮነትን በሚያጎለብት መልኩ ማክበር ያስፈልጋል።
በድጋሚ እንኳን ለከተራና ለጥምቀት በዓል በሠላም አደረሳችሁ። አደረሰን።
መልካም በዓል!
አቶ ሮቤል ጌታቸው
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
ኮሌጁ የታዳጊና ወጣቶችን ፈጠራ ለማሳደግ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ተገለጸ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በአስተዳደሩ ከሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ለተወጣጡ ተማሪዎች ግንዛቤ መስጫ መድረክ አካሄደ::
በመድረኩ ለታዳጊዎች መልዕክት ያስተለፉት የኮሌጁ ም/ል ዲን እና የቴ/ሽ/ኢ/ኤ/አ ዋና ስራ ሂደት ሃላፊ አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ በንግግራቸውም በቅድሚያ የብቁ ሞያተኞችና ችግር ፈቺ ቴክኖሎጂዎች መፍለቂያ ወደ ሆነው ተቋማችን እንኳን ደህና መጣችሁ ያሉ ሲሆን እዚህ እንድትገኙ የሆነበት ምክንያት አሁን ላይ በንድፍ ምትማሯቸውን ትምህርቶችን በተግባር ችግሮችን ለመፍታት የምትጠቀሙበትን አግባብ ለማስገንዘብ እንዲሁም ያላችሁን የፈጠራ ሀሳብ ከወዲሁ መሰረት የምታሲዙበትን መንገድ ለማመቻቸት እንደሆነም ገልፀዋል::
ባደጉት ሀገራት ከፍተኛ ተከፋይ መሆን የሚያስችሉት የክህሎት ሙያዎች እንደሆኑ የገለፁት በኮሌጁ የEASE ፕሮጀክት አስተባባሪ ኢ/ር ፋሲል ማዘንጊያ ሲሆኑ እንደ ፕሮጀክት በነዚህ ጉዳዮች ላይ ድጋፍ ለማድረግ ስናስብ አስተዳደሩ ላይ ያሉ ወጣቶች የራሳቸው ሙያ ኖሯቸውና ከስራ ጋር ተገናኝተው እራሳቸውንም ሆነ ቤተሰባቸውን እንዲደግፉ ለማስቻል ነውም ብለዋል::
በመድረኩ የፈጠራ ሀሳብን ወደ ተግባር አሳድጎ ችግር ፈቺ ቢዝነሶችን እውን የማድረግን ፅንሰ ሀሳብ በተመለከት የጥናትና ቴክኖሎጂ ሽግግር አስተባባሪ በሆኑት አቶ ያሬድ ሁሉአለም አማካኝነት ግንዛቤ መፍጠር የተቻለ ሲሆን በተጨማሪም በሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስና እና ሂሳብ(STEM) ምንነትና በዘርፉ ያለውን ከፍተኛ አስተዋፅኦ የቴክኖሎጂ ባለሙያዎች ለታዳጊዎቹ ግንዛቤ ሰጥተዋል::
በቀጣይም የፈጠራ ሀሳብ ያላቸውን ታዳጊዎች በመለየት ሀሳባቸው ወደ ችግር ፈቺ ቢዝነሶች መለወጥ የሚያስችላቸውን ክህሎቶች በተቋሙ እንደሚሰጣቸውም ተገልፀዋል::
በእለቱ በተካሄደው የግንዛቤ መድረክም የኮሌጁ አሰልጣኝ መምህርትና እና ሰልጣኝ ተማሪ ለ2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎቹ በዘርፉ ያደረጏቸውን ስኬታማ ጉዞዎች እና የህይወት ልምዳቸውን ማካፈልም ችለዋል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ጥር 9/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
"በአስተዳደሩ በስራ እድል ፈጠራ ወጣቶችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏ".. ክቡር አቶ ከድር ጁሀር የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ
በኢፌድሪ የሥራ እና ክህሎት ሚንስቴር የተመራው የድጋፍ እና ክትትል ልዑክ ቡድን በሶማሌ፣በሐረር ክልሎች እና በድሬዳዋ አስተዳደር ያካሄደውን ክትትል እና ድጋፍ የማጠቃለያ መርሃ ግብር በድሬዳዋ ከተማ አካሂዷል።
በማጠቃለያ መርሃ ግብሩም ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ክቡር ከንቲባ ተገኝተው እንደገለጽት በአስተዳደሩ በገጠር እና በከተማ በተፈጠሩ የስራ እድሎች ወጣቶችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል።
በተለይም በሁለቱ የቴክኒክ እና ሙያ ኮሌጆች ወጣቶችን በማሰልጠን እና በማብቃት በአስተዳደሩ ከሚገኙ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ጋር በማስተሳሰር ለወጣቶች ሰፊ የስራ እድል መፍጠር መቻሉን ገልፀዋል።
የሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ አቶ ዳንኤል ተሬሳ የሥራ እና ክህሎት ሚንስቴር በ11 የክልል ከተሞች እና የከተማ አስተዳደሮች የድጋፍ እና ክትትል ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን እና የተቋም ግንባታን እና የአሰሪ እና ሰራተኛን ጉዳይ ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር እንዲሁም ቅንጅታዊ አሰራሮችን ለማጠናከር ዓላማ ያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም በባለፉት አራት አመታት ከ16 ሚሊዮን በላይ ለወጣቶች የስራ እድል መፍጠር መቻሉን ተናግረዋል።
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በበኩላቸው በባለፉት ስድስት ወራት በተቋም ግንባታ፣ ከክህሎት ልማት፣ ከስራ እድል ፈጠራ ከአሰሪ እና ሰራተኛ ዘርፍ በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን ገልጸዋል።
በመድረኩም በክትትል እና ድጋፍ የተገኙ ጠንካራ እና ምርጥ ተሞክሮች እንዲሁም በዘርፉ የታዩ ማነቆዎች እና የመፍትሄ አቅጣጫዎች በስፋት ተዳስሰዋል።
በመርሃ ግብሩም የክልል እና የአስተዳደሩ የዘርፉ ከፍተኛ አመራሮች እና ባለሙያዎች ተገኝተዋል።
©️DGC ጥር 9/2018 ዓ.ም
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
